ህዳሴ ሚዲያ ማዕከል Gidduugala Odeeffannoo Hiddaasee
Open in Telegram
ህዳሴ ሚዲያ ማዕከል Gidduugala Odeeffannoo Hiddaasee ይህ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቦሌ ክፍለ ከተማ በወረዳ 14 ትምህርት ጽ/ቤት የህዳሴ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የህዳሴ ሚዲያ ማዕከል የቴሌግራም ቻናል ነው። https://t.me/HSMC2016
Show more873
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-1230 days
Posts Archive
📩ማሳሰቢያ
✅በ2017 ዓ.ም ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል የተፈታኝ ዉድ ተማሪ ወላጆች እና ዉድ መምህራን እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በሙሉ
✅የ2017ዓ/ም የ6ኛ እና8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ የሞዴል ፈተና የሚዘጋጀው የ6ኛክፍል ፈተና( ከ5ኛ እና 6ኛ ክፍል) የመጀመሪያዉ መንፈቅ አመት እንዲሁም የ8ኛ ክፍል(7ኛ እና 8ኛ ክፍል) የመጀመሪያዉ መንፈቅ አመት የሞዴል ፈተናዉ ከጥር 6 እስከ ጥር 9 ቀን 2017 ዓ/ም መሆኑን አውቃችሁ ለተማሪዎቻቹህ አስፈላጊውን እገዛ እንድታደርጉ እናሳስባለን።
በህብረት ይቻላል!!
ቀን 04/04/2017ዓ/ምማስታወቂያ ለዉድ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች በሙሉ ት/ቤታችን ነገ ማለትም ቅዳሜ ታህሳስ 5 ቀን 2017ዓ/ም በሚከተሉት አጀንዳዎች
1. የወርሃዊ ፈተና የተማሪዎች ዉጤትና የ4ዮሽ ዉል ስምምነትን፤ 2. የተማሪዎች ስነ-ምግባርን እና 3. የቅዳሜ ማጠናከሪያ ትምህርትንበተመለከተ ከእናንተ ጋር ዉይይት ለማድረግ ቀን ቆርጧል። በመሆኑም ሁሉም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪ ወላጆች በተባለዉ ቀን ከጠዋቱ 2:30 ላይ በት/ቤቱ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳስባለን። ት/ቤቱ
+4
የህዳሴ ትምህርት ቤት የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአንደኛው ወሰነ ትምህርት አጋማሽ ፈተና ከ4ኛ-8ኛ ዛሬ መሰጠት ተጀመረ።ህዳር 16 ቀን 2017 ዓ.ም (ህ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በሁሉም ክፍለ ከተሞችና ወረዳዎች ባሉ ት/ቤቶች ወጥ የሆነ የፈተና ፕሮግራም ማዘጋጀቱ ይታወቃል። በዚሁ መሰረት የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የአንደኛው ወሰነ ትምህርት አጋማሽ ፈተና ከመሰጠቱ አስቀድሞ ለፈታኝ መምህራን እና ለተፈታኝ ተማሪዎች የፈተናውን ሂደት በተመለከተ በትምህርት ቤቱ የሥርዓተ ትምህርት ም/ር/መ/ር አቶ ጉልላት ስዩም ገለጻ ተደርጓል። በፈተና ኮሚቴ (በትምህርት ክፍል ኃላፊዎች) አስተባባሪነት የመጀመሪያው አጋማሽ ፈተና ተማሪዎችን በተገቢው ሁኔታ የሚመዝኑ ፈተናዎች እንዲዘጋጁ ከመገምገምና ግብረ መልስ በማዘጋጀት እና እርማት ከመሥጠት ጀምሮ የህትመት እና ሥርጭት፣ በፈተና ወቅትም የሱፐርቪዥን ሥራዎችን ለማከናወን አስፈላጊውን ሁሉ ቅድመ ዝግጅት ተደርጎ በቅንጅት እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል። ፈተናው ከህዳር 16-18/2017 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ሲሆን ፈተናው ከተጠናቀቀ በኋላ ሁሉም መምህራን ህዳር 19/2017 ዓ.ም ግብረመልስ የሚሰጡ ይሆናል።
#Ethiopia #Hidase_Media_Center #HMC_Addis_Ababaህዳሴ ሚዲያ ማዕከል የትምህርት ቤቱ ልሳን ▭▭◎⃝◎⃝◎⃝◎⃝◎⃝◎⃝◎⃝▭▭
ህዳር 15 ቀን 2017 ዓ.ም
ለፈተና ለመዘጋጀት የሚጠቅሙ 9 ነጥቦችውድ እና የተከበራችሁ የት/ቤቶቻችን ወላጆች በሙሉ ከሰኞ ህዳር 16 ቀን 2017 ጀምሮ ትምህርት ዘመኑ የመጀመሪያው ሩብ አመት ማጠቃለያ ፈተና መሰጠት ይጀምራል።ታዲያ በዚህ ወቀት ለተማሪዎች የፈተና ዝግጅት ጠቃሚ መሆናቸውን በባለሙያዎች የሚመከሩ 9 ጠቃሚ ነጥቦችን ልንነገራችሁ ወደናል፤መልካም ንባብ፡፡ 1. ቁርስና ጠቃሚ ምግቦች ሰውነታችን በአግባቡ ሥራውን እንዲሰራ ኃይል ያስፈልገዋል፤ አንጎላችን ደግሞ ትኩረት እንዲኖረውና የማስተዋል አቅማችን እንዲጨምር በቂ የሆነና ያልተቆራረጠ የኃይል አቅርቦት ይፈልጋል። ጥናቶች እንደሚያሳዩት ቁርሳቸውን ተመግበው ወደፈተና የሚገቡ ተማሪዎች የተሻለ ውጤት ያስመዘግባሉ። የተመጣጠነ ምግብ ተመግበው ለፈተና የሚቀርቡት ደግሞ የበለጠ የማስታወስና የማስተዋል አቅም ይኖራቸዋል። ስለዚህ ሁሌም ቢሆን ፈተና ያለባቸው ተማሪዎች እንደ የገብስ ገንፎ፣ ዳቦ፣ ሩዝና ድንች ያሉ በካርቦሃይድሬት የበለጸጉ ምግቦችን በቁርስ ሰዓት ተመግበው ቢወጡ ይመከራል። እርጎ፣ እንቁላል፣ አሳ፣ ጎመን፣ ቲማቲምና አቮካዶ ዓይነት ምግቦችም እጅጉን ጠቃሚ ናቸው። 2. በጠዋት ወደ ጥናት መግባት ሁሌም ቢሆን ነገሮችን አስቀድሞ መጀመርን የመሰለ ነገር የለም። ለፈተናም ቢሆን ጥናት በጠዋት ተነስቶ መጀመር በፈተና ወቅት የተረጋጋ መንፈስ እንዲኖረን ይረዳል። ጠዋት ላይ ጭንቅላታችን እረፍት አድርጎ በአዲስ መንፈስ ሁሉንም ነገር ስለሚጀምር፤ በዚህ ሰዓት ማጥናት ውጤታማ ያደርጋል። በተለይ ደግሞ የክለሳ ጥናቶችን ለከሰዓት ማሸጋገር ተገቢ አይደለም። 3. ከፋፍሎ ማጥናት የክለሳ ጥናትን ከፋፍሎ ማካሄድን የመሰለ ነገር የለም። አንድ የትምህርት ዓይነት ላይ 10 ሰዓት ሙሉ ከማሳለፍ በየቀኑ አንድ ሰዓት በማጥናት በ10 ቀን መጨረስ ይበልጥ ውጤታማ ያደርጋል። ያጠናነውን ነገር ለማስታወስና በቀላሉ ለመሸምደድ ጭንቅላታችን ጊዜ ይፈልጋል። ከፋፍሎ ማጥናት ደግሞ ለዚህ ፍቱን መድሃኒት ነው። ከፋፍሎ ማጥናት እጅግ ውጤታማው መንገድ እንደሆነም በመላው ዓለም የተሰሩ የተለያዩ ጥናቶች ያለመክታሉ። 4. ራሳችሁን ቶሎ ቶሎ ፈትኑ የሥነ አዕምሮ ጥናት ባለሙያዎች እንደሚሉት የማስታወስ ችሎታን ለማዳበርና በራስ መተማመናችንን ለመጨመር ራስን መፈተን ውጤታማ ያደርጋል። ከዚህ በተጨማሪ እየተዘጋጀንበት ያለነውን ጉዳይ በደንብ እንድናውቀው ከማድረጉ በተጨማሪ የረሳናቸው አልያም የዘለልናቸው ርዕሶችን ለመለየት ይረዳናል። 5. መምህር መሆን ከባዱን የክለሳና ራሳችሁን የመፈተን ሥራውን ካከናወናችሁ በኋላ ጓደኞቻችሁን ሰብሰብ አድርጋችሁ በጭንቅላታችሁ የሚመጣውን ነገር በሙሉ ንገሯቸው። ራሳችሁን በመምህር ቦታ አድርጋችሁ እውቀታችሁን ለማካፈል ሞክሩ። ምን ያህል እንደምታስታውሱ ለማወቅ ከመርዳቱ በተጨማሪ ጓደኞቻችሁንም ትጠቅሟቸዋላችሁ። 6. ከተንቀሳቃሽ ስልኮች መራቅ ስልኮች በጣም ብዙ ጥቅም አላቸው። ነገር ግን በጥናት ወቅት ከጥቅማቸው ይልቅ ጉዳታቸው ነው የሚያመዝነው። በተለይ ደግሞ ማህበራዊ ሚዲያዎችን የምትጠቀሙ ከሆነ። ብዙ ጥናቶች እንዳረጋገጡት ብዙ ጊዜያቸውን ስልካቸው ላይ የሚያሳልፉ ተማሪዎች የትምህርት ውጤታቸው ሁሌም ቢሆን ዝቅ ያለ ነው። 7. ቋሚ እረፍትና አካላዊ እንቅስቃሴ ውጤታማ የክለሳ ጥናት ማለት እረፍት አልባ ጥናት ማለት አይደለም። በጥናታችን መሀል መሀል ላይ ጥሩ አየር ለማግኘትና ሰውነታችንን ለማፍታታት ወጣ ብሎ እንቅስቃሴ ማድረግ የማስታወስ ችሎታችንን በደንብ ከፍ ያደርገዋል። ከዚህ በተጨማሪ ሰውነታችን እና ጭንቅላታችን በእጅጉ የተሳሰሩ በመሆናቸው እንቅስቃሴ ስናደርግ የደም ዝውውራችን ይስተካከላል፤ ይህ ደግሞ በቂ ኦክስጅን ወደ ጭንቅላታችን እንዲሄድ ይረዳል። አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ተዘርዝሮ የማያልቅ ጥቅሞች ያሉት ሲሆን ጭንቀትን መከላከልና በራስ መተማመንን መጨመር ከነዚህ መካከል ይጠቀሳሉ። 8. እንቅልፍ ከፈተና በፊት ያለችውን ምሽት ጥሩ እንቅልፍ አግኝቶ ማሳለፍ ተገቢ እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ። ነገር ግን ጥሩ እንቅልፍ ፈተናው ሲቃረብ ብቻ ሳይሆን ከሳምንታት በፊት ገና ዋናው ጥናት ሲደረግና ክለሳ በሚደረግበት ወቅትም እጅግ ወሳኝ ነው። በጠዋት ተነስቶ ውጤታማ የክለሳ ጥናት ካደረጉ በኋላ በጊዜ ተኝቶ ጥሩ እንቅልፍ ማግኘት ሰውነታችንና ጭንቅላታችን በደንብ ተግባብተው እንዲሰሩ ይረዳቸዋል። ሌሊቱን በሙሉ ለማጥናት ሙከራ አታድርጉ ይላሉ የዘርፉ ባለሙያዎች። ምክንያቱም ራሳችን ላይ ጫና እያሳደርን ስለሆነ። 9. መረጋጋትና በጎ በጎውን ማሰብ ተማሪዎች እስካሁን የተዘረዘሩትን ነገሮች ሁሉ ተግባራዊ ካደረጉ ምንም የሚያሳስባቸው ነገር ሊኖር አይገባም። ዘና ብለው ወደ ፈተና መግባት ብቻ ነው የሚቀራቸው፡፡ ምናልባት ጥሩ ያልሆነ አጋጣሚ ቢገጥማቸው እንኳን እሱን ረስተው ለቀጣዩ በጥሩ መንፈስ ለመዘጋጀት መሞከር ነው ፡፡ ውድ ወላጆቻችን፡- በእያንዳንዱ የፈተና ጊዜ ልጆቻችሁን ማገዝ እና ማበራታታት እንዲሁም ሞራል መስጠት አትርሱ። ውድ ተማሪዎቻችን መልካም ፈተና!!! ህዳሴ ት/ቤት
ህዳሴ ቅ/አንደኛ፣አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት
ከህዳር 16-18/2017 ዓ.ም ድረስ በትምህርት ቤታችን ከ4ኛ-8ኛ ክፍል ተማሪዎች የአጋማሽ ፈተና እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡
ከፈተና በፊት ማድረግ የሚገባን :-
• ለፈተና ስንዘጋጅ አዎንታዊ እና በጎ ሀሳቦችን ማሰብ፡፡
• ፈተና ማለት ከዚህ ቀደም ከተማርነው ነገር የተረዳነውን እና የቀሰምነውን እውቀት የምንለካበት መመዘኛ መሆኑን አውቀን በመርሀግብር የተመራ በቂ ዝግጅት ካደረግን የምንፈልገውን ዉጤት ማምጣት እንደምችል በማመን ከት/ቤት መልስ በቤት ዉሥጥ በመምህራን የተሰጡ የመማር ተግባራት / የቤት ስራ፣ የግል ስራ ወ.ዘ.ተ/ በአግባቡ መሰራትና እርማት መውሰድ፤ በተጨማሪም በቤት ዉስጥ ቋሚ የጥናት መርሀግብር ማዘጋጀት እና በተዘጋጀው መርሀ ግብር መሰረት ጥናት ማከናወን፡፡
• ማወቅ ያለብን አንድ ነገር መሳሳትን አለመፍራት እና ሁሌም ለማወቅ እና ራስን ለማሻሻል ዝግጅ መሆንን ነው ። እንዲሁም አሁን የምንፈተነው ፈተና እንዳሰብነው እንኳን ውጤቱ ባያስደስት ለቀጣይ ማስተካከል እና ማሻሻል እንደሚቻል ማመን።
• ከጓደኞቻችን ጋር ያጠናነውን ነገር በጋራ ሆነን መጠያየቅ እና እርስ በርስ ያወቅነውን ነገር መለዋወጥ፡፡ ይህ ዘዴ ይበልጥ የማስታወስ ብቃታችንን እንደሚጨምር እና የተጠያየቅነው ነገር እንዳይረሳን ያረጋል ። ከዚህም በተጨማሪ የተሳሳትነውን ነገር ድጋሚ እንድንከልስ እና እርማት እንድናረግ ያግዘናል።
• የፈተና ቀን ሲቃረብ እንደ ወትሮው ዘና ማለት እና በቂ እረፍትና በቂ እንቅልፍ መተኛት ። ይህም ጭንቀትን ይቀንስልናል፣ እንዲሁም ተረጋግተን ያጠናነውን ነገር አስበን እንድንሰራ ይረዳናል።
ፈተና ከጀመርን በኋላ ማድረግ የሚገቡን ነገሮች (ፈተና ላይ እያለን):-
• ወደ ፈተና ከመሄዳችን ቀደም ብለን ለፈተና የሚረዱንን መሳሪያዎች እና የመፈተኛ ቁሶችን ማዘጋጀት።
• አብዝተን ፈተናን እና የምናመጣውን ነጥብ ስሌት አለመገመት ።
• ፈተና ስንጨርስ የተሳሳትነውን ጥያቄ አብዝቶ ማሰብ እና ሌላ ተማሪ መጠየቅ ጭንቀት ውስጥ ስለሚከተን ከዚህ ይልቅ ቤት ሄደን እረፍት ማድረግ እና ለቀጣይ ፈተና መዘጋጀት ።
• በፈተና ጊዜ ድንገተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ ከገጠመን ወዲያው የምንሰራውን ገታ አድርገን በጥልቀት አየር በአፍንጫችን ስበን ወደ ሳንባ እያስገባን መልሰን ማስወጣት ይህንንም እስክንረጋጋ መደጋገም ። ከዚህ በመቀጠል የማረጋጊያ ቃላትን ለራስዎ መንገር::
• ፈተና በምንሰራ ጊዜ ግራ ያጋባንን እና እርግጠኛ ያልሆንበትን ጥያቄ በይለፍ ማቆየት እና ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ይህም ጊዜያችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። ነገር ግን ምልክት አድርገን ማለፍ፤
• በተመሳሳይ እርግጠኛ ያልሆልንበትን መልስ ላይ ተደናግጠን መሰረዝ እና መደለዝን መቀነስ ይህም ስንደነግጥ እና ስንጨነቅ የምናውቀውን መልስ ትተን ሌላ መልስ እንድሰጥ ስለሚያረግ መሰረዝና መደለዝን መቀነስ ።
• ፈተናውን ወደ ማገባደድ ስንደርስ በይለፍ ያስቀመጥናቸውን ግራ ያጋቡንን ጥያቄዎች ጥቂት አስበንበት መልስ መስጠት።
መልካም ፈተና
19ኛው የብሄር-ብሄረሰቦች በዓል ተከበረ።
(ህዳር 4/2017 ዓ.ም) በህዳሴ ቅ/አንደኛ፣አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት
ለ19ኛ ጊዜ የሚከበረውን የብሄር ብሄረሰብ በዓል ዛሬ በቀን 4/2017 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ ተከብሯል። በዓሉ ሀገራዊ መግባባት ለህብረ-ብሄራዊ አንድነት በሚል መሪቃል የተከበረ ሲሆን በብሄር ብሄረሰብ አልባሳት፣በባህላዊ ሙዚቃና ውዝዋዜ እንዲሁም በተማሪዎች መካከል የጥያቄና መልስ ውድድር በማካሄድ ዝግጅቱ ተጠናቋል።
