924
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-2730 days
Posts Archive
924
ክንፍ ነበረኝ✨✨
"አይገርምም ክንፍ ነበረኝ....እድለ ቢስነቴን እርሳው...ክንፍ እንደነበረኝ ብቻ ልብ በልልኝ..ከሰማይ ከፍ ብዬ የምበርበት.....አይገርምም እኔም ልዕልት ነበርኩ...አታስታውስም "የኔ ልዕልት".... ብለህ ትጠራኝ ነበር...እንደ ዛሬው የፀሀይ ወገግታን ወይም የንፋስ ሽውታን ለመቀላመድ የሚገፉ እጆች ሳያስፈልጉኝ በፊት ነው ምልህ .... ያኔ ድሮ ነው የምልህ ...እኔም ሮጬ አውቃለሁ።
አውቃለሁ አሁን ያቺን ርግብ አይደለሁም...አንተም የማውቅህ አባት አይደለህም...አንተ አይደለህም...አ...አ..አይደለ...."....መጨረስ አልቻልኩም...እምባዬ ከነተሸራረፈው ስሜቴ ተቀበለኝ...
"አሁን ለምን ዝም ብለሽ አትበይም...የማይረባ ተረት ተረት ከምትዘላብጂ...."...ሊያጎርሰኝ ከነዘረጋው እጁ ነው ይሄን ያለው...በእጁ ሰይፍ የጨበጠ ይመስል ፊቴን በምችለው መጠን ወደኃላ አሸሸሁት...
"እንቆቅልሽ..."....በንዴት የጨበጠውን እህል ወደ ሰሀኑ አሽቀነጠረው...
"አደጋው ወደ ጭንቅላትሽም ሳይሄድ አልቀረም..."...አለና የሹፈት ሳቁን ሳቀ።
"ምናውቅልሽ አትለኝም...."....ሊወርድ ከሚተናነቀኝ እንባዬ ጋር እየታገልኩ እነተርከው ይዣለሁ....የእርሱን መልስ መጠበቅ ትቼ ማውራቴን ቀጠልኩ።
"አራት እግር ያለው ወንዝ የማይሻገር...."...የጨዋታዬ አዝማምያ ገባው መሰለኝ ፊቱን ከፊቴ አሸሸ...
"መልሳ...መቼም ይሄ አይከብድህም...."...ሙጫ ሆንኩበት።
" ሀገር እንድሰጥህ እየጠበቅክ አይደለም አአ...."
"እኔ ነኝ...እኔ...በደንብ እየኝ እኔ ነኝ...አባት እኔ ነኝ...
እሺ ወንዝ አልሻገር.. ግን ምናለበት ይሄ የስልቸታ ፊትህን ከማይ አይኔን ቢጋርድልኝ...ምናል እሺ ብሎኝ ይሄ ዘለፋህን የምኮመኩምበት ጆሮዬን አደንቁሮ ቢገላግለኝ...ከፀሀይ ልጣላ ወይ ደመናን ልርሳ ጉዳዬ አይደለም...አባት አንተን እየረሳሁህ ነው...እግዜር ከረሳኝ በላይ...ከተወኝ በላይ ወስጤ እየተወህ ነው...."
ከአይኔ መሸሹን ፀንቶበታል...ፊቱን ወደ መስኮቱ ሰዷል..
አምሮበታል... ድሮ ድሮ እጄን ከማርመሰምስበት ከጥቅጥቅ ፀጉሩ ጀምሬ የፊቱን ጠርዝ በቀጭኑ ይዞ ወደ ጉንጩ እና አገጩ በሰፊው ወደተበተነው ፂሙ ወረድኩ... ልዳብሰው ዳዳኝ...ሽባ መሆኔ ትዝ ሲለኝ እኔም አጅኔን ከእሱ ነቅዬ ወደ መስኮቱ አማተርኩ....
"እባክሽ ብይ..."....ያለመደበትን ልምምጥ ጀመረ...
"ተወኝ ልሙትበት..."
"ምን ማለት ነው...."
"ልብ ብለህ አይተኃኝ ታውቃለህ...እየሞትኩ ነው...በቃ ይለይልኝ..."
"ተይ...በዚህ መንገድ አይሆንም...ላብላሽና ልሂድ...."
"እባክህን በምችለው ልሙት... የትኛው እጄ ሰርቶልኝ የቱ ደምስሬን ልቁረጥ...በየቱ እጄ በርትቼ መታነቂያዬን ልስራ...ተው አባት ትሁት ለመሆን አትሞክር...ተወኝ በምችለው ልሙት...አሁን ሂድ አዲሷን ሚስትህን አታስጠብቃት..."
ምንም ሳይለኝ ሄደ...አፌ ሂድ ቢለውም የሆነ ነገሬ አትሂድ እያለው ነበር... አፌን ሰማ።
የረሳውን እቃ ብሎ ከተመለሰ ብዬ በአይኔ ክፍሉን ቃኘሁት...ከእኔ ውጪ ምንም የረሳው እቃ የለም።
የመጨረሻው ክፍል ነገ...
ሸዊት።
https://t.me/shewitdorka
924
ቀደም ሲል በህይወትህ የሆነውን መለወጥ አትችልም።
ለዛ ነገር እራስክን ሰለባ ለማድረግ ማቆም እና መተው መማር አለብክ።
አእምሮህን ካለፈው ስህተት ክብደት ነፃ ማድረግ አለብህ።
ጥሩም ይሁን መጥፎ ፣ ያለፈው ተግባርህ አንተን ለማጎልበትና ለማስተማር እንጂ በመንገድ እንድትቀር ለማድረግ አይደለም።
ማሰናከያም እንዳይሆን። ለነዚ ስህተቶች እራስህን ይቅር ማለት አለብህ ወይም ለጥሩ ነገሮችህ እራስህን ማበረታታት አለብህ ፣ የሆነውን በፀጋ ተቀበል እና ያለፈውን ለሚመጣው ስትል ልቀቀው።
አሁን በአእምሮህ የምትፈጥራቸው የተሻሉ ውብ እና አስደናቂ ነገሮች አሉህ። ለዛ ተዘጋጅ በሁሉም ነገርህ ፈጣሪን አስቀድም።
Sher 👇👇
@fkrlovelove
924
ሀይ ቤተሰብ እንደት ናችሁ...?
ተመልሰናል 👇👇👇👇
ብዙ ሰው የሚናገረው ነገ አንደበቱ እንደሚታሰር ሆኖ አይደለም ። ብዙ ሰው የሚሮጠው ነገ እንደሚቆም ዘንግቶ ነው ።
ብዙ ሰው የሚጨነቀው ሞት የሚባል ጥሪ እንዳለ ረስቶ ነው ። ሰው ሞት እንዳለ እያሰበ ቢራመድ አይደናቀፍም ።
ትልቁ ሞኝነት ወዳጅን እየቀበሩ እኔ አልሞትም ብሎ ማሰብ ነው ። ልጅን እየቀበሩ ገና ግፍ የሚሠሩ ወላጆች መኖራቸው ይገርማል ። ሞቱን የሚያስብ ትልቅ ጠቢብ ነው። የቀረን ዘመን በጣም አጭር ነው ።
የምንዘገየው ለጥቂት ቀን ነው ። ስለዚህ አንደበታችንን መጠበቅ አለብን ። ዘግይቶ የተፈታው አንደበት ቀድሞ ይዘጋልና ለአንደበታችን ጠንቃቃ መሆን ይገባናል ።
“እኔ መንገደኛ ተሸኝቶ አዳሪ ፣
ምን ክፉ አናገረኝ እንግዲህ ከቀሪ "
@fkrlovelove
@fkr_love_love
924
ማንም ምንም ሊልህ ይችላል። ህሊናህ እና ልብህ የሚልህ ግን እርሱ ብቻ እውነት ነው! ሰው ሊወድህም ሊጠላህም ፤ ሊያከብርህም ሊንቅህም ይችላል። ለሰው ብለህ አትኑር ልብህን ጠብቅ! ህሊናህን ተከተል። ✌🏾😍
924
ሁሉንም ማስደሰት አትችይም!
ነፍስሽ ምን ያህል ንጹህ ብትሆን እንኳን አንዳንድ ሰዎች ….. ምን አልባትም ሳይረዱት …ምን አልባትም ሳያስቡበት…. ወደራሳቸው አስጠሊታና መርዛማ ዓለም ሊስቡሽ ይሞክሩ ይሆናል-- ምክንያቱም ብቻቸውን በዛ ዓለም ውስጥ መሆን ያስፈራቸዋል፡፡ በራስሽ የሰላም ውቂያኖስ ውስጥ መንሳፈፍ ከቻልሽ፤ እነዚህ ሰዎች ከራሳቸው አለም ወደ አንቺ ዓለም እንድትጎትቻቸው እጃቸውን ይዘረጉልሻል፡፡
@fkrlovelove
@fkrlovelove
924
Repost from ጥበብ ፍልስፍና
📖ርዕስ:- ዮቶር ኮብላይ ካህን
📖📚ደራሲ:- አለማየሁ ደመቀ
📖ዘውግ፡- ልቦለድ
══════════════════
✅የአንድን ወጣት የመንፈሳዊ እድገት የሚያሳይ የተፈጥሮ ሚሰጥርን ሲመረምር፣ ሲተረጉምና ለሌሎች ሲያካል የሚስተዋልበት ድንቅ መጽሐፍ ነው፡፡ ታሪኩ የሚጀምረው በነገሮች አለመሳካት የተሰላቸ፣ በኑሮው የተማረረና ከፍቅረኛው የተጣላ (የተካደ) አንድ ወጣት ከከተማ ወጣ ብሎ በአንድ ጫካ ውስጥ ከራሱ ጋር ግለወግ በያዘበት ሰዓት በአጠገቡ አንድ ሰው ያልፋል፡፡ አልፎት ግን አልሄደም ይልቁን ሰላምታ ያቀርብለትና ስለራሱ ራሱ ብቻ የሚያውቃቸውን ዕውነቶች ይነግረዋል፡፡ በዚህም ግራ የተጋባው ወጣት ለዚህ ሰው ትኩረቱን ይሰጣል፡፡
✅ይህ ሰው ሽማግሌ ሲሆን ሳጥን የተጫነባት አህያ እየነዳ የመጣ ነው፡፡ ይህ መንገደኛ ሰላምታ ሰጥቶት የልቡን ሲያወራው ማንነቱን ለማወቅ ይሻል ፡፡ ‹‹ … እንዴት ታሪኬን ሳተውቅ ምስጢሬን ልታውቅ ቻልክ ይቅርታ አድርግልኝና አንተ ማነህ ›› ብሎ ሲጠይቀው የሚሰጠው ምላሽ ‹‹ … ስለ እኔ ማወቅ ከፈለክ ግን እኔ ካህን ነኝ፤ ገበሬም ነኝ፡፡ እንዲሁም መንገደኛም ነኝ፡፡ ዮቶር ብለህም ጥራኝ፡፡›› በማለት ይመልስለታል፡፡
በዚህ መልኩ ከዚህ ካህን ጋር ትውውቅ ይጀምራሉ፡፡ ይህ መሄጃ የጠፋው ዓለሙ የተገለባበጠበት ወጣትም በካህኑ የአብረን እንጓዝ ግብዣ ይስማማል፡፡ አብረውም ጉዞ ይጀምራሉ፡፡ በጉዟቸውም ጊዜ ብዙ ቃላዊና ተግባራዊ ትምህርት ይሰጠዋል፡፡
924
★★★
አንድ የህግ ባለሙያ በባቡር እየተጓዘ ሳለ አንድ
በጣም ቆንጆ የሆነች ልጅ መጥታ ፊት ለፊቱ ከሚገኘው ወንበር ላይ
ተቀመጠች። በዚህም የህግ ባለሙያው ደስ አለው። ቀና ብሎ ሲመለከታት አይን
ለአይን ተያዩ ከዛም ፈገግ አለች። አሁን ደግሞ በይበልጥ ደስ አለው። ትንሽ
ቆይታ አጠገቡ ሄዳ ተቀመጠች። በዚህን ጊዜ እጅግ በጣም ደስ አለው። ትንሽ
ቆየችና ወደ ጆሮው ጠጋ ብላ በሹክሹክታ "ያለህን ገንዘብ; የATM ካርድህን
ከነፓስ ዎርዱ እና የሞባይል ቀፎህን አሁኑኑ ካልሰጠኸኝ ስትጎነትለኝ እንደ
ነበረና ፆታዊ ትንኮሳ እንደደረሰብኝ እዚህ ባቡር ውስጥ ላሉት ሁሉ በመንገር
እጮኃለሁ።" አለችው። የህግ ባለሙያው በቸልተኝነት ቀና ብሎ ተመለከታትና
ከቦርሳው ውስጥ ወረቀትና እስክሪብቶ አውጥቶ እንዲህ ብሎ ፃፈላት "ይቅርታ
መናገርና መስማት የተሳነኝ ነኝ። እባክሽን ማለት የፈለግሽውን ሁሉ እዚህ
ወረቀት ላይ ፃፊልኝ።"
ልጅቷም ቀደም ብላ ስትነግረው የነበረውን ሁሉ ጽፋ ሰጠችው።
የህግ ባለሙያው ወረቀቱን ተቀብሏት በጥሩ ሁኔታ አጥፎ ኪሱ ከከተተው በኋላ
ከተቀመጠበት ተነስቶ ጎርነን ባለ ድምጽ ምን ቢላት ጥሩ ነው "አሁን
እንደፈለግሽ መጮህ ትቺያለሽ።"
የታሪኩ ምግባር: ሰነድን በአግባቡ መያዝ ምን ግዜም አስፈላጊ ነው።
@fkrlovelove
924
Repost from ግጥም
#አልተኛም_ከእንግዲህ
በህልም ዓለም መጥተሽ
በሁኔ ከማጣሽ
አትምጪ ልንገርሽ
ድሮም ስቃዬ ነሽ
ስተኛ አይሻለለሁ
ስነቃ አጣሻለሁ
አንቺ የጠዋት ጤዛ
መጥተሽ መሄድ በዛ
በህልሜ እየመጣሽ መንገዴን ከምስት
አልተኛም ከእንግዲህ አንቺን ላለማየት።
♡ ㅤ ❍ㅤ ⌲
ˡᶦᵏᵉ ᶜᵒᵐᵐᵉⁿᵗ ˢʰᵃʳᵉ
924
አንድ ቀን መምህሩ ወደ ማስተማሪያ ክፍሉ ከገባ በሁዋላ ተማሪዎቹን ለድንገተኛ ፈተና እንዲዘጋጁ ይነግራቸዋል። ተማሪዎቹ ያልጠበቁት ፈተና ስለሆነ በጭንቀት ጥያቄውን ይጠባበቁ ጀመር።
መምህሩ፣ ጥያቄ የሰፈረባቸውን ወረቀቶች ለተማሪዎቹ በጠረጴዛ በጠረጴዛቸው ላይ አስቀመጠላቸው። ከዚያ ወረቀቱን ለሁሉም ተማሪዎች ካዳረሰ በሁዋላ፤
‹‹አሁን መጀመር ትችላላችሁ›› አላቸው።
ሁሉም እየተጣደፉ ወረቀቱን ገልብጠው ሲያዩት አንድም ጥያቄ የለም። ደነገጡ። ከዚያ ልብ ብለው ሲያጤኑ ወረቀቱ መሐል ላይ አንዲት ጥቁር ነጥብ አለች… ከእሷ ውጭ ሌላ ነገር የለም። ዞር ዞር እያሉ እርስ በእርስ ተያዩ። መምህሩ ይሄን ግዜ እንዲህ አላቸው።
‹‹ወረቀቱን ስታዩ እንደተደነቃችሁ እያስተዋልኩ ነው። በሉ ያያችሁትን ጻፉ… ፈተናው ምን እንዳያችሁ በትክክሉ መጻፍ ነው።››
ተማሪዎቹ በድጋሚ ተያዩና ወደ ወረቀቱ አቀርቅረው የመሰላቸውን መሞነጫጨር ጀመሩ።
ለፈተናው የተመደበው ጊዜ አለቀና ወረቀቱ ሁሉ ተሰበሰበ። ከዚያ መምህሩ እያንዳንዱን ወረቀት እያነሳ ተማሪዎች የሰጡትን መልስ ጮክ ብሎ ያነብላቸው ጀመር። የሚደንቀው ነገር ሁሉም ተማሪዎች ለማብራራት ሲጣጣሩ የነበረው ስለዚያች ጥቁር ነጥብ እንጂ ስለሌላ ነገር አልነበረም።
ነጥቧን በተመለከተ እያንዳንዳቸው፥ ስለ ጥቁረቷ፣ ስላለችበት ቦታ፣ ስለ ግዝፈቷ፣ ስለሌላም ሌላም ጥቁሯን ነጥብ ስለተመለከቱ ጉዳዮች ትንታኔዎችን አቅርበዋል።
መምህሩ አንብቦ ሲጨርስ ዐይኑን መለስ ቀለስ እያደረገ የተማሪዎቹን ፊት ሲያስተውል ቆየ። ከዚያም ‹‹ተማሪዎች አንዳችሁም ትክክለኛ መልስ አልሰጣችሁም። ስለዚህ ይሄን ፈተና ውጤት አልሰጥበትም። ነገር ግን አንድ ነገር ላስተምራችሁ እፈልጋለሁ›› አላቸው።
ሁሉም ተማሪ መምህሩ የሚናገረውን ለመስማት ጓጉተው መጠበቅ ጀመሩ። መምህሩም ንግግሩ ቀጠለ።
‹‹ከመካከላችሁ አንዳችሁም ስለነጩ ወረቀት አልጻፋችሁም። ሁላችሁም ትንሽዬዋን ነጥብ ዐይታችሁ፥ ትልቁንና ሰፊውን ወረቀት እስከናካቴው ረሳችሁት።
በሕይወታችሁም ላይ አንዲት እንከን ስታገኙ በዚህ መልኩ ያላችሁን ጸጋ ሁሉ ጠቅልላችሁ የምትረሱ ከሆነ በጣም ትጎዳላችሁ።
በሚሊዮን የሚቆጠሩ መልካም ስጦታዎች እያላችሁ ስለ አንዲቷ እንከን አብዝታችሁ የምታስቡ ከሆነ እውነቴን ነው የትም አትደርሱም፤ ቆሻሻ ውስጥ ትቀራላችሁ።
የገንዘብ ማጣቱ አስጨንቋችሁ ታማርሩ ይሆናል፤ ነገር ግን ከገንዘብ የበለጠ ጥሩ ፍቅር፣ ጥሩ ጤና፣ ጥሩ ሰላም፣ ጥሩ ቤተሰብ ወዘተ ካላችሁ ዓለም ላይ ተዓምር መሥራት ትችላላሁ።
ስኬታማ ሕይወት ለመምራት ዋናው ነገር ያላችሁ ዐቅም ስፋት ላይ ማተኮር ስትችሉ እንጂ የጎደላችሁ ኢምንት ነገር ላይ ስታተኩሩ አይደለም።
እንዲህ ማሰብ ከጀመራችሁ ያለጥርጥር እንደ እናንተ ደስተኛ ሰው አይኖርም። በተቃራኒው ጉድለት ብቻ ተመልካች ከሆናችሁ ምንም ብታገኙ እርካታ የሚባል አይኖራችሁ።››
እንግዳውስ
አመስጋኝ ባሪያ እንሁን 🙏
👇👇👇👇👇👇
@fkrlovelove
@fkr_love_love
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ሁሉም ሰው ከሳቂታ እና ከተጫዋች እንዲሁም ሁሉም ደና ከሚባለው ማንነቱ ጀርባ ማንም የማያቀው ለሸክም የከበደ ብቻውን ያዘለው ሚስጥር ፣ በሰው ምን ይለኛል የተሸሸገ ፀባይ ወይም ለራሱ እራሱ በቃላት አውቶ እንዲህ ነው ብሎ የማይናገረው ሰቅጣጭ ያለፈ ታሪክ ፣ በሳቅ እና በተጫዋችነት እንዲሁም በዝምተኝነት ወይም እሷማ ግዴለሽ ናት በሚባለው ማንንት የተሸፈነ ድብቅ ማንነት አለን።
እናም ሀሉም ሰው ይሄን ማንነቱን አውቶ ለማሳየት እንዲሁም ለአይምሮውም ሆነ ለነፍሱ ስንት አመት ሙሉ ያስጨነቀውን ሚስጥር አንደራሱ ሚስጥር ጠብቆ ፣ ቁስሉን ተካፋሎ ሸክሙን ለማቅለል በጥሩ አድማጭ መደመጥን ይሻል። አድማጭ እና መደመጥ ...... ሲሰሙ ቀላል የመሰሉ ነገር ግን ተግባራቸው ረቂቅ የሆኑ ሁለት ቃላቶች! የሚሰማ ሁሉ አድማጭ አይደለም ፣ ጆሮውን ሰቶ ስለሰማህም ተደመጥክ አይባልም ።
ችግርክን ባይፈታልህም ፣ ያለፈ ታሪክህን ባይለውጠውም ፣ የቆሰለው ልብህን ባያድነውም ፣ ግን ያለ ምንም ግምገማ አና መጥፎ ተልእኮ፤ ንፁህ ልቡን አና ጆሮውን በሚሰጥህ አድማጭ በነፍስ ወዳጅ መደመጥን የመሰለ ነገር የለም። ምክኒያቱም ከህመም ሁሉ ህመም አለመደመጥ ነውና። የሚሰማ ፣ የሚያዳምጥ የሚረዳ መተንፈሻ ፣ጭንቀት አቅላይ ማልቀሻ ትክሻ አለማግኘት ነውና ። አዎ እሱ ህመም......የኔ የሚባል ሰው አቶ በጭንቀት እና በሀዘን አንዲሁም በሲቃ ብቻን መብሰልሰል..... እናም አድማጭ ሰውን የማጣት ህመም...ካለብን ጭንቀት እና ስቃይ ያየለ ነው። አናም ሰዎች በጥሩ አድማጭ ተደመጡ። እናንተም በዙሪያችሁ ላሉ ሰዎች ጥሩ አድማጭ ያድርጋችሁ።
join 👇👇👇
@fkrlovelove
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ማስመሰል ✍✍
ማስመሰል ማለት በአጭሩ የራሳችን ያልሆነ የሌላ ሰው ባህሪ መልበስ ወይም የራስህን ባህሪ በሌላ መተካት ማለት ነው ብዙ ጊዜ ሰዎል የሚያስመስሉ የሚፈልጉትን ነገር በቀላሉ ለማግኘት ይረዳቸዋል የሚፈልጉትን ካገኙ በኋላ እውነት አትደበቅም እና እውነተኛ ባህሪው ስገለጽ በፊት ስያስመስል ከነበረው እጅግ ተቃራኒ ሆኖ ይገኛል
በተለይ የብዙ ትዳር መፍረስ በፍቅረኛሞች መካከል ያለው አለመግባባት ከማስመሰል የመነጨ እንደሆነ ብዙዎች ይስማማሉ
የሚፈልገውን ለማግኘት ከልክ በላይ ደግነት ቅንነት ታታሪነት ይለብሳሉ ትኩረት መሳብ ስለሚፈልጉ ሁሉንም ለመሆን ይሞክራሉ
ለምሳሌ ; አስመስሎ በሁሉም ነገር ቅን በጎ ታገሽ ታታሪ ሆኖ ልብሽን ይስባል አላማው አንቺን ማግኘት ስለሆነ ሀሳብሽን ልክ ባይሆን እንኳ መቃወም አይፈልግም ፈገግታ የበዛል አንድ ቀን ግን ጠጥቶ ወይ ስሜታዊ ሆኖ ወደ እውነተኛ ባህሪው ስመለስ በፍጹም ሌላ ሰው ይሆናል ድንገት ከመንገድ ላይ የተጋጫችሁ ሰው ጋር ያለው አለመግባባት ያክል በመካከላችሁ ይፈጠራል ያኔ ፍቅር ይቅርታ ትዕግስት መተሳሰብ የለም መላያየት ብቸኛ መፍትሄ ታደርጊዋለሽ✍✍
join አድርጉ👇👇👇
@fkrlovelove
@fkt_love_love
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ወድቆ የማይቀር ማንነት!
ታላቅ ለመሆን ተፈጥረሀል! ደስተኛ ሆነህ ለመኖር ተፈጥረሀል! አሁን ያለህበትን አይተህ ራስህን ዝቅ አታርገው፤ ብርሀን ከጨለማ ጋር ምንም ህብረት የለውም፤ ያንተም ድክመት ወይ መሳሳት ጊዜያዊ ነው፤ ለምን ካልከኝ ጥሎ የማይጥል ፈጣሪና ወድቆ የማይቀር ማንነት ስላለህ!👌
Join us👇👇👇
@fkr_love_love
@fkrlovelove
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
``እያንዳንዱ ሰው በሌላ ሰው ጥላ ስር የሚኖር ፤ የሌላ ሰው አስተያየትና መላምት የእጅ ስራ ነው ። ራሳችን ከሆነውና ካደረግነው ይልቅ ሌላ ሰው ስለእኛ ያለው ሆዳችንን ይበላናል ። ሰው ራሱ ስለራሱ ሊፅፈው የሚችለው ስንት ቁምነገር እያለ ፤ ሌላ ሰው በፃፈው የግል አስተያየት ህይወቱን ማስተዳደሩና ማሸርገዱ ሰው የመሆን መራራ እውነታ ነው ።''
. . .
."ለምሳሌ ቆንጆ መልክሽና ተግባቢ ሰብዕናሽ በቀላሉ የሰዎችን ቀልብ ሊስብ ይችላል። ባህሪሽም ሰዎችን መርዳትና ቀርቦ ስሜታቸውን መረዳት ሳታስቢው የምታሳይው ዝንባሌ መሆኑ ደካማና የተዛባ የስሜት ስሌት ያላቸው ሰዎች በቀላሉ አንሻፈው ሊያነቡት ይችላሉ።
ለማገዝና ደግ ለመሆን ያደረግሽው ነገርም ለመቅረብ የምትቀይ አይነት መሆንሽ የይሁንታ ፈቃድ መስሏቸው ሰዎች በተሳሳተ መንገድ ሊረዱሽ ይችላሉ።"
👇👇👇👇
@fkr_love_love
@fkrlovelove
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ለምን እንዲህ ታደርጋለህ?
ለራስህ ክብርን ሳትሰጥ፤ራስህ ያላከበርከውን ማንነትህን ሌሎች እንዲያከብሩልህ ለምን ትመኛለህ?ራስህ ያልወደድከው አንተነትህን እንዴት ሌሎች ይወዱታል?...ብዙ ከንቱ ምኞት እንዳለህ አውቃለሁ ይሄን ግን ከሁሉ አብልጬ እጠላልሃለው።
እኔ ሁልጊዜ ለምን እያልኩ እጠይቃለሁ
ለምንድነው የሄደ የምለምነው?
ለምንድነው የማይገባኝን የምጠብቀው?(የሚገባውን ሳላደርግ )
ለምን ማነስ ለእኔ በቂ ሆኖ ተሰማኝ ?
ራስን መውደድ ማለት በብልጠት ለሰዎች የሚገባውን መንጠቅ አይደለም።እራሱን የሚወድ ሰው ከሚገባው በታች አይቀበልም።እራስህን ስትወድ ከሚገባኝ በላይ ስጡኝ ብለህም ሰዎችን አታስጨንቅም።
ለምንድነው?ሰዎችን ባለን ነገር በጠፊ ኮተት(ገንዘብ፣ልብስ...) እንዲወዱን እንዲያከብሩን የምንፈልገው?እሺ የሌለንስ ጊዜ ቢጠሉን፣ቢንቁን ስህተት ነው?እንደዛ እንዲወዱን አድርገናቸዋል።አየህ አንተም ጋር ችግር አለ።የሆነ ነገር አሳይተህ ያቀረብካቸው ወዳጆችህ ያጣህ ቀን መራቃቸው አይቀርም።(ባይርቁህ እንኳን አንተ እንደዛ ማሰብህ አይቀርም)
አንተ ላንተ ያልሰጠኸውን እንዴት ሌሎች ይሰጡሃል?ምንግዜም ሰዎች ባለህ ነገር ሳይሆን ባለህ ማንነት እንዲወዱህ ማድረግ ነው ያለብህ፤ማንነትህንም መልካም አድርገው ያኔ ከሌሎች መልካም መቀበል ይችላል።
ማንነት-"Defined personality"ይኑርህ በነፈሰበት አትንፈስ፤ሰዎችን ግራ አታጋባ።(ሰው ሁን!)
"ሰው የሆነ ሰው ሌላውም ሰው እንደ ራሱ ክብር እንዲገባው ያውቃል።ሰው የሆነ ሰው ሌላ ሰው አይንቅም!
@fkrlovelove
@fkrlovelove
ሼር 🙏🙏
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ሕይወት በትግል የታቀፈች አለም ናት። ሁሌ እንታገላለን። ያለ ትግል የምንውልበት ቀን የለም። ስለ ገንዘብ ፍላጎታችን ወዲህ ወዲያ ስንሮጥ እንውላለን; ስለ እውቀት ብለን ትምህርት ቤቶች ወይም አብያተ መጽሐትን እንጎበኛለን; ለቤተሰቦቻችን እና ለወዳጆቻችን ደስታ ከመገኛቸው አቅንተን እንጠይቃለን; በሥራ ስለተባለ አካላችን ረፍት ስንል ጥቂት ረፍት ወይም መዝናኛ ቢጤ እንቃርማለን። ሁሉንም ስንሰራ ታዲያ የፈጣሪ ፍላጎት መጠበቁን ስለመገምገም መዘንጋት የለብንም።
በኑሮ ትግላችን የምንመኘው ጫፍ ደስታ መሆኑ ግልፅ ነው። ሙሉ ቀን በስራ ተወጥሮ የሚውል ነጋዴ ወይም ሰራተኛ በሚያገኘው ገንዘብ ፍላጎቱን ያሟላል ወይም ደስታውን ይገዛል። የሀይማኖተኛ ደስታ በሞራል ስልት በተቃኙ ተግባራት ይደምቃል። ለዝህ ለዛው ደግሞ የፈጣሪውን ፍላጎት ይጠብቃል። ይህን በማድረጉ ደሞ ከሌሎች የተሻለ የትዕግስት ባለሟል ይሆናል።
👇👇👇👇👇
@fkrlovelove
@fkrlovelove
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ጊዜህን ቢራቢሮዎችን 🦋 በማባረር አታባክን ምክንያቱም የበለጠ ታሸሻቸዋለህ እንጂ አትይዛቸውም ይልቅስ ጊዜህን ቆንጆ የአትክልት ቦታ በመስራት ስታሳልፍ ቢራቢሮዎቹ በራሳቸው እንዲመጡ ታደርጋቸዋል!
☀️አንዳንድ በረከቶች አሳደሀቸው ሳይሆን ባንተ ተስበው ለመምጣት ያንተን የተዘጋጀ እና የተስተካከለ ነፍስ ይፈልጋሉ! ከሁሉ በፊት ቅድሚያ ራስህ ለይ አተኩረህ ስራ @fkrlovelove
@fkrlovelove
@fkrlovelove
Sher አድርጉ 🙏🙏
