ጥበብ ፍልስፍና
Open in Telegram
ተፈጥሮን በጥልቀት ተመልከት ያን ጊዜ ሁሉንም ነገሮች በተሻለ ትረዳለህ ፫፮፱ ፤ ሰዉም ትሆናለህ!!
Show more2 774
Subscribers
+124 hours
+207 days
+8430 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+41
in 0 channels
August '26
+145
in 0 channels
Get PRO
July '26
+142
in 0 channels
Get PRO
June '26
+84
in 0 channels
Get PRO
May '26
+118
in 0 channels
Get PRO
April '26
+86
in 0 channels
Get PRO
March '26
+62
in 0 channels
Get PRO
February '26
+45
in 0 channels
Get PRO
January '26
+54
in 0 channels
Get PRO
December '25
+66
in 0 channels
Get PRO
November '25
+75
in 0 channels
Get PRO
October '25
+74
in 1 channels
Get PRO
September '25
+117
in 0 channels
Get PRO
August '25
+93
in 0 channels
Get PRO
July '25
+80
in 0 channels
Get PRO
June '25
+88
in 0 channels
Get PRO
May '25
+111
in 1 channels
Get PRO
April '25
+176
in 1 channels
Get PRO
March '25
+115
in 0 channels
Get PRO
February '25
+108
in 0 channels
Get PRO
January '25
+241
in 0 channels
Get PRO
December '24
+237
in 0 channels
Get PRO
November '24
+249
in 0 channels
Get PRO
October '24
+223
in 0 channels
Get PRO
September '24
+107
in 0 channels
Get PRO
August '24
+245
in 0 channels
Get PRO
July '24
+88
in 0 channels
Get PRO
June '24
+44
in 0 channels
Get PRO
May '24
+91
in 0 channels
Get PRO
April '24
+140
in 0 channels
Get PRO
March '24
+90
in 0 channels
Get PRO
February '240
in 1 channels
Get PRO
January '24
+5
in 0 channels
Get PRO
December '23
+35
in 1 channels
Get PRO
November '23
+27
in 1 channels
Get PRO
October '23
+388
in 1 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 10 September | +1 | |||
| 09 September | +4 | |||
| 08 September | +4 | |||
| 07 September | +3 | |||
| 06 September | +4 | |||
| 05 September | +6 | |||
| 04 September | +5 | |||
| 03 September | +7 | |||
| 02 September | +4 | |||
| 01 September | +3 |
Channel Posts
| 2 | «If you kill a cockroach you are a hero. If you kill a butterfly, you are bad. Morality has aesthetic criteria.»
―Nietzsche
ይህቺ አባባል ጀርመናዊው ፈላስፋ ፍሬድሪክ ኒቼ በ #On_The_Genealogy_of_Morals መፅሐፉ ላይ የተናገራት ጠለቅ ያለች ፍልስፍና ነች። #On_The_Genealogy_of_Morality
ስለሞራል ምንነት ሰፊ ሃተታ ያደርጋል። ሞራል ከየት መጣ እንዴት ተፈጠረ የሚለውን በጥልቀት ይመረምራል፤ በተለምዶ «ጥሩ እና መጥፎ» የምንለው ፍርድ ትክክለኛው እውነት ሳይሆን ከታሪክ፣ ከሥልጣን፣ ከስነልቦናና ከማኅበራዊ ባህሎች የመጣ መሆኑን በደንብ አድርጎ ያሳየናል። ኒቼ የሚለን አብዛኛውን ግዜ የሰዎች ፍርድ በስሜት፣ በልማድ እና በባህል ግንባታ እንጂ በንጹህ ሎጂክ ላይ አልተመሰረተም ነው። በተለይ የብዙ ሰዎች ሥነ ምግባር በውበት ላይ የተመረኮዞ ፍርድ መሆኑን የሚያትትበት section አጥብቄ ነው የምወደው። በነገራችን ላይ ከካንት ቀጥሎ በ «ሞራሊዝም» ላይ ጥልቅ ትንታኔን ያደረገው ኒቼ ነው።
ኒቼ ሞራልን ወይም በአንድ ነገር ላይ መልካም እና ክፉ ብለን ፍርድ የምንሰጥበትን የስነ-ምግባር ባህሪን ከውበት ጋር አያይዞ ያነሳዋል። ልክ መልከ ጥፉን እንደ ክፉ፤ ቆንጆዎችን ደግሞ የጥሩ ስነ-ምግባር ባለቤት አድርጎ የመውሰድ ልማዳዊ አስተሳሰብ ነው። ለምሳሌ ሁላችንም በሚባል ደረጃ መኪና እየነዳን ከነፍሳት አንዷ በረሮ በጎማችን ብንጨፈልቃት ቅንጣት ታህል ምንም አይመስለንም። ለዛች በረሮ ጥቂት እንኳን የርህራሄ ልባችን አይከፈትም። ቢሆንም ግን በተቃራኒው በቀለማት ያሸበረቀች ወፍ ወይም አንዲት ነጭ ድቡልቡል ድመት በድንገት እየሮጠች መኪናችን ውስጥ ገብታ ብትገጭ ወፏም ሆነች ድመቷ መጎዳቷን አስመልክቶ ሀዘን ይሰማናል።
ይህ የተለመደ የአለም ህግ ነው፤ በአንድም ሆነ በሌላ በሰው ልጅ ነፍስ እና ስነልቦና ውስጥ ግራ የሚያጋባ ባህሪ ይንጸባረቃል። ደግ ልብ ያላት ሴት ለተራበው ውሻ አዝና ከተገደለው የበሬ ስጋ አጥንት አንስታ ትሰጠዋለች። ለውሻው አዝናለች ነገር ግን ልጅቷም ሆነች ውሻው ስለሚበሉት ስለዛ ታርዶ ስለተጣለው የእንስሳ ነፍስ በፍጹም አይራሩም። ስብሐት ገ/እግዝአብሔር #ሌቱም_አይነጋልኝ በሚለው መፅሃፍ ላይ #ፍልስፍና የምትል section አለች። ስብሐት በዛ ምዕራፍ ስር ስለሞራል ምንነት በጥቂቱ ገልጾ አልፏል። እንደውም ምን አለ.....
ትንሽ ብታስብበት መብላት እጅግ የሚያሳፍር ተግባር ነው። ቄራ ውረድና ለአንድ ሰአት ያህል አስተውል። በሬውን አንገቱን ገዝግዘው ሲያርዱት፣ ቆዳውን ሲገፉት፣ ብልቱን ሲለያዩት፣ ፈርሱን ሲጎለጉሉት ተመልከት። ሆቴል ግባና አይንህን ጨፍነህ ህዝቡ ሲያኝክ፤ አጥንት ሲቆረጣጥም ስማ። አክ..! ምን አይነት መጨማለቅ! ይሄ ሁሉ ያቺን የግማት ስልቻ ለመሙላት። ቀበቶህን ባጠበቅክ ቁጥር ፈርስ እንደምጨፈለቅ አስበህበታል? ። ልክ እንደ ጎለጎሉት የበሬው ፈርስ የሚመስል። ለመሆኑ በሬውን ሲያርዱት በስመአብ ብለው ሲጀምሩ አይገርመህም? እኔ በበኩሌ ይህን በስመአብ ብሎ ማረድ የጀመረው ቀልደኛ ቄስ ነው እላለሁ። ቀልድ ካልሆነ እንዴት የአብን ፍጡር በአብ ስም ትገድለዋለህ?»
ብቻ የፈለገውን ያህል ለማወቅ ብንጥር የሰው ልጅ ስነ ልቦና እጅግ በጣም የተወሳሰበ ነው። ቢሆንም ገገማ ሆነን ይሄን ለመረዳት ብንጥር መላውን ዩኒቨርስ የመረዳት ያህል ከባድ ሆኖ እናገኘዋለን። ለዛ ነው ኒቼ እንዲህ ያለው..
በረሮ ከገደልክ ጀግና ነህ፤ ቢራቢሮ ብትገድል መጥፎ ነህ፤ ሥነ ምግባር የውበት መሥፈርት አላት..»
| 890 |
| 3 | ሲኖር ብቻ የሚገባ ሙዚቃ.. ብቻ እየኖርን.... | 823 |
| 4 | "Would you die for me?"
"Yes"
"No.. no.. no! that's too easy. Would you live for me¿"
#Agape & #Eros
በዓለም ላይ ፍቅርን የወከሉ ሁለት መሠረታዊ ዋልታዎች ናቸው። አጋፔ መለኮታዊ ወይንም ለፈጣሪ ያለን ፍቅር ሲሆን seeketh not it's own የእኔነት ምንምነት የሚገልጽ እንኳን ሌላን ይቅርና እራስን ሙሉ በሙሉ ለእግዚአብሔር ፍቅር መስጠት ማለት ነው።
#The_Greek_god_of_erotic
ኤሮስ ወይንም የግሪክ የፍትወት አምላክ በመባል ይታወቃል። በስጋ አምሳል አስቀምጠው ከሞት በኋላ የማይዘልቅና ህይወት የሌለው 'ፍቅር' ቢያደርጉትም፤ በዘመናችን ኤሮስ የፈጠረው የሁለት ፆታ ግንኙነት ሞት ችሎ የማይበጥሰው ጠንካራ ትስስሮሽ እንደሆነ ተመልክተናል።
#Suicide_squad የተሰኘ ፊልም ላይ፤ 'ሃርሊ ኩዊን' የምትባል ሴት ጆከር እስር ቤት በነበረት ጊዜ ካለበት Psychopath/የእብደት ዓለም ለማስጠወጣት ስነ-ልቦናዊ እገዛ የምታደርግለት ዶክተር ነበረች፤ ኋላ ኋላ ግን በእርሱ ፍቅር ኩፍኛ ተይዛ የለየላት እብድ ሲወጣት ያሳያል። በፍቅሯ ውስጥ የጆከር ግዴለሽነት ተጨምሮ ለ Trauma/መቃወስ ይዳርጋታል። ይህ ምናባዊነቷ በዝቶ ሙሉ በሙሉ በመስጠም እብድ ወንጀለኛ ትሆናለች። የያዛት ፍቅርም #ኤሮሳዊነትን ጋርዶ የጆከርን ግዴለሽነት ውሃ ለበስ ያደርግበታል። ይህ ውትወታ ሲታክተው አንድ ጥያቄ ይጠይቃታል
- ለኔ ብለሽ ትሞቻለሽ?
‘አዎ!’
-አይ..አይ ቆይ ይህ ቀላል ነው፤ ለእኔ ብለሽ ትኖሪያለሽ !¿|
ይህ dialogue ተራ ቢመስልም እጅግ ጥልቀት ይታይበታል።
በአጋፔ ውስጥ አንድ ሰው ለፍቅር ብሎ ነፍሱን ለመስዋት ያቀርባል፤ ለዛ መለኮታዊ ፍቅርም ይሞታል። በተቃራኒው በፆታዊነት የተከበበው ኤሮስ ውስጥ አንድ ግለሰብ ለሚያቀረው ሰው እስከ ሞት ድረስ ይሄዳል። ነገር ግን በኤሮስ ውስጥ አፍቃሪው ለአንድ ሰው ሲል መስዋትነትን ቢመርጥም፤ አብሮ በመኖር ውስጥ ብዙ እንከንና መሠለቻቸት ምን አልባትም አንድ ሺህ አንድ ግዜም የመለያየት ሀሳቦች ተነስተው ይሆናል። ያ እንኳን ቀርቶ አንድ ሰው ከመኖር ህላዌነት አልፎ ለሚያፈቅረው ሰው እንዲሞት ግድ ሲሆንበት ክህደት ሲፈጽም ይታያል። ይህን ታላቅና ጥልቅ በሚባለው አጋፔ ውስጥ ይሁዳ እና ጴጥሮስ በመጨረሻ ለክርስቶስ ያላቸውን መለኮታዊ ፍቅር ሲፈተን ማየት በቂ መገለጫ ነው።
በአጋፔ ውስጥ ሰው ለፈጣሪው ፍቅር ሊሞት ሰማዕትም ሊሆን ይችላል ይህ ቀላል ነው። ነገር ግን ለእግዜሩ ብሎም ለሃይማኖቱ ሲል በመሰቃየት እንግልትንም በማየት ባጭሩ በመኖር አገልግሎት ውስጥ እስከመች ይዘልቃል?። ለዚህ መልስ ሊሆን የሚችለው በእኛ ሀገር ተፈጥረው ለነበሩ #Religion_paradox ስሜት አዘል መልሶች ናቸው። ሃይማኖታቸው ወይንም አምላካቸው የሚገፋ ተግባር ሲፈጸም ይህን ግፍ ለመቃወም እስከሞት ድረስ የሚደርሱት ሃይማኖታቸው ላይ ብዙም ጠንካራ ያልሆኑ ሰዎች ናቸው። እነዚህ ግለሰቦች በህይወታቸው ውስጥ አገልግሎታቸውን ለፈጣሪ ያልሰጡ ሆነው ሳለ ለፈጣሪ ለመሞት ግን ከእነርሱ በላይ የሚፈጥን የለም። በዚህ መስዋት ወይንም 'ሰማዕት' መሆን የበፊት እድፋቸውን በጠቅላላ የሚጸዳ ነው ተብሎ ስለሚታሰብ ይህ አቋራጭ መንገድ ይበል የሚያሰኝ ተመራጭ መንገድ ሆኖ ተቀምጧል።
በመጨረሻም ለፍቅር ወይንም ለምንወደው ነገር ብለን የሞት ሰይፍ ውስጥ አንገታችንን ለማስገባት ከመሮጣችን በፊት፤ እራሳችንን እንጠይቅ። ለዛ ነገር ለመኖር ዝግጁ ነበርን ወይ..¿ | 1 510 |
| 5 | No text... | 1 057 |
| 6 | #Stockholm_Syndrome
የሆኑ ሰዎች አትታዘቡም ከሚቀጠቅጣቸው ሰው ጋር በፍቅር ሲወድቁ : የሚያንቋሽሻቸውን ፍቅረኛ የሚመርጡ : ደስታ ከማይሰጣቸው ሰው ጋር ክንፍ የሚሉ : ሁሌ እየጠጣ እየገባ የሚያሰቃያትን ባል በፍቅር እያበደች አትንኩብኝ የምትል?
ታዲያ ለምን እንዲ እያሰቃያት አትፈታውም? ለምን ጥላው አትሄድም? ብላቹ ግራ ይገባቹሀል አይደል። ሁኔታውን ብትረዳው ምናልባት ልትረዳቸው ትችላለህ። ነገሩ #Stockholm_Syndrome ይባላል : በዚ ችግር የተጠቁ ሰዎች በቃ በፍቅር ክንፍ የሚሉት ከሚያሰቃያቸው ሰው ጋር ከሚያንገላታቸው ሰው ጋር በፍቅር ያብዳሉ። እንደ ሌላው ሰው በፍቅር የሚያሽሞነሙናቸው ሳይሆን አሳራቸውን ከሚያበላቸው ሰው ጋር ነው ጨርቃቸውን የሚጥሉት።
የቃሉ ስያሜ የመጣው በ 1973 GC በስዊድን stockholm በሚባለው ግዛት በነበረ የ አንድ ባንክ ዘረፋ ወቅት ነው። ዘረፋውን ለማከናወን አጋቾቹ ለ ስድስት ቀን የባንኩን ሰራተኞች አግተዋቸው ነበር። በዚህ በስድስት ቀን ውስጥ በነበራቸው ግንኙነት በእገታው ጊዜ ከነበረ ሁኔታ ነው። በቃ ታጋቾቹ በፍቅር ከነፉ ከዘራፊዎቹ ከእገታውም ቡኋላ ለሌቦቹ ሲከራከሩና መረጃ ሲደብቁ ተስተዋሉ ያኔ ነው ይሄን አይነትም ችግር አለ ብለው አፅንዖት የሰጡት ለጉዳዩ።
እና ይሄ ችግር ካጠቃህ የሚያሰቃይህን ሰውዬ በፍቅር ክንፍ ትላለህ። አንዳንዴ ያቺ አፄ ቴዎድሮስ ቤተሰቧን በሙሉ ገሎባት እየተከታተለች ስትሰድበው ኖራ በመጨረሻ እራሱን ሲያጠፋ እንደገጠመችለትና እንዳለቀሰችለት ታሪክ ላይ ይነገራል እንግዲህ #Stockholm_syndrome ማለት ይህ ነው።
#Explore_ur_mentality | 1 274 |
| 7 | መላእክትና ጻድቃን ያለ ጉቦ በማይሠሩበት ሀገር የትራፊክ ፖሊሶችና ገቢዎች ላይ ማካበድ አግባብ አይደለም!፡፡ ስእለት, ነዝር ይባላል እንጂ ያው ጉቦ ነው የምድሩን ጨርሰህ ሰማዩንም ብራይብ ታደርጋለህ። ሼኪው ያለ ጉቦ (የበርጫ ¡ ካልተሰጠው ዱአ የማያደርግበት ፓስተሩ ያለ ጉቦ ጸሎት የማይጸልይበት ቄሱ ያለ ጉቦ የማይፈታበት ኑሮ ውስጥ እየኖርክ ዓለማውያን በምን ዕዳቸው ነው በነጻ የሚሠሩት? ባይሆን ባያበዙት። መንግሥትም ጉቦን ለማጥፋት ባይደክም ጥሩ ነው። ጻድቃን ሙስና እየላፉ ኃጥኣን ጻድቃን ይሁኑ ማለት በቀላሉ አይሳካም። | 1 301 |
| 8 | ፍቅረኛዬ እግሮቿ ውብ ናቸው። በየትኛውም አምሳለ ፍጡር ያልተሳሉ፣ ያልተቀረጹ። በራስ ቤት ነው ያደገቸው፣ የራስ ልጅ፡፡ ጠቢባን እሑድን ማኅሌት አድርሰው ሲመለሱ ቁርስ አፋቸው አድርገው ጌቶች ለስብሰባ እስኪጠሩዋቸው የልዕልቲቷን እግር እንዲስሉና እንዲቀረፁ ተፈቅዶላቸዋል፡፡
በቀደሙት ሳምንታት የምትወደው ክፍለ ጊዜ ነበር በቆይታ መሰላቸትን አመጣች በዛ ላይ አንጀት አርስ ሰዓሊ ልብ የሚሞላ ቀረፂ አለመገኘቱ ያዝላት ተያያዘ፡፡ ከፊቷ ተጎልተው እኒያ ጠቢባን እግሮቿ ላይ ተተክለው ሲያፈጡ እርሷም ደፋ አለች የዓይኖቿ ብርሃን ከእግሮቿ ሳይደርሱ መከፋትና ፅንስ ያረገዘው ሆዴ መንገዷን ገታት፡፡ ዐይኗ እንባ አቀረረ ፊቷ ፍም መሰለ በራስ ቤት አንዲት ዘለላ እንባ እንኳ ማውረድ የተከለከለ ነው
ያን ያደረገች እንደሆነ በተለይ እንግዶች ፊት፣ እንደ አሽከር መታጠቂዋ ተፈቶ ጀርባዋን ትገረፋለች፡፡ ያን ለመቀበል አልፈለገችም ጭኗን በእጇ ዳመጠችውና ከእንባዋ ቀድማ ፈንደድ ብላ ተነሳች። እኔም የራስ ልጅ ነበርኹ አዪ ''ነበር ለካ እንዲ ቅርብ ነው'' አሉ የብጡል ልጅ እቴጌ ጣይቱ እውነትም ነበር ለካ እንዲ ቅርብ ኑሯል በዛን ሰንበት እነርሱ ግዛት ለአባቷ ከአባቴ የተላከ ሥጦታን ለማስረከብ ስጋልብ አርፍጄ በጊዜ ደረስኩ
የልዕልቲቱ አባት ከመኝታ ቤታቸው ነበሩና ከሰፊው ክፍል እንድንጠብቅ በአክብሮት ተጋበዝን አንድ ፈርጣማ ወጣት እየመራን አስገባን ያኔ ነው ከልዕልቲቱ እንባ ያቀረሩ ዐይኖች ጋር የተላተምነው። እምታምር እንቡጥ ደም ግባታም ሴት ነች ለአፍታ ዐይኗን ሰርስሬ ዐየሁት ጠቢባኑ የተተከሉበት እግሮቿን በዓይኔ ሰረሰርኩት፣ ፍም እሣት ነው ለበለበኝ፣ ጉልበቴ ሊረድ ዳዳው። እጅ ነሳኋት፥ እጅ ነሳችኝ ።
የአግርሽ ውበት ፈጀኝ አልዃት 'ውሰደኝ' አለችኝ። ሻሞላዬን ከሰገባው መዘዝኩ መልካም የተቀበለን አገልጋይዋ ጦሩን ቀሰረ:: ጠባቂዎቼና ጠባቂዎቻቸው መሳሪያ ተለካካን ተጎዳዳን በግርግር እንደ አዲስ ሙሽራ አቅፌት ወጣሁ። እየጋለብን ጠፋን ተሰደድን፡፡ አሁን እርቀን እንኖራለን ዛሬም እሑድ ነው እረፋዱ ላይ።
ከመስኮቱ ጎን የሙላቱ አስጣጥቄን ጃዝ እንሰማለን የቡና ጭስ በስሱ ወደ ሰርናችን ይገባል ፤ ቀሚሷን እስከ ጉልበቷ ሰበሰበችው ሔድኹ እግሯን ሳምኩት በወይራ ዘይት ውብ እግሮቿን ታፋዬን አስረግጬ ከባቷ እስከ ጣቶቿ ጫፍ..... ፤ ያን ዕለት ሰንበት ስለሆኑት ነገሮች እያወጋኋት እየተረኩላት፣ አሻታለሁ። የአባቷን ስም ስጠራ ቅርም ንድድም ይላታል ናፍቃለችም፡፡ በግዛቴ ሳለሁ አንዲት የራስ ልጅ ከአባቷ እንዳረገዘች ይነገር ነበር፡፡ አንስቼባት አላውቅም። እንባዋን አልሻም፡፡ ባባቷ ግዛት መሳል መቀረፅ አልፈለገችም በራሷ ግዛት መዳበስ መፃፍ ነበር የፈለገቸው። ቸሩ መድኀንያለም የልቧን መሻት ፈፀመ ፡፡ | 1 393 |
| 9 | No text... | 1 424 |
| 10 | #Ego #ንቁ_አእምሮ
ታዋቂው የስነ-ልቦና ጠበብት #Carl_Gustav_Jung የሰው አእምሮ (psyche) እጅግ ውስብስብ የስነ-ልቦና ስርዓት (Analytical Psychology) አለው ይለናል።በተለያዩ የማንነት ክፍሎችም የተዋቀረ መሆኑንም ይገልፃል። ከነዚህም ክፍሎች ውስጥ አንዱ ኢጎ ነው።
"#Ego" (#ኢጎ ) በትክክል ምንድነው?
እንደ ዩንግ እይታ፣ ኢጎ የንቁ አእምሯችን #Consciousness ማእከል ነው። "እኔ" ብለን የምንጠራው ማንነታችን (Identity) ሁሉ በኢጎ ስር ይጠቃለላል። ኢጎ ከልጅነታችን ጀምሮ እኔ ብለን የምንገልፀው ባህሪያችን፣ ስራችን፣ የምንወደውን ነገር እንዲሁም በንቁ ትውስታችን ያለ ሁሉ ከዚህ የአእምሯችን ክፍል ጋር ይገናኛል።
ኢጎ አለምን ከራሳችን አንፃር የምንተረጉምበት እና ህይወታችንን የምንመራበት አቅጣጫ የሚወስንልን የማንነት ክፍል ነው። እንዲሁም በስራ ፣ በቤተሰብ ፣ በማህረሰብ ውስጥ ራሳችንን የምናስቀመጠው ቦታ እና ያለንን ሚና (value) የሚቆጣጠር ነው።
– እንደ jung ማብራሪያ ኢጎቸው ያለደገ ሰዎች ከሰዎች ጋር ባላቸው ግንኙነት መስመር (boundary) የሌላቸው በመሆኑ በሰዎች መጠቀሚያ ለመሆን የቀረቡ ናቸው። እንዲሁም ራሳቸውን የማይከላከሉ ፣ የራሳቸውን ክብር የማያስጠብቁ በመሆናቸው በሌሎች ፍላጎትና ተፅዕኖ ስር የመውደቅ ዕድል አላቸው ይለናል።
– ኢጎቸው ከመጠን በላይ ከፍ ያሉ ሰዎች ደግሞ ለራሳቸው የተጋነነ ግምት ያላቸው ሲሆን በየትኛውም ሁኔታ እነርሱ ብቻ ትክክል እንደሆኑ ያስባሉ። ከዛም አልፎ የራሳቸውን ጥቅምና ክብር ለማስጠበቅ የሰዎችን ህይወት ያመሰቃቅላሉ።
ኢጎ ሊዛነፍ የሚችልብት ሁኔታም ይኖራል። በልጅነታችን ቤተሰብ ወይም ማህብረስብ የተጣመመ ማንነት ሰጥተውን ካደግን ያ ማንነት አድገን ራሳችንን በምንፈልግብት ጊዜ እንደ ማነቆ ሆኖ ላያራምደን ይችላል።ከዛ ማንነትም ለመላቀቅም ረጅም ጊዜ ሊወስድብን ይችላል።
ኢጎ ከገንዘብ፣ ከቁስ ፣ ከዝና ወይም ከሌሎች ነገሮች ጋር የበዛ ቁርኝነት ካለው ደግሞ የስቃይ ምንጭ ይሆናል።ለምሳሌ ከገንዘብ ጋር የበዛ ቁርኝነት(attachment ) ያላቸው ሰዎች በህይወት ያለቸው ደስታ እና ሰላም በዛ ነገር ማግኘት እና ማጣት ላይ ይወሰናል። የተቆራኙትን ነገር ባጡት ጊዜም የማንነት ቀውስ (identity crisis) ሊያጋጥማቸው ይችላል።
እንደ ዩንግ እሳቤ ኢጎ ከማንነታችን ጋር ያለውን ጉዳዮች የሚወስልን የ concious mind ማዕከል ስለሆነ ህይወትን ትርጉም ባለው መንገድ ለመምራት ይጠቅመናል ሆኖም ግን ኢጎአችን ጤናማ ና የተመጣጠነ (balanced) ሊሆን ይገባል ይለናል።
#Explore_ur_mentality | 1 413 |
| 11 | “ እነሆ የምስክርነቴን ሽንቁር እደፍን ዘንድ ጀርባዬን ለሰጠሁት መልክአ ምድር ደረቴን አቀበልኩ። ወገኖቼ እንደገቦ ፍሬ በያሉበት ተንጠባጥበው ዐየሁ። ሕብረት አጥተዋልና በጥንቱ ኩራት ፈንታ ከፊታቸው ፍርሐትና ድንጋጼ ወሯቸው ዐየሁ። በምድራቸው ሁሉ ፈጣሪያቸው ጆሮውን አላዘነበለም። በፊታቸውም መልካም ሆኖ የታያቻውን ኹሉ ሳይመረምሩ ያደርጋሉ። "
“ ወገኖቼ ከማነሳቸው የተነሳ ዕውነትና ትዕምርት ቀርቶ ውሸትና ቅዥት እንኳ መለየት የማይችሉ ኾነዋል፣ ሲገድሉም ኾነ ሲሞቱ አለማወቅ ውስጥ ኾነው በኩራት ተንጠርብበው ነው።"
"አባቶቻችን ብቻ ሳይሆን ወንድሞቻችንንም አጥብቀን የምንጠላ ኾንን። ይኸው እዚህ ደረስን። ከእዚህ ማን ያውጣን? ጌትነታችን አባቶቻችን በገነቡት ቤት ውስጥ ቀርታለች። “ዓመቶች እየቀጠሉ በኼዱ ቁጥር ባልደረሱ የተሻለ ነበር የሚያሰኙ የሚታዩና የሚያሰቃዩ ብዙ ነገሮች አሉ” እንደተባለ ፣ እንዲሁ ሆነ።"
"ሀገር የማይተማመኑበት ሽሽት ኾኗል። ህዝቡ ወዴት? እንዴት? እንደምን? ለምን? እንደሚኼድ የማያውቅ ደራሽ ኾኗል። ”
“ እንደመስቀል ደመራ ከየቤቱ የተውጣጣ የክፋት ችቦ ለኩሰናል። እኛኑ መልሶ እስኪያቃጥለን ድረስ በደስታ ሞቀነዋል። ”
ከፈሪሳ የመፅሀፍ ገፆች የተቆነጠሩ መስመሮች | 1 027 |
| 12 | ዴዚዴራታ
በዚህ ዓለም ጥድፊያና ውካታ ሳትበገር በርጋታ ኑር። ከጸጥታ ሰላም ሊገኝ የሚችል መሆኑንም አትዘንጋ ያለ አግባብም ሳትበለጥ የተቻለህን ያህል ከሰዎች ሁሉ ጋር ስምምነት ይኑርህ። እውነት ነው ብለህ የያዝከውን ነገር በጥሞና እና በግልጽ ከመናገር ወደ ኋላ አትበል። ሌሎች የሚናገሩትን ከመስማትም አትቦዝን። ሆነ ብሎ ለሚያዳምጣቸው ከዳተኞችም ሆነ ከደደቦች ቁም ነገር አይታጣም ከጯሂዎች እና ከእኔ አለሁ ባዮች ራቅ፤ እንዲህ ያሉ ሰዎች መንፈስን ያውካሉና። ራስህን ከሌሎች ሰዎች ማመዛዘን ከያዝክ እብሪተኛና መንፈሰ መራራ ልትሆን ትችላለህ። ምክንያቱም ከሰዎች መካከል ካንተ የሚበልጡም የሚያንሱም አይታጡም። በምትሠራው ሥራ መሳካትም ሆን በወደፊት ውጥንህ ተደሰት ፤ የምትሠራው ሥራ ዝቅተኛም ቢሆን የእኔ ነው ብለህ ያዘው። በዚህ ወረቱ ተለዋዋጭ በሆነ ዘመን የሚያዋጣው የአንድ ሙያ ባለቤት ሆኖ መገኘቱ ነው። ዓለም በሸፍጥ የተሞላ በመሆኑ ገንዘብን በሚመለከት ነገር ጥንቃቄ አይጉደልህ። ይህ ሲባል ሰው ሁሉ ክፉ ነው ብለህ በደፈናው አትገምት። ከፍተኛ ቁም ነገር ያለው ተግባር ለመፈጸም የሚጣጣሩ ብዙ ሰዎች መኖራቸውን እና ሕይወትም ብዙ ጀብዱ የሞላበት መሆኑን አትሳት። በራስህ ተማመን!። በተለይም ፍቅር ማስመሰልን የሚጠላ መሆኑን እወቅ። እንዲያውም ፍቅር በዘፈቀደ የሚታለፍ ነገር አይደለም። በዚህ የመንፈስ ድርቀትና መሰልቸት በሚያጠቃው ዓለም እንደ ሜዳ ሳር ጠውልጎ የሚለመልም ፍቅር ብቻ ነውና የወጣትነት ወራት ፍላጎትህ ብዙ ዘመን ለተጠራቀመ የሽምግልና ምክር በለዘብታ ይገዛ። ሳታስበው ለሚያጋጥምህ መከራና ችግር ድጋፍ እንዲሆንህ የመንፈስ ጽናት ይኑርህ። ሆናም እንዲህ ያለ ነገር ሳይደርስብኝ አይቀርም እያልክ በከንቱ ልብህ አይታወክ፡ ብዙውን ጊዜ ፍርሃት የሚመነጨው ከመዳከምና ከብቸኝነት ነው። ወግ ባለው ሁኔታ ኑሮህን መቁጣጠር አስፈላጊ ቢሆንም እንኳን፣ ራስህን መንከባከብ ቸል አትበል ከዕፅዋትና ከከዋክብት የማታንስ የዚህ ታላቅ ፍጥረተ ዓለም ዝርያ ስለሆንክ፣ በዚች ዓለም ላይ የመኖር መብት አለህ። ሁኔታው ላንተ ግልጽ ሆኖ ባይታይም፤ ይህ ታላቅ ፍጥረተ ዓለም ያለ ጥርጥር ምስጢሩ እያደር እየተገለጠ በመሄድ ላይ ይገኛል? ስለዚህ ሕሊናህ አውጥቶ አውርዶ ከተቀበለው አምላክ ጋር ግንኙነትህ የሠመረ ይሁን ከትግልህና ከወደፊት ምኞትህ ጋር በዚህ ትርምስ በበዛበት ዓለም ስለምትኖር ለነፍስህ ሰላም አትንፈጋት ከክፋቱም፣ ከልፋቱም ሆነ ከውጣ ውረዱ ጋር ይህ ዓለም ግሩም ስፍራ ነው። እንግዲህ ለኑሮህ እወቅበት። ደስተኛ ለመሆንም ተጣጣር።
@ethiosecret | 1 499 |
| 13 | No text... | 1 |
| 14 | ከእውቀት ጥበብ ይበልጣል ፤ ከጥበብ እውነት ይበልጣል፡፡ እውቀት መናገር ነው። ጥበብ የሚናገሩትን ማወቅ ነው። እውነት ያወቁትን መሆን ነው! የምንናገረውን ሁሉ አናውቀውም ይህ እውቀት ነው፡፡ የምናውቀውን ሁሉ አንናገረውም ይህ ጥበብ ነው። ነገር ግን መሆን ስለራሱ ይናገራል ይህ እውነት ነው!!
@enlightment33 | 1 097 |
| 15 | የሶቪየት ሶሻሊስት ሪፐብሊክ ህብረት (USSR) ብሔራዊ መዝሙር (1977-1991) በታዋቂው የሩሲያ አቀናባሪ አሌክሳንደር ቫሲሊየቪች አሌክሳንድሮቭ (1883-1946) በ 1938 ዓ.ም. አካባቢ ተቀናብሯል። መጀመሪያ ላይ ለቦልሼቪክ ፓርቲ መዝሙር እንዲሆን የተሰራ ነበር። ግን በ 1944 ዓ.ም. (በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት) ይፋዊ ብሔራዊ መዝሙር ሆነ። የመጀመሪያው ግጥም በሰርጌይ ሚክሃልኮቭ እና ጋብሪዬል ኤል-ሬጊስታን የተፃፈ ሲሆን የጆሴፍ ስታሊንን ስም በግልጽ ያካተተ ነበር። ከስታሊን ሞት (1953) በኋላ፣ በ1956 ዓ.ም. በተጀመረው ዲ-ስታሊናይዜሽን (ከስታሊን አምባገነናዊነት የመላቀቅ) ምክንያት፣ መዝሙሩ ለ20 ዓመታት ያህል ያለ ግጥም መሳሪያ ቅንብር ብቻ ይቀርብ ነበር። በ1977 ዓ.ም. የጥቅምት አብዮት 60ኛ ዓመት እና አዲሱ የሶቪየት ህገ-መንግሥት ክብረ-በዓል በማስመልከት ሰርጌይ ሚክሃልኮቭ የቀድሞውን ግጥም በማሻሻል አዲስ መዝሙር አዘጋጀ። ስታሊንን የሚያወድሱ ክፍሎች ተወግደው የጦርነት አውዶች ተለውጠው እና በኮሙኒዝም ድልና የህዝቦች አንድነት ተተክተዋል። ይህ መዝሙር እስከ 1991 ዓ.ም. የሶቪየት ህብረት መፍረስ ድረስ አገልግሏል። ዛሬም ይህ ዜማ በተለያዩ ግጥሞች በሩሲያ ብሔራዊ መዝሙር ሆኖ ቀጥሏል። ሙዚቃዊው ባህሪያቱ የአሌክሳንድሮቭ ዜማው ጀግነትና፣ ድፍረት እና ሐያልነት የያዘ እና በጣም ማራኪ ዜማ ያለው ነው። በሩሲያ ባሕላዊ ዘፈኖች፣ የቤተ-ክርስቲያን ዝማሬዎች እና የወታደራዊ ሰልፍ ሙዚቃ ተጽዕኖ ያደረበት ዜማ ነው። ዜማው አንድነትን ታላቅነትን፣ ኩራትን እና የብሩህ የወደፊት ተስፋን ያስተጋባል። በትላልቅ ስታዲየሞች፣ በወታደራዊ ሰልፎች ወይም በታሪካዊ ፊልሞች ሲደመጥ የሚፈጥረው ተጽዕኖ አስደናቂ ነው። ብዙ ሰዎች ይህን ዜማ ከዓለም ምርጥ ብሔራዊ መዝሙሮች ጋር ያወዳድሩታል። የግጥሙ ትርጉም የህዝቦች አንድነትን፣ የሌኒን ፓርቲን፣ የኮሙኒዝምን ድል እና ለቀይ ባንዲራ ያለውን ታማኝነት ያወድሳል። ግጥሙ ባጭሩ ...
አልል በይ፣ ነጻዋ የአባት ምድር፣ የህዝቦች ወዳጅነት የጸናው ምሽግሽ! የሌኒን ፓርቲ የህዝቡ ብርታት፣ ወደ ኮሙኒዝም ድል ይመራናል! ማይሞተው የኮሙኒዝም ዕሳቤ ድል ውስጥ፣ የሀገራችንን ብሩህ ተስፋ እናያለን። ለክብርት እናት ሀገርና ለቀይ ሰንደቅ ዓላማዋ፣ ሁልጊዜም በታማኝነት እንቆማለን!
ይህ መዝሙር የሶቪየት ርዕዮተ-ዓለምን የአንድነት፣ የጥንካሬ እና የተስፋ በጥሩ ሁኔታ የሚገልፅ ሲሆን ታሪካዊ ጠቀሜታው እጅግ ትልቅ ነው። ☭ ✊☭ | 1 191 |
| 16 | No text... | 842 |
| 17 | #MEMENTO_MORE
ሕይወት ከባድ ነች - በጭንቀቶች፣ በውጥረት፣ በአስፈሪ ክስተቶች የተሞላች፡፡ እና ይህንን ሁሉ _ ጠራርጎ ለማስወገድ ምን ማድረግ ይኖርብናል? እንዴትስ እነዚህን ሁሉ ችግሮች እንደ ተራ ነገር ንቀን ልናልፋቸው እንችላለን? .... ፍልስፍና ቀላል ሆኖ ሊተገበር የሚችል መፍትሄ ያቀርብልናል #MEMENTO_MORE
"#MEMENTO_MORE " የላቲን ሃረግ ሲሆን ትርጓሜውም “እንደምትሞት አስታውስ” ማለት ነው። አይቀሬ ስለሆነው ሞት ስታስብ ለዚህ ሁሉ ጥቃቅን ጉዳይ መጨነቄ አግባብ ነው ወይ? የሚል ጥያቄን ታነሳለህ። የሮም ንጉስ እና ፈላስፋ የነበረው #ማርክስ_አውሬሊየስ ይህን ሃሳብ አጥብቆ ይወደዋል። ሞት ተፈጥሯዊ እና አይቀሬ ነው እናም ንብረትን ለማፍራት መሮጥ፣ አለማዊ ሃብትን ማሳደድ... ይህ ሁሉ ልፋታችን ይዘነው ለማንሄደው ኮተት ነው ይለናል፡፡ አንድ ቀን አፈር እንሆናለን፤ ስለምንስ ምድራዊ ጊዜያችንን በጭንቀት ውስጥ እናሳልፋለን?
በጥንታዊ ግብጻውያን ዘንድ አንድ ባህል አለ፤ በታላቅ ግብዣ ወቅት ግብር አሳላፊው በማድረቂያ መድሃኒት የደረቀ የሞተ ሰው አስክሬን ይዞ ይመጣል ፤ በታዳሚዎችም ፊትም ይዞት ይዞራል፤ እንዲህም እያለ ይጣራል - “በቅርቡ እንደዚህ ትሆናላችሁና ብሉ ... ጠጡ.. ተደሰቱ ፤ #ጠቢቡ_ሰለሞንም በመፀሀፈ መክብብ ላይ እንዲህ ይለናል ... ከሚበላውና ከሚጠጣው ደስም ከሚለው በቀር ለሰው ከፀሐይ በታች ሌላ መልካም ነገር የለውምና እኔ ደስታን አመሰገንኩ ከፀሐይም በታች ከድካሙ እግዚአብሔር በሰጠው በሕይወቱ ዘመን ይህ ደስታው ከእርሱ ጋር ይኖራል።”
ፈረንሳዊው ፈላስፋ #ሚካኤል_ዴ_ሞንቴን " ከቻልን ሕይወታችንን ከመቃብር ስፍራ አጠገብ እንኑር ይለናል፡፡ “የሞትን እንግዳነት እንቀማው፤ ሞትንም እንላመደው” ሲልም ጽፏል። ሞትን ማስታወስ ስለ መዋቲነት መቆዘም ማለት አይደለም፤ ይልቁኑ መኖር እንዳለብን ማስታወሻ ይሆነናል፡፡ “ነገ ልሞት ነገር፤ ዛሬ ላይ ይህ ሁሉ ጭንቀት ምንድን ነው?” የሚልም ሃሳብ ይፈጥርልናል፡፡
በመካከለኛው ዘመን የነበሩ ፈላስፋዎች በቤተ መጻህፍታቸው ውስጥ የሰው የራስ ቅል ቅርጽ ያስቀምጡ ነበር፡፡ ይህንን ያደረጉትም ሞትን አቅርቦ ለማሳየት እና እየኖሩት ያለው ሕይወት ይበልጥ ጣፋጭ እንዲሆን በማሰብ ነው፡፡ ከቻልክ አሁኑኑ ሞክረው፤ ስለምትሞትባት ቅጽበት አስብ፤ እንደውም መቼ፣ የት፣ ለምን እና እንዴት እንደምትሞትም በጥልቀት አስብ፡፡ ፍርሃቱ ይሰማህ ፤ ከሞት በኋላ ስላለው የማይታወቅ ዓለም፣ ከምትወዳቸው እና ከሚወዱህ ወዳጆችህ መነጠልህን እና ለብቻህ መቅረትህን አስብ፡፡ ለጥቂት ደቂቃዎች ሞት ምን እንደሚመስል በሃሳብህ ሳል።
ሞት አይቀሬ ነው! በሞት ላይ በጥልቀት ካሰብክበት፤ የእለት ተዕለት ጥቃቅን ጭንቀቶችህ ተጠራርገው ይሄዳሉ፡፡ አለቃህ ምንስ ቢያስብ ምን ያስጨንቅሃል? ከሚስትህ ጋር የሚያጋጩህ ጥቃቅን ሃሳቦች ስለምን ያስጨንቁሃል? ስለምን የሚወዱህን በመጥፎ ቃላት ታስከፋለህ? ሕይወት በዘላለማዊ ጨለማ መሃል የምታበራ የአጭር ጊዜ ሻማ ናት፤ ዋጋ በሌላቸው ነገሮች ላይስ ስለምን ታባክናታለህ? ይህ ሁሉ መጨነቅህ .. ይህ ሁሉ መከፋትህ .. ሻማዋ በጠፋች ቅጽበት ያበቃል... | 1 654 |
| 18 | ⁸"#Love_is_a_serious_mental_disease"
ዓለምን መቀየር ከፈለክ ከትዳር በፊት አድርገው፤ ምክንያቱም ካገባህ በኋላ የቲቪ ቻናል እንኳን መቀየር ከቻልክ አንተ ጀግና ነህ..👐🏼 | 1 082 |
| 19 | ሸ ፡ሌ ለመሆን እንኳን መስፈርት አላሟላሁም። ለሽር*ጥና እንኳን ከደረጃ በታች ነኝ። ፤ መልከ-ጥፉ ሴት ነኝ .... እርግጥ መልከ-ጥፉ ነኝ ማለት ይቸግረኛል። አስቀያሚ ሴት ለመሆን ተጨማሪ ማማር ያስፈልገኛል። እግዚአብሔር አስቀያሚ መልክ ምን እንደሚመስል ለማሳየት የፈጠረኝ ይመስለኛል.....
ጥርሶቼ ዘርዛራ ናቸው። ግራ አይኔ ወደ ቀኝ ዘሟል። ቀኝ አይኔ ወደ ግራ ዘወር ብሏል። ጡቶ፡ቼ ከ ቅጥነቴ ጋ አይመጣጠኑም። ጡ፡ቴ የፈረንጅ ላም ጡ፡ት ያህላል። ቂ፡ጥ የለኝም። አራት ማዕዘን የሚመስል ፊቴ ላይ ያለመጠን የረዘመ አፍንጫ ተጋድሟል። ሞ፡ጀሌ እግሬን አንሻፎታል።
አስቀያሚ ነኝ!
እግዚአብሔር በደል የሚጨማምርብኝ ለምንድ ነው? ሴት መሆኔ ሳያንስ መልከ-ጥፉ ሴት ሆንኩ። መልከ-ጥፉ ሴትነቴ ላይ የድሃ ልጅነት ተደምሮበታል። የድሃ ልጅነት ላይ ገጠሬነት ተጨምሮበታል።
የገጠር ሴት መሆን ብቻውን በቂ ቀንበር አይደለም? ድህነት ፥ ሴትነትና የገጠር ልጅነት የተባሉ ሦስት ቀንበሮች ብቻቸውን ብዙ አይደሉምን? እዚህ ላይ መልከ-ጥፉነት የተጨመረበኝ ለምንድነው?
ዘርዛራ ጥርሴ ሹል ነው። ገጣ፡ጣ ነኝ...ገጣ፡ጣ ጥርሴ ላይ ቅርፅ የለሽ ከንፈር ተለጥፎበታል። ከ ከሰል የምስተካከል ጥቁር ነኝ።
መገፋትን የተማርኩት ከቤተሰቤ ጭምር ነው። የገዛ ወላጆቼ በመልኬ ይሳለቁ ነበር። ትምህርት ስጀምር ፥ መምህራን አሾፉብኝ። ተማሪዎች ቀለዱብኝ። ሰይ፡ጣን የሆንኩ ይመስል በሁሉም የምጠላ ነበርኩ።
ድንግል አይደለሁም!።
ከሦስት ወንዶችጋ ተኝቻለሁ። ሦስቱም የወሲብ መለማመጃቸው ነበርኩ። መወሰብ ሲለምዱ ሸሹኝ። ከሴት ሲተኙ እንደ ጀብድ ለአገር ምድሩ የሚያወሩቱ ከኔ መተኛታቸው ሚስጥር እንዲሆን ፈለጉ።
ትምህርት ያቆምኩት በልጅነቴ ነው። መሰደቡ ሲለቸኝ ትምህርት ጠላሁ። የተወለድኩባትን የገጠር መንደር ትቼ ወጣሁ። ከተማ ገባሁ፤ የሰው ቤት ስራ ተቀጠርኩ። ፤ እንደ ባሪ፡ያ መኖር ሲሰለቸኝ ፥ የተቀጠርኩበትን ቤት ትቼ ወጣሁ። ሴተ፡ኛ አዳሪ ለመሆን ወሰንኩ።
የሴ፡ተኛ አዳሪነት እድሜዬ የአንድ ቀን ነው። ቢሻቴ ተራ ተሰለፍኩ። ቢሻቴ መልከ-ጥፉም መልከ-ቀናም ሴቶች ገላቸውን የሚቸረችሩበት ቦታ ነው። ቢሻቴ ተራ የሻሸመኔ ወንዶች ወሲብ የሚለማመዱበት የሽር፡ሙጥና ገበያ ነው።
ገዢ አጣሁ። መልኬ ገበያውን አልመጠነም።
ሴት መሆኔ ሳያንስ ፥ አስቀያሚ ሴት መሆን ነበረብኝ? የዚህን አለም ክፋት እንዴት ልፋለም ነው? በታችም በድሎኝ በላይኛውም ሲኦል ይጠብቅሻል ተባልኩ ፈጣሪም እንደ ሰው እንደ ዐለም ጨከነብኝ!!
| 2 368 |
| 20 | አንድ ሰው አንድን ሰው ለምን ይወዳል?
አንድ ብላቴና አንዲትን ኮረዳ የሚወዳት ለምንድን ነው? ስለሌሎቹ አላውቅም:: እኔ ግን ወሰንን የወደድኳት በብርሃን ተከባ ስላየሁዋት ነበር:: ሰዎች ሊያምኑኝ አይችሉም:: ግን በብርሃን ተከባ ስላየሁዋት ነው::
ለመስቀል ለመስቀል የከተማችን ሕዝብ በጠቅላላ ተሰብስቦ ዳመራ የሚያቀጣጥልበት ጉብታ ከከተማው ወጣ ብሎ አለው:: እስላሙ የሙስጠፋ አባት እንኳን ከነ ቤተሰባቸው ለወሬ ብለው ይመጣሉ:: ሲመሽ አንድና ሁለት ሰዓት ገደማ ሕዝቡ ዳቦቱን ይዞ ከየቤቱ ሲወጣ የንፋስ መውጪያ ከተማ ከሰማይ የወረደ የኮኮብ ስብርባሪ ትመስል ነበር፡፡ እውነቴን ነው ያን ዕለት ማታ ከሰማይ የወረደች ትመስል ነበር:: አሳዳጅ ጥላ ሞቷ ሁሉ ስለሚጋረድ እንኳን ንፋስ መውጪያ ተወለድኩ ያሰኛል:: የዳመራው እርጥብ እንጨት በእሳት ተበልቶ ሳያልቅ፣ ሰዎች ሁሉ ፊታቸው በፈገግታ እንደ ተከፋፈተ፣ አባት የልጁን እጅ ይዞ ወደ ዳመራው ቦታ እየመራው በየጓዳቸው በእንጉርጉሮ ባሽ እየመረቀ…ፈራ ተባ የሚለው ጨለማ ከተማዋ ሰማይ ላይ እንደረጋ…የችቦዎቹ ብርሃን እንዳፈጠጠ…ንፋስ መውጪያ እንዲያ እንዳማረባት ብትኖር እወድ ነበር።
የዚህ የደመራ ማንደጃ ኮረብታ ዙሪያው ሙልጮ ነው የመላጣ ሰው ጭንቅላት ይመስል ነበር:: ደመራውን ቀን በብርሃን በተለይ ከመሃል የሚቆመውን ቃወት አዛውንቶች ይገነቡትና ማታ ችቦ ይዘን መጥተን እንለኩሰዋለን…….ከፊሉ የደመራው ግድግዳ ላይ የሚነድ ችቦ እንደ ጦር ወርውሮ ይሰካል…ከፊሉ እንደመፋቂያ ወስዶ ይሸጉጣል…ከፈሉ እቃ እንደሚጥል አድርጐ ይወረውራል…ታዲያ ሁሉ ፊት ላይ ደስታ አያለሁ:: የሚገርመኝ ነገር የዕውነት ሳቅ አይ ነበር…ሁሉ ከየቤታቸው እየተኮረኮሩ የመጡ ይመስላል፡፡
ታዲያ ደመራው በየቤታችን በችቦ ተሸክመን ባመጣነው እሳት ይለኩስና ይቀጣጠላል፡፡ ሲቀጣጠል ሰዎች ዙሪያውን ከበው ይዘፍናሉ…'ኢዮሀ አበባዬ!' 'ሎጋው ሽቦዬ!' ይላሉ:: ሌላ ሌላ ሁሉ ዐይነት ዘፈንም ይዘፍናሉ፡፡ ብዙ ጊዜም ደመራው ከሚነድበት ምን አልባት ሁለት ኪሎሜትር የምትርቀውን የአድባር ዛፍ(7) ነክቶ የመመለስ ሩጫ ውድድር ይደረጋል:: የመጀመሪያው ሦስቱ አሸናፊዎች ያማረ ጠላ በቀንድ (ቀንድ?) ዋንጫ ይሰጣቸዋል:: ጉራቸው መከራ ነበር:: በዚህ ሁሉ መሃል መጠጥ ይቀዳል። ድፎ ዳቦ ይቆረሳል... የተከመረው የሚቃጠል እንጨት በእሳቱ እየተናደ፣ ቁመቱ እያጠረ፣ ፍምና አመድ እየሆነ የዘፋኙና የጨፋሪው ድምዕ እንደ ቅራሪ መቅጠን ሲጀምር ሰዎች ወደ፡የቤታቸው ይበታተናሉ:: ልጆች ግን 'ብዙ አታምሹ ተብሎ እንመከርና ወደ ሁዋላ እንቀራለን (እኔን ማለቴ አይደለም)…እንደ እናት ወተት የሚሞቅ እሳት ዙሪያ እንደ ገበጣ ጠጠር ተደርድረን::
ወሰን የለሽን ያየሁዋት ይሄን ጊዜ ነበር:: ሰዎች ወደ የቤታቸው ለመሔድ መበተን ሲጀምሩ ወደ እሳቱ ተጠግታ ተቀመጠች:: ብን ያለች ነጭ ኩታ ለብሳለች። አንዳንዴ ወንዝ የማያቸውን ትናንሽ እግረ-ቀጫጭን ወፎች ትመስል ነበር፡፡ ቅጥነትዋ ደሞ የሆነች ዝሃ:: እንግዲህ እሳቱ አጠገብ መጥታ ስትቀመጥ የእሳቱ ወጋገን የሚያበራበት ፊቷ በእኔ በኩል ይሆናል፡፡ ታዲያ ያምራል። የእውነቴን ነው ያምራል:: ለምን እንደሆነ አላውቅም ያምራል:: ተጨማሪ ጐንዋ ቆመው የነበሩ ሰዎች ገለል ገለል ብለው ከእሳቱ ራቅ ብለው ወሬ ጀመሩ:: ከሁዋላዋ የአገር ልብስ የለበሱ ሴቶች የኖራ ግድግዳ መስለው ቆመው ነበር:: የወሰን ፊት ፀጥ ያለ ነበር:: ሠላም ያለበት ይመስላል፡፡ አልፎ አልፎ ምክንያቱን ባላውቅም በትንሹ ፈገግ ትላለች:: አፌን ከፍቼ አያታለሁ::
ከበስተሁዋላዋ የቆመው ከነጠላና ከጋቢ የተሰራው የሰው ግድግዳ ሲፈርስ ተአምር ተፈጠረ፡፡ ያ የኖራ አገር ባሕል ልብስ ግድግዳ ሰማይ ላይ የምትፎልል ድፍን ጨረቃ ከልሎ ኖሮአል:: ታዲያ ጠቆር ያለው የወሰን ጭንቅላት ድፍንዋ ጨረቃ መሐል ላይ የተቀመጠ መሰለ፡፡ አቅጣጫው:: ጨረቃዋ ቢጫ ናት:: የጨረቃዋ ማድያት የለም:: ታዲያ ወሰን በስዕል ላይ የማያትን ትንሽ ማሪያም መሰለችኝ:: አፌን በለጠጥኩ:: ትንፋሽ አጠረኝ:: የደመራውን እሳት ትቼ እሷ ላይ ዐይኖቼን እንደመዥገር አጣበቅሁ:: ወሰን በቀስታ ብትነቃነቅም ጭንቅላቷ ከጨረቃዋ ክብ አልወጣም:: ብዙ ሳይቆይ እስኪበቃኝ ሳላያት ያ የኖራ፣ የአገር ልብስ ግድግዳ ቀድሞ እነበረበት ተመለሰ፡፡
እንደ አጋጣሚ ዞር ብላ አየችኝ:: ያውም ያን የተረገመ አፌን እንደከፈትኩ፡፡ እጅ ከፍንጅ:: አልሮጥ ነገር:: እሳት ውስጥ ዘልዬ አልገባ ነገር:: ታዲያ ከዛን ቀን ጀምሮ ያቺ ምስልዋ አንጀቴ ውስጥ ገብታ ከሌሎች ሰዎች ያልተለየች መሆንዋን ብረዳም ምክንያቱን ልገልጠው በማልችልበት ሁኔታ ልዩ አድርጋ አሳቀለችኝ::
አንድ አንድ ሴቶች አንደበታቸው ብቻ ያምራል፤ አንዳንድ ልጃገረዶች ፊቶቻቸው ብቻ ያምራሉ፣ አንዳንድ ሴቶች ቂጣቸው ብቻ ያምራል፣ አንዳንድ ልጃገረዶች አለባበሳቸው ብቻ ያምራል…በብርሃን የሚከበቡ ግን ከወሰን ሌላ ያሉ አልመሰለኝም::
📖 ግራጫ ቃጭሎች | 1 266 |
