924
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-2730 days
Posts Archive
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ለውጥ ህመም አለው!
ብዙ ጊዜ አብረውን ይኖሩ የነበሩ ወይም ደግሞ በቅርብ የምናውቃቸው ሰዎች እራሳቸውን ቀይረው ወይም ከነበሩበት ተሽለው ስናገኛቸው እድል ይመስለናል ነገር ግን የመጡበትን መንገድ ብትጠይቋቸው ስኬት በተወሰነ ቅፅበት ውስጥ የሚከሰት ነገር ሳይሆን የብዙ ውጣውረድና መሰናክሎች ውጤት እንደሆነ ትረዳላችሁ።
ወዳጆቼ በህይወታችሁ ውስጥ ሁሌም ቢሆን ይህን አስታውሱ:-ለመለወጥ ስታስቡ እራሳችሁን ለብዙ ውጣውረዶች ማዘጋጀት መቻል አለባችሁ።
🙏🙏🙏🙏 @fkrlovelove
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ለራስህ ጥሩ ጓደኛ ሁነው!
ለራስህ ከራስህ በላይ ማንም አይኖርም።አዕምሮህ ላይ እየተመላለሰ የሚያስጨንቅህ ነገር ሲኖር ፀጥ ያለ ቦታ በመሆን ውስጥህን አዋራው።
ህይወት ምስቅልቅል ስትልብህ አንተነትህን ቁጭ ብለህ ፈልገው።አንተ ውስጥ ትልቅ መፍትሄ,ምርጥ የሆነ የህይወት መስመር የሚያሳይህ ትክለኛው ያንተ ማንነት አለና።
@fkrlovelove
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ዲግሪ ወይስ ህይወት?
በትምህርት አለም የመጀመሪያ ወይም ቀዳሚ በመሆንና በህይወታችን ውስጥ ቀዳሚና ምርጥ የህይወታችን መሪ በመሆን መካከል በጣም ትልቅ ልዩነት አለ።
በትምህርትህ ወደቅክ ማለት የህይወት ህልምህ አከተመለት ማለት አይደለም በትምህርትህ አለፍክ ማለት ደግሞ የህይወትህን ግብ አሳክተህ ጨረስክ ማለት አይደለም።ዲግሪህ በፍፁም የስኬትህ መጨረሻ አድርገህ እንዳትዝ።
እያንዳንዱ የህይወት መንገድ የተለያዩ ውሳኔዎችን ይፈልጋል እያንዳንዱ ውሳኔህ ደግሞ የህይወትህን አቅጣጫ ይወስነዋል።ዲግሪ እና ማስተር መያዝ ከወረቀት ያለፈ value የለውም።
ወረቀትህ ላይ የምትፅፋቸው ነገሮች የወረቀትህን value እንጂ የህይወትህን value ሊወስኑት አይችሉም ከዚያ ይልቅ አዕምሮህ ላይ የምትፅፈውን ነው ህይወትህን የሚወስነው።
@fkrlovelove
924
Repost from ጥበብ ፍልስፍና
አንባብያን 888 የሚለውን ርእሱን በሚያዩበት ጊዜ ምንይኾን?
ለምን ይኽነን ርእስ መረጠው? ሳይሉ እንደማይቀሩ እገምታለኍ፡፡ ይኸውም ከ6 ዓመታት በፊት ላይ "ቀመር 888 እና መጽሐፍ ቅዱስ" በሚል ርእስ "888" ከወሩ፣ ከቀኑ፣ ከዓመቱ ጋር
መገጣጠሙን በማሰብ በ2008 ዓ.ም. በቀን 8 በ8ተኛ ወር ላይ በፌስቡክ ላይ ዘርዘር አድርጌ በመጻፍ ለአንባብያን አንድ ጽሑፍ አጋራኊ፡፡ ያነንም ጽሑፍ ብዙዎች በጊዜው አንብበውት ነበር፡፡
የሚገርመው ነገር ከ6 ዓመታት በኋላ በ2014 ዓ.ም. ልክ ያነን ጽሑፍ በለቀኩበት ዕለት በ8ኛው ወር በሚያዝያ፣ በ8ተኛው ቀን፣ በ8ኛው ሰዓት ላይ 24ተኛው መጽሐፌ "ማዛሮት" በድምቀት ተመረቀ፡፡ በዚያ የመጽሐፍ ምረቃት መርሐ ግብር ላይ ኾኜ ይኽነን ግጥጥሞሽ ችላ ብዬ አልተመለከትኩትም፡፡
ይልቁኑ እንደ ትልቅ ምልክት በማሰብ በዚያው መጽሐፌ በሚመረቅበት ዕለት ይኽነን የ888 ምስጢርን፣ ይልቁኑ በግእዝ ፊደላት ውስጥ ያሉትን አቅማራትን፣ ምድራዊና ሰማያዊ ምስጢር ለአንባብያን አዘጋጅቼ ለማቅረብ ለራሴ ቃል ገባኊ፡፡
የወርቅ ዘንግ መጽሐፍን ለአንባብያን ያበቃው በቀመር 7 ላይ ምርምር የሚያደርገው መምህር መስፍን ሰሎሞንም ይኽነን
ዕውቀት በልቤ ይዤው እንዳልቀር ይልቁኑ ለትውልድ በጽሑፍ እንዳስተላልፈው አብዝቶ ይጠይቀኝ ስለነበር እንድጽፈው አንዱ ምክንያት ስለኾነኝ በዚኹ አጋጣሚ አመሰግናለኊ፡፡
የትምህርት ታላቁ ግብ አስቀድሞ ራስን ማወቅ ከዚያም በዕውቀት፣ በጥበብ ብርሃንነት ሐሰትን ከእውነት፣ ብርሃንን ከጨለማ መለየት፣ ሀገርን በቅንነት፣ በእውነተኛነት ማገልገል እንጂ በአንድ የማሠልጠኛ ተቋም ውስጥ ገብቶ የመመረቂያ ልብስ
ለብሶ፣ የምስክር ወረቀት መቀበል ብቻ አይደለም፡፡
በመኾኑም የኹላችኹም የኢትዮጵያውያን ሀብት የኾነው
ይኽነን ፊደል ለብዙ ሺሕ ዘመን የያዘውን ታላቅ ጥበብና ሰማያዊ ምስጢርን በዕውቀት፣ በማስተዋል መረዳት ስትዠምሩ ያን ጊዜ ፊደላችኹን መውደድ፣ ማክበር፣ መጠበቅ ትጀምራላችኊ፡፡
በዚኹ አጋጣሚ ፊደላችን የያዘውን ታላቅ ምስጢር ዐውቀው በምቀኝነት ለማጥፋት ከሚተጉ ከክፋት ሰራዊት፤ ዳግመኛም አለማወቅ ድቅድቅ ጨለማ ነውና ሳያውቁትም
በሞኝነት ፊደላቱን ለማጥፋት ከአጥፊዎች ጋር ከሚተባበሩ ጠብቃችኊ ለመጪው ትውልድ የተቀበላችኹትን አደራ እንድታሸጋግሩት ወደ እውነተኛው የጥበብ ብርሃን እንድትደርሱበት ሐሳቤ ነው፡፡
ዶ/ር ሮዳስ ታደሰ
@ethiosecret
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
አሉታዊ አመለካከት ካላቸው ሰዎች ራቅ!
አንዳንድ ሰዎች ምንም ይሁን ምን አንድን ነገር ለማጣጣል ሁሌም አፋቸው እንደሾለ ነው። አንድን ነገር ምን ያህል በጥራት እንደተሰራ ከማስተዋል ይልቅ ምን ያህል ስህተቶች(ጉድለቶች) እንዳሉት ማስላሰል ይቀናቸዋል:: ማጣጣሉና ማንቋሽሹን ሙያዬ ብለው የያዙት ይመስላሉ::በእያንዳንዱ ሰውና በእያንዳንዱ ሁኔታዎች የሚቀናቸው ስህተትን መንቀስ ነው፡፡
እንደዚህ አይነት ሰዎች በየቤታቸው,በየቢሮውና በማናቸውም ቦታዎች ታገኟቸዋላችሁ::እነኚህ ሰዎች በአጭሩ ሀይል መጣጮች,የሚሰሩ እጆችን የሚሰብሩ እና ምንም አይነት ተስፋ የማይሰጡ ጨለምተኛ ሰዎች ናቸው።ስለዚህ ከእንደነዚህ አይነት ገዳይ ሰዎች እራስህን አግል።
@fkrlovelove
@fkrlovelove
@fkr_love_love
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ከመዝለልህ በፊት የምትዘልበትን ቦታ እመነው!
እምነትህ አላማህና ግብህን ለማሳካት ወሳኝ መሳሪያህ ነው ።የውሸት የምታምን ከሆነ ላመንክበት ነገር ማድረግ ያለብህን አታደርግም,መክፈል ያለብህን መስዋዕትነት አትከፍልም,መሄድ እስካለብህ ቦታ ድረስ ለመሄድ በፍፁም ዝግጁ አትሆንም::ፍርሀትና ጥርጣሬህ ከነፃነትህና ህይወትህን በአግባቡ ከመምራት ያግድሃል።
በህይወትህ የሚያስፈልጉህ ሁለት ነገሮች ማመንና ባመንከው ነገር ላይ ቆራጥ እርምጃ መውሰድ ናቸው።በልጅነትህ ወንዝ ወይም ሀይቅ ለዋና ሄደህ ጓደኞችህ ሲዘሉ አንተ ግን ዳር ቁጭ ብለህ የነሱን ዝላይ ትመለከት የነበረበትን ጊዜ አስታውስ።ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ውሀው የዘለልከው ውሃውን ያመንከው ቀን ነበር:: እየቆየህ ስትመጣ ደግሞ ምርጥ ዋናተኛ እና በሌሎች ጓደኞችህ እምነት የሚጣልብህ ሰዉ ሆንክ።
ህይወትም ልክ እንደ ውሃዋ ነች።ካመንክና መዝለል ስትጀምር የህይወት ጀግና ትሆናለህ:: ሁሌም አንድ ነገር አስታውስ ||ሁኔታዎች መስለው እንደሚታዩህ አይደሉም አንተም ''ነኝ'' ብለህ የምታስበውን አንተም አይደለህም።ትልቅ አቅምና ችሎታ ያለህ ሰዉ ነህ!!
@fkrlovelove
924
እሱ እረስቶት ይሆናል...ለእኔ ግን እንደ ትናንት ትዝ ይለኛል....ያ መልኩን አስታውሰዋለሁ...ምን መልኩን ብቻ እየያንዳድዋን sily moment አእምሮዬ ውስጥ ቆልፌባታለሁ..ለዛ ነበር አይኑን ባየሁበት ቅፅበት ሁሉ ከእምባዬ ጋር ትንቅንቅ ምገጥመው....
እጄን ይዞ ከትምህርት ቤት ሲያመጣኝ...በዛ እድሜዬ ለእኔ የማይገባኝን የፍቅር ዘፈን ሲያንጎራጉር ድምፁ ውስጤ ቀርቷል...ልቡን አውቀዋለሁ...ከአፉ መጥፎ ቃል ሲወጣ ሰምቼው አላውቅም..."አባትሽ ነኝ...እኔ እስካለሁ ድረስ ላንቺ የሚገባሽን ሁሉ አደርግልሻለሁ..."...ይለኝ ነበር አባት የለኝም ብዬ ሳማርር...ሲያመኝ አይተኛም ነበር...በባነንኩ ቁጥር ቁጭ ብሎ ሲጠብቀኝ አገኘዋለሁ...በጤናዬስ መች አስተኛው መሰላችሁ ...የባጥ የቆጡን እየቀበጣጠርኩበት ቀባጥሬም ሳበቃ መብራት ከጠፋ ፈራለሁ አይጥ ይመጣብኛል ብዬ እበጠብጥ ነበር...እኔን አስተኝቶ መብራት ካላጠፋ አይተኛም ነበር...ደሞ በመሀል ከባነነንኩ ጩኸቴ መከራ....
በመንገድ እየሄድን የኔ ቢጤ ረግጦ አያልፍም..."የሮጠ አይቅደምህ..."...የሚለው ምርቃት አሁንም ድረስ ውስጤ አለ...አውቃለሁ ሁሉንም እረስቶታል...እኔ ግን ሁሉንም አስታውሳለሁ....
የተበጣጠሰ ጫማ ከመጫማቱ በፊት ትንሽ አቧራ እንዴት ይጠየፍ እንደነበር አውቃለሁ...ያቺ የሁላችንም እድሜ...እኮ ያቺ አለምን መቀየር የምንችል የሚመስለን እድሜያችን አለች አይደል...እሱ ያቺ እድሜው ላይ እኔ ደግሞ ልጅነቴ ላይ ነበርኩ...
አንድ ያለኝ ቤተሰብ እርሱ ነው...እናቴን ልምሰል አባቴን አላውቅም...ሰፊው አፍንጫዬ እና እብድ የሚያህል ከንፈሬ ተደምረው ከግንባሬ ፊት አውራሪነት ጨምሮ ጥቀርሻ የሚያስንቀው ጥቁረቴን ከማን እንደወረስኩ አላውቅም....ወንዝ ዳር ተጥዬ ነው ያገኘኝ.....
"...ቆሻሻ ሁልጊዜ መጥፎ አይደለም..እንደ እኔ ከታደልክ ቆሻሻ ልትጥል ወጥተህ ወርቅ ይዘህ ትመለሳለህ..."...ይል ነበር እኔን ያገኘበትን አጋጣሚ ሲተርክ...
ለዛ ነው መሰለኝ "ወርቅነሽ" ብሎ ስም ያወጣልኝ...ደግሞ እኮ አመሌ..."ይሄን ስም እንደው ምነው ምን አርጌህ ነው...ካልጠፋ ስም...ቲቲ...ሜላት...ሰላም...ኧረ ስንት አለ አንተ ድሮም ስለማትወደኝ ነው"...እለው ነበር በእንጭጭ ጭንቅላቴ..ተማሪዎች በስሜ ሲቀልዱ እኔ ደግሞ ወቀሳውን አዥጎደጉደው ነበር።
አሁን ላይ ለሚያወራው ነገር ከእኔ በቀር ቦታ የሚሰጥ ሰው የለም...ይግባኝም አይግባኝም አንገቴን እያወዛወዝኩ እሰማዋለሁ...ባያስቀኝም ቀልድ ብሎ ለነገረኝ ነገር ጥርሴ ሰንፎ አያውቅም...በሳቅኩለት ቁጥር "ወርቅ ነሽ የምልሽ እኮ ለዚያ ነው "...እያለ እንደ ልጅነቴ ያቅፈኛል...
ወዳጆቹ መሸሻቸውን ከሱ አብልጬ አማርራለሁ...
"እነርሱም እንደ ዘንድሮ ሽንኩርት ሆኑብን እኮ....ብር ሲጠፋ ጠፉ..."...እላለሁ ክፍት ሲለኝ...በስሱ ፈግጎ እንዲህ ይመልስልኛል.....
"ሰው ሲንቅሽ አትጥዪ...እግዚአብሄር የሚያከብርሽ የመናቅ ፅዋሽ ሲሞላ ነው...".....ተገርሜ አፈጥበታለሁ...
"ኧረ ሽንኩርት የሌላት ሽሮአችን አትብረድ አምጫት...."...ብሎ ከግርምቴ ይመልሰኛል...
ይሄ ነው አንድ ግን ብቻውን ሺህ የሆነ ቤተሰቤ................
አሁን ላይ ሁሉም ታልፎ "ዶክተር ወርቅ ነሽ ተካልኝ" ተብዬ ስጠራ እንደ ድሮ በስሜ አልናደድም...የምናደደው በእኔ ፈንታ እርሱ "ዶክተር ተካልኝ" ባለመባሉ ነው...
የምርቃት ጋውኔን ለብሼ ፊቱ ስቆም "አስከበርሽኝ ልጄ ..."...ብሎ ግንባሬን ሳመኝ...ቀጥሎም አቀፈኝ...መልሶ ለቀቀኝና ፀጉሬን ሳመኝ...የእንባው እርጥበት ቆዳዬ ጋር ደረሰ...ተመልሶ ደግሞ አቀፈኝ...የሚያረገኝ ግራ ገባው...ፊቱ ፀዳል መሰለ...
"የመናቅ ፅዋዬ ሞላ ልጄ...አስከበርሽኝ ክበሪ...የሮጠ አይቅደምሽ...አግኝተሽ አትጪ...."....መረቀኝ....እኔ ግን "የሮጠ አይቅደምሽ".... ጋር ነኝ....አልረሳውም ነበር ማለት ነው።
✍Shewit dorka
https://t.me/shewitdorka
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ባህርያችን ከእኛ ጋር የሚቆዩትን ይወስናል
በሕይወታችሁ ምን አይነት ሰው እንደምትገናኙ የሚወስንላችሁ ጊዜና ገጠመኝ ነው፡፡ ከምትገናኟቸው ሰዎች መካከል የትኞቹን እንደምትፈልጓቸው የሚወስንላችሁ የልባችሁ ሁኔታ ነው፡፡ ከፈለጋችኋቸው ሰዎች መካከል ደግሞ የትኞቹ ከእናንተ ጋር እንደሚቆዩ የሚወስንላችሁ ባህሪያችሁ ነው፡፡
በየጊዜው የምትገናኟቸው ሰዎች ጉዳይ በአብዛኛው ከቁጥጥራችሁ ውጪ ስለሆነ ብዙም ባያሳስባችሁ ችግር የለበትም፡፡ ከዚያ በበለጠ ሁኔታ ሊያሳስባቸሁ የሚገባው ከእነሱ መካከል ፍላጎት ያሳደሩባችሁ ሰዎች ናቸው፡፡ምክንያቱም የምትፈልጓቸው ሰዎች የውስጣችሁን ዝንባሌ ስለሚያንጸባርቅ ማለት ነው፡፡ከእነዚህ ሁሉ በጣም ሊያሳስባችሁ የሚገባው ግን ከእናንተ ጋር ለመቆየት የወሰኑት ሰዎች ጉዳይ ነው፡፡ ምክንያቱም ከእናንተ ጋር የሚቆዩትን የሚያቆያቸው ባህሪያችሁ ስለሆነ ነው፡፡
ስለባህሪያችሁ በሚገባ ስታስቡበትና መልካም ማንነት ስታዳብሩ ይህ ባህሪያችሁ ከእናንተ ጋር የሚቆዩትንና የማይቆዩትን ይወስንላችኋል፡፡ ጤናማዎቹም ሆነ ጤና-ቢሶቹ ሰዎች እንዲሁ አይርቋችሁም እንዲሁም አይቀርቧችሁም፡፡ በተለይም ጤናማ ሰዎች ሲርቋችሁና ጤና-ቢስ ሰዎች ሲቀርቧቸሁ ራሳችሁን በሚገባ መመልከታችሁን አትዘንጉ፡፡
@fkrlovelove
924
እንደመደበርም እንደመሰልቸትም አድርጎኝ ነበረ። ለመኖር ምክንያት አጣሁ ማለት ጀምሬ ነበረ።
እነዚህ ትናንሽ ሀሳቦች ቀኔን መረበሽ ጀመሩ ። ጠዋት መነሳትና ድጋሜ ሌላ ተመሳሳይ አድካሚ ቀን መዋል ትርጉሙ አልታይሽ ብሎኝ ነበረ።
ከዛ ግን ቀልቤን ገዛሁ የእናቴን እጅ አየሁት። ቆዳዋ ተሸብሽቦ ደምስሮቿ በጉልህ ይታዩ ነበረ። ደነገጥኩ ያ እንደዛ የሚያሳሱ ቀያይ እጆቿ አሁን መዳፎቿ ሳይቀሩ ጠቋቁረዋል።
ውሎዋን አየሁት እንደነገሩ ነው የምትለብሰው ያ ሁሉ መሸቀርቀር የት እንደ ሄደ ግራ ገባኝ። ፈጥና ያረጀችም መሰለኝ።
ከዛ ድግስ ተጠርተን ዘመድ ቤት ስንሄድ በእያንዳንዱ ነገር ላይ የምትሰጠውን የሰላ ሂስ ሰማሁ።
እቤት ስንገባ ጠየኳት ለምን ስራሽን ተውሽው እስካሁን በጣም ምርጥ ጭንቅላት አለሽ እኮ አልኳት በቁጭት
"ኤድያ ተይው ባክሽ ሁሉም ነገር ከቤተሰቤ አይበልጥብኝም" አለች
"እስኪ ተመልከቺ እንዴት ትናንሽ እንደነበራችሁ "በእጇ ህፃን ሆነን እኔና እህቴ የተነሳነውን ፎቶ ይዛ
"አሁን ያላችሁበት ደረጃ ለኔ ከምንም ነገር በላይ ነው" አለቺኝ በፈገግታ።
እንዴት እንደሆነ ባላውቅም መሰልቸቱ መደበሩ ቀርቶ ጭራሽ አዲስ ጉልበት ይሰማኝ ጀመረ።
ስለእሷ ማሰብ ከአልጋዬ ተስፈንጥሮ ለመነሳት በቂ ነበረ። እሷ መኖር ያቆመችው ለኔ ስትል አልነበር ስለዚህ እኔም የምልፈሰፈስበት ምክንያት አልነበረኝም።
ለኔ ማማር የሷ መጎሳቆል ይበልጥ አጠነከረኝ። በደንብ በኔ እስክትኮራ ድረስ...
✍nani
Join for more👉https://t.me/justhoughtsss
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ጠንካራ ሰዎች እንደ ደካማ ሰዎች ብዙ ስህተቶችን ይሳሳታሉ ። ልዩነቱ ጠንካራ ሰዎች ስህተቶቻቸውን አምነው፣ ከእነርሱ መማር ነው። በዚህ መንገድ ጠንካሮች ይሆናሉ
@fkrlovelove
924
"በቂ ነህ....?....እንደዛ ነው የምታስበው...?በእኔ ሚዛን ስንት እንደሆንክ ነው የሚሰማህ....?የእኔን እንባ ለማየት የተገባሁ ነኝ ነው ምትለው..."
"ምንድን ነው የሆንሺው...ተረጋጊ"...
"አልረጋጋም...አልረጋጋም...እንደውም አትመልስልኝ...እኔው ራሴ መልስልሀለሁ...በደንብ ስማኝ...አትበቃም...አትመጥንም...የእኔን አእምሮ ለመቆጣጠር ቅንጣት ነህ...ቅንጣት...."....ከአፏ የሚወጡት ቃላቶች ከሚዥጎደጎደው እምባዋ ጋር እሽቅድድም ገቡ...
"አለሜ አሁን ይሄን ምን አመጣው...እሺ አልመጥንም...እሺ ቅንጣት ነኝ...እሺ ...ሁሉንም እሺ...አሁን ምን እንደተፈጠረ ንገሪኝ...."....ደንግጧል...ሰላም እንደነበሩ ትዝ ይለዋል...ብዙም አልራቀም...ትናንት ከስራ ከወጡ በኃላ አብረው አምሽተዋል...በጨረቃ ብርሀን ታጅበው እንጨት እንጨት በሚል ቀልዱ ተንፈራፍራለች....አሳሳቋ ገርሞት "አንቺ ብቻ እኮ ነሽ ምትስቂልኝ" ብሏታል....መጨረሻም መጀመሪያም ላይ የሚታወሰው ነገር ሳቋ ነው።
"ምን ሆነሻል..."....ጥያቄ ደገመ...መልሷን እየጠበቀ ነው...እርሷ አይን አይኑን እያየች እምባዋ ቀደማት...
እምባዋ አልገራ ሲል ወደራሱ ስቦ አቀፋት...መንጭቃው ከእቅፉ ወጣች....
"አለሜ ምንድን ነው ያጠፋሁት...ንገሪኝ አታስጨንቂኝ"
"አፈቀርኩህ...ድምፅህን መራብ ጀመርኩ እኮ...በምናብ ካንተ ጋር መዋል ጀመርኩ እኮ...ትናፍቀኝ ጀመር...እነዚህ ሁሉ የማልፈልጋቸው ስሜቶች አንተን ተከትለው መጡ..."...ሳግ እየተናነቃት መለሰችለት...
ደስ አለው...በስሰት እያያት እንባ ያረጠበው አይኗን ሳመ...ቀስ አድርጎ ወደራሱ ሳባት....አጥብቆ አቀፋት...ባሁኑ አልተወራጨችም...
"አቅም አሳጣኸኝ..."....ከበፊቱ አጥብቆ አቀፋት።
✍Shewit dorka
https://t.me/shewitdorka
924
"አጉል እምነት ላይ ሙጥኝ ብለህስ ቢሆን ሳሚ?" አልኩት ለመቶ ምናምነኛ ጊዜ
" ኧረ አብርሽ አንተ እንኳን ተረዳኝ እንጂ እኔም እኮ እውነት ባይሆንና እየቃዠሁ ቢሆን ደስ ባለኝ ግን ይሄ ስንተኛ ጊዜ ነው?"ብሎ በረጅሙ ተነፈሰ
"እሺ ቢያንስ ምን ስትሆን ነው የተሰበረው" አልኩት ግራ ቢገባኝ
"ድንገት ትዝ አለቺኝና እንደውም ለምን ዛሬ እሷ የገዛችልኝን ሰዓት አላረግም ብዬ ገና ከመሳቢያው ሳወጣው እኮ ነው ወድቆ ብትንትኑ የወጣው ደግሞ 'ተጠንቀቅ እዚ አገር የሚሰራው አታገኝም ቢበላሽ እንኳን' ብላኝ ነበረ።"ብሎ ፊቱ ሀዘን ሽው አለበት።
ከመሬት ተነስታ የዘጋችው የ4 ወር ፍቅረኛው ነች
"እና?"አልኩት ነገሩ ስለሰዓት መሰበር ብቻ አለመሆኑ ስለገባኝ
"እናማ በቃ አለመመለሷ እርግጥ ሆነ ማለት ነው።"
አለኝ እንደመበሳጨትም አደረገኝ " እንደው አንተ ደግሞ አንድ ሰዓት ተሰበረ ማለት እንደማትመለሱ እንዴት ማረጋገጫ ይሆናል አልኩት
" እሺ ይሄ አጋጣሚ ከሆነ ለምን ከሀዊ ጋር እንደዛ ከመጣላታችን አንድ ቀን በፊት የሰጠቺኝ የአንገት ብር ጠፋ እሺ እሱም አጋጣሚ ነው በል ታዲያ ሄኖክ ከመሄዱ በፊት አብረን የገዛነው ሀብል እሱ በሄደ ማግስት የተበጠሰው እሺ ይሄም አጋጣሚ ነው ልትለኝ ነው ብሎ አፈጠጠብኝ
"አጋጣሚ ላይሆን ይችላል ምናልባት ያንተ ዝርክርክነት እና overthinker ጭንቅላትህ አብረው የፈጠሩት ችግር ሊሆን ይችላል ብዬ ተረብኩት
በፊት ቢሆን የባሰ ነርቭ የሚነካ ትረባ ነበር መልሶ ሚሰነዝረው።
አሁን ግን ጭራሽ እመር ብሎ ተነስቶ "የገባህ አልመሰለኝም! አትመለስም እኮ ነው ያልኩህ ድሮም እንደማይገባህ አውቄ ነበር" ብሎ ግርግዳውን በቡጢ ነርቶ ወጣ።
ወይ ሳሚ እሱን ግን ይሄ ፍቅር የሚሉት ነገር ስንቴ ነው የሚያንገላታው....
✍nani
https://t.me/justhoughtsss
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
"የፈለግከው ነገር ለማድረግ የሚያቆምህ ምንም ምክንያት የለም!!!"
ብዙዎች ሰው መለወጥ! መሻሻል! መበልጸግ! ይፈልጋል!!! ለዚህ የፈለገውን ነገር ለማግኘት ቁርጠኛ አይደለም!!! "ቆይ እስቲ አሁን ጊዜውም አይደለም "ይላል። አትሸወድ ጊዜው አሁን ነው!!! "አሁን ለዚህ የሚሆን ገንዘብ የለኝም "ይላል። አትሸወድ! አሁንገንዘብ ያለው ሁሉ እንዲሁ እንዳተ በባዶ ኪስና አለም ቆርጦ የተነሳ ሰው መሆኑ አትርሳ!ገንዘብ በገንዘብ አይመጣም!ገንዘብ የሚመጣ በባዶ ኪስ በዚህ ቅፅበት ሜዳ ሙጥኝ ብሎ ለሰራ ነው!!!" አንዳንዶቹ ደግሞ ከጎኔ የሚቆም ሰው የለም"ይላሉ።አትሸወድ! በዚህ ጊዜ ሰው አሏቸው የምትላቸው ሰዎች ሁሉ ያን ጊዜ ብቻቸው የጀመሩ ናቸው።ከጎንህ ሰው እንዲኖር ከፈለግክ መጀመርያ ከራስህ ከትክክለኛው ማንነትህ ጋር ከጎኑ ቁምና ተአምሩ ታያለህ! " አንዳንዶቹ ደግሞ ለዚያ የሚመጥን አቅም የለኝም"ሲሉ ይደመጣሉ።አትሸወድ! በውስጥህ ገደብ የሌለው አቅም አለ።አንተ ልዩ ነህ!ልዩ የተደበቀ ሀይል በውስጥህ ፈጣሪ ማስቀመጡ አትርሳ!!!ስለሆነም በዚህ ቅፅበት ያልሆንከው ነገር ነገ እንዲሆንልህ አትመኝ!!! ለመሆን የተመኘሀው የምታራዝምበት ም-ን-ም ምክንያት የለም!!!
ያሰረህን EGO በጥሰህ ውጣ!!!አሁን በዚህ ቅፅበት ያልሆንከው ነገር መቼም ልትሆነው እንደማትችል ቀስ ብየ በምስጢር ብነግርህ ትደነግጣለህ እንዴ!????ምንም ማድረግ አልችልም!እውነቱ እሱ ነውና! ለፈለክው ነገር ፈጣሪህን አስቀድመህ ደፍረህ እርምጃ በዚህ ቅፅበት ውሰድ! የተዘጋጉ በሮች የሚከፈቱበት ምስጢር በዚህ ቅፅበት የተወሰደ እርምጃ ነው!!!እሱ ነው የህይወት አዲስ መድሀኒት!!!!
ደስታቸው አለም!!!
@fkrlovelove
924
Repost from ጥበብ ፍልስፍና
ታሪክ
World War ✍️✍️✍️
በ1914 እ.ኤ.አ ሐምሌ 28 ምሽት ላይ የኦስትሪያ እና ሀንጋሪ ጥምር መንግስት አልጋ ወራሽ የነበረው ልዑል ፍራንዝ ፈርዲናንድ እና እርጉዝ የነበረችው ባለቤቱ ሶፊያ በቅጥር ነፍሰ ገዳዮች ተገደሉ። የኦስትሪያ እና ሀንጋሪ ጥምር መንግስት ለድርጊቱ የሰርብያ መንግስትን ተጠያቂ በማድረግ በሰርቢያ መንግስት ላይ ይፋዊ ጦርነት አወጀ።
ይህን ተከትሎ 30 ሀገራት በሁለት ቡድኖች ተከፍለው ለአራት አመታት የተዋጉበት የመጀመሪያው የአለም ጦርነት ተጀመረ።
አንደኛው ቡድን allies ተብሎ ይጠራል። ሰርቢያ፣ ሩስያ፣ ብሪቴን፣ፈረንሳይ፣ አሜሪካ እና ጣሊያንን ጨምሮ አብዛኞቹ ሀገራት በዚህ ቡድን ውስጥ ነበሩ። ኦስትሪያ-ሀንጋሪ፣ ጀርመን፣ ቡልጋሪያ እና ቱርክ ደግሞ central powers ተብሎ በሚጠራው ሁለተኛው ቡድን ውስጥ ነበሩ።
በደቡብ አውሮፓ ውስጥ የተጀመረው ይህ ጦርነት በወቀቱ የአለምን አንድ አራተኛ ሀገራት በቅኝ አገዛዝ ታስተዳድር የነበረችው ብሪታኒያ ስትጨመርበት ወደ መላው አውሮፓ፣ አፍሪካ እና መካከለኛው ምስራቅ የተዛመተ አለም አቀፍ ጦርነት ሆነ።
አንደኛው የአለም ጦርነት ላይ የተሳተፉት ወታደሮች አብዛኛዎቹን ጦርነቶች የተዋጉት "trench" ወይም "የቀበሮ ጉድጓድ" ተብለው በሚጠሩ የአንድ ሰው ቁመት ጥልቀት ባላቸው እና ጠመዝማዛ መስመሮችን ተከትለው በተቆፈሩ ቦይ መሰል ምሽጎች ውስጥ በመሆን ነበር። ጦርነቱ በቆየባቸው አራት አመታት ውስጥ በአጠቃላይ ከ750 ኪሎሜትር የበለጠ ርዝመት ያላቸው የቀበሮ ጉድጓዷች ተቆፍረዋል።
ከቀበሮ ጉድጓዶች ውጪ የተደረጉ ሌሎች ትላልቅ ውጊያዎችም ነበሩ። ከእነዚህ ትላልቅ ዉጊያዎች መካከል battle of somme, battle of jutland, battle of verdun እና battle of marne በተባሉት የጦር ግንባሮች ላይ ብዙ ቁጥር ያላቸው ወታደሮች ተሰውተዋል። ለምሣሌ battle of somme በተጀመረበት የመጀመሪያው ቀን ላይ ብቻ ከ60,000 በላይ ወታደሮች አልቀዋል። battle of verdun ደግሞ ለረጅም ጊዜ የቆየ ውጊያ የተካሄደበት የጦር ግንባር ሲሆን ለ300 ተከታታይ ቀናት የዘለቀ ጦርነት ተካሂዶበታል።
በመጨረሻ የcentral powers አባል የነበረችው ጀርመን "Armistice" የተባለ የስምምነት ውል ፈረመችና ለአራት አመታት የዘለቀው ጦርነት ህዳር 11,1918 ላይ በallies ሀገራት አሸናፊነት ተጠናቀቀ።
በአንደኛው የአለም ጦርነት ላይ 65 ሚሊዮን ወታደሮች የተሳተፉ ሲሆን 4 ሚሊዮን ጠመንጃዎች፣ 250 ሺ መትረየሶች፣ 52 ሺ ተዋጊ አውሮፕላኖች፣ 2,800 ታንኮች እና 170 ሚሊዮን የጥይት እርሳሶች አገልግሎት ላይ ውለዋል።
ጀርመን በመጀመሪያው የአለም ጦርነት ፍፃሜ ላይ በፈረመችው የarmistice ሰነድ ውስጥ Treaty of Versailles የተሰኘ ክፍል የተካተተ ሲሆን ይህ ክፍል ጀርመን ከፍተኛ መጠን ያለው የገንዘብ ካሳ በጦርነቱ ለተጎዱት ሀገራት እንድትሰጥ እና ግዛቶቿ ከነበሩት ክልሎች መካከል የተወሰኑትን ለፈረንሳይ፣ ለቤልጅየም፣ ለፖላንድ እና ለቼኮስሎቫኪያ አሳልፋ እንድትሰጥ የሚያስገድድ አንቀፅ ነበረው።
ይቀጥላል . . . . . . .
924
Repost from አስተማሪ ሀሳቦች እና አጫጭር ወጎች
ከዕለታት አንድ ቀን አንበሳና ነብር ውሃ በጣም ተጠምተው በየግላቸው በፍለጋ ስንከራተቱ እያለ ሁለቱም አንድ ወንዝ ጋር እኩል ይደረሳሉ። በዉኃ ጥም የደከመው ሰውነታቸውን ለማርካት ና ለመበረታት ሁለቱም በቀጥታ ወደ ዉኃው ይገሰጌሳሉ።ብዙም ሳይቆይ ትኩረታቸውን ዉኃውን ከመጠጣት ላይ ይነሳና በመጀመረያ ማን ይጠጣ? ወደሚለው ሀሳብ ይዞራል። በዚህ ምክንያት ጸብ ጀመረው መታገል ጀመሩ። ብዙ ከታገሉ በጓላ ሁለቱም እጅግ እየደከሙ ሲመጡ ከላይ አንድ ድምፅ ሰሙ። ሁለቱም በድንገት የሰሙት ድምፅ ምን እነደሆነ ለማየት ከጸባቸው መለስ ብለው ቀና ስሉ አንድ ጥንብ አንሳ(አሞራ) በቅርብ ርቀት ሆኖ ያንዣብባል። ጥንብ አንሳው በጸቡ ምክንያት የምሞተውን ጠብቆ የሟቹን ሬሳ ለመብላት ነበረ የሚጠብቀው። ይህንን ሁኔታ የተመለከቱ እነዚህ ጠብኞች ልክ ተነጋግረው እንደተገባቡ ያህል ወዲያው አንድ ነገር ፍንትው ብሎ በራላቸው። በዚህ ጸብ ሁለቱ አንዳኞቸው ምናልባትም ደግሞ ሁለቱም እስከሞት በሚያደርስ ጉዳት እንደሚጓዱና መጨረሻ ላይ የሚጠቀሙው ይህን ጥንብ አንሳ እንደሆነ ገባቸው። ይህን ሁኔታ ከበራላቸው በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመስማማት ወሰኑ። ተለያይተው ሌላ ከሚበላቸው አንድ ሆነው ወንዙ በጋራ መጠጣት በሕይወት ለመኖር ወሰኑ። በዚህም ስምምነታቸው መሰረት ሁለቱም የሚበቃቸውን ያህል ጠጥተው ወደ መንገዳቸው ሄዱ።
ከዚህ የምንማር ነገር፦
©ለሁላችንም የሚበቃ ስፍራና አቅርቦት በዙሪያችን እያለ ሌላውን ካልጣልን እኛ የማንቆም፣
©ሌላውን ከላስራበን እኛ የማንጠግብ ሌላውን ካላጠፋን እኛ የማንኖር፣ ሌላውን ካላስወጣን እኛ መኖር የማንችል ሲመስለን አጥፍተን የምንጠፋ እንሆናለን።
@fkrlovelove
924
#ከድርጊቱ_አሻግረህ_ተመልከት!
"እሱን አትቀየመው ። ሆን ብሎ አይሆንም ። ውስጡ ባዶ ነው ። " ሲባል ሰምተህ ታውቃለህ? ሰምተህ የምታውቅ ከሆነ ከድርጊት አሻግሮ መመልከት ምን ማለት እንደሆነ ተረድተሀል ማለት ነው ። ወላጅ ከሆናችሁ ከድርጊቱ አሻግሮ ይቅር ማለት በደንብ ታውቃላችሁ። ልጆቻችንን የምንወዳቸው በድርጊታቸው ላይ ተመስርተን ከሆነ እነሱን መውደድ አስቸጋሪ ይሆንብናል ። ፍቅር በድርጊት ላይ የተመሰረተ ከሆነ በጉርምስና እድሜ ላይ እያለን የሚወደን ቤተሰብ መኖሩ ያጠራጥራል።
ይህንን ከድርጊቱ አሻግሮ በመልካምነት ሰውን መውደድ ሁሉም ሰዎች ላይ ብንተገብርስ? ልጆቻችን የማይሆን ድርጊት ሲያደርጉ ከድርጊቱ አሻግረን እደምንወዳቸው፤ የሚያጋጥሙን ሰዎች ሀሉ እኛ የማንቀበለው ድርጊት ሲያደርጉም ከድርጊቱ አልፈን መመልከት ብንችል አለም ምን ያህል ጥሩ ቦት ትሆን ነበር?
ይህ ማለት ግን ጭንቅላታችን አሸዋ ውስጥ ቀብረን ሰዎች እንዲረማመዱብን መፍቀድ ወይም የሰዎች ክፉ ድርጊት በሙሉ እንቀበል (እንደግፋለን) ማለት አይደለም። ከዛ ይልቅ ነገሮችን ከሌላ አቅጣጫ ለመመልከት ፈቃደኛ ነን ማለት ነው። ለምሳሌ ባንክ ሄደህ ሰራተኛው ቀስ እያለ የሚሰራው ምናልባት ከቤቱ ተበሳጭቶ መጥቶ ሊሆን ይችላል፣ ምናልባት በሕይወቱ ከባድ ነገር አጋጥሞት ትኩረቱን መሰብሰብ አቅቶት ሊሆን ይችላል ብሎ ማሰብ ነው ። ባለቤትህ ተቆጥታ ስትናገርህ ከድርጊቷ ባሻገር እንደምትወድህ እንድታውቅ እንደምትፈልግ ለመረዳት መሞከር ማለት ነው ። ከድርጊት አሻግሮ መመልከት ከምታስበው በላይ ቀላል ነው። ሞክረው ጥሩ ስሜት ሲሰማህ እራስህን ታገኘዋለህ።
@fkrlovelove
924
ክንፍ ነበረኝ✨✨
በነጋታው ባስለመደኝ ሰአት መጣ....የተለመዱትን ነገራት አደረገልኝ...ዛሬ አልበላም ብዬ ብል እንኳን ሆዴ አፍ አውጥቶ መራቤን ይነግርብኛል...አይሆንም አልኩ ለራሴ...በዚህ መልኩ መሞት ጊዜ ይወስዳል አልኩ መልሼ....
ጥርግ አድርጌ በላሁ.....ድሮ ድሮ ከእንቁላል ውጪ መስራት የሚችለው ነገር አልነበረም...ይሄን ሙያ ከየት እንዳመጣው ባላውቅም በያይነቱ ያበስልልኛል.....
'ለእኔ ብሎ አጭር ኮርስ ወስዶ ይሆናል' እለዋለሁ 'አሁን ጠልቶሻል' ለሚለኝ ጎኔ...
እርሱም አይረታም...'እና እንደዛ እያልሽ ነው ራስሽን የምታፅናኚው'...ይለኛል...አንዳንዴ ጎኔን ማድመጥ ትቼ ለእኔ እየሆነ ያለውን ነገር እቆጥራለሁ....
ይመጣል...ማታ ካስቀመጠኝ ቦታ ያነሳኝና ዊልቸሬ ላይ ይሰይመኛል...መፀዳጃ ቤት ይወስደኛል...ምግብ ያበስልልኛል...ያጎርሰኛል...በየመሀሉ ይሰድበኛል...ይወጣል...ወደ ማታ ተመልሶ ይመጣል...የቅድሙን ደግሞት አልጋ ላይ ወርውሮኝ ይወጣል...ማን እንዲህ ያደርጋል...?....
እቅፉን የማገኘው ወንበር በሚያቀያይርልኝ ቅፅበት ነው...ያኔ ነው ፊቱን በቅርበት የማየው.....ለምን ሰራተኛ እንደማይቀጥርልኝ እንጃ....
ዛሬ እንደወትሮው ስራውን ከጨረሰ በኃላ ትቶኝ አልወጣም...ፊት ለፊቴ ተቀመጠ...ግራ ገባኝ..."ምነው"...ጠየቅኩ....ምንም ሳይለኝ ግራ እጄን ያዘኝ....ልክ ድሮ ቀለበት ሊያረግልኝ ሲል እንደያዘኝ መያዝ...አንደ ድሮዋ ልዕልት ተሽኮረመምኩ....የእጁን ልስላሴ ባላጣጥመውም...እጄ ቢደነዝዝም በአይኔ ብቻ ብዙ ብዙ አልኩ..."መኖር ያን ያሀል አይከብድም "..."ይወደኛል እኮ..."..."አባት ተመለሰ...."....ልቤ የድሮው ቦታው ሊሾመው ቸኮለ...አሁን ጠፍቶ የተመለሰን ሎሌ ወዲያው ጓዳ ለማስገባት መጣደፍ ምን ይሉታል...ተጣደፍኩ...መመለሱን ሳላውቅ ተጣደፍኩ።
እጄን ከዊልቸሩ መደገፊያ አንስቶ ወደራሱ አስጠጋው...እስከዚህ ምንም አልተነፈሰም...ያወለቀው ቀለበት እጁ ላይ አለ...የጋብቻ ቀለበታችን...ኪሱን ሲደባብስ ጥድፊያዬ ጣሪያ ነካ...ገላዬን ሲያጥበኝ በግዴለሽነት የጣለብኝን ቀለበት ሊተካልኝም መሰለኝ...ከረጅም ጊዜ በኃላ ፈገግ አልኩ...አሁንም ጥድፊያው አለቀቀኝም...ባለፈው እንኳን ነገርኩት...መናገሬና እንባዬ እንደሚመልሰው ባውቅ ያኔ ድሮ አደርገው አልነበር እንዴ...ተጣደፍኩ...እጄ ቢሰራልኝ እኔ ራሴ ከኪሱ አውጥቼ እንደማጠልቀው እርግጠኛ ነበርኩ...
ከኪሱ እስኪሪፕቶ አወጣ...ከዛ ከቦርሳው ወረቀት መዘዘ...በእስኪርፕቶው አውራ ጣቴን አቀለመ...ያቀለመው ጣቴን ከወረቀቱ ጠርዝ ካለው ክፍት ቦታ ለተመ...አሁን ቀዘቀዝኩ።
"የፍቺ ወረቀት ነው...እንደምትስማሚ እርግጠኛ ነኝ...ባለሽበት ሁኔታ ምክንያት ፍርድ ቤቱ በአካል አለመገኘትሽን...."...ብዙ አብራራ...
"ሰራተኛ ቀጥሬልሻለሁ...ጨርሰናል....አመሰግናለሁ...."....አለና ንግግሩን ቋጨ።
በተራዬ ተለጎምኩ...አይኔ ደረቀ...አካላቴን አደጋው ባበደነው ልክ እሱም ልቤን አበደነው...ዝምምምም ጭጭጭጭጭ.......ረጭጭጭጭ
...ጩሂ ጩሂ አለኝ...ግን አልጮህኩም...ማልቀስ ፈለግኩ ግን ለእሱም ደከመኝ...ጥያቄም አለኝ ግን ከምን እንደምጀምር አላውቅም...
እኔን ትቶ የሄደላት ሴት ህይወት ፊቷን ያዞረችባት እንደው እርሱም እንደሚያዞርባት ታውቅ ይሆን...."እኔን ሳያውቅ ያደረገው ነገር ነው..."...ብላ ችላ ትለው ይሆን...ምን እንዳፈራረሰ ታውቅ ይሆን...በቁም ቀብሮ እንደመጣ ታውቅ ይሆን....?
"የሚያስፈልግሽ ነገር ሲኖር ለሰራተኛሽ ንገሪያት ታሳውቀኛለች....ደህና ሁኚ"...ስንብት መሆኑ ነው።
"ለእኔም ቀን አለ..."....ደህና ሁን ልለው አልችልም....
✍Shewit dorka
https://t.me/shewitdorka
924
ክንፍ ነበረኝ✨✨
በነጋታው ባስለመደኝ ሰአት መጣ....የተለመዱትን ነገራት አደረገልኝ...ዛሬ አልበላም ብዬ ብል እንኳን ሆዴ አፍ አውጥቶ መራቤን ይነግርብኛል...አይሆንም አልኩ ለራሴ...በዚህ መልኩ መሞት ጊዜ ይወስዳል አልኩ መልሼ....
ጥርግ አድርጌ በላሁ.....ድሮ ድሮ ከእንቁላል ውጪ መስራት የሚችለው ነገር አልነበረም...ይሄን ሙያ ከየት እንዳመጣው ባላውቅም በያይነቱ ያበስልልኛል.....
'ለእኔ ብሎ አጭር ኮርስ ወስዶ ይሆናል' እለዋለሁ 'አሁን ጠልቶሻል' ለሚለኝ ጎኔ...
እርሱም አይረታም...'እና እንደዛ እያልሽ ነው ራስሽን የምታፅናኚው'...ይለኛል...አንዳንዴ ጎኔን ማድመጥ ትቼ ለእኔ እየሆነ ያለውን ነገር እቆጥራለሁ....
ይመጣል...ማታ ካስቀመጠኝ ቦታ ያነሳኝና ዊልቸሬ ላይ ይሰይመኛል...መፀዳጃ ቤት ይወስደኛል...ምግብ ያበስልልኛል...ያጎርሰኛል...በየመሀሉ ይሰድበኛል...ይወጣል...ወደ ማታ ተመልሶ ይመጣል...የቅድሙን ደግሞት አልጋ ላይ ወርውሮኝ ይወጣል...ማን እንዲህ ያደርጋል...?....
እቅፉን የማገኘው ወንበር በሚያቀያይርልኝ ቅፅበት ነው...ያኔ ነው ፊቱን በቅርበት የማየው.....ለምሰራተኛ እንደማይቀጥርልኝ እንጃ....
ዛሬ እንደወትሮው ስራውን ከጨረሰ በኃላ ትቶኝ አልወጣም...ፊት ለፊቴ ተቀመጠ...ግራ ገባኝ..."ምነው"...ጠየቅኩ....ምንም ሳይለኝ ግራ እጄን ያዘኝ....ልክ ድሮ ቀለበት ሊያረግልኝ ሲል እንደያዘኝ መያዝ...አንደ ድሮዋ ልዕልት ተሽኮረመምኩ....የእጁን ልስላሴ ባላጣጥመውም...እጄ ቢደነዝዝም በአይኔ ብቻ ብዙ ብዙ አልኩ..."መኖር ያን ያሀል አይከብድም "..."ይወደኛል እኮ..."..."አባት ተመለሰ...."....ልቤB የድሮው ቦታው ሊሾመው ቸኮለ...አሁን ጠፍቶ የተመለሰን ሎሌ ወዲያው ጓዳ ለማስገባት መጣደፍ ምን ይሉታል...ተጣደፍኩ...መመለሱን ሳላውቅ ተጣደፍኩ።
እጄን ከዊልቸሩ መደገፊያ አንስቶ ወደራሱ አስጠጋው...እስከዚህ ምንም አልተነፈሰም...ያወለቀው ቀለበት እጁ ላይ አለ...የጋብቻ ቀለበታችን...ኪሱን ሲደባብስ ጥድፊያዬ ጣሪያ ነካ...ገላዬን ሲያጥበኝ በግዴለሽነት የጣለብኝን ቀለበት ሊተካልኝም መሰለኝ...ከረጅም ጊዜ በኃላ ፈገግ አልኩ...አሁንም ጥድፊያው አለቀቀኝም...ባለፈው እንኳን ነገርኩት...መናገሬና እንባዬ እንደሚመልሰው ባውቅ ያኔ ድሮm አደርገው አልነበር እንዴ...ተጣደፍኩ...እጄ ቢሰራልኝ እኔ ራሴ ከኪሱ አውጥቼ እንደማጠልቀው እርግጠኛ ነበርኩ...
ከኪሱ እስኪሪፕቶ አወጣ...ከዛ ከቦርሳው ወረቀት መዘዘ...በእስኪርፕቶው አውራ ጣቴን አቀለመ...ያቀለመው ጣቴን ከወረቀቱ ጠርዝ ካለው ክፍት ቦታ ለተመ...አሁን ቀዘቀዝኩ።
"የፍቺ ወረቀት ነው...እንደምትስማሚ እርግጠኛ ነኝ...ባለሽበት ሁኔታ ምክንያት ፍርድ ቤቱ በአካል አለመገኘትሽን...."...ብዙ አብራራ...
"ሰራተኛ ቀጥሬልሻለሁ...ጨርሰናል....አመሰግናለሁ...."....አለና ንግግሩን ቋጨ።
በተራዬ ተለጎምኩ...አይኔ ደረቀ...አካላቴን አደጋው ባበደነው ልክ እሱም ልቤን አበደነው...ዝምምምም ጭጭጭጭጭ.......ረጭጭጭጭ
...ጩሂ ጩሂ አለኝ...ግን አልጮህኩም...ማልቀስ ፈለግኩ ግን ለእሱም ደከመኝ...ጥያቄም አለኝ ግን ከምን እንደምጀምር አላውቅም...
እኔን ትቶ የሄደላት ሴት ህይወት ፊቷን ያዞረችባት እንደው እርሱም እንደሚያዞርባት ታውቅ ይሆን...."እኔን ሳያውቅ ያደረገው ነገር ነው..."...ብላ ችላ ትለው ይሆን...ምን እንዳፈራረሰ ታውቅ ይሆን...በቁም ቀብሮ እንደመጣ ታውቅ ይሆን....?
"የሚያስፈልግሽ ነገር ሲኖር ለሰራተኛሽ ንገሪያት ታሳውቀኛለች....ደህና ሁኚ"...ስንብት መሆኑ ነው።
"ለእኔም ቀን አለ..."....ደህና ሁን ልለው አልችልም....
✍Shewit dorka
https://t.me/shewitdorka
