ቤርያ youth ministry
Open in Telegram
ናይዚ ቻናል ራእይ👇👇👇👇 የሱስ ክርስቶስ ዝመስል ሕይወት ዘለዎም ፣ ብቃል ሓቂ ናይ ሓሶት ትምህርቲ ዝቃወሙ ፣ ብወንጌል ምኽንያት ካብ ዝተፈላለዩ ዓይነታት ተፅዕኖ ሓራ ዝኾነ መንኣሰይ ምእመንና አገልገልቲ ፈርዮም ምርኣይ 👉 ቻናልና ስብስክራይብ ብምግባራ ቤተሰብ ይኹኑ 👉https://t.me/bhham5a2e0r1e5b
Show more246
Subscribers
No data24 hours
-37 days
+130 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
January '25
January '25
+5
in 0 channels
December '24
+2
in 0 channels
Get PRO
November '24
+2
in 0 channels
Get PRO
October '24
+8
in 0 channels
Get PRO
September '24
+17
in 0 channels
Get PRO
August '24
+242
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 19 January | 0 | |||
| 18 January | 0 | |||
| 17 January | 0 | |||
| 16 January | 0 | |||
| 15 January | 0 | |||
| 14 January | 0 | |||
| 13 January | 0 | |||
| 12 January | 0 | |||
| 11 January | 0 | |||
| 10 January | 0 | |||
| 09 January | 0 | |||
| 08 January | +2 | |||
| 07 January | +1 | |||
| 06 January | 0 | |||
| 05 January | 0 | |||
| 04 January | +2 | |||
| 03 January | 0 | |||
| 02 January | 0 | |||
| 01 January | 0 |
Channel Posts
🔥አዳኝ ተወለደ 🔥
✍️ አንድ ወረ ወጣ ከወደ ቤተልሔም
ተሰምቶ የማያቅ በምድር በሰማይም
ፍጥረቴ ዓለሙን በሙሉ ሚያስደምም
አምለክ በረት ወርዶ ተወልዷል ለዓለም
✍️ እነማ ስሰማው ለጆሮዬ ከብዶ
ስሉኝ ተወልደ በበረት ተዋርዶ
የሰውን ልጅ ሊያድን ፈጣሪ ተሰዶ
ከመንበረ ዙፋን ከሰማያት ወርዶ
✍️ ሊያከብረን አስቦ ውርደታችንን ወስዶ
የአብ ልጅ ከስፍራው ከፍቅሩ ወርዶ
በከብቶች በረት ውስጥ ለዝያውም በባዶ
ፍቅር ተወለደ እኔን አንተን ወዶ ተወልደ
✍️ኢየሱስ ተወልዶ ባይሰብርልን ቀንበር
ሰይጣንን ባይቀጣው መጥቶ ወደ ምድር
በጨለማው መንግሥት በተሰቃየን ነበር
ኢየሱስ ተወልዶ ሰበረብን ቀንበር 🙏🙏
| 2 | No text... | 150 |
| 3 | በሥጋ መጣ
ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ መጣ ማለት በሥጋ ሳይመጣ በፊት ያለ ሥጋ ነበረ፤ ኋላ ግን በሥጋ መጣ ማለት ነው። በሥጋ ሳይመጣ በፊት ያለ ሥጋ ነበረ፤ ቃል ነበረ፤ መለኮት ነበረ። በሥጋ ሲመጣ ደግሞ መለኮትን ሳይተው ሥጋን ጨመረ።
ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ ሲመጣ፥ ካለመኖር ወደ መኖር አይደለም የመጣው። ከመኖር ወደ መኖር ነው የመጣው። መለኮት ብቻ ሆኖ ከቀድሞው ለዘላለም መኖር፥ መለኮትም ሰውም ሆኖ በአንድ አካል ከመጣበት ወዲህ ለዘላለም ወደ መኖር ነው የመጣው።
ይህንን በሥጋ መምጣቱን የማይቀበል፥ የማያምን፥ የማይታመን ሁሉ፥ ኢየሱስ መለኮት አይደለም፤ ሰው ብቻ ነው፤ የሚል ሁሉ፥ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ እርሱ የክርስቶስ ተቃዋሚ መንፈስ ነው።
የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፥ ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥ አሁንም እንኳ በዓለም አለ። 1ዮሐ. 4፥2-3
ብዙ አሳቾች ወደ ዓለም ገብተዋልና እነርሱም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የማያምኑ ናቸው፤ ይህ አሳቹና የክርስቶስ ተቃዋሚው ነው። 2ዮሐ. 7 | 420 |
| 4 | No text... | 86 |
| 5 | No text... | 1 |
| 6 | 👉 ቆም ብለን እናስብ🤔🤔
✍️ የኛ እና የኛ ዘመን አገልግሎት፣ ለቀጣዩ ትውልድ ቢጻፍ፦ ምን ይጻፍልን ይሆን? መጽሐፍ ቅዱስ፣ በእኛ ዘመን ቢጻፍ እና የሁላችንንም ታሪክ ቢያካትት ምን ዐይነት ገጸ ባሕርይ ይወጣናል? 🥺🥺
✍️ እንደ መጥምቁ፣ ኢየሱስን ያላቀ አገልግሎት ነበራቸው ይባል ይሆን? ወይስ አገልግሎታችን ኢየሱስን አደብዝዞ፣ ታሪካችን ደብዝዞ ይቀራል?🤔
✍️ የእምነት ታሪካችን፣ እንደ ቶማስ፣ "ካላየሁ አላምንም" የሚል የጥርጣሬ ይሆናል? ወይስ "ሳያዩ የሚያምኑ" የሚል የብፅዕና ታሪክ ይኖረናል? 🤔
✍️ እንደ ይሁዳ፣ ከኢየሱስ ይልቅ ገንዘብን የመውደድ ታሪክ ይኖረን ይሆን? 🤔
✍️ እንደ ጳውሎስ፣ ስለ ኢየሱስ ጥቅሞችን የመተው ወይስ በጥቅሞች ምክንያት ኢየሱስን የመተው ታሪክ ይኖረናል? 🤔
✍️ እንደ ጢሞቴዎስ፣ የክርስቶስን የመፈለግ ወይስ የራስን ጥቅም የማሳደድ ታሪክ ይጻፍልናል? 🤔
✍️ እንደ ዴሞስ፣ ዓለምን ወዶ ጥሪን ጥሎ የመሄድ ወይስ ዓለምን ከነጓዟ ጥሎ የመምጣት? የቱ ይዘገብልናል? 🤔
✍️ እንደ ዲዮጥራጢስ፣ በስልጣን ጥም እውነተኛ መሪዎች ላይ በር የመዝጋት ታሪክ ይጻፍልን ይሆን?
✍️ እንደ ሄኔሲፎሩ እና ቤተ-ሰቡ፣ ከእውነተኞች ጋራ የመቆም ወይስ እንደ አንጥረኛው እስክንድሮስ እውነተኞችን የመግፋት ታሪክ ይኖረናል? 🤔
👉 #መጻፋችንን ብቻ ሳይሆን፣ #ምን አብሮ እንደሚጻፍልን እናስብ! 🥺🥺🥺 | 481 |
| 7 | No text... | 89 |
| 8 | በነገራችን ላይ ከእግዚአብሔር ያልመጣ የትኛውም ነገር ተመልሶ ቢሄድ በረከት ነው
🙏🙏🙏 | 564 |
| 9 | 💥“የምገዛው ራሴን ነው”🔥
✍️ የታላቂቱ ፕሩሺያ ንጉስ የነበረው ታላቁ ፍሬደሪክ አንድ ጊዜ በበርሊን መንገድ ላይ ሲሄድ ሳለ አንድ በእድሜው እጅግ የሸመገለ ሰው ልክ እንደሱ በመንገድ ላይ ሲሄድ አገኘው፡፡ ይህ እድሜ-ጠገብ ሰው የነበረው አረማመድ የንጉሱን ትኩረት ሳበው፡፡ ይህ ሰው ቀና ብሎ፣ ደረቱን ገልብጦና አይኖቹ በትኩረት እያዩ ግርማ-ሞገስ ያለው ገዢ አይነት አካሄድ እየሄደ ነበር፡፡ ንጉስ ፍሬደሪክ የሰውየውን በራስ መተማመን በመመልከት ለማነጋገር ፈለገ፡፡
ንጉስ ፍሬደሪክ፡- “አንተ ማን ነህ?”
ሽማግሌው፡- “እኔ ንጉስ ነኝ”
ንጉስ ፍሬደሪክ፡- “ግዛትህ ምንድን ነው?
ሽማግሌው፡- “የምገዛው ራሴን ነው”
ይህ ታላቅ ገዢና ንጉስ በዚህ አዛውንት አነጋገር የማይረሳውን ትምህርት አግኝቶ መንገዱን ሄደ፡፡
✍️ ለካ፣ የገዢነት ሁሉ ገዢነት ራስን መግዛት ነው!
✍️ ለካ፣ የአመራር ሁሉ አመራር ራስን መምራት ነው!
✍️ ለካ፣ የኋላ ቀርነት ሁሉ ኋላ ቀርነት ራስን ሳይገዙ ሰውንና ሕብረተሰብን ለመግዛት መሞከር ነው!
✍️ ለካ፣ የውድቀት ሁሉ ውድቀት ራስን ሳይመሩ ሌላውን ለመምራት መሞከር ነው! 🙏🙏🙏 | 574 |
| 10 | No text... | 158 |
| 11 | 🔥 አንድ ትውልድ 🔥
✍ በዘመናት መሃል ላንተ የተለየ
ከሚጠፋው ይልቅ የሰማዩን ያየ
ብድራቱን አይቶ አንተን የሚከተል
ባንተ ከመጡበት ወደዋላ የማይል.
አንድ ትውልድ
✍ ከራሱ ፈቃድ አንተን ያስበለጠ
ከምድር ብልጭልጭ አንተን የመረጠ
ለመንግስትህ ትጉ ብርቱ ሰራተኛ
በምቾቱ ታንቆ ላፍታ የማይተኛ
ለተቀን ለወንጌል የሚሮጥ ታታሪ
ትውልዱን ለመድረስ አዋጅ ተናጋሪ.
አዎ አንድ ትውልድ
✍ አለ በዘመኔ ላየው ምናፍቀው
በፀሎት በእንባ ለአምላኬ ምነግረው
እንደ ኤሊ ልጆች ከመንገድ የሚቀር
እያየ ዝም የሚል ስምህ ሲደፈር
ባንተ የተጠላ እጅግ የተናቀ
በዓለም ስሙ ገኖ በፊትህ ያልታወቀ
አይደለም ያ ትውልድ ላየው ምፈልገው
በዘመን ፍፃሜ ተነስቶ የማየው.
ይልቅስ
✍ እንደዮሴፍ ቆራጥ አንተን የሚፈራ
የሕይወት መንገዱ ባንተ የተሰራ
በዘመኑ ሁሉ አንተን ያስቀደመ
የአንደበቱ ቃል ባንተ የተቀመመ.
አዎ ይሄ ነው የኔ ትውልድ
✍ በዘመኔ ሁሉ ላየው ምፈልገው
የሚታየው ነገር ጠልፎ የማይጥለው
ልክ እንደ ኤልሳ ማንንም የማይሰማ
ራሱን ላንተ ሚሰጥ አንዳች ሳያቅማማ
ይሄ ነው ምርጥ ትውልድ ላንተ የተለየ
ለነፍሱ ማይሳሳ ላንተ ከተባለ. 🙏🙏
| 580 |
| 12 | No text... | 288 |
| 13 | 👉 የዩኒቨርስ ( አጽናፍ ዓለም ) መነሻ እግዚአብሔር ቢሆንስ ??🤔🤔
👉ይህ የምንኖርበት ዓለም ዩኒቨርስ ከየት መጣ ? ለምንስ መጣ ? ማንስ አመጣው ? ዩኒቨርስን ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣው ምክንያት ( አካል ) ምንድነው ?? ወይም ማነው ???🙄🙄🙄
👉 አስትሮፊዚክስ ማለት ስለጠፈር ፣ ስለ ክዋክብትና ስለ ፕላኔቶች በአጠቃላይ ስለህዋ አካላት አፈጣጠር ፣ ፀባይና ሥርዓት የሚቆጣጠሩ ህጎችን የሚያጣና የፊዚክስ ቅርንጫፍ ነው ። ዩኒቨርስ የተፈጠረበት ሂደት ታላቁ ፍንዳታ The Big Bang ተብሎ ይጠራል ስለዚህ ታላቁ የዩኒቨርስ የልደት ቀኑ ነው ።
አስትሮፊዚክስ የሚናገረው ዩኒቨርስ ወደ መኖር የመጣው በታላቁ ፍንዳታ አማካይነት ከ13.8 ቢሊዮን ዓመታት በፊት እንደሆነ ነው ። ይህ የሚያሳየን ዩኒቨርስ መነሻ ጊዜ እንዳለው ነው ።
👉 ዩኒቨርሽ መነሻ ጊዜ ካለው ደግሞ ከዚያ በፊት አልነበረም ማለት ነው ። ዩኒቨርስ ከዚያ በፊት ያልነበር ከሆነ ደግሞ ዩኒቨርስን ያስገኘ አንድ አካል አለ ማለት ነው ። ይህ አካል ማን ይሆን ???
ይህንን አካል ነው ሳይንስ ማግኘት ያቃተው ። መጽሐፍ ቅዱስ ግን ይህንን አካል እግዚአብሔር መሆኑ ገልጠታል
👉 የዩኒቨርስ መነሻ ራሱን በራሱ የተፈጠረ ነው ካልን ደግሞ ሎጂካል አይደለም ። አንድ ነገር በራሱ ተፈጠረ ማለት የምክንያታዊነትን ህግ ( law of causality ) ያልተከተለ ስለሆነ ተቀባይነት የለውም ። የትኛውም ህይወት ያለውም ሆነ ግዑዝ ነገር በመጀመርያ ያልነበረ ከሆነ እራሱን በራሱ ሊፈጥር አይችልም ። የትኛውም ነገር እራሱን ካለመኖር ወደ መኖር ማምጣት አይችልም ።
👉 ለምሳሌ ጀበና ጭቃ አቡክታ እራሷን መሥራት አትችልም ። የግድ ሸክላ ሠሪ ያስፈልጋታል ፣ ምክንያቱም ጀበና ጭቃ አቡክታ እራሷን መሥራት ቻለች ማለት ያለምክንያት ውጤት ( effect without a cause) ተገኘ ማለት ነው ። ያለምክንያት ደግሞ ውጤት ሊገኝ አይችልም ። ለጀበና መገኘት ምክንያቱ cause የሸክላ ሠሪ መኖር ነው ። ለዩኒቨርስ መገኘት ደግሞ ምክንያቱ የፈጣሪ መኖር ነው ። ይህም ፈጣሪ የመጽሐፍ ቅዱሱ እግዚአብሔር ነው ።
👉 በመጀመርያ እግዚአብሔር ሰማይና ምድሪ ፈጠረ
ዘፍ 1፥1 ይለናል ታላቁ መጽሐፍ ቅዱስ ። ስለዚህ የዩኒቨርስ መነሻ ወይም ፈጣሪ እግዚአብሔር ነው ። እግዚአብሔር የፍጥረት ሁሉ ፈጣሪ አምላክ ነው ።🙏🙏 | 569 |
| 14 | No text... | 138 |
| 15 | የለም ሌላ አዳኝ ፤ ገንዘብ አያድንም ፣ ዕውቀት አያድንም ፣ ስልጣን አያድንም ፣ ዘር አያድንም ፣ ዝና አያድንም የሚያድን እግዚአብሔር ብቻ ነው 🙏🙏🙏 | 625 |
| 16 | ህይወት ማለት ከኢየሱስ ጋር ያለን " Relationship" እንጂ መማር ፣ መመረቅ ፣ ትዳር መያዝ ፣ መበልጠግ ፣ ከዚያ ማለፍ አይደለም🙏 | 655 |
| 17 | No text... | 577 |
| 18 | በህይወታቹ መጨነቅ ያለባቹ ነገ ስለምታጭዱት አዝመራ ሳይሆን ዛሬ ስለምትዘሩት ዘር ነው ። ውጤቱን መቀየር አትችሉም መንስኤውን እንጂ ። አዝመራውን ለመቀየር ዘሩን መቀየር ጥበብ ነው 🙏🙏🙏 | 488 |
| 19 | No text... | 163 |
| 20 | 👉 ጽዮን ማናት ?🤔🤔🤔
ኢሳ 60፥14 " የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ" የሚለው ስለ ቅድስት ማርያም ነው የሚናገረው ይላሉ ?
👉 ኢሳ 60፥10 በቁጣዬ ቀሥፌ በፍቅሬ ምሬሻላኹና ይላል ። መቼ ማርያም እግዚአብሔር የቀጣት ደግሞ የማራት ??
👉 ኢሳ 60፥15 ከሰውም ማንም እስከማያልፍብሽ ድረስ የተተውሽና የተጣላሽ ነበርሽ ይላል። ምን ማለቱ ነው ? ለማርያም ነው ?
👉 ጽዮን ግን እግዚአብሔር ትቶኛል ጌታም ረስቶኛል አለች ኢሳ 49፥14 ለቅድስት ማርያም ጌታ ረስቷት ወይም ትቷት ያውቃል እንዴ ?? ጌታ ካንቺ ጋር ነው ያላት ገብርኤል ሉቃ 1፥28 አይጋጭም ወይ ?
👉 ኢሳ 60፥14 ክፍል የሚናገረው ወደ ባቢሎን የተማረኩት የይሁዳ ሰዎች ከምርኮ በመመለስ የሚጽናኑበት ዘመን እንደሚመጣ ፣ የማረኳቸውና አስጨንቀው ለሰባ ዓመታት የገዟቸው አሕዛብም ዐንገታቸውን ደፍተው ፣ እስራኤላውያንን ወደ ማክበር እንደሚመለሱ ፣ ጽዮንም ተመልሳ እንደምትታነጽ የሚገልጥ ነው ።
👉 ሌላ ስለ ቅድስት ማርያም "ሰው እናታችን ጽዮን ይላሉ ። መዝ 87 ፥7 ይህ ክፍል ስለ ማርያም የሚናገረው ካልን ጽዮን አንድ ሰው ብቻ ሳይሆን ብዙ አለቆች ከእርሷ ውስጥ እንደ ተወለዱ ይናገራል ከ 1-6 ቁጥር ያለው ታድያ ማርያም ብዙ ልጆች አላት ማለት ነው ??
መዝ 87ን አስተውሎ ላነበበው ሰው ስለ ጽዮን ከተማ እንጂ ስለ ቅድስት ማርያም አይናገርም ።
✍️ ለመኾኑ ጽዮን ማናት ? መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይላል ??🤔🤔🤔
👉 1ኛ. ጽዮን የኢየሩሳሌም ከተማ ከተሰራችባችው ተራራዎች አንዱ ሲኾን የቃሉ ትርጉም ደግሞ አምባ / ምሽግ/ ማለት ነው ። የጽዮን ተራራ በስተ ሰሜን አቅጣጫ ይገኛል መዝ 48፥2 ። ጽዮን የመጀመርያ የተመሸገችው በኢያቡሳውያን ነበር ዳዊት በኢያቡሳውያን ሥር የነበረችውን የጽዮን ተራራ ሙሉ በሙሉ ድል አድርጎ ተቆጣጠረ ጽዮንንም ያዘ ( 2ሳሙ 5፥6-10 ፣ 1ዜና 11፥4-7 ) ከዚ ሀሳብ የምንረዳው ጽዮን የሚለው ስለ ቅድስት ማርያም ሳይሆን ከተማ ወይም ቦታ መሆኑ ነው የሚያሳየን ።
👉 2ኛ. ጽዮን የሚለው መላውን ኢየሩሳሌም ሕዝብ የሚወክል ነው ። 1ነገ 18 ፥35 ፣ 19፥21 ፣ መዝ 69፥35 ፣ 147፥12 ጽዮን የሚለው የእስራኤል ሕዝብ ያመለክታል ። ከዚህ ሀሳብ የምንረዳው ደግሞ ጽዮን የሚለው ማርያም ሳይሆን መላውን ቤተ እስራኤል ትወክላለች ።
👉 3ኛ. ጽዮን የሚለው ቃል መንፈሳዊ ( ሰማያዊት ) ጽዮንንና ቤተ ክርስቲያንን ያመለክታል ። ሰማያዊቱ ጽዮን በእግዚአብሔር የተስፋ ቃል መሠረት በክርስቶስ ያመኑ ምእመናን ሁሉ አሁን በእምነት የገቡበትንና ወደ ፊትም በጌታ ዳግም ምጽአት የሚወርሷትን መንግስተ ሰማያትን ታመለክታለች ። ገላ 4፥2-6 ፣ ዕብ 12፥22 ፣ ራእ 3፥12 ፣ 21፥2,10 ከዚህ ሀሳብ የምንረዳው ጽዮን የሚለው ስለ ቅድስት ማርያም ሳይሆን ስለ ሰማያዊት ጽዮን ትወክላለች ።
👉 እንግዲህ የጽዮን ትርጉም ይህን ሲመስል ከዚህ ውጭ በተናጠል ለማርያም ተሰጥቶ መተርጎም መናፍቅነት ነው ።🙏🙏 | 695 |
