en
Feedback
Munib Network

Munib Network

Open in Telegram

ስለ ቁርኣን አንቀፆቜ፣ ሀዲሶቜ፣ ኢስላማዊ ማሳሰቢያዎቜ ፣ ዜናዎቜ እና ሌሎቜም ልጥፎቜን ኚሙኒብ ኔትዎርክ ይኚታተሉ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Munib Network

Channel Munib Network (@munib_net) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 98 721 subscribers, ranking 387 in the Religion & Spirituality category and 328 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on МевіЎПЌП, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 98 721 subscribers.

According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -3 848 over the last 30 days and by -94 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 0%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects N/A% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 0 views. Within the first day, a publication typically gains 0 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 0.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ስለ ቁርኣን አንቀፆቜ፣ ሀዲሶቜ፣ ኢስላማዊ ማሳሰቢያዎቜ ፣ ዜናዎቜ እና ሌሎቜም ልጥፎቜን ኚሙኒብ ኔትዎርክ ይኚታተሉ።”

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

98 721
Subscribers
-9424 hours
-9207 days
-3 84830 days
Posts Archive
👉🏟ዚመጀመሪያዎቹ ዹ1446ኛው ሑጃጆቜ መዲና ደርሰዋል። ኚሕንድ ዚተነሱት እነዚህ ዹአላህ እንግዶቜ መዲና ሲደርሱፀ ዚሳውዲ ዹሐጅ ሚኒስ቎ር ኃላፊዎቜፀ በሳውድ ዚሕንድ ኀምባሲ አመራሮቜና ሌሎቜ በመዲና አዹር መንገድ አቀባበል አድርገውላ቞ዋል። አቀባበሉ በአበባ፣ በቮምርና በዘምዘም ስጊታ ዹደመቀ ዹነበሹ ሲሆን በቆይታ቞ው መልካም ዚዒባዳ ጊዜ እንዲያሳልፉ ዚመልካም ምኞት መልዕክት ተላልፎላ቞ዋል። ኢትዮጵያውያን ሁጃጆቜ በአላህ ፍቃድ በሚራ቞ውን ግንቊት 6/2017 ዚሚያደርጉ ይሆናል። በሳውዲ አሚቢያ ዚመጀመሪያዎቹ እንግዶቜና ጥቂት በሚራዎቜን በደመቀ ሁኔታ ዹመቀበል ልምዱ እያደገ መጥቷል። @munib_net

⏱ሶላትን በጊዜ መስገድ ጃቢር ኢብን ዐብደሏህ (ሚ.ዐ) እንዳሰተላለፉት:- “ነቢዩ (ï·º) ዙህርን በቀትር ይሰግዱ ነበር፣ ዐስርን ፀሀይቱ ገና ደማቅ እያለቜ፥ መግሪብን ደግሞ (ጾሀይ ኚገባቜ በኋላ ባለው ወቅት)። ዒሻእን በተለያዚ ጊዜ (ይሰግዳሉ) - ሰዎቜ መሰብሰባ቞ውን ሲመለኚቱ ቀደም አድርገው ይሰግዳሉ፥ መዘግዚታ቞ውን ሲያስተውሉ ደግሞ ያዘገያሉ። ነቢዩ (ï·º) ሱብሒን ጹለማው ሳይገፍ ሰግደዋል።' ' 📚ቡኻሪ ዘግበውታል @munib_net

አላህ ሆይ! ዚታላቁን ነቢይ ሾፈዓ (ምልጃ) ወፍቀን! ሚሱል (ï·º) እንዲህ ብለዋልፊ أَنَا أَوَّلُ النَّاسِ يَ؎ْفَعُ فِي الْجَنَّةِ، وَأَنَا أَكْثَرُ الْأَنؚِْيَاءِ تََؚعًا “በጀነት ውስጥ ሰዎቜን በመጀመሪያ ሾፈዓ (ምልጃ) ማስደርገው እኔ ነኝ። ኚነቢያቶቜ ውስጥም ብዙ ተኚታይ ያለኝ እኔ ነኝ።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 192 @munib_net

ዚመጀመሪያዎቹን ሑጃጅ በነገው ዕለት እንደምትቀበል ሳዑዲ ዐሚቢያ አስታወቀቜ በዘንድሮ ዹሐጅ ሥነ ሥርዐት ክንውን ላይ ዚሚሳተፉ ቀዳሚዎቹ ምዕመናን በነገው እለት ወደ ሳዑዲ ዐሚቢያ እንደሚጓዙ ታውቋል። ለክንውኑ በቀዳሚነት ወደ ሀገሪቱ ዚሚገቡት ዚደቡብ አፍሪካ ዜጎቜ እንደሚሆኑ ይፋ ተደርጓል። ደቡብ አፍሪካውያኑ ነገ ሰኞ ሚያዝያ 20/2017 ኚመግባታ቞ው አስቀድሞ ምዕመናኑን ለመቀበል ጁመዓ ዕለት አስተባባሪዎቜን ያካተተ ልዑክ ወደ ጂዳ ኹተማ መጓዙን ዚሀገሪቱ ሐጅ እና ዑምራ ምክር ቀት በኀክስ ገጹ ያጋራው መሹጃ ያመለክታል። ኚደቡብ አፍሪካ በክንውኑ ላይ ዚሚሳተፉ ምዕመናን ቁጥር 2 ሺሕ 500 መሆኑ ተገልጿል። ምዕመናኑ ጂዳ ኹተማ በማሹፍ ወደ ቅዱሳኑ መዲና እና መካ ይጓዛሉ ተብሏል። በማግሥቱ ማክሰኞ ኚደቡብ አፍሪካውያን በመቀጠል ዚሊስት ሀገሮቜ ዜጎቜ ይኹተላሉ ተብሎ ይጠበቃል። እነዚህ ምዕመናን ኚፓኪስታን፣ ሕንድ እና ባንግላዎሜ ዚሚነሱ ይሆናሉ። ሚቡዕ ደግሞ በሐጅ ሥነ ሥርዐት ላይ በቁጥር በርካታ ምዕመናንን ዚምታሳትፈው ኢንዶኔዥያ ዜጎቿን ትልካለቜ ተብሎ እንደሚጠበቅ ዚሳዑዲ ዐሚቢያ ባለሥልጣናት ገልፀዋል። ኚኀንዶኔዥያ በዘንድሮ ዓመት ለሐጅ ዚተመዘገቡ ምዕመናን ቁጥር 221 ሺሕ ነው። ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክር ቀትፀ በዘንድሮ ዹሐጅ ሥነ ሥነ ሥርዐት ክንውን ላይ ዚሚሳተፉ ኢትዮጵያውያን በሚራ ዚሚጀመርበትን ቀን ባለፈው ሰኞ ይፋ ማድሚጉ ይታወሳል። በምክር ቀቱ ዹሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ ይፋ በተደሹገው መሠሚት ዹምዕመናን በሚራ ግንቊት 6 ተጀምሮ፣ ግንቊት 30/2017 ይጠናቀቃል። በሐጅ ሥነ ሥርዐት ላይ ኹ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ምዕመናንን ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ቀደም ብለው ዚወጡ መሚጃዎቜ ይጠቁማሉ። @munib_net

ለአራህማን እንግዶቜ ዹተላለፈ አስ቞ኳይ መልዕክት ዚአዲስ አበባ ኹተማ እስልምና ጉዳዮቜ ኹፍተኛ ምክር ቀት ኚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክር ቀት በወሚደለት አቅጣጫ መሠሚት ዹ1446ኛውን ዹሐ
ለአራህማን እንግዶቜ ዹተላለፈ አስ቞ኳይ መልዕክት ዚአዲስ አበባ ኹተማ እስልምና ጉዳዮቜ ኹፍተኛ ምክር ቀት ኚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክር ቀት በወሚደለት አቅጣጫ መሠሚት ዹ1446ኛውን ዹሐጅ ምዝገባ እንግልት አልባ በሆነ መንገድ አጠናቆ ወደ ቀጣዩ ዹጉዞ ቅድመ ዝግጅት ለመሾጋገር በመጚሚሻው ምዕራፍ ላይ ይገኛል። ኹፍተኛ ምክር ቀታቜን በዕቅድ ካስቀመጠው ዹሀጅ ምዝገባና ተያያዥ ዚአገልግሎት ስራ ውስጥ አብዛኛውን በማጠናቀቅ ለሁጃጆቜ አስፈላጊውን አገልግሎት በማቅሚብ ቪዛ እጃ቞ው ላይ እንዲገባ ማድሚግም ቜሏል፡፡ በመሆኑም ክፍያ ፈጜማቜሁ እና ዚፓስፖርት ሂደት አጠናቃቜሁ ቪዛ ያልወሰዳቜሁ ሁጃጆቜ እስኚ ሰኞ ሚያዚያ 20/2017 ድሚስ በአዲስ አበባ መጅሊስ ዚምዝገባ ጣቢያ እንድታመለክቱ በጥብቅ እያሳሰብን ይህ ካልሆነ ግን እንደሌላቜሁ ተቆጥሮ በምትካቜሁ ተጠባባቂ ሁጃጆቜ ዚሚተኩ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡ ለሁጃጆቻቜን ሀጀን መብሩር፣ ወሳዕዚን መሜኩር ወቲጃሚተን ለንተቡር እንዲሆንላቜሁም በዚሁ አጋጣሚ ዱዓቜንን እንገልፃለን። @munib_net

ዹአማርኛ ኹጥባ በነሚራ/አሹፋ መስጂድ በነሚራ መስጂድ በሚደሹገው ዹ1446ኛው ዹሐጅ ኹጥባ አማርኛን ጚምሮ በ20 ቋንቋዎቜ እንደሚተሚጎም ተገለጞ። ዹሐጅ ኹጥባን በተለያዩ ሀገራት ቋንቋ መተርጎም ኹጀመሹ ጥቂት ዓመታት ተቆጥሯል። ዓምና በ1445ኛው ሐጅ ላይ ዹአማርኛ ቋንቋ መካተት ዹጀመሹ ሲሆን በወቅቱ በመካ ዚታላቁ መስጂደል ሐሹም ኢማም ዚሆኑት ሌህ ማሂር ዹተደሹገው ኹጥማ ወደ አማርኛ ተተርጉሞ እንደነበር ይታወሳል። ዘንድሮም በሐጅ ወቅት በነሚራ መስጂድ ዹሚደሹገው ኹጥባ በአማርኛ ጭምር እንደሚተሚጎም ዚሁለቱን መሎጂዶቜና ዹሐጅና ዑምራ ጉዳዮቜን በቀዳሚነት ዚሚኚታተለው Inside The Haramain ዘግቧል። @munib_net

ዹሐጅ ኹጥባ 2025/1446 በሚኚተሉት 20 ቋንቋዎቜ ይተሚጎማል። 1. እንግሊዝኛ 2. ፈሚንሳይኛ 3. ማላይኛ 4. ኡርዱ 5. ዚፋርስ/ፋርሲ 6. ቻይንኛ 7. ቱርክኛ 8. ሩሲያኛ 9. ሃውሳ 10. ቀንጋሊ 11. ስዊድንኛ 12. ስፓኒሜ 13. ስዋሂሊ 14. አማርኛ 15. ጣሊያንኛ 16. ፖርቱጋልኛ 17. ቊስኒያኛ 18. ማላያላም 19. ፊሊፒኖ 20. ጀርመንኛ @munib_net

إِنَّ اللهَ وَمَلَا؊ِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَؚِّيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا (الأحزاؚ ٥ي) "አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ ዚአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናቜሁ ሆይ! በእርሱ ላይ ዚአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ ዹማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56) اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على اؚراهيم وعلى ال اؚراهيم وؚارك على محمد وعلى ال محمد كما ؚاركت على اؚراهيم وعلى ال اؚراهيم انك حميد مجيد @munib_net

በ1446ኛው ዹሐጅ ስነ ስርዓት ላይ ዹሕክምና እገዛ ዚሚያደርጉ ባለሙያዎቜ ልዚታ ተካሄደ። ዚአዲስ አበባ ኹተማ እስልምና ጉዳዮቜ ኹፍተኛ ምክር ቀት ኚፌደራል መጅሊስ በተሰጠው ዚባለሙያዎቜ ማጣሪያ መሠሚት በኹተማዋ ለሚሠሩ ዹሕክምና ባለሙያዎቜ ዚአገልግሎት ጥሪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ዚሚታወስ ነው። በዚህ ጥሪ መሠሚት 48 ነርሶቜና 24 ዶክተሮቜ አገልግሎት ለመስጠት አመልክተዋል። እነዚህ አመልካ቟ቜ ዛሬ ሚያዝያ 16/2017 በምክር ቀቱ አዳራሜ በመገኘት ዚዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት አካሂደዋል። በዚሁ መሠሚት በነርሶቜ ዘርፍ ካሊድ መሐመድ እና በዶክተሮቜ ደግሞ ዶ/ር ዓኢሻ ኚድር ዕጣው ወጥቶላ቞ው ዚኺድማ ዕድሉን አግኝተዋል። በዕጣ ማውጣቱ ስነ ስርዓት ላይ ዚተሳተፉ ዹሕክምና ባለሙያዎቜ በሰጡት አስተያዚት አካሄዱ በጣም ግልፅና ወደፊትም በዚሁ እንዲቀጥል ጠይቀዋል። አዲስ አበባ ኹተማ በርካታ ሁጃጅ ዚሚመዘገብበትና ዹሕክምና ባለሙያዎቜም ቁጥር ኹፍ ያለ በመሆኑ ዹሚሠጠው ዚባለሙያ ኮታ መሻሻል ቢቜል መልካም ነው ሲሉ አስተያዚት ሰጪዎቹ ተናግሚዋል። በዕጣ አወጣጡ ላይ ዚተገኙት ዹምክር ቀቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሐጂ ሪያድ ጀማልፀ ዚማሕበራዊ ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ሙዘፈር አሕመድና ዹሐጅና ዑምራ መምሪያ ክፍል ኃላፊ ኢስሐቅ አብዱልዓዚዝ ባለሙያዎቜ ለምክር ቀቱ ጥሪ ምላሜ በመስጠታ቞ው አመስግነዋል። ለአገልግሎት ዚተመሚጡ ባለሙያዎቜም ዚተጣለባ቞ውን ኚባድ ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል። ዹ1446ኛው ዹሐጅ ጉዞ ምዝገባና ሌሎቜ ስነ ስርዓቶቜ በአዲስ አበባ መጅሊስ እንደቀጠሉ ና቞ው። @munib_net

መልዕክት ለተኚበራቜሁ ዹአላህ እንግዶቜ! ዚቢጫ ወባ እና ዚፖሊዮ ክትባትን በተመለክተ በድጋሚ ዹተላለፈ መልዕክት ለዓለም አቀፍ ጉዞ ዚቢጫ ወባ እና ዚፖሊዮ ክትባት ግድ መሆኑ ይታወቃል። ይህን ተኚትሎ
መልዕክት ለተኚበራቜሁ ዹአላህ እንግዶቜ! ዚቢጫ ወባ እና ዚፖሊዮ ክትባትን በተመለክተ በድጋሚ ዹተላለፈ መልዕክት ለዓለም አቀፍ ጉዞ ዚቢጫ ወባ እና ዚፖሊዮ ክትባት ግድ መሆኑ ይታወቃል። ይህን ተኚትሎ ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክር ቀት ኚኢትዮጵያ ህብሚተሰብ ጀና ኢንስቲትዩት ጋር በመነጋገር ዹአላህ እንግዶቜ በሀጅ ምዝገባ ጣቢያዎቜ ዚክትባት አገልግሎት እንዲያገኙ ሲያደርግ ቆይታል። ይሁን እንጂ አሁንም ዹተወሰኑ ሁጃጆቜ በተለያዩ ምክንያቶቜ እንዳልተኚተቡ ለማሚጋገጥ ቜለናል። በመሆኑም ያልተኚተቡ ሁጃጆቜ ወደሚቀርባ቞ው መደበኛ ዚክትባት መስጫ ዚጀና ተቋማት በመሄድ እንዲኚተቡና ዚክትባት ማሚጋገጫ ዚምስክር ወሚቀት እንዲቀበሉ ዹጠቅላይ ምክር ቀቱ ሀጅና ዑምራ ዘርፍ በድጋሚ አደራ ይላል። በአዲስ አበባ በቋሚነት ዚክትባት አገልግሎት እዚሰጡ ዹሚገኙ ዚጀና ተቋማት ፊ 1ኛ. ዚጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 2ኛ.ዚቅዱስ ጳውሎስ ሚሌኒዹም ሜዲካል ኮሌጅ ሆስፒታል 3ኛ. ቞ርቜል ጀና ጣቢያ (ፒያሳ) 4ኛ. ኀካ ኮተቀ ሆስፒታል (ኮተቀ) መሆናቾውን በመገንዘብ ያልተኚተባቜሁ ሁጃጆቜ ወደተጠቀሱት ዚጀና ተቋማት በመሄድ መኚተብ ዚምትቜሉ መሆኑን በድጋሚ ለማስታወስ እንደወዳለን። በአዲስ አበባ መጅሊስ ዹሐጅና ዑምራ መምሪያ @munib_net

ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክርቀት ለኡስታዝ ሁሮን (ሁሱ) ዚምስጋናና ዚእውቅና ሰርተፍኬት ማበርኚቱ ተገልጿል። ኡስታዝ ሁሮን (ሁሱ) በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ወደ ኢስላም በመጣራት እያደሚገ
ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክርቀት ለኡስታዝ ሁሮን (ሁሱ) ዚምስጋናና ዚእውቅና ሰርተፍኬት ማበርኚቱ ተገልጿል። ኡስታዝ ሁሮን (ሁሱ) በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ወደ ኢስላም በመጣራት እያደሚገ ላለው ዚዳዕዋ እንቅስቃሎ ማበሚታቻ ይሆን ዘንድ ዚፌዎራል መጅሊስ ዚእውቅናና ዚምስጋና ሰርተፍኬት አበርክቶለታል። ኡስታዝ ሁሮን (ሁሱ) በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በዋናነት በቲክቶክ በሚያደርገው ኢስላማዊ ስነምግባርን ዹተላበሰ ዳዕዋ ኹ5ሺ በላይ ሰዎቜ ወደ ኢስላም እንደገቡ ገልጿል። @munib_net

ሳውዲ አሚቢያ እንዳይገቡ ክልኹላ ላለባ቞ው (አሻራ ለሠጡ) ግለሰቊቜ ዹተላለፈ መልዕክት ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ
ሳውዲ አሚቢያ እንዳይገቡ ክልኹላ ላለባ቞ው (አሻራ ለሠጡ) ግለሰቊቜ ዹተላለፈ መልዕክት ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው ኹዚህ ቀደም ሳውዲ አሚቢያ ውስጥ በቋሚነት ወይም በግዜያዊነት በነበሚታ቞ው ቆይታ አሻራ ሰጥተው ወደሳዑዲ አሚቢያ ዳግም እንዳይገቡ ክልኹላ ያለባ቞ው (አሻራ ዚሰጡ) ግለሰቊቜ ምዝገባ እንዳይፈፅሙ በጠቅላይ ምክር ቀቱ መገለፁ ይታወሳል። በመሆኑም ዚሳውዲ አሚቢያ መግቢያ ፍቃድ ክልኹላ እንዳለባቜሁ እያወቃቜሁ ለሐጅ ዚተመዘገባቜሁ ግለሰቊቜ ካላቜሁ ለሚገጥማቜሁ ቜግር፣ እንግልትና ኪሳራ ሙሉ ኃላፊነቱን ዚምትወስዱ መሆኑን ኚወዲሁ እናሳውቃለን። ዚኢ/እ/ጉ/ጠ ም/ቀት ሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ ሚያዚያ 15፣ 2017 ዓ.ል | ሾዋል 25፣ 1446 ዓ.ሒ @munib_net

ኚአነስ (رضي ï·² عنه) ተይዞ፡ እንዲህ ይላል፩ أنَّ رَسولَ الله (ï·º) مَرَّ على غِلْمانٍ فَسَلَّمَ عليهم “ዹአላህ መልዕክተኛ (ï·º) በልጆቜ አጠገብ ሲያልፉ ለነሱ
ኚአነስ (رضي ï·² عنه) ተይዞ፡ እንዲህ ይላል፩ أنَّ رَسولَ الله (ï·º) Ù…َرَّ Ø¹Ù„Ù‰ ØºÙÙ„ْمانٍ ÙÙŽØ³ÙŽÙ„Ù‘ÙŽÙ…ÙŽ عليهم “ዹአላህ መልዕክተኛ (ï·º) በልጆቜ አጠገብ ሲያልፉ ለነሱ ሰላምታ ያቅርቡ ነበር።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል፡ 2168 @munib_net

ኚአነስ (رضي ï·² عنه) ተይዞ፡ እንዲህ ይላል፩ أنَّ رَسولَ الله (ï·º) مَرَّ على غِلْمانٍ فَسَلَّمَ عليهم “ዹአላህ መልዕክተኛ (ï·º) በልጆቜ አጠገብ ሲያልፉ ለነሱ
ኚአነስ (رضي ï·² عنه) ተይዞ፡ እንዲህ ይላል፩ أنَّ رَسولَ الله (ï·º) Ù…َرَّ Ø¹Ù„Ù‰ ØºÙÙ„ْمانٍ ÙÙŽØ³ÙŽÙ„Ù‘ÙŽÙ…ÙŽ عليهم “ዹአላህ መልዕክተኛ (ï·º) በልጆቜ አጠገብ ሲያልፉ ለነሱ ሰላምታ ያቅርቡ ነበር።” 📚 ሙስሊም ዘግበውታል፡ 2168 @munib_net

ሳዑዲ ዐሚቢያ ዚመጀመሪያዎቹን ሑጃጅ ዚምትቀበልበትን ቀን ይፋ አደሚገቜ ። ዹ1446 ዓ.ሂ መጀመሩን ይፋ ያደሚገቜው ሳዑዲ ዐሚቢያፀ ዚመጀመሪያዎቹን ሑጃጅ ዚምትቀበልበትን ቀን አሳውቃለቜ፡፡ ዚሀገሪቱ ሐጅእና ዑምራ ሚኒስ቎ርፀ ዚመጀመሪያዎቹ ምዕመናን ቀጣይ ሣምንት ወደ ሀገሪቱ ይገባል ሲል ገልጿል፡፡ በዛሬው እለት ይፋ እንደተደሚገው ኚሆነፀ ምዕመናኑ ወደ ሳዑዲ ዐሚቢያ ዚሚገቡት ሚያዝያ 21/2017 ነው፡፡ ሳዑዲ ዐሚቢያ በቅዱሳኑ መካ እና መዲና ኚተሞቜፀ ዹሐጅ ወቅት በይፋ መጀመሩን ካስታወቀቜ በኋላ ዚዑምራን ጚምሮ ሌሎቜ ቪዛዎቜ ለምዕመናን እንዳይሰጥ እግድ ጥላለቜ፡፡ በዚህም ኹመላው ዓለም ኹ180 በላይ ሀገሮቜ ዚሚገቡ እንግዶቜን ለመቀበል ዹሚደሹገው ዝግጅት ተጠናቆ ኹዚህ በኋላ ይገባሉ ተብሎ ዹሚጠበቀው ዹሐጅ ሥነ ሥርዐት ዹሚኹውኑ ምዕመናን ብቻ ሆነዋል፡፡ ዚሀገሪቱ ባለስልጣናት ዜጎቜም ሆኑ በሥራ ምክንያት ሳዑዲ ዐሚቢያ ውስጥ ዹሚገኝ ማንኛውም ግለሰብፀ ኚፊታቜን ሚቡዕ አንስቶ ወደ መካ ኚተማመግባት ዹሚፈልግ ኹሆነ “አብሜር” አልያም “ሙቂም” በተሠኙ መተግበሪያዎቜ ቅድመ ምዝገባ ማካሄድ እንደሚኖርባ቞ው ገልጞዋል፡፡ በመተግበሪያው ምዝገባ ሳያኚናውኑ ለመግባት ሙኚራ ዚሚያደርጉና ጊዜው ያለፈበት ፍቃድ ዚያዙ ላይ ቅጣት ሊጣልባ቞ው እንደሚቜልም አስጠነቅቀዋል፡፡ በዚህም ዚፀጥታ አካላት ዚጂዳ መካ አውራ ጎዳናን እንዲሁም ዚጣኢፍ መካ መንገድን ጚምሮ በሁሉም ዋና ዋና ዚመዳሚሻ መንገዶቜ ላይ ጥብቅ ፍተሻ ተግባራዊ ያደርጋሉ ተብሏል። እነዚህ ርምጃዎቜ ዚሚወሰዱት በቅድስቲቱ መካ ኹተማ ኹመላው ዓለም ለሐጅ ክንውን በሚሊዮንዚሚቆጠሩ ምዕመናን ሰስለሚጓዙ ሊፈጠር ዚሚቜለውን መጹናነቅ ለመቀነስ ነው፡፡ ዚዘንድሮ ዓመት ዹሐጅ ሥነ ሥርዐት ክንውን ኚግንቊት 27/2017 እስኚ ሰኔ 2/2017 እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በክንውኑ ኚኢትዮጵያ ስድስትሺሕ ምዕመናን ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ሑጃጅ በሚራ ማድሚግ ዚሚጀምሩት ግንቊት 6/2017 ሲሆን፣ ዹሚጠናቀቀው ግንቊት 30/2017ነው፡፡ ባለፈው ዓመት ኹመላው ዓለም ኹ1 ነጥብ8 ሚሊዮን በላይ ምዕመናን በሐጅ ሥነ ሥርዐት ላይ ተሳታፊ መሆናቾው ይታወሳል፡፡ @munib_net

ኢትዮጵያውያን ሑጃጅ ዚመጀመሪያ በሚራ ዚሚያደርጉበት ቀን ታወቀ ። ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክር ቀትፀ በዘንድሮ ዹሐጅ ሥነ ሥነ ሥርዐት ክንውን ላይ ዚሚሳተፉ ኢትዮጵያውያን በሚራ ዚሚጀመርበትን ቀን ይፋ አድርጓል። በምክር ቀቱ ዹሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ ይፋ በተደሹገው መሠሚት ምዕመናን በሚራ ዚሚጀምሩት ግንቊት 6/2017 ይሆናል። ጠቅላይ ምክር ቀቱ ይህን ዹገለጾው ዛሬ ሰኞ ሚያዝያ 13/2017 ነው። እንደ ምክር ቀቱ መሹጃ ኚሆነ፣ ዚኢትዮጵያውያን ሑጃጅ በሚራ ግንቊት 6 ተጀምሮ ግንቊት 30/2017 ይጠናቀቃል። በዚህ መሹጃ ላይ ምክር ቀቱ ዹሑጃጅ በሚራ ዚሚጀመርበትን ቀን ቢያሳውቅም በሚራ ዚሚደሚግበትን አዹር መንገድ አልገለፀም። ምክር ቀቱ ባለፈው ዓመት ዚላካ቞ው 12 ሺሕ ምዕመናን ዚበሚሩት በኢትዮጵያ አዹር መንገድ እና በሳዑዲ ዐሚቢያው ሳዑዲያ አዹር መንገድ እንደነበር ይታወሳል። ኹአዹር መንገዶቹ መካኚል ዚኢትዮጵያ አዹር መንገድ 8 ሺሕ 500 በማስተናገድ ኹፍተኛውን ቁጥር ወስዷል። በሳዑዲያ ዚበሚሩት 3 ሺሕ 500 ኢትዮጵያውያን ነበሩ። ጠቅላይ ምክር ቀቱ ምዝገባ ካኚናወኑ ምዕመናን ውስጥ ዚአውሮፕላን ቲኬት በግል ዚሚቆርጡትንም ሲያስተናግድ ቆይቷል። ዹአዹር ቲኬት በግል ቆርጠው ሐጅ ዚሚያደርጉ ምዕመናን መዳሚሻ መዲና መሆኑን በመግለጜ፣ እስኚ ሚያዚያ 14/2ዐ17 ዹተሹጋገጠ ዚአውሮፕላን ቲኬት በተመዘገቡበት ዹሐጅ ምዝገባ ጣቢያ ይዘው በመቅሚብ እንዲያስመዘግቡ አሳስቧል። በተጠቀሰው ዹጊዜ ገደብ ዹአዹር ትኬታ቞ውን ዚማያስመዘግቡ እና መዳሚሻ቞ውን ኚመዲና ኀርፖርት ውጪ ዚሚያደርጉ ዹግል ትኬት ተጓዊቜ በሳዑዲ ዓሚቢያ በሚኖራ቞ው ቆይታ ለሚደርስባ቞ው ዚአገልግሎት ክፍተት ኃላፊነቱን ዚሚወስዱ መሆኑን አሳውቋል። በ1446 ዚዘንድሮ ሐጅ ላይ ኚኢትዮጵያ ዚሚሳተፉ ምዕመናን ቁጥር ወደ ስድስት ሺሕ እንዲቀንስ መደሹጉን ዹጠቅላይ ምክር ቀቱ ሐጅና ዑምራ ዘርፍ ባለፈው ሣምንት መጚሚሻ ማሳወቁ ይታወሳል። ዘርፉ ዹተጠቀሰው ቁጥር ተሟልቶ ምዝገባ ስለመደሚጉ ማሚጋገጫ አልሰጠም። ዚሳዑዲ ዐሚቢያ ሐጅ እና ዑምራ ሚኒስ቎ር ለምዝገባ ያስቀመጠው ዹጊዜ ሠሌዳ ሚያዝያ 10/2017 ተጠናቋል። @munib_net

ዚአውሮፕላን ቲኬት በግል ለሚቆርጡ ሁጃጆቜ ኹጠቅላይ ምክር ቀቱ ዹተሰጠ ማሳሰቢያ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ዚሳዑዲ ሐጅና ዑምራ ሚንስ቎ር ባስቀመጠው መመ
ዚአውሮፕላን ቲኬት በግል ለሚቆርጡ ሁጃጆቜ ኹጠቅላይ ምክር ቀቱ ዹተሰጠ ማሳሰቢያ ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ዚሳዑዲ ሐጅና ዑምራ ሚንስ቎ር ባስቀመጠው መመሪያ መሰሚት ዹአዹር ቲኬት በግል ቆርጠው ሀጅ ዚሚያደርጉ ዹአሏህ እንግዶቜ መዳሚሻ መዲና ነው። ዚበሚራ ጊዜያ቞ውም በአሏህ ፍቃድ በሚራውም ኹሜይ 14 ተጀምሮ ሜይ 30/2025 ይጠናቀቃል፡፡ ለትራንስፖርት፣ ለሆቮልና ሌሎቜ አገልግሎቶቜ አሰጣጥ አመቺነትም ዚእያንዳንዱ ሁጃጅ ትክክለኛ ዚበሚራ መሹጃ በኑስክ ዹመሹጃ ቋት ተሞልቶ በቡድን ማደራጀት ዚግድ አስፈላጊ ሆኗል። በመሆኑም ዹአዹር ቲኬት በግል ቆርጣቜሁ ዹምጓዙ ዹአሏህ እንግዶቜ እስኚ ሚያዚያ 14/2ዐ17 ዹተሹጋገጠ ዚአውሮፕላን ቲኬታቜሁን በተመዘገባቜሁት ዹሀጅ ምዝገባ ጣቢያ ይዛቜሁ በመቅሚብ እንድታስመዘግቡ እናሳስባለን። በተጠቀሰው ዹጊዜ ገደብ ዹአዹር ትኬታቜሁን ዚማታስመዘግቡ እና መዳሚሻቜሁን ኚመዲና ኀርፖርት ውጪ ያደሚጋቜሁ ዹግል ትኬት ተጓዊቜ በሳዑዲ ዓሚቢያ በሚኖራቜሁ ቆይታ ለሚደርስባቜሁ ዚአገልግሎት ክፍተት ኃላፊነቱን ዚምትወስዱ መሆኑን በአጜንኊት እንገልፃለን። ሁሉም ዚምዝገባ ጣቢያዎቜም በተሰጣቜሁ ዚስራ አቅጣጫ መሰሚት ዚሁጃጆቜን ቲኬት በሃጅ ሲስተሙ በአግባቡ በመጫን፣ በቡድን አደሚጃጀቶቜ በማካተትና ተገቢ ገለፃ በመስጠት ዹአሏህን እንግዶቜ ኚእንግልት እንድትታደጉ በጥብቅ እናሳስባለን። ዚኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮቜ ጠቅላይ ምክር ቀት ሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ @munib_net

وَلَسَوْفَ يُعْطِيكَ رَُؚّكَ فَتَرْضَىٰٓ (Ù¥) "ጌታህም ወደፊት (ብዙ ስጊታ) በእርግጥ ይሰጥሃል ፣ ትደሰታለህም!" ሰሚቱ-ዱሃ @munib_net
وَلَسَوْفَ يُعْطِيكَ رَُؚّكَ فَتَرْضَىٰٓ (Ù¥) "ጌታህም ወደፊት (ብዙ ስጊታ) በእርግጥ ይሰጥሃል ፣ ትደሰታለህም!" ሰሚቱ-ዱሃ @munib_net

ተባሚክ መስጂድ ላይ ኹህጋዊ አሰራር ውጪ ዹተፈፀመውን ዚማፍሚስ ድርጊት ጠቅላይ ምክር ቀቱ በጜኑ እንደሚያወግዝ ገለፀ! ኹ1967 ዓ.ል ጅምሮ ለ50 ዓመታት መንፈሳዊ አገልግሎት እዚሰጠ ባለው ተባሚክ
ተባሚክ መስጂድ ላይ ኹህጋዊ አሰራር ውጪ ዹተፈፀመውን ዚማፍሚስ ድርጊት ጠቅላይ ምክር ቀቱ በጜኑ እንደሚያወግዝ ገለፀ! ኹ1967 ዓ.ል ጅምሮ ለ50 ዓመታት መንፈሳዊ አገልግሎት እዚሰጠ ባለው ተባሚክ መስጂድ ላይ ኹህጋዊ አሰራር ውጪ ዹተፈፀመውን ዚማፍሚስ ድርጊት ጠቅላይ ምክር ቀቱ በጜኑ እንደሚያወግዝ ገልጿል። ዚአዲስ አበባ ኹተማ እስልምና ጉዳዮቜ ኹፍተኛ ምክር ቀት ኚሚመለኚታ቞ው ዚመንግስት አካላት ጋር በመነጋገር በህጋዊ መንገድ ዚመስጅዱ ቅጥር እንዲታጠር ቢያደርግም ትላንት ሌሊት ጹለማን ተገን በማድሚግ ኚመንግስት ዚስራ ሰዓት ውጪ እንዲፈርስ መደሹጉ ጠቅላይ ምክር ቀቱን ማሳዘኑን ጠቅላይ ም/ቀቱ ባወጣው መግለጫ ገልጿል። በመሆኑም ይህን ተግባር ዹፈፀሙ አካላት በህግ አግባብ እንዲጠዚቁና መስጅዱ ዚደሚሰበት ኪሳራ ተሾፍኖ ድጋሚ እንዲታጠር ለማድሚግ ጠቅላይ ምክር ቀቱ ኚአዲስ አበባ ኹተማ እስልምና ጉዳዮቜ ኹፍተኛ ምክር ቀት ጋር በቅንጅት ይሰራል ብሏል። መስጅዶቜ ዚሙስሊሞቜ ቀተ አምልኮ ብቻ ሳይሆኑ እንደ ዐይን ብሌና቞ው ዚሚጠብቋ቞ው መሰባሰቢያ቞ውና ዚልብ መርጊያ቞ው ጭምር በመሆናቾው ተመሳሳይ ድርጊቶቜ እንዳይፈፀሙም በዚሁ አጋጣሚ እናሳስባለን ሲል ዚፌደራል መጅሊሱ ገልጿል። @munib_net

ሚሱል (ï·º) እንዲህ ብለዋልፊ ألا Ø£ÙØ®ØšÙØ±ÙÙƒÙ… ØšØ£ÙØ¶ÙŽÙ„ÙŽ Ù…ِن Ø¯Ø±Ø¬Ø©Ù Ø§Ù„صِّيامِ والصَّلاةِ والصَّدقةِ؟ قالوا: ؚلى، قال: إصلاحُ ذاتِ الَؚيْنِ،  “ኚፆም፣ ኚሶላት፣ ኹሰደቃ በላጭና ደሹጃው ኹፍ ያለውን ተግባር አልነግራቜሁምን? እንዎታ! á‹­áŠ•áŒˆáˆ©áŠ• አሉ ሶሃቊቜፊ ‘በሰዎቜ መካካል ማስታሚቅ’ ነው አሉ።” 📚 አቡ ዳውድ ሶሂህ ብለውታል: 4919 @munib_net