Munib Network
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Munib Network 的分析概览
频道 Munib Network (@munib_net) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 98 846 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 388,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 328 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 98 846 名订阅者。
根据 06 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -3 913,过去 24 小时变化为 -162,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 0%。内容发布后 24 小时内通常能获得 N/A% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 0 次浏览,首日通常累积 0 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“ስለ ቁርኣን አንቀፆች፣ ሀዲሶች፣ ኢስላማዊ ማሳሰቢያዎች ፣ ዜናዎች እና ሌሎችም ልጥፎችን ከሙኒብ ኔትዎርክ ይከታተሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 07 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
98 846
订阅者
-16224 小时
-9177 天
-3 91330 天
帖子存档
98 846
👉🏾የመጀመሪያዎቹ የ1446ኛው ሑጃጆች መዲና ደርሰዋል።
ከሕንድ የተነሱት እነዚህ የአላህ እንግዶች መዲና ሲደርሱ፤ የሳውዲ የሐጅ ሚኒስቴር ኃላፊዎች፤ በሳውድ የሕንድ ኤምባሲ አመራሮችና ሌሎች በመዲና አየር መንገድ አቀባበል አድርገውላቸዋል።
አቀባበሉ በአበባ፣ በቴምርና በዘምዘም ስጦታ የደመቀ የነበረ ሲሆን በቆይታቸው መልካም የዒባዳ ጊዜ እንዲያሳልፉ የመልካም ምኞት መልዕክት ተላልፎላቸዋል።
ኢትዮጵያውያን ሁጃጆች በአላህ ፍቃድ በረራቸውን ግንቦት 6/2017 የሚያደርጉ ይሆናል።
በሳውዲ አረቢያ የመጀመሪያዎቹ እንግዶችና ጥቂት በረራዎችን በደመቀ ሁኔታ የመቀበል ልምዱ እያደገ መጥቷል።
@munib_net
98 846
⏱️ሶላትን በጊዜ መስገድ
ጃቢር ኢብን ዐብደሏህ (ረ.ዐ) እንዳሰተላለፉት:-
“ነቢዩ (ﷺ) ዙህርን በቀትር ይሰግዱ ነበር፣ ዐስርን ፀሀይቱ ገና ደማቅ እያለች፥ መግሪብን ደግሞ (ጸሀይ ከገባች በኋላ ባለው ወቅት)። ዒሻእን በተለያየ ጊዜ (ይሰግዳሉ) - ሰዎች መሰብሰባቸውን ሲመለከቱ ቀደም አድርገው ይሰግዳሉ፥ መዘግየታቸውን ሲያስተውሉ ደግሞ ያዘገያሉ። ነቢዩ (ﷺ) ሱብሒን ጨለማው ሳይገፍ ሰግደዋል።' '
📚ቡኻሪ ዘግበውታል
@munib_net
98 846
አላህ ሆይ! የታላቁን ነቢይ ሸፈዓ (ምልጃ) ወፍቀን!
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿أَنَا أَوَّلُ النَّاسِ يَشْفَعُ فِي الْجَنَّةِ، وَأَنَا أَكْثَرُ الْأَنْبِيَاءِ تَبَعًا﴾
“በጀነት ውስጥ ሰዎችን በመጀመሪያ ሸፈዓ (ምልጃ) ማስደርገው እኔ ነኝ። ከነቢያቶች ውስጥም ብዙ ተከታይ ያለኝ እኔ ነኝ።”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 192
@munib_net
98 846
የመጀመሪያዎቹን ሑጃጅ በነገው ዕለት እንደምትቀበል ሳዑዲ ዐረቢያ አስታወቀች
በዘንድሮ የሐጅ ሥነ ሥርዐት ክንውን ላይ የሚሳተፉ ቀዳሚዎቹ ምዕመናን በነገው እለት ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ እንደሚጓዙ ታውቋል። ለክንውኑ በቀዳሚነት ወደ ሀገሪቱ የሚገቡት የደቡብ አፍሪካ ዜጎች እንደሚሆኑ ይፋ ተደርጓል።
ደቡብ አፍሪካውያኑ ነገ ሰኞ ሚያዝያ 20/2017 ከመግባታቸው አስቀድሞ ምዕመናኑን ለመቀበል ጁመዓ ዕለት አስተባባሪዎችን ያካተተ ልዑክ ወደ ጂዳ ከተማ መጓዙን የሀገሪቱ ሐጅ እና ዑምራ ምክር ቤት በኤክስ ገጹ ያጋራው መረጃ ያመለክታል። ከደቡብ አፍሪካ በክንውኑ ላይ የሚሳተፉ ምዕመናን ቁጥር 2 ሺሕ 500 መሆኑ ተገልጿል። ምዕመናኑ ጂዳ ከተማ በማረፍ ወደ ቅዱሳኑ መዲና እና መካ ይጓዛሉ ተብሏል።
በማግሥቱ ማክሰኞ ከደቡብ አፍሪካውያን በመቀጠል የሦስት ሀገሮች ዜጎች ይከተላሉ ተብሎ ይጠበቃል። እነዚህ ምዕመናን ከፓኪስታን፣ ሕንድ እና ባንግላዴሽ የሚነሱ ይሆናሉ።
ረቡዕ ደግሞ በሐጅ ሥነ ሥርዐት ላይ በቁጥር በርካታ ምዕመናንን የምታሳትፈው ኢንዶኔዥያ ዜጎቿን ትልካለች ተብሎ እንደሚጠበቅ የሳዑዲ ዐረቢያ ባለሥልጣናት ገልፀዋል። ከኤንዶኔዥያ በዘንድሮ ዓመት ለሐጅ የተመዘገቡ ምዕመናን ቁጥር 221 ሺሕ ነው።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፤ በዘንድሮ የሐጅ ሥነ ሥነ ሥርዐት ክንውን ላይ የሚሳተፉ ኢትዮጵያውያን በረራ የሚጀመርበትን ቀን ባለፈው ሰኞ ይፋ ማድረጉ ይታወሳል። በምክር ቤቱ የሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ ይፋ በተደረገው መሠረት የምዕመናን በረራ ግንቦት 6 ተጀምሮ፣ ግንቦት 30/2017 ይጠናቀቃል።
በሐጅ ሥነ ሥርዐት ላይ ከ1 ነጥብ 8 ሚሊዮን በላይ ምዕመናንን ተሳታፊ ይሆናሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ቀደም ብለው የወጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ።
@munib_net
98 846
ለአራህማን እንግዶች የተላለፈ አስቸኳይ መልዕክት
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በወረደለት አቅጣጫ መሠረት የ1446ኛውን የሐጅ ምዝገባ እንግልት አልባ በሆነ መንገድ አጠናቆ ወደ ቀጣዩ የጉዞ ቅድመ ዝግጅት ለመሸጋገር በመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ይገኛል።
ከፍተኛ ምክር ቤታችን በዕቅድ ካስቀመጠው የሀጅ ምዝገባና ተያያዥ የአገልግሎት ስራ ውስጥ አብዛኛውን በማጠናቀቅ ለሁጃጆች አስፈላጊውን አገልግሎት በማቅረብ ቪዛ እጃቸው ላይ እንዲገባ ማድረግም ችሏል፡፡
በመሆኑም ክፍያ ፈጽማችሁ እና የፓስፖርት ሂደት አጠናቃችሁ ቪዛ ያልወሰዳችሁ ሁጃጆች እስከ ሰኞ ሚያዚያ 20/2017 ድረስ በአዲስ አበባ መጅሊስ የምዝገባ ጣቢያ እንድታመለክቱ በጥብቅ እያሳሰብን ይህ ካልሆነ ግን እንደሌላችሁ ተቆጥሮ በምትካችሁ ተጠባባቂ ሁጃጆች የሚተኩ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
ለሁጃጆቻችን ሀጀን መብሩር፣ ወሳዕየን መሽኩር ወቲጃረተን ለንተቡር እንዲሆንላችሁም በዚሁ አጋጣሚ ዱዓችንን እንገልፃለን።
@munib_net
98 846
የአማርኛ ኹጥባ በነሚራ/አረፋ መስጂድ
በነሚራ መስጂድ በሚደረገው የ1446ኛው የሐጅ ኹጥባ አማርኛን ጨምሮ በ20 ቋንቋዎች እንደሚተረጎም ተገለጸ።
የሐጅ ኹጥባን በተለያዩ ሀገራት ቋንቋ መተርጎም ከጀመረ ጥቂት ዓመታት ተቆጥሯል። ዓምና በ1445ኛው ሐጅ ላይ የአማርኛ ቋንቋ መካተት የጀመረ ሲሆን በወቅቱ በመካ የታላቁ መስጂደል ሐረም ኢማም የሆኑት ሼህ ማሂር የተደረገው ኹጥማ ወደ አማርኛ ተተርጉሞ እንደነበር ይታወሳል።
ዘንድሮም በሐጅ ወቅት በነሚራ መስጂድ የሚደረገው ኹጥባ በአማርኛ ጭምር እንደሚተረጎም የሁለቱን መሴጂዶችና የሐጅና ዑምራ ጉዳዮችን በቀዳሚነት የሚከታተለው Inside The Haramain ዘግቧል።
@munib_net
98 846
የሐጅ ኹጥባ 2025/1446 በሚከተሉት 20 ቋንቋዎች ይተረጎማል።
1. እንግሊዝኛ
2. ፈረንሳይኛ
3. ማላይኛ
4. ኡርዱ
5. የፋርስ/ፋርሲ
6. ቻይንኛ
7. ቱርክኛ
8. ሩሲያኛ
9. ሃውሳ
10. ቤንጋሊ
11. ስዊድንኛ
12. ስፓኒሽ
13. ስዋሂሊ
14. አማርኛ
15. ጣሊያንኛ
16. ፖርቱጋልኛ
17. ቦስኒያኛ
18. ማላያላም
19. ፊሊፒኖ
20. ጀርመንኛ
@munib_net
98 846
﴿إِنَّ اللهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا﴾ (الأحزاب ٥٦)
"አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡" (አል-አህዛብ 56)
اللهم صل على محمد وعلى ال محمد كما صليت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم وبارك على محمد وعلى ال محمد كما باركت على ابراهيم وعلى ال ابراهيم انك حميد مجيد
@munib_net
98 846
በ1446ኛው የሐጅ ስነ ስርዓት ላይ የሕክምና እገዛ የሚያደርጉ ባለሙያዎች ልየታ ተካሄደ።
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከፌደራል መጅሊስ በተሰጠው የባለሙያዎች ማጣሪያ መሠረት በከተማዋ ለሚሠሩ የሕክምና ባለሙያዎች የአገልግሎት ጥሪ ማስታወቂያ ማውጣቱ የሚታወስ ነው። በዚህ ጥሪ መሠረት 48 ነርሶችና 24 ዶክተሮች አገልግሎት ለመስጠት አመልክተዋል።
እነዚህ አመልካቾች ዛሬ ሚያዝያ 16/2017 በምክር ቤቱ አዳራሽ በመገኘት የዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት አካሂደዋል።
በዚሁ መሠረት በነርሶች ዘርፍ ካሊድ መሐመድ እና በዶክተሮች ደግሞ ዶ/ር ዓኢሻ ከድር ዕጣው ወጥቶላቸው የኺድማ ዕድሉን አግኝተዋል።
በዕጣ ማውጣቱ ስነ ስርዓት ላይ የተሳተፉ የሕክምና ባለሙያዎች በሰጡት አስተያየት አካሄዱ በጣም ግልፅና ወደፊትም በዚሁ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
አዲስ አበባ ከተማ በርካታ ሁጃጅ የሚመዘገብበትና የሕክምና ባለሙያዎችም ቁጥር ከፍ ያለ በመሆኑ የሚሠጠው የባለሙያ ኮታ መሻሻል ቢችል መልካም ነው ሲሉ አስተያየት ሰጪዎቹ ተናግረዋል።
በዕጣ አወጣጡ ላይ የተገኙት የምክር ቤቱ ዋና ስራ አስኪያጅ ሐጂ ሪያድ ጀማል፤ የማሕበራዊ ዘርፍ ዳይሬክተር አቶ ሙዘፈር አሕመድና የሐጅና ዑምራ መምሪያ ክፍል ኃላፊ ኢስሐቅ አብዱልዓዚዝ ባለሙያዎች ለምክር ቤቱ ጥሪ ምላሽ በመስጠታቸው አመስግነዋል።
ለአገልግሎት የተመረጡ ባለሙያዎችም የተጣለባቸውን ከባድ ኃላፊነት በአግባቡ እንዲወጡ አሳስበዋል።
የ1446ኛው የሐጅ ጉዞ ምዝገባና ሌሎች ስነ ስርዓቶች በአዲስ አበባ መጅሊስ እንደቀጠሉ ናቸው።
@munib_net
98 846
መልዕክት ለተከበራችሁ የአላህ እንግዶች!
የቢጫ ወባ እና የፖሊዮ ክትባትን በተመለክተ በድጋሚ የተላለፈ መልዕክት
ለዓለም አቀፍ ጉዞ የቢጫ ወባ እና የፖሊዮ ክትባት ግድ መሆኑ ይታወቃል።
ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በመነጋገር የአላህ እንግዶች በሀጅ ምዝገባ ጣቢያዎች የክትባት አገልግሎት እንዲያገኙ ሲያደርግ ቆይታል።
ይሁን እንጂ አሁንም የተወሰኑ ሁጃጆች በተለያዩ ምክንያቶች እንዳልተከተቡ ለማረጋገጥ ችለናል።
በመሆኑም ያልተከተቡ ሁጃጆች ወደሚቀርባቸው መደበኛ የክትባት መስጫ የጤና ተቋማት በመሄድ እንዲከተቡና የክትባት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እንዲቀበሉ የጠቅላይ ምክር ቤቱ ሀጅና ዑምራ ዘርፍ በድጋሚ አደራ ይላል።
በአዲስ አበባ በቋሚነት የክትባት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የጤና ተቋማት ፦
1ኛ. የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል
2ኛ.የቅዱስ ጳውሎስ ሚሌኒየም ሜዲካል ኮሌጅ
ሆስፒታል
3ኛ. ቸርችል ጤና ጣቢያ (ፒያሳ)
4ኛ. ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል (ኮተቤ) መሆናቸውን በመገንዘብ ያልተከተባችሁ ሁጃጆች ወደተጠቀሱት የጤና ተቋማት በመሄድ መከተብ የምትችሉ መሆኑን በድጋሚ ለማስታወስ እንደወዳለን።
በአዲስ አበባ መጅሊስ የሐጅና ዑምራ መምሪያ
@munib_net
98 846
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክርቤት ለኡስታዝ ሁሴን (ሁሱ) የምስጋናና የእውቅና ሰርተፍኬት ማበርከቱ ተገልጿል።
ኡስታዝ ሁሴን (ሁሱ) በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ወደ ኢስላም በመጣራት እያደረገ ላለው የዳዕዋ እንቅስቃሴ ማበረታቻ ይሆን ዘንድ የፌዴራል መጅሊስ የእውቅናና የምስጋና ሰርተፍኬት አበርክቶለታል።
ኡስታዝ ሁሴን (ሁሱ) በማህበራዊ ሚዲያ ላይ በዋናነት በቲክቶክ በሚያደርገው ኢስላማዊ ስነምግባርን የተላበሰ ዳዕዋ ከ5ሺ በላይ ሰዎች ወደ ኢስላም እንደገቡ ገልጿል።
@munib_net
98 846
ሳውዲ አረቢያ እንዳይገቡ ክልከላ ላለባቸው (አሻራ ለሠጡ) ግለሰቦች የተላለፈ መልዕክት
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው
ከዚህ ቀደም ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በቋሚነት ወይም በግዜያዊነት በነበረታቸው ቆይታ አሻራ ሰጥተው ወደሳዑዲ አረቢያ ዳግም እንዳይገቡ ክልከላ ያለባቸው (አሻራ የሰጡ) ግለሰቦች ምዝገባ እንዳይፈፅሙ በጠቅላይ ምክር ቤቱ መገለፁ ይታወሳል።
በመሆኑም የሳውዲ አረቢያ መግቢያ ፍቃድ ክልከላ እንዳለባችሁ እያወቃችሁ ለሐጅ የተመዘገባችሁ ግለሰቦች ካላችሁ ለሚገጥማችሁ ችግር፣ እንግልትና ኪሳራ ሙሉ ኃላፊነቱን የምትወስዱ መሆኑን ከወዲሁ እናሳውቃለን።
የኢ/እ/ጉ/ጠ ም/ቤት ሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ
ሚያዚያ 15፣ 2017 ዓ.ል | ሸዋል 25፣ 1446 ዓ.ሒ
@munib_net
98 846
ከአነስ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፡ እንዲህ ይላል፦
﴿أنَّ رَسولَ الله (ﷺ) مَرَّ على غِلْمانٍ فَسَلَّمَ عليهم﴾
“የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) በልጆች አጠገብ ሲያልፉ ለነሱ ሰላምታ ያቅርቡ ነበር።”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል፡ 2168
@munib_net
98 846
ከአነስ (رضي ﷲ عنه) ተይዞ፡ እንዲህ ይላል፦
﴿أنَّ رَسولَ الله (ﷺ) مَرَّ على غِلْمانٍ فَسَلَّمَ عليهم﴾
“የአላህ መልዕክተኛ (ﷺ) በልጆች አጠገብ ሲያልፉ ለነሱ ሰላምታ ያቅርቡ ነበር።”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል፡ 2168
@munib_net
98 846
ሳዑዲ ዐረቢያ የመጀመሪያዎቹን ሑጃጅ የምትቀበልበትን ቀን ይፋ አደረገች ።
የ1446 ዓ.ሂ መጀመሩን ይፋ ያደረገችው ሳዑዲ ዐረቢያ፤ የመጀመሪያዎቹን ሑጃጅ የምትቀበልበትን ቀን አሳውቃለች፡፡ የሀገሪቱ ሐጅእና ዑምራ ሚኒስቴር፤ የመጀመሪያዎቹ ምዕመናን ቀጣይ ሣምንት ወደ ሀገሪቱ ይገባል ሲል ገልጿል፡፡
በዛሬው እለት ይፋ እንደተደረገው ከሆነ፤ ምዕመናኑ ወደ ሳዑዲ ዐረቢያ የሚገቡት ሚያዝያ
21/2017 ነው፡፡
ሳዑዲ ዐረቢያ በቅዱሳኑ መካ እና መዲና ከተሞች፤ የሐጅ ወቅት በይፋ መጀመሩን ካስታወቀች በኋላ የዑምራን ጨምሮ ሌሎች ቪዛዎች ለምዕመናን እንዳይሰጥ እግድ ጥላለች፡፡ በዚህም ከመላው ዓለም ከ180 በላይ ሀገሮች የሚገቡ እንግዶችን ለመቀበል የሚደረገው ዝግጅት ተጠናቆ ከዚህ በኋላ ይገባሉ ተብሎ የሚጠበቀው የሐጅ ሥነ ሥርዐት የሚከውኑ ምዕመናን ብቻ ሆነዋል፡፡
የሀገሪቱ ባለስልጣናት ዜጎችም ሆኑ በሥራ ምክንያት ሳዑዲ ዐረቢያ ውስጥ የሚገኝ ማንኛውም ግለሰብ፤ ከፊታችን ረቡዕ አንስቶ ወደ መካ ከተማመግባት የሚፈልግ ከሆነ “አብሽር” አልያም “ሙቂም” በተሠኙ መተግበሪያዎች ቅድመ ምዝገባ ማካሄድ እንደሚኖርባቸው ገልጸዋል፡፡
በመተግበሪያው ምዝገባ ሳያከናውኑ ለመግባት ሙከራ የሚያደርጉና ጊዜው ያለፈበት ፍቃድ የያዙ ላይ ቅጣት ሊጣልባቸው እንደሚችልም አስጠነቅቀዋል፡፡ በዚህም የፀጥታ አካላት የጂዳ መካ አውራ ጎዳናን እንዲሁም የጣኢፍ መካ መንገድን ጨምሮ በሁሉም ዋና ዋና የመዳረሻ መንገዶች ላይ
ጥብቅ ፍተሻ ተግባራዊ ያደርጋሉ ተብሏል። እነዚህ ርምጃዎች የሚወሰዱት በቅድስቲቱ መካ ከተማ ከመላው ዓለም ለሐጅ ክንውን በሚሊዮንየሚቆጠሩ ምዕመናን ሰስለሚጓዙ ሊፈጠር የሚችለውን መጨናነቅ ለመቀነስ ነው፡፡
የዘንድሮ ዓመት የሐጅ ሥነ ሥርዐት ክንውን ከግንቦት 27/2017 እስከ ሰኔ 2/2017 እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በክንውኑ ከኢትዮጵያ ስድስትሺሕ ምዕመናን ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ኢትዮጵያውያኑ ሑጃጅ በረራ ማድረግ የሚጀምሩት ግንቦት 6/2017 ሲሆን፣ የሚጠናቀቀው ግንቦት 30/2017ነው፡፡
ባለፈው ዓመት ከመላው ዓለም ከ1 ነጥብ8 ሚሊዮን በላይ ምዕመናን በሐጅ ሥነ ሥርዐት ላይ ተሳታፊ መሆናቸው ይታወሳል፡፡
@munib_net
98 846
ኢትዮጵያውያን ሑጃጅ የመጀመሪያ በረራ የሚያደርጉበት ቀን ታወቀ ።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፤ በዘንድሮ የሐጅ ሥነ ሥነ ሥርዐት ክንውን ላይ የሚሳተፉ ኢትዮጵያውያን በረራ የሚጀመርበትን ቀን ይፋ አድርጓል። በምክር ቤቱ የሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ ይፋ በተደረገው መሠረት ምዕመናን በረራ የሚጀምሩት ግንቦት 6/2017 ይሆናል።
ጠቅላይ ምክር ቤቱ ይህን የገለጸው ዛሬ ሰኞ ሚያዝያ 13/2017 ነው። እንደ ምክር ቤቱ መረጃ ከሆነ፣ የኢትዮጵያውያን ሑጃጅ በረራ ግንቦት 6 ተጀምሮ ግንቦት 30/2017 ይጠናቀቃል።
በዚህ መረጃ ላይ ምክር ቤቱ የሑጃጅ በረራ የሚጀመርበትን ቀን ቢያሳውቅም በረራ የሚደረግበትን አየር መንገድ አልገለፀም። ምክር ቤቱ ባለፈው ዓመት የላካቸው 12 ሺሕ ምዕመናን የበረሩት በኢትዮጵያ አየር መንገድ እና በሳዑዲ ዐረቢያው ሳዑዲያ አየር መንገድ እንደነበር ይታወሳል። ከአየር መንገዶቹ መካከል የኢትዮጵያ አየር መንገድ 8 ሺሕ 500 በማስተናገድ ከፍተኛውን ቁጥር ወስዷል። በሳዑዲያ የበረሩት 3 ሺሕ 500 ኢትዮጵያውያን ነበሩ።
ጠቅላይ ምክር ቤቱ ምዝገባ ካከናወኑ ምዕመናን ውስጥ የአውሮፕላን ቲኬት በግል የሚቆርጡትንም ሲያስተናግድ ቆይቷል። የአየር ቲኬት በግል ቆርጠው ሐጅ የሚያደርጉ ምዕመናን መዳረሻ መዲና መሆኑን በመግለጽ፣ እስከ ሚያዚያ 14/2ዐ17 የተረጋገጠ የአውሮፕላን ቲኬት በተመዘገቡበት የሐጅ ምዝገባ ጣቢያ ይዘው በመቅረብ እንዲያስመዘግቡ አሳስቧል።
በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የአየር ትኬታቸውን የማያስመዘግቡ እና መዳረሻቸውን ከመዲና ኤርፖርት ውጪ የሚያደርጉ የግል ትኬት ተጓዦች በሳዑዲ ዓረቢያ በሚኖራቸው ቆይታ ለሚደርስባቸው የአገልግሎት ክፍተት ኃላፊነቱን የሚወስዱ መሆኑን አሳውቋል።
በ1446 የዘንድሮ ሐጅ ላይ ከኢትዮጵያ የሚሳተፉ ምዕመናን ቁጥር ወደ ስድስት ሺሕ እንዲቀንስ መደረጉን የጠቅላይ ምክር ቤቱ ሐጅና ዑምራ ዘርፍ ባለፈው ሣምንት መጨረሻ ማሳወቁ ይታወሳል። ዘርፉ የተጠቀሰው ቁጥር ተሟልቶ ምዝገባ ስለመደረጉ ማረጋገጫ አልሰጠም። የሳዑዲ ዐረቢያ ሐጅ እና ዑምራ ሚኒስቴር ለምዝገባ ያስቀመጠው የጊዜ ሠሌዳ ሚያዝያ 10/2017 ተጠናቋል።
@munib_net
98 846
የአውሮፕላን ቲኬት በግል ለሚቆርጡ ሁጃጆች ከጠቅላይ ምክር ቤቱ የተሰጠ ማሳሰቢያ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
የሳዑዲ ሐጅና ዑምራ ሚንስቴር ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት የአየር ቲኬት በግል ቆርጠው ሀጅ የሚያደርጉ የአሏህ እንግዶች መዳረሻ መዲና ነው። የበረራ ጊዜያቸውም በአሏህ ፍቃድ በረራውም ከሜይ 14 ተጀምሮ ሜይ 30/2025 ይጠናቀቃል፡፡
ለትራንስፖርት፣ ለሆቴልና ሌሎች አገልግሎቶች አሰጣጥ አመቺነትም የእያንዳንዱ ሁጃጅ ትክክለኛ የበረራ መረጃ በኑስክ የመረጃ ቋት ተሞልቶ በቡድን ማደራጀት የግድ አስፈላጊ ሆኗል።
በመሆኑም የአየር ቲኬት በግል ቆርጣችሁ የምጓዙ የአሏህ እንግዶች እስከ ሚያዚያ 14/2ዐ17 የተረጋገጠ የአውሮፕላን ቲኬታችሁን በተመዘገባችሁት የሀጅ ምዝገባ ጣቢያ ይዛችሁ በመቅረብ እንድታስመዘግቡ እናሳስባለን።
በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ የአየር ትኬታችሁን የማታስመዘግቡ እና መዳረሻችሁን ከመዲና ኤርፖርት ውጪ ያደረጋችሁ የግል ትኬት ተጓዦች በሳዑዲ ዓረቢያ በሚኖራችሁ ቆይታ ለሚደርስባችሁ የአገልግሎት ክፍተት ኃላፊነቱን የምትወስዱ መሆኑን በአጽንኦት እንገልፃለን።
ሁሉም የምዝገባ ጣቢያዎችም በተሰጣችሁ የስራ አቅጣጫ መሰረት የሁጃጆችን ቲኬት በሃጅ ሲስተሙ በአግባቡ በመጫን፣ በቡድን አደረጃጀቶች በማካተትና ተገቢ ገለፃ በመስጠት የአሏህን እንግዶች ከእንግልት እንድትታደጉ በጥብቅ እናሳስባለን።
የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት
ሐጅ እና ዑምራ ዘርፍ
@munib_net
98 846
وَلَسَوْفَ يُعْطِيكَ رَبُّكَ فَتَرْضَىٰٓ (٥)
"ጌታህም ወደፊት (ብዙ ስጦታ) በእርግጥ ይሰጥሃል ፣ ትደሰታለህም!"
ሰረቱ-ዱሃ
@munib_net
98 846
ተባረክ መስጂድ ላይ ከህጋዊ አሰራር ውጪ የተፈፀመውን የማፍረስ ድርጊት ጠቅላይ ምክር ቤቱ በጽኑ እንደሚያወግዝ ገለፀ!
ከ1967 ዓ.ል ጅምሮ ለ50 ዓመታት መንፈሳዊ አገልግሎት እየሰጠ ባለው ተባረክ መስጂድ ላይ ከህጋዊ አሰራር ውጪ የተፈፀመውን የማፍረስ ድርጊት ጠቅላይ ምክር ቤቱ በጽኑ እንደሚያወግዝ ገልጿል።
የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ጋር በመነጋገር በህጋዊ መንገድ የመስጅዱ ቅጥር እንዲታጠር ቢያደርግም ትላንት ሌሊት ጨለማን ተገን በማድረግ ከመንግስት የስራ ሰዓት ውጪ እንዲፈርስ መደረጉ ጠቅላይ ምክር ቤቱን ማሳዘኑን ጠቅላይ ም/ቤቱ ባወጣው መግለጫ ገልጿል።
በመሆኑም ይህን ተግባር የፈፀሙ አካላት በህግ አግባብ እንዲጠየቁና መስጅዱ የደረሰበት ኪሳራ ተሸፍኖ ድጋሚ እንዲታጠር ለማድረግ ጠቅላይ ምክር ቤቱ ከአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ጋር በቅንጅት ይሰራል ብሏል።
መስጅዶች የሙስሊሞች ቤተ አምልኮ ብቻ ሳይሆኑ እንደ ዐይን ብሌናቸው የሚጠብቋቸው መሰባሰቢያቸውና የልብ መርጊያቸው ጭምር በመሆናቸው ተመሳሳይ ድርጊቶች እንዳይፈፀሙም በዚሁ አጋጣሚ እናሳስባለን ሲል የፌደራል መጅሊሱ ገልጿል።
@munib_net
98 846
ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦
﴿ألا أُخبِرُكم بأفضَلَ مِن درجةِ الصِّيامِ والصَّلاةِ والصَّدقةِ؟ قالوا: بلى، قال: إصلاحُ ذاتِ البَيْنِ، ﴾
“ከፆም፣ ከሶላት፣ ከሰደቃ በላጭና ደረጃው ከፍ ያለውን ተግባር አልነግራችሁምን? እንዴታ! ይንገሩን አሉ ሶሃቦች፦ ‘በሰዎች መካካል ማስታረቅ’ ነው አሉ።”
📚 አቡ ዳውድ ሶሂህ ብለውታል: 4919
@munib_net
