Ajeba Emmanuel united church
Open in Telegram
እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” — ዮሐንስ 5፥24 (አዲሱ መ.ት)
Show more259
Subscribers
-224 hours
-27 days
-430 days
Posts Archive
#ኃጢአተኛ_በርባን_ነበረን🙌
#ፍርድ የሚገባን
#ሞት የሚገባን ኃጢአተኞች ነበረን🙌
ማቴዎስ 27
¹⁵ በዚያም በዓል ሕዝቡ የወደዱትን አንድ እስረኛ ሊፈታላቸው ለገዢው ልማድ ነበረው።
¹⁶ በዚያን ጊዜም በርባን የሚባል በጣም የታወቀ እስረኛ ነበራቸው።
¹⁷ እንግዲህ እነርሱ ተሰብስበው ሳሉ ጲላጦስ፦ በርባንን ወይስ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤
¹⁸ በቅንዓት አሳልፈው እንደ ሰጡት ያውቅ ነበርና።
¹⁹ እርሱም በፍርድ ወንበር ተቀምጦ ሳለ ሚስቱ፦ ስለ እርሱ ዛሬ በሕልም እጅግ መከራ ተቀብያለሁና በዚያ ጻድቅ ሰው ምንም አታድርግ ብላ ላከችበት።
²⁰ የካህናት አለቆችና ሽማግሎች ግን በርባንን እንዲለምኑ ኢየሱስን ግን እንዲያጠፉ ሕዝቡን አባበሉ።
²¹ ገዢውም መልሶ፦ ከሁለቱ ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤ እነርሱም፦ በርባንን አሉ።
²² ጲላጦስ፦ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን እንግዲህ ምን ላድርገው? አላቸው፤ ሁሉም፦ ይሰቀል አሉ።
²³ ገዢውም፦ ምን ነው? ያደረገው ክፋት ምንድር ነው? አለ፤ እነርሱ ግን፦ ይሰቀል እያሉ ጩኸት አበዙ።
²⁴ ጲላጦስም ሁከት እንዲጀመር እንጂ አንዳች እንዳይረባ ባየ ጊዜ፥ ውኃ አንሥቶ፦ እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ፤ እናንተ ተጠንቀቁ ሲል በሕዝቡ ፊት እጁን ታጠበ።
²⁵ ሕዝቡም ሁሉ መልሰው፦ ደሙ በእኛና በልጆቻችን ላይ ይሁን አሉ።
²⁶ በዚያን ጊዜ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ገርፎ ሊሰቀል አሳልፎ ሰጠ።
#ለእኛ የሚገባውን እርሱ 👉ክርስቶስ 👈ተቀብሏል።
👇
ኢሳይያስ 53
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው።
⁵ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
⁶ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።
⁷ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።
⁸ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?
#እኛ_በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።
— 2ኛ ቆሮ 5፥21
👆👇
#ኢየሱስስስስ ለኔኔኔኔ ኃጢአት ሆኖ እኔ ጽድቅ ሆኛለሁ 🙌
ከወንድም ታምራት ሳሙኤል
ውድ የአማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን channel ተከታዮች እንኳን የትንሣኤ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ 🙌💜
#የኢየሱስን_ስም🙌
📍የሞተ የሚያስነሳውን ስም
📍ሽባን የሚተረትረውን ስም
📍በሽተኞችን የሚፈወሰውን ስም
📍አጋንንት የሚንቀጠቀጥለትን ስም
📍የማይቻለውን የሚያስችለውን ስም እጠራለሁ
በኢየሱስ ስም አሜን🙏
ስለ በዳላችን ደቀቀ
ስለ ሀጢያታችን ቆስለ
ስለ መተላለፋችን ሞተ
በመገረፉ ቁስል ፈወሰን
በቀራንዮ ስፍራ በመስቀል የሞተው
በእሾህ ሲጎነጉኑት ደሙ የፈሰሰው
በጦር ጎኑን ሲሉት በአለንጋ ሲልጡት
ዝም ማለቱ ለእኛ ነው መራራን ሲያጠጡት
ፍፁም አላፈረም
እርቃኑን ሲታይ ስለእኛ ለአለም
ስሙ ይክበር
ዘላለም ይንገስ ወልድ እግዚአብሔር
በራስ ቅሉ መንደር የፈሰሰው ደሙ ንፁህ ነው
ያለዋኖስ ያለበጎች ደም የአለምን በደል ጠረገው
ደሙን ይዞ ገባ ወደ አባቱ
አወረደ ከላይ ምህረቱን
አመፃችን ሁሉ ተወግዶ ተቆጠረ በእኛ ላይ ጽድቁ
ፍፁም አላፈረም
እርቃኑን ሲታይ ስለእኛ ለአለም
ስሙ ይክበር
ዘላለም ይንገስ ወልድ እግዚአብሔር
እጅ እግሩን በችንካር አጥበቀው ወጠሩ
ጀርባውን በጅራፍ እያቆስሉ
የአለማትን ፈጣሪ ያለእፍረት ቢንቁት
ፀሀይና ጨረቃ እርሱን አከበሩት
በምህረቱ ነው ባለጠጋ
እኛን ሊምር ወደደ ጌታ
በምህረቱ ነው ባለጠጋ
እኔን ሊምር ወደደ ጌታ
እኛን አለን ሩሃማ
እኛን አለን ሩሃማ
እኔን አለኝ ሩሃማ
Selam Desta 🙏
