Ajeba Emmanuel united church
Open in Telegram
እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” — ዮሐንስ 5፥24 (አዲሱ መ.ት)
Show more259
Subscribers
-224 hours
-27 days
-430 days
Posts Archive
ክፍል አራት
#የመኖሪያ_አቅም
ፀጋ እና ሰላም
መኖር ፈልገህ ለመኖር አቅም ታጣለህ ። ሰላም ፈልገህ ሰላም መልሶ ይርብሃል ።በቅድስና ለመኖር ቆርጠህ ሳለ መልሰህ በሰራከው የቀደመ ሐጢያት ትወድቃለህ ። ይህን ነገር አላደርገውም ብለህ ምለህ ተገዝተህ መልሰህ ማትወደውን ስታደርግ ራስህን ታገኛለህ ። ምን ይሻለኛል ? ብለህ ትጠይቃለህ ሰዎች ያለህበት ቦታ ተመችቶህ ያለህበት መስሏቸው ያሙሃል የደላው እያሉ ይናገሩሃል ። የውስጥህን ስብራት ከቶ ማንም አያውቀውም ። ለመውጣት እየታገልክ ነገር ግን አቅም እንዳጣህ ይሰማሃል ።
ዛሬ የምስራች እነግራችኋለሁ የመኖር አቅም የሚሰጥ ስጦታ ተሰጥቶናል ።ይህን ማወቅ ያሳርፋል ።
ጳውሎስ እንዲህ ይላል ።
‹‹ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።›› ገላ 1:3
ይህ የተለመደ የጳውሎስ የምኞት አዘል ሰላምታ ነው ፡፡ በተለያዩ ክፍሎች ይህንን ሰላምታ ይጠቀማል ፡፡ በ ሮሜ 1፡7 በ1ኛ ቆሮ 1፡1፡3 ፣2ኛ 1ቆሮ 1፡2 ኤፌ 1፡2 …… ጳውሎስ በመግቢያ ንግግሩ ብቻ ሳይሆን በመልዕክቱ መጨረሻ ላይም ይህንን ቃል በተደጋጋሚ ይጠቀማል ፡፡ በገላ 1፡3 ላይ በእዚሁ መንገድ ሰላም እያለ በመግባት ላይ ሆኖ የፀጋ እና የሰላም መገኛ #ማን እንደሆነም ይነግረናል ፡፡
ይህም አባታችን እግዚአብሄርና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ይለናል ፡፡ ይህ ፀጋ እና ሰላም የአማኞች መተዳደሪያ በጀታችው ጭምር ነው በብራቸው ገዝተው መብላት ያልቻሉ ብዙ ባለ ሃብቶች አሉ በልተውም የማይደሰቱ በሕይወታቸው ደስተኛ ያለሆኑ አሉ ስለለህ ብቻ ሁሉ አይሰምርም አያሳርፍም ፡፡ በእግዚአብሄር ፀጋ የሚኖሩ ግን በጌታችንም ፀጋ እና ሰላም የሚመላለሱ በመሆናቸው የእረፍት ሕይወት ይበዛላቸዋል ።ለእነርሱም ከእነዚህ ውጪ ለመኖር እጅጉን ከባድ እና የማይቻል ነው፡፡ የፀጋው ባለቤት ሁከት በሆነ ሁኔታ እንኳን የራሱን ሰላም እየሰጠ ያረጋጋቸዋል ። አሜን🙏
በእዚህ ክፍል አስገራሚው ነገር የመገኛው ጉዳይ ነው ፡፡ የት ይገኛሉ የሚለው ሌላ ቦታ በመፈለግ እንዳንደክም በእዚህ ክፍል ውስጥ ይመሳል ፡፡ #ከአባታችን_ከእግዚአብሄር_አብና_ከጌታችን_ከኢየሱስ ክርስቶስ ይላል ወደ ሌላ ቦታ በመሄድ የሚገኙ አይደሉም ፡፡ ስፍራቸው እዚህ ነው። የፀጋ እና የሰላም መገኛው ወዲህ ነው ሰው ሌላ ቦታ ቢፈልግ አያገኘውም ፡፡ የፀጋ መገኛ በመለኮት ስር ነው የቀረበ ያገኘዋል።
የዕብራውያን መፅሐፍ ፀሐፊ አማኞች ፀጋ ከፈለጉ ወዴት መምጣት እንዳለባቸው ሲናገር እንዲህ ይላል ፡፡
‹‹ከኃጢአት በቀር በነገር ሁሉ እንደ እኛ የተፈተነ ነው እንጂ፥ በድካማችን ሊራራልን የማይችል ሊቀ ካህናት የለንም።እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።››
ዕብ 4፡15-16
ይህ ፀጋ ምን ያደርጋል
🔸በሚያስፈልገን ጊዜ ይረዳናል። ነገሮች በሚያስፈልጉን ጊዜ ዞር የሚል በበዛበት በእዚህ ዘመን የአምላካችን እና የጌታ ፀጋ ግን በእዚህ ሰአት ይረዳናል ። ሀሌ ሉያ!!
አቅሙ የደከመ ሰው ካለ አንድ የምስራች አለለት እርሱም ወደ ፀጋው ዙፋን በመቅረብ ይህን የሚረዳ ፀጋ እንዲቀበል መንገዱ ተመረቆ ተከፍቶለታል ፡፡
🔸ይህ ፀጋ መቆሚያ ነው
🔸ይህ ፀጋ መበርቻ ነው ፡፡
🔸ይህ ፀጋ እንደገና መነሻ ድጋፍ ነው ጳውሎስ በሚያምር ቋንቋ እንዲህ ይገልፀዋል ፡፡
‹‹ሰዎችን ሁሉ የሚያድን #የእግዚአብሔር_ጸጋ ተገልጦአልና፤ #ይህም_ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤››
ቲቶ 2፡11-13
ይህ ፀጋ ተመልከቱት
🔸ሰውን ሁሉ ያድናል ይላል ።
🔸ኀጢያተኝነትን እና አለማዊ ምኞትን ያስክዳል
🔸የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እንድጠብቅ ያግዘናል
🔸ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ደግሞ ያስተምረናል ፡፡
ታዲያ ከእዚህ በላይ ምን ያስፈልገናል?
🔸 ለመዳን
🔸በፅድቅ ለመኖር
🔸ሐጢተኝነትን ለመካድ
🔸የጌታችን የኢየሱስን ክብር መገለጥ ለመጠብቅ ..... ይህ ፀጋ ያስፈልጋል ።
ተወዳጆች በእውነት እግዚአብሄር ይህንን ፀጋ ያብዛላችሁ ይብዛልን ፡፡
አሜን🙏
ይቀጥላል
Girum Difek
@highlight
ወንድም ንጉሤ ቡልቻ፣ በኒቆዲሞስ ሾው ባደረጉት ቆይታ፣ ስለ ወንጌል ምን አሉ?
በዚህ ዘመን ``... የወንጌልን ምንነት ማጽናት አስፈላጊ`` እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡ ``ወንጌል ምንድን ነው? በምን መልኩ እንገልጸዋለን?`` ለሚለው፣ ሐዋርያው ጳውሎስ ለሮሜ ክርስቲያኖች የጻፈውን ደብዳቤ፣ የመጀመሪያ ምዕራፍ የመጀመሪያዎቹን ቁጥሮች ለብያኔ ያቀርባሉ፡፡ የወንጌልን ምንነት ለማስረዳት፣ ጳውሎስ ስለኢየሱስ የተናገረውን ይጠቅሳሉ፡፡
``የወንጌል እምብርት መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነው፤ ክርስቶስ ካልተነሳ ወንጌል አልተነገረም፤ ርሱን ካላነሳነው፣ ዙሪያ ዙሪያ ስንል ዋልን እንጂ ወንጌል አልተናገርንም፡፡``
``ወንጌል .... ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነውን ኢየሱስ ክርስቶስን ማዕከል ያደረገ ነው፡፡``
``ከሙታን በመነሣቱ ስለሚል፣ ወንጌል ሞቱን መስቀሉን ያጠቃልላል፡፡ አንድ መካከለኛው ምስራቅ የተወለደ ሰው ብለን አናቆምም፤ ይህ ሰው ስለኃጢአታችን የሞተ፣ የተቀበረ፣ ስለጽድቃችን ከሙታን የተነሳ፣ ብለን ሞቱ ላይ መስቀሉ ላይ እናተኩራለን፡፡ ይህ ካልተነገረ ወንጌል አልተነገረም፡፡``
``ወንጌል የሚነገረው ሰዎች እንዲያምኑት ነው፡፡ እንዴት ደስ ይላል!? እያለ እንዲያደንቅ አይደለም፤ ለተዝናኖት አይደለም፡፡``
``ወንጌል በ2ኛ ቆሮንቶስ 5፡18 20 መሰረት የእርቅ ሰነድ ነው፡፡ አምላክና ሰው በምን ይታረቁ? በወንጌል መሰረት፡፡``
``ወንጌል ለድኅነታችን የተሰጠ የእግዚአብሔር እቅድ ነው፡፡``
በመቀጠል፣ "ወንጌል ምን አይደለም?" የሚለውን ያብራራሉ።
``ወንጌል የሰው አስተያየት አይደለም፡፡ ወንጌል የሰው ፍልስፍና አይደለም፡፡ ወንጌል የሕግጋት ዝርዝር አይደለም፡፡``
``የሥነ ምግባር ሐተታ ወንጌል አይደለም፡፡ ለምሳሌ፦ እንዳታጨስ፣ እንዳጠጣ፣ እዚህ እንዳትሄድ፣ እዚህ እንዳትሠራ፣... የሚሉ የሥነ ምግባር ዝርዝሮች። አትግደል፣ አታመንዝር፣ አትስረቅ ራሱ ወንጌል አይደለም፡፡ በቦታው ትክክል ቢሆንም፣ ሥነ ምግባር የወንጌል ፍሬ እንጂ ወንጌል አይሆንም፡፡ እንደዚህ ሚዲያ አግኝቼ ለአንድ ሰው ወንጌል ብናገር ስለ ክርስቶስ እነግረዋለሁ እንጂ የሥነ ምግባር ዝርዝር አልነግረውም፡፡ ሰውየው ከዳነ በኋላ ሥነ ምግባሩ መለወጥ አለበት፤ እርሱ አይቀርም፡፡ መጀመሪያው ወይም ዋና እምብርቱ ግን ይህ አይደለም ማለት ነው፡፡``
``ወንጌል የድንቃድንቆች ርችት አይደለም፡፡ ...
ታምሜ ነበር ተፈወስኩኝ ትልቅ ምስክርነት ነው ወንጌል ግን አይደለም፡፡ ልጄ ... ነጻ ወጣች ጥሩ ምስክርነት ነው፤ ወንጌል ግን አይሆንም፡፡ ... ዋናው ጥያቄ የነፍሱ ድኅነት ነው፡፡ ... የክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ዋናው ጉዳይ ነው፡፡ እርሱ በሌለበት ስፍራ ስለ ተአምራት ማውራት ወንጌል አይደለም፡፡``
``በወንጌል ስም የሚነገሩ የተሳሳቱ ትምህርቶች አሉ፤ ጸጋውን ብቻ አሳይቶ ... ጸጋ የመጣበትን አላማ የሚዘነጋ ወንጌል አይደለም፡፡``#የመሥዋዕቱ_በግ 🙌
👇👇👇
ዘጸአት 29
¹ እኔንም በክህነት እንዲያገለግሉኝ ትቀድሳቸው ዘንድ የምታደርግባቸው ነገር ይህ ነው፤ ነውር የሌለባቸውን አንድ ወይፈንና ሁለት አውራ በጎች ትወስዳለህ።
…
¹⁰ ወይፈኑንም ወደ መገናኛው ድንኳን በር ፊት ታቀርበዋለህ፤ አሮንና ልጆቹም እጆቻቸውን በወይፈኑ ራስ ላይ ይጭናሉ።
¹¹ ወይፈኑንም በመገናኛው ድንኳን በር አጠገብ በእግዚአብሔር ፊት ታርደዋለህ።
¹² ከወይፈኑም ደም ወስደህ በመሠዊያው ቀንዶች ላይ በጣትህ ትረጨዋለህ፤ ደሙንም ሁሉ ከመሠዊያው በታች ታፈስሰዋለህ።
…
¹⁴ የወይፈኑን ሥጋ ግን፥ ቁርበቱንም፥ ፈርሱንም ከሰፈር ውጭ በእሳት ታቃጥለዋለህ፤ የኃጢአት መሥዋዕት ነው።
#ዕብራውያን 9
¹³ የኮርማዎችና የፍየሎች ደም በረከሱትም ላይ የተረጨ የጊደር አመድ ሥጋን ለማንጻት የሚቀድሱ ከሆኑ፥
¹⁴ ነውር የሌለው ሆኖ በዘላለም መንፈስ ራሱን ለእግዚአብሔር ያቀረበ የክርስቶስ ደም እንዴት ይልቅ ሕያውን እግዚአብሔርን ልታመልኩ ከሞተ ሥራ ሕሊናችሁን ያነጻ ይሆን?
#አሮንና ልጆቹ ወደ መገናኛው ድንኳን ገብተው እንዲያገለግሉ ነውር የሌለባቸውን አውራ በጎች ወስደው ወደ መገናኛው ድንኳን በር ፊት ያቀርባል ፤ አሮንና ልጆቹም እጆቻቸውን በበጎ ራስ ላይ ይጭናሉ።
➫ ነውር የሌለው በግ አሮንና ልጆቹን ካህናት ወይም አገልጋዮች አድርጎ ለማብቃት ኃጢአታቸውን መሸከም እና መታረድም ፣መቀጠል ነበረበት። ነውር የሌለው በግ የአሮንና የልጆቹን ኃጢአት በመሸከሙ እነርሱ ካህናት ሆኖ ይቀደሳሉ። 👇
#አሮንና ልጆቹ ነውር በሌለው በወይፈኑ ወይም በበጉ ደም ምክንያት ካህናት ሆኖ እንደተቀደሱ እኛም በክርስቶስ ደም ተቀድሰናል፥ጸድቀናል፥ታጥበናል።👇
#እኛ_በእርሱ ሆነን የእግዚአብሔር ጽድቅ እንሆን ዘንድ ኃጢአት ያላወቀውን እርሱን ስለ እኛ ኃጢአት አደረገው።
— 2ኛ ቆሮ 5፥21
#ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው #ኃጢአታችንን_በእንጨት_ላይ_ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥24
#አሮንና ልጆቹ ነውር በሌለው በበጉ መታረድ ምክንያት በነፃነት ወደ መገናኛው ድንኳን ገብተው መገልገል ችሏሉ። እኛ ደግሞ በክርስቶስ ሥራ ወደ አብ መግባት ችለናል። 👇
#ኤፌሶን 2
¹³ አሁን ግን እናንተ በፊት ርቃችሁ የነበራችሁ በክርስቶስ ኢየሱስ ሆናችሁ በክርስቶስ ደም ቀርባችኋል።
…
¹⁸ በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና።
ቀጣይ እሁድ ከቀኑ10 ሰዓት እንቀጥላለን
►Teka.E
የሚታረቀን እግዚአብሔር ራሱ አስታራቂው እንደሆነ ቃሉ በግልጥ የሚነግረንን ካስተዋልን ይህ ጥያቄ አይሆንብንም። ወንጌል እግዚአብሔር በክርስቶስ ከራሱ ጋር እንዳስታረቀን ይናገራል። “እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበር” ነው የሚለው (2ቆሮ.5፥18-19)። “በክርስቶስ ከራሱ ጋር አስታረቀን” ሲል የሚታረቀንም የሚያስታርቀንም እግዚአብሔር መሆኑ በግልጥ ይታያል። በዕርቁ ክርስቶስ መካከለኛ መሆኑንም ደግሞ ያሳያል። በሌላም ስፍራ እንዲህ ይላል፦
“እግዚአብሔር ሙላቱ ሁሉ በእርሱ (በክርስቶስ) እንዲኖር፥ በእርሱም በኩል በመስቀሉ ደም ሰላም አድርጎ በምድር ወይም በሰማያት ያሉትን ሁሉ ለራሱ እንዲያስታርቅ ፈቅዶአል።” (ቆላ.1፥19-20)
ዕርቁ ከእግዚአብሔር ወደ ሰው እንጂ ከሰው ወደ እግዚአብሔር አልመጣም። “... እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለ ክርስቶስ መልክተኞች ነን፤ ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለ ክርስቶስ እንለምናለን” ነው የሚለው (2ቆሮ.5፥20)።
“አማልዱኝ” ብሎ ወደ ተበዳይ አማላጅ መላክ የበዳይ ሥራ ነው። እዚህ እየሆነ ያለው ግን የተገላቢጦሽ ነው። “... እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ (መታረቂያ) ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም” ይላል (1ዮሐ.4፥10)። ደግሞም “ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ታረቅን” ይላል (ሮሜ.5፥10)።
* * *
ውድ አንባቢ፣ የዘላለም ሕይወት እንዲኖርህ ትፈልጋለህ?
ኢየሱስ ክርስቶስ ስለ ኃጢአትህ እንደሞተ፥ እግዚአብሔር ከሙታን እንዳስነሣውና፥ ጌታ እንደሆነ እመን። ንስሐ ግባ፥ ኃጢአትህም እንዲሰረይልህ በስሙ ተጠመቅ። እግዚአብሔር ይቀበልሀል፤ መንፈስ ቅዱስንም ይሰጥሀል። በአቅራቢያህ የሚገኝ የወንጌል አማኞች ቤተክርስቲያን አባል ሁን። ከቅዱሳንም ጋር ዘወትር ተሰብሰብ። የጌታ በረከት እዚያ ያገኝሀል።
መልእክቱ ለወዳጆችዎ እንዲደርሳቸው Share ያድርጉት።
አዳዲስ መልእክቶቻችን በየጊዜው እንዲደርሱዎት የቴሌግራም ቻናላችንን Join ያድርጉ።
ቴሌግራም፦ https://t.me/VoiceOfProphecy
ዓለምን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበር
የኢየሱስ ክርስቶስን አዳኝነት (አማላጅነት) ለመካድ ጫፍ ድረስ ተሂዷል። “ስለ እኛ የሚማልደው ክርስቶስ ኢየሱስ ነው” የሚለውን ቃል (ሮሜ.8፥34) “ስለ እኛ የሚፈርደው” በሚል ቀይረውት “መጽሐፍ ቅዱስ” እንዳሳተሙ ሰምቻለሁ።
ክርስቶስ አይፈርድም አይደለም፤ በእርግጥ ይፈርዳል። ለዚህ በርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ቃሎች አሉልን። እዚህ ላይ ግን ሐዋርያው የሚነግረን ፈራጅነቱን ሳይሆን በእግዚአብሔር ፊት የሚያጸድቀን ክርስቶስ መሆኑን ነው።
ምዕመኑ ግን እውነቱን አሁን ያውቃል። በዚህ ርዕስ ላይ የሃይማኖቱ አስተምህሮ በእግዚአብሔር ቃል መሠረት ቢሆን ኖሮ ከአስተምህሮው ጋር እንዲስማማ ቃሉን መቀየር ባላስፈለጋቸው ነበር። አሁን ግን ለትምህርታቸው እንዲያመች አድርገው ቃሉን ስለቀየሩት ትምህርታቸው በቃሉ ላይ የተመሠረተ አለመሆኑን ራሳቸው አረጋግጠውልሃል።
ይህ ራስን ማታለል ነው። አይጠቅማቸውም። በእውነት ነው እንጂ በሐሰት ወደ እግዚአብሔር መድረስ የለም። እውነትን እንጂ ሐሰትን በማመን ድነት አይገኝም። “... በእውነት አምናችሁ እንድትድኑ መርጧችኋል” ነው የሚለው (2ተሰ.2፥13)። በተጨማሪም ሕዝቡ እውነቱን እንዳያውቅ ስለሚያስቱት ተጠያቂ ናቸው። መድኃኒት መደበቅ ወንጀል ነው። የቤተክርስቲያን ተልእኮስ መድኃኒቱን ክርስቶስን ለሰዎች ሁሉ መግለጥ ነበር።
የክርስቶስ አዳኝነት በአንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ላይ የተንጠለጠለ አይደለም። ስንቱን አፍነው ይዘልቁታል። ሕግም ነቢያትም ሐዋርያትም ሁሉም በአንድ ድምፅ አዳኝነቱን ይመሰክራሉ። የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ እንበል።
1- አዳኝነትና አማላጅነት አንድ ናቸው።
ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት ነው ሲባል የሚያድነን ከኵነኔ ፍርድ ነው። “በእርሱ በሚያምን አይፈረድበትም ...” ይላል (ዮሐ.3፥18)። ፍርደኛውን የሚያድን ደግሞ “አማላጅ” ይባላል።
በዚህ ርዕስ ላይ በጻፍናቸው በቀደሙት መልእክቶቻችን ውስጥ እንደጠቀስነው፣ “መማለድ” ወይም “ማማለድ” ማለት ስለ ሌላው ሆኖ፥ የሌላውን ጉዳይ ይዞ መፍትሔና ብያኔ ለማግኘት ተተኪ ሆኖ መቆም ማለት ነው። ከዚሁ ጋር ተያይዞ “ፍርደኛውን ማዳን ወይም ነጻ ማውጣት” የሚል ትርጉም አለው። ይህን ተግባር የሚፈጽመው አካል ደግሞ “አማላጅ” ይባላል። “አማላጅ” ማለት “የሚማልድ”፣ “የሚያማልድ”፣ “አስታራቂ”፣ “መካከለኛ” ማለት ነው፤ በደለኛ ምሕረትን እንዲያገኝ የበደለኛውን ጉዳይ ይዞ ወደ ተበዳይ የሚገባ ወይም በፈራጁ ፊት የሚቆም፤ ፍርደኛውን የሚያስምር። በዚህ አግባብ ሐዋርያው ዮሐንስ እንደውም ጌታ ኢየሱስ በእግዚአብሔር ዘንድ ጠበቃችን መሆኑን ነው የሚያረጋግጥልን። እንዲህ ይላል፦
“... ማንም ኃጢአትን ቢያደርግ ከአብ ዘንድ ጠበቃ አለን እርሱም ጻድቅ የሆነ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። እርሱም የኃጢአታችን ማስተስሪያ ነው፥ ለኃጢአታችንም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን ለዓለሙ ሁሉ ኃጢአት እንጂ።” (1ዮሐ.2፥1-2)
በተለይም ቃሉ የሊቀ ካህናትን ተግባር ለመግለጽ ሲውል “ማማለድ” ማለት “መሥዋዕትን በማቅረብ በደልን ማስተስርየትና የእግዚአብሔርን ቁጣ ከሰው ማራቅ” ነው። የጌታ ኢየሱስ አማላጅነት በዚህ አግባብ ነው።
በአሁኑ ጊዜ ግን “ማማለድ” ማለት “ስለ ሌላው ሰው መጸለይ (መለመን)” የሚል ትርጉም ብቻ የተሰጠው ይመስላል። ዳሩ ግን የሙሴ ሊቀ ካህናት እንኳ ስለ ሕዝቡ የሚያማልዱት በሕጉ መሠረት የበደል ማስተስሪያ መሥዋዕትን በማቅረብ እንጂ በመለመን አልነበረም። “... እርሱም (ሊቀ ካህናቱ) ስለ ራሱና ስለ ሕዝቡ ስሕተት የሚያቀርበውን ደም ሳይዝ አይገባም” ይላል (ዕብ.9፥7)። “... ደምም ሳይፈስ ስርየት የለም” (ዕብ.9፥22)።
ጌታ ኢየሱስ ከኃጢአታችን ያጸደቀን ራሱን የኃጢአታችን ማስተስሪያ አድርጎ በመሠዋት ነው (ዕብ.9፥26)። ጠበቃ የሆነን የኃጢአታችን ማስተስሪያ እርሱ ራሱ በመሆኑ ነው (1ዮሐ.2፥2)። የጠበቃ ሥራው ተከሳሹ ከተከሰሰበት ወንጀል ነጻ መሆኑን ለፍርድቤቱ ማስረዳትና በማስረጃ ማረጋገጥ ነው። እርሱ ራሱ የኃጢአታችን ማስተስሪያ ስለሆነ፥ ሰይጣን እኛን ስለ ኃጢአታችን በሚከስበት በእግዚአብሔር ፊት ከኃጢአታችን መጽደቃችንን የሚያረጋግጠው ጌታ ኢየሱስ ራሱ ነው። የሰይጣንን ክስ የሚረታልን እርሱ ነው። ከኵነኔ የሚያድነን በዚህ አግባብ ነው፤ እንዲህ እንደሚል፦
“... ስለ እነርሱ እየማለደ ሁልጊዜ በሕይወት ስለሚኖር፣ በእርሱ በኩል ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል።” (ዕብ.7፥25/አ.መ.ት.)
ትርጉማቸውን በሚገባ የተረዳ ሰው አዳኝነትና አማላጅነት አንድ መሆናቸው አይጠፋውም። አዳኝነትን ለክርስቶስ አማላጅነትን ደግሞ እነርሱ “ቅዱሳን” ብለው ለሚጠሯቸው ሌሎች አካላት መስጠት የሚፈልጉ ወገኖች ናቸው የተለያዩ እንደሆኑ አድርገው የሚያቀርቧቸው። ይህ ቃል ግን አንድ መሆናቸውን ያለ ጥርጥር ያሳያል። ክርስቶስ በእርሱ በኩል ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን የሚያድናቸው ስለ እነርሱ እየማለደ ሁልጊዜ በሕይወት ስለሚኖር መሆኑን ያረጋግጣል።
በመሆኑም ለመዳን “በእርሱ በኩል ወደ እግዚአብሔር መምጣት” ያስፈልጋል። እሱም ጌታ ኢየሱስ “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም” (ዮሐ.14፥6) ባለው መሠረት ከእግዚአብሔር ጋር ግንኙነት ለመፍጠርና ኅብረት ለማድረግ የእርሱን አማላጅነት መሻት በእርሱ አማላጅነት መታመን ነው።
“በእርሱ በኩል” ወደ እግዚአብሔር መምጣት የሚቻልበት መካከለኛው ክርስቶስ ብቻ ነው። “አንድ እግዚአብሔር አለ፥ በእግዚአብሔርና በሰውም መካከል ያለው መካከለኛው ደግሞ አንድ አለ፥ እርሱም ሰው የሆነ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው” ይላል (1ጢሞ.2፥5)። ደግሞም “... ነገር ሁሉ በእርሱ በኩል የሆነ እኛም በእርሱ በኩል የሆንን አንድ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ አለን” ይላል (1ቆሮ.8፥6)።
ክርስቶስ ራሱ ወደ እግዚአብሔር መቅረቢያችን ሆኖ ሳለ የእርሱን መካከለኝነት የማይቀበሉ ወገኖች ክርስቶስ በአማላጅ እንጂ በቀጥታ ሊቀርቡት የማይቻል እንደሆነ ያስባሉ። መካከለኝነቱንም መካከለኛ ላልሆኑት ይሰጣሉ። ይህ ወንጌሉን እንደሚቃረን አንባቢው ያስተውል።
ኃጢአትህን ታውቃለህ። እንግዲያስ ተስፋህ ምንድነው? እግዚአብሔር በዓለም ላይ ሊፈርድ ቀን ቀጥሯል። በእርሱ ፊት ከኃጢአትህ እንድትጸድቅና ከሞት ፍርድ (ከሁለተኛው ሞት) እንድትድን በማን ተስፋ ታደርጋለህ?
እነርሱ ራሳቸው በክርስቶስ በማመን የሚድኑ ናቸው እንጂ አንተን ሊያድኑ የማይችሉትን “ቅዱሳን” ብለህ የምትጠራቸውን ሰዎች? ወይስ ኃጢአትህ በእርሱ በኩል እንዲሰረይልህ የሞተልህን ጌታ ኢየሱስን?
2- አስታራቂውም እግዚአብሔር ራሱ ነው።
ከእግዚአብሔር ጋር የሚያስታርቀን ክርስቶስ መሆኑን ወንጌሉ በማያሻማ ቃል ምንም ደጋግሞ ቢናገር ይህን የማይቀበሉ ወገኖች ላለመቀበል የሚያመካኙባቸው ምክንያቶች አሏቸው። አንዱ፣ ክርስቶስ ራሱ መለኮት (እግዚአብሔር) ስለሆነ አስታራቂ ሊሆን አይችልም የሚል ነው። “እርሱ ራሱ መለኮት ነው፤ እንዴት አስታራቂ ይሆናል? ከማንስ ያስታርቀናል?” ይላሉ።
በገዛ ደሙ እርቅ አወረደ፣
የጠፋሁትን ስለወደደ፤
ሐጥእ ተብዬ ስም ለወጣልኝ፣
በደሙ አንፅቶ ፃድቅ አስባለኝ፤
ከደጉ አባቴ አሁን ታረኩኝ፣
በቅዱስ ደሙ ስለታጠብኩኝ፤
ሌላ አማላጅ ሳያስፈልገኝ፣
በቀኙ ቆምኩኝ ደሙ አቀረበኝ፤
🙏Share share share share🙏
Tiktok telegram YouTube
የተፈታው በርባን
ቀን 04/08/2016 ዓ.ም
#በክርስቶስ_ደም_እርቅ_ሆኗል!
ሮሜ 5
⁶ ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና።
⁷ ስለ ጻድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና፤ ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት እንኳ የሚደፍር ምናልባት ይገኝ ይሆናል።
⁸ ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል።
⁹ ይልቁንስ እንግዲህ አሁን በደሙ ከጸደቅን በእርሱ ከቍጣው እንድናለን።
¹⁰ ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን፤
¹¹ ይህም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን አሁን መታረቁን ባገኘንበት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእግዚአብሔር ደግሞ እንመካለን።
AJEBA EMMANUEL UNITED CHURCH
በወንድም ጥላሁን ማቴዎስ👈
ክፍል ሁለት
#የጳውሎስ_የሰላምታ_እጅ_ውስጥ
ጳውሎስ ሰላምተኛው ያለ ሰላምታ አይጀምርም ጳውሎስን ትኩር ብላችሁ ተመልከቱት፡፡ ተቆጥቶም ሰላምታ ሰጥቶ ነው የሚጀምው መቆጣቱ ሰላምታ እንዳይሰጥ አይከለክለውም ፡፡
ጳውሎስ በመልእክቶቹ ውስጥ ሁሉ መግቢያ እና መውጫ አለው ፡፡ ሲገባ ሰላም ሰጥቶ ተደራሲያኑን ጨብጦ ነው የሚገባው፡፡ በሰላምታ ውስጥ ሊያወራ የፈለገውን መልዕክት ብልጭ አድርጎ ገበሬ ዘር ለመዝራት መሬት እንደሚያለሰልስ እንደዛ የመልዕክት ተቀባዮችን ልብ ያለሰልሳል ለዘር ያዘጋጃቸዋል ፡፡ በኤፌ በሮሜ በገላቲያ በፊሊጲስዮስ …… በለሌሎቹም መልዕክቶች ውስጥ ይህ ሁሉ አለ !! በእውነት ጳውሎስን በጥንቃቄ ያየ ብዙ ያተርፋል ፡፡
ጳውሎስ ለሰላምታ እጁን ሲዘረጋ እነዚህ ቃላት
ይፅፋል ገላ 1፡1-5
‹‹በኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታንም ባነሣው በእግዚአብሔር አብ ሐዋርያ የሆነ እንጂ ከሰዎች ወይም በሰው ያልሆነ ጳውሎስ ከእኔም ጋር ያሉት ወንድሞች ሁሉ፥ ወደ ገላትያ አብያተ ክርስቲያናት፤ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታችንም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።ክፉ ከሆነ ከአሁኑ ዓለም ያድነን ዘንድ እንደ አምላካችንና እንደ አባታችን ፈቃድ ስለ ኃጢአታችን ራሱን ሰጠ።ለአብ ከዘላለም እስከ ዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን።›› ገላ 1፡1-5
ጳውሎስ መልዕክታቱን ሲፅፍ በሰላምታ ነው የሚጀምረው አንዳንድ ጊዜ አጠር ያለ ሰላምታ በማቅረብ ወደ ጉዳዩ ይፈጥናል አንዳንድ ጊዜ ደግሞ ረጀም ሰላምታ ያቀርባል ፡፡ ምናልባት ይህንን የሚወስነው ተደራሲያኑ ወይም ሊፅፍ ያሰበው ጉዳይ አገብጋቢነት ነው ፡፡ በገላቲያ አጠር ያለ ሰላምታ ሲያቀርብ በሮሜ ደግሞ ረዘም ያለ ሰላምታ ያቀርባል ፡፡ ሮሜ 1፡1-7 ገላ 1፡1-3
በገላቲያ መፅሐፍ ውስጥ ጳውሎስ የተቆጣበት ወይም የተበሳጨበት ጉዳይ ስላለ በፍጥነት ወደ መልዕክቱ ይገባል ፡፡ ሁል ጊዜ ጳውሎስ የሚያበሳጨው ነገር የመዳን እውነት ሲነካ ሰዎች አይናቸው ከክርስቶስ ላይ ሲቅሉ ለመዳኛ ሌላ አማራጭ ሲፈልጉ ነው ፡፡
የገላቲያ ሰዎች እንዲህ አይነት ነበሩ ስለዚህ በቁጣ ቃል ይናገራል ፡፡ 👉አይጠቅማቹሁም ፣ ከጸጋ ትወድቃላችሁ ፣ ከክርስቶስ ትላያላችሁ እያከ ከባድ ማስጠንቀቂያ ያስጠነቅቃቸዋል ፡፡ ገላ 5፡1-1-5 ገላ 3፡1
ጳውሎስ ብዕር እና ወረቀት አዋዶ የሚፅፋቸው የሚከትባቸው ፅሁፎች እጅግ ውድ ንብረቶች ናቸው ፡፡ እንደ ቀልድ አይቶ የሚፅፋቸው ነገሮች የሉትም ፡፡ ሰላምታዎች እንኳ ለጳውሎስ መልዕክት ማስተላለፊ መንገዶች ናቸው ፡፡
በጳውሎስ የመግቢያ ሰላምታ ንግግሮች ውስጥ ያሉ እውነታዎች እኚህ ናቸው ።
🔸1ኛ የሐዋሪያነት ምንጭ ቁ 1-2
🔸2ኛ የተደራሲያን ስፍራ ቁ 1-2
🔸3ኛ ፀጋ እና ሰላም ቁ 3
🔸4ኛ ለመዳናችን የሆነው ነገር ቁ 4
🔸5ኛ ምስጋና ቁ- 5
እነዚህ ሃሳቦች በዝርዝር እንመልከት
1ኛ የሐዋሪያነት ምንጭ ቁ 1-2
‹‹በኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታንም ባነሣው በእግዚአብሔር አብ ሐዋርያ የሆነ እንጂ ከሰዎች ወይም በሰው ያልሆነ ጳውሎስ ከእኔም ጋር ያሉት ወንድሞች ሁሉ፥ ወደ ገላትያ አብያተ ክርስቲያናት ››
ጳውሎስን ሐዋሪያ ያደረገው ማነው ?
ይሄ ጥያቄ ለጳውሎስ አንገብጋቢ ጥያቄ እና መልስ የሚያሻው ጥያቄ ነው ፡፡ ምክንያቱም ጳውሎስ የሚያስተምረውን ትምህርት ላለመቀበል የጳውሎስ ሐዋሪያነት ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ሰዎች ነበሩ ፡፡ ጳውሎስ ሐዋሪያ አይደለም ይሉት ነበር ፡፡ ይህ በገላቲያ ብቻ ሳይሆን በሌሎችም አብያተ ክርስቲያናት የተከሰተ ጥያቄ ነበር ።
የጳውሎስን አገልግሎት ላለመቀበል ጥያቄ ያነሱ ስለነበር በተደጋጋሚ ጳውሎስ ምላሽ ይሰጣል ፡፡1ኛ ቆሮ 1፡1 ሮሜ 1፤5
እዚህ ጋር መረዳት ያለብን እውነት ይህ ነው። ብዙዎች እውነተኛ ሆነክ እንኳ አንተን ላለመቀበል ይታገላሉ ፡፡ ነገር ግን ሰው አልተቀበለህም ማለት ሐሰተኛ ነህ ማለት አይደለም ፡፡ ሁል ጊዜ ራስህ መጠየቅ ያለብህ ከእግዚአብሄር ጋር ያለህ ግንኙነት ምን እንደሚመስል ለቅዱሳት መፅሐፍት ታማኝ ነኝ ወይ ? የሚለውን ነው፡፡ጳውሎስን በአብዛኛው ቤተ ክርስቲያን እሱን ላለመቀበል ምክንያት የሚደረድሩ ልበ ሻካራ ሰዎች ነበሩ ፡፡ በተለይም ሐዋሪያነቱ ላይ ጥያቄ እያነሱ ነበር ፡፡ ብዙ የሙግት ነጥቦችን በማንሳት እራሱን ቢከላከልም በ1ኛ ቆሮ መልክቱ ግን ጠንከር ያለ ሙግት ያቀርባል ፡፡
1ኛ ቆሮ 9፡1-5
‹‹እኔ ነጻ አይደለሁምን? ሐዋርያስ አይደለሁምን? ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስንስ አላየሁትምን? እናንተስ በጌታ ሥራዬ አይደላችሁምን?የሐዋርያነቴ ማኅተም በጌታ እናንተ ናችሁና ለሌሎች ሐዋርያ ባልሆን ለእናንተስ ምንም ቢሆን ሐዋርያ ነኝ።ለሚመረምሩኝ መልሴ ይህ ነው። ልንበላና ልንጠጣ መብት የለንምን?እንደ ሌሎቹ ሐዋርያትና እንደ ጌታ ወንድሞች እንደ ኬፋም፥ እኅት ሚስታችንን ይዘን ልንዞር መብት የለንምን?››
በአዲሱ መደበኛ ትርጉም እንዲህ ይላል
‹‹ እኔ ነፃ ሰው አይደለሁምን ? ሐዋርያስ አይደለሁምን ? ጌታችን ኢየሱስን አላየሁትምን? እናንተስ በጌታ የድካሜ ፍሬዎች አይደላችሁምን ? ለሌሎች ሐዋርያ ባልሆን እንኳ ለእናንተ ሐዋርያ ነኝ ምክንያቱም በጌታ የሐዋሪያነቴ ማኅተምእናንተ ናችሁ …..፡፡››
ስለዚህ ጳውሎስ ሐዋርያ መሆኑን በተለያየ መንገድ ለማሳያት ይሞክራል ፡፡ ጳውሎስ ሐዋርያ መሆኑን ብቻ ሳይሆን የሐዋርያነት ምንጩንም ይናገራል ፡፡ የሱ ሐዋሪያነት ከየት መጣ? ማን ሰጠው? የመስጠትስ ስልጣን የማን ነው? ጳውሎስ ይህንን በገላቲያ መግቢያ ላይ ይመልሳል ፡፡
የእውነት ሐዋሪያ ስለነበር የእውነት ይመልሳል ፡፡ ይህ የሁላችንም ገንዘብ መሆን አለበት እውነት ሰፈር አለመጥፋት ውሸት ሰፈር አለመገነት ።
በእርግጥ እግዚአብሔር እንደጠራን እናምናለን? በእኛ መስራት የሚፈልገው ነገር እንዳለስ እርግጠኞች ነን? አንድ እውነት ልንገራቹ እግዚአብሔር ሊጠቀምባት የማይፈልገው አማኝ የለም እናንተ ለእግዚአብሔር የጨለማን ሰፈር የሚያብራባችሁ ውዶቹ ናችሁ ። ስለዚህ አለም የሚለጥፍባቹን የውሸት ስያሜ በእውነት ብርሃን ገልጣችሁ ለትልቁ አላማ ተነሱ ።
የጌታ ፀጋ ይብዛላችሁ !!! አሜን
ይቀጥላል.......
የመጨመር ጣጣ
#ገላቲያዊነት
ገላቲያ ክፍል አንድ
ስለ ነገ የማያስብ ስለ ነገ የማይጨነቅ ሰው አለ ብሎ ማሰብ ከባድ ነው ፡፡ ነገን የማይፈራ ጀግና ማግኘት ከጭድ ውስጥ መርፌ ፈልጎ የማግኘት ያህል ከባድ ነው ፡፡ ነገ ግዙፍ ነው ነገ ሃያል ነው ነገ ገናና ነው ፡፡ ወላጆች ልጆቻቸውን ነጋቸውን አስበው በጨቅላ ወራት የተመጣተነ ምግብ ያበሏቸዋል ትምህርት ቤት ያስገቧቸዋል ሌላም ሌላም ...የጎረመሱ ሰዎች ስነ ነገ ማሰብ ይጀምራሉ ስለ ስራ፣ ስለ ትዳር፣ ነገ ስለሚሳካ የዛሬ አላማቸው ሌላም ሌላም … ለዚህም ነው የነገው ጌታ ኢየሱስ ስለ ነገ አትጨነቁ ከመጠን በላይ አታስቡ የሚል ማበረታቻ አዘል ቃላት የተናገረው ሰው መጨነቁ አይቀርማ !! ነገ ያስፈራል አዎ ግን
#ዘላለምስ???
ገላቲያ ቤተ ክስርቲያን ውስጥ በክርስትና ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ አጠቃላይ ስብሰባ ያስጠራ ጉባዬ ያዘረጋ ችግር ተፈጠረ ዘመኑ በ 49 አ.ም አከባቢ ነው ፡፡ ጳውሎስ በመጀመሪያው የሐዋሪያዊ ጉዞ የመሰረታት ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ልብ የሚያናውጥ፣ በደቀ መዝሙር ጫንቃ ላይ ቀንበር በሚያከብድ ጉዳይ የተነሳ ቤተ ክርስቲያ በሁለት ጎራዎች ተወጥራ ተጨንቃለች ይህ ጭንቅ ጉባዬን ወለደ ፡፡ የመጀመሪያው የሐዋርያት ጉባዬ ተብሎ ይጠራል ።
የመጀመሪያው ጉባዬ በኢየሩሳሌም ተጠራ የሐዋ ስራ ምዕራፍ አስራ አምስት የእዚህ ጉዳይ ሪፖርት ነው ፡፡
የመጨመር ጣጣ የወለደው ጉባዬ
የችግሩ ምንጭ እንዲህ ይነበባል ፡፡
የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 15፡1-2
‹‹አንዳንዶችም ከይሁዳ ወረዱና። እንደ ሙሴ ሥርዓት ካልተገረዛችሁ #ትድኑ ዘንድ አትችሉም ብለው ወንድሞችን ያስተምሩ ነበር። በእነርሱና በጳውሎስ በበርናባስም መካከል ብዙ ጥልና ክርክር በሆነ ጊዜ፥ ስለዚህ ክርክር ጳውስና በርናባስ ከእነርሱም አንዳንዶች ሌሎች ሰዎች ወደ ሐዋርያት ወደ ሽማግሌዎችም ወደ ኢየሩሳሌም ይወጡ ዘንድ ተቈረጠ።››
ጉዳዩን አንገብጋቢ የሚያደርገው #የመዳን ጉዳይ መሆኑ ነው ፡፡
🔸 እንደ ሙሴ ስርአት ካልተገረዛችሁ ትድኑ ዘንድ አትችሉም ቁ 1
በድጋሚ ይህንን ሃሳብ የሚያጠናክር ቃል ቁጥር አምስት ላይ እናገኛለን
‹‹ከፈሪሳውያን ወገን ግን ያመኑት አንዳንዶቹ ተነሥተው። ትገርዙአቸው ዘንድና የሙሴን ሕግ እንዲጠብቁ ታዙአቸው ዘንድ ይገባል አሉ።›› ሐዋ ስራ 15፡5
ለምን እንዲህ አሉ ብለን የጠየቅን እንደሆነ ፡- መልሱ ትድኑ ዘንድ ነው ፡፡ ለመዳን ተገረዙ የሙሴን ሕግ ጠብቁ !!
ችግሩ ይህ ነው !!
በክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከክርስቶስ ውጪ
🔸የመዳንን መንገድ የመፈለግ እና የመዳከር ሕይወት
🔸ክርስቶስ አይበቃኝም የሚል የመቅመዝበዝ ጉዞ
🔸ለባህሌ አደላለው በማለት የተፈጠረ በሰዎች መዳን ላይ የተጋረጠ አደጋ !!!
ኢየሱስ ሲደመር ሕግ
ክርስቶስ ላይ መጨመር መዘዙ ከባድ ነው ፡፡
ጳውሎስ በእዚህ ጊዜ እንደ አራስ ነብር ተናዷል ጭራዋ እንደተረገጠ ድመት ተቆጥቷል ፡፡ መልዕክቱን ሲፅፍ ሰላምታ እንኳን አያስረዝምም ፡፡ ወደ ጉዳዩ ለመግባት ይጣደፈል ፡፡
ለምን ?
🔸 የተነካው የመዳን ጉዳይ ነው ፡፡
🔸ከይሁዳ የወረዱት ሰዎች በዘላለም ጉዳይ ላይ ነው የተጋረጡት
ይሄ ለእኛ ትምህርት ነው
መቼ ነው ምንናደደው ?
🔸በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ክብራችን ሲነካ ወይስ የዘላለም አጀንዳ ሲነካ
🔸እኛ ስንደፈር ወይስ የእግዚአብሄር እውነት ሲደፈር
🔸እኛ በምክንያት ገለል ስንደረግ ወይስ የመለኮት ሀሳብ ከመድረኩ ገለል በመድረጉ
የገላቲያ መፅሐፍ በ49 ዓ.ም አከባቢ በአህዛቡ ሐዋርያ ማለትም ለአሕዛብ ሐዋሪያ ሊሆን በተጠራው የተፃፈ በስድስት ምዕራፎች የተዋቀረ በ149 ቁጥሮች የተደረደረ በደቡብ ገላትያ ላለች አብያተ ክርስቲያት የተፃፈ ለመጀመሪያ ጊዜ የተከበ የአዲስ ኪዳን መፅሐፍ ነው ፡፡
ታዲያ ጳውሎስ የመጀመሪውን ደብዳቤ ለመፃፍ ሲነሳ የተነሳው በክርስቶስ የሚገኘው መዳን ሲደፈር ሲነካ ነው ፡፡
ለእግዚአብሄር እውነት መቆም ይሁንልን አሜን!!
ይቀጥላል .....
በመምህር ግሩም ድፋቅ👈
