Ajeba Emmanuel united church
Open in Telegram
እውነት እላችኋለሁ፤ ቃሌን የሚሰማ፣ በላከኝም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ ከሞት ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም።” — ዮሐንስ 5፥24 (አዲሱ መ.ት)
Show more259
Subscribers
-224 hours
-27 days
-430 days
Posts Archive
#እርሱ_ሰላማችን_ነው👇↙
#ኢየሱስ
➫ #እርሱ_ሰላማችን_ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን #የጥል_ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ #ሰላምንም_ያደርግ ዘንድ፥
— ኤፌሶን 2፥14-15
#የመሥዋዕቱ_በግ ክፍል 6ድስት
👇👇👇👇👇👇👇
➫በመሥዋዕቱ በግ በኢየሱስ ኃጢአታችን ተወግዷል።
➫ዘሌዋውያን 16
⁵ ከእስራኤልም ልጆች ማኅበር ለኃጢአት መሥዋዕት ሁለት አውራ ፍየሎች፥ ለሚቃጠልም መሥዋዕት አንድ አውራ በግ ይውሰድ።
..
⁷ ሁለቱንም አውራ ፍየሎች ወስዶ በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ አጠገብ በእግዚአብሔር ፊት ያቆማቸዋል።
⁸ አሮንም በሁለቱ ፍየሎች ላይ ዕጣ ይጥልባቸዋል፥ አንዱን ዕጣ ለእግዚአብሔር ሌላውንም ዕጣ ለሚለቀቅ።
⁹ አሮንም የእግዚአብሔር ዕጣ የሆነበትን ፍየል ያቀርባል፥ ስለ ኃጢአትም መሥዋዕት ያደርገዋል።
¹⁰ የመለቀቅም ዕጣ የሆነበትን ፍየል ያስተሰርይበት ዘንድ፥ ለመለቀቅም ወደ ምድረ በዳ ይሰድደው ዘንድ በሕይወቱ በእግዚአብሔር ፊት ያቆመዋል።
…
²⁰ መቅደሱንም፥ የመገናኛውንም ድንኳን፥ መሠዊያውንም ማስተስረይ ከፈጸመ በኋላ ሕያውን ፍየል ያቀርባል፤
²¹ አሮንም ሁለቱን እጆቹን በሕያው ፍየል ራስ ላይ ይጭናል፥ በላዩም የእስራኤልን ልጆች በደል ሁሉ መተላለፋቸውንም ሁሉ ኃጢአታቸውንም ሁሉ ይናዝዛል፤ በፍየሉም ራስ ላይ ያሸክመዋል፥ በተዘጋጀው ሰውም እጅ ወደ ምድረ በዳ ይሰድደዋል።
²² ፍየሉም ኃጢአታቸውን ሁሉ ወደ በረሀ ይሸከማል፤ ፍየሉንም በምድረ በዳ ውስጥ ይለቅቀዋል።
➫ምሥራቅ ከምዕራብ እንደሚርቅ፥ እንዲሁ ኃጢአታችንን ከእኛ አራቀ።
— መዝሙር 103፥12
➫በሁለቱ ፍየሎች ላይ ኃጢአትን / የእስራኤልን ልጆች በደል ሁሉ መተላለፋቸውንም ሁሉ በፍየሉም ራስ ላይ ያሸክመዋል፥ ከሁለቱ አንዱን አውራ ፍየል ስለ ኃጢአትም መሥዋዕት ያደርገዋል። አንዱን ደግሞ በበረሃ /በምድረ በዳ ውስጥ ይለቅቀዋል።
➫ነገር ግን እነዛ መሥዋዕቶች እና የመሥዋዕት ሥርዓቶች ኃጢአትን ከቶ ሊያስወግዱ አልቻሉም ።
➫ የኮርማዎችና የፍየሎች ደም ኃጢአትን እንዲያስወግድ የማይቻል ነውና።
— ዕብራውያን 10፥4
➫በሚታረደውም ቢሆን ኃጢአትን አሸክሞ ወደ በረሃ/ ወደ ምድረ በዳ በሚለቁት በፍየሎች ደም ኃጢአት ሊወገድ/ ኃጢአትን እንዲያስወግድ የማይቻል ነውና።ነገር ግን ጌታ ኢየሱስ ሁሉቱንም በመሆን ኃጢአታችንን ከእኛ አስወግዷል።
➫ ማቴዎስ 27 ➻ማር 15:22
¹¹ ኢየሱስም በገዢው ፊት ቆመ፤ ገዢውም፦ የአይሁድ ንጉሥ አንተ ነህን? ብሎ ጠየቀው፤ ኢየሱስም፦ አንተ አልህ አለው።
¹² የካህናት አለቆችም ሽማግሎችም ሲከሱት ምንም አልመለሰም።
¹³ በዚያን ጊዜ ጲላጦስ፦ ስንት ያህል እንዲመሰክሩብህ አትሰማምን? አለው።
¹⁴ ገዢውም እጅግ እስኪደነቅ ድረስ አንዲት ቃል ስንኳ አልመለሰለትም።
…
²⁷ በዚያን ጊዜ የገዢው ወታደሮች ኢየሱስን ወደ ገዢው ግቢ ውስጥ ወሰዱት ጭፍራውንም ሁሉ ወደ እርሱ አከማቹ።
²⁸ ልብሱንም ገፈው ቀይ ልብስ አለበሱት፥
²⁹ ከእሾህም አክሊል ጎንጉነው በራሱ ላይ፥ በቀኝ እጁም መቃ አኖሩ፥ በፊቱም ተንበርክከው፦ የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ ዘበቱበት፤
…
³¹ ከዘበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት ሊሰቅሉትም ወሰዱት።
➫ኢየሱስንም ይዘው ወሰዱት፤ መስቀሉንም ተሸክሞ በዕብራይስጥ ጎልጎታ ወደ ተባለው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሉት ወጣ።
— ዮሐንስ 19፥17
➫እንደዚህማ ባይሆን፥ የሚያመልኩት አንድ ጊዜ ነጽተው ከዚያ በኋላ በሕሊናቸው ኃጢአትን ስላላወቁ ማቅረብን በተዉ አልነበረምን?”
— ዕብራውያን 10፥2
➫ዮሐንስ 1
²⁹ በነገው ዮሐንስ ኢየሱስን ወደ እርሱ ሲመጣ አይቶ እንዲህ አለ፦ እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።
…
³⁶ ኢየሱስም ሲሄድ ተመልክቶ፦ እነሆ የእግዚአብሔር በግ አለ።
➫እርሱም ኃጢአትን ሊያስወግድ እንደ ተገለጠ ታውቃላችሁ፥ በእርሱም ኃጢአት የለም።
— 1ኛ ዮሐንስ 3፥5
➫ዕብራውያን 10
¹¹ ሊቀ ካህናትም ሁሉ ዕለት ዕለት እያገለገለ ኃጢአትን ሊያስወግዱ ከቶ የማይችሉትን እነዚያን መሥዋዕቶች ብዙ ጊዜ እያቀረበ ቆሞአል፤
¹² እርሱ ግን ስለ ኃጢአት አንድን መሥዋዕት ለዘላለም አቅርቦ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀመጠ፥
➫እንዲህ ቢሆንስ፥ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ ብዙ ጊዜ መከራ ሊቀበል ባስፈለገው ነበር፤ አሁን ግን በዓለም ፍጻሜ ራሱን በመሠዋት ኃጢአትን ሊሽር አንድ ጊዜ ተገልጦአል።”
— ዕብራውያን 9፥26
#ኢየሱስ_የተሸከመው_ኃጢአታችንን እንጂ ኃጢአቱን አይደለም።
➫ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።
— 1ኛ ጴጥሮስ 2፥24
➻ቀጣይ እሁድ ሰምንት ክፍል7 እንቀጥላለን
#Tèká. E
ክርስቶስ ማን ነው?
➫ይህንን መጽሐፍ እንድታነቡና አንዳንድ በነገረ-ክርስቶስ ላይ ያላችሁ አመለካከት እንዲዳብር ስል እጋብዛችኋለው፡፡👇👇👇
የተሃድሶ አባት በመባል የሚታወቀው ሉተር ከመነሳቱ ከ30 ዓመታት በፊት ኢትዮጵያ ውስጥ የተሀድሶ (Reformation) እንቅስቃሴ ተነስቶ እንደነበር ያውቃሉ? እንግዲያውስ ይህንን "ደቂቀ እስጢፋኖስ" የተሰኘ መፅሃፍ ያንብቡ::
🔴በአሁን ወቅት ገበያ ላይ በቀላሉ አይገኝም::
በኢትዮጵያ አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን ትምህርት ክፍል የተዘጋጀ የመዳን ትምህርት ዛሬም ቀጥለናል....
ትምህርቱን የምትፈልጉ በPDF መልክ በውስጥ መስመር ታገኛለችሁ🙌
ይሄንን የመጽሐፍ ቅዱስ እውነት እንደቀየሩት ያውቃሉ?
“ኢየሱስም፦ እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።”
— ዮሐንስ 14፥6
የሚለውን በ2000ው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ
"ጌታችን ኢየሱስም እንዲህ አለው የእውነትና የሕይወት መንገድ እኔ ነኝ በእኔ በኩል ካልሆነ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም" በማለት ቀይረው ተርጉመውታል።
እናስተውል!
ኢየሱስ እውነትም ሕይወትም መንገድም ነው እንጂ ወደ እውነትና ወደ ሕይወት የሚወስድ መንገድ ብቻ አይደለም። ሕይወትና እውነት ሌላ አካል ሆኖ ኢየሱስ መድረሻ መንገድ አድርጎ የተረጎመው የ2000ው መጽሐፍ ቅዱስ ዶግማዊ ተፋልሶ እያስከተለ ነው።
ኢየሱስ ወደ እውነት መሄጃ ወይም ወደ ሕይወት መድረሻ ሳይሆን ራሱ እውነትም ሕይወትም መንገድም ነው።
➫ አ ል ጠ ፋ ም👈🙅
↙↙↙↙↙↙↙↙↙↙↙↙
#አልጠፋም_ብዬ_ሲል፦
1.እረኛዬን ኢየሱስ ነው እያልኩኝ ነው።
👇👇
መዝሙር 23
¹ እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፥ የሚያሳጣኝም የለም።
² በለመለመ መስክ ያሳድረኛል፤ በዕረፍት ውኃ ዘንድ ይመራኛል።
³ ነፍሴን መለሳት፥ ስለ ስሙም በጽድቅ መንገድ መራኝ።
⁴ በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ አንተ ከእኔ ጋር ነህና ክፉን አልፈራም፤ በትርህና ምርኵዝህ እነርሱ ያጸናኑኛል።
⁵ በፊቴ ገበታን አዘጋጀህልኝ፤ በጠላቶቼ ፊት ለፊት ራሴን በዘይት ቀባህ፥ ጽዋዬም የተረፈ ነው።
⁶ ቸርነትህና ምሕረትህ በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ይከተሉኛል፥ በእግዚአብሔርም ቤት ለዘላለም እኖራለሁ።
👇
👉ዮሐንስ 10
⁹ በሩ እኔ ነኝ፤ በእኔ የሚገባ ቢኖር ይድናል፥ ይገባልም ይወጣልም መሰማርያም ያገኛል።
…
¹¹ መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።
¹² እረኛ ያልሆነው በጎቹም የእርሱ ያልሆኑ ሞያተኛ ግን ተኵላ ሲመጣ ባየ ጊዜ በጎቹን ትቶ ይሸሻል፤ ተኵላም ይነጥቃቸዋል በጎቹንም ይበትናቸዋል።
…
¹⁴-¹⁵ መልካም እረኛ እኔ ነኝ፥ አብም እንደሚያውቀኝ እኔም አብን እንደማውቀው የራሴን በጎች አውቃለሁ የራሴም በጎች ያውቁኛል፤ ነፍሴንም ስለ በጎች አኖራለሁ።
…
²⁸ እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም።
²⁹ የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ ከአባቴም እጅ ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም።
2.#የበላሁት_ኢየሱስን_ነው_እያልኩኝ ነው።
➫እኔ አልጠፋም ብዬ ሲነገር የበላሁት መና አይደለም እያልኩኝ ነው
👇👇
✔ዮሐንስ 6
⁴⁹ አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱም፤
⁵⁰ ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው።
⁵¹ ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው።
3.#የተወለድኩት_ከማይጠፋ_ዘር_ነው_እያልኩኝ_ነው።👇👇
➫ዳግመኛ የተወለዳችሁት ከሚጠፋ ዘር አይደለም፥ በሕያውና ለዘላለም በሚኖር በእግዚአብሔር ቃል ከማይጠፋ ዘር ነው እንጂ።
— 1ኛ ጴጥሮስ 1፥23
4.#አዲስ_ፍጥረት_ነኝ_እያልኩኝ ነው።👇👇
➫ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል።”
— 2ኛ ቆሮ 5፥17
➫ አ ል ጠ ፋ ም.....እንቀጥላለን 🙌🙌
➾Teka.E
#መዳን👈👇
➫መዳን ማለት ምን ማለት ነው ከሚለው እንነሳ፦
1. አዲስ ሕይወት መቀበል/አዲስ ፍጥረት መሆን(2ቆሮ 5:17)
2. ከኃጢአት ነጻ መሆን(የዳነ ሰው ኃጢአት ይሰራል እንጂ ኃጢአተኛ አይደለም)።" ጴጥሮስም። ንስሐ ግቡ፥ ኃጢአታችሁም ይሰረይ ዘንድ እያንዳንዳችሁ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቁ፤ የመንፈስ ቅዱስንም ስጦታ ትቀበላላችሁ።
(የሐዋርያት ሥራ 2:38)
3. ከኃጢአት ፍርድ ማምለጥ(የኃጢአት ዋጋ ሞት ነው እንደሚል ከዘላለም ወይንም ከእሳት መዳን::" ይልቁንስ እንግዲህ አሁን በደሙ ከጸደቅን በእርሱ ከቍጣው እንድናለን።"(ወደ ሮሜ ሰዎች 5:9)
➫ እግዚአብሔር ለቍጣ አልመረጠንምና፥ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መዳንን ለማግኘት ነው እንጂ።
(1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 5:9)
4. ከኃጢአት ኃይል መዳን(" የሞት መውጊያ ኃጢአት ነው የኃጢአትም ኃይል ሕግ ነው፤"
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:56)
#ማነው_የማዳን_ሥልጣን_ያለው?👇
➫ማዳን የእግዚአብሔር ድርሻ ብቻ ነው(የትኛውም ፍጥረት የሰውን ልጅ የማዳን ሥልጣን የለውም(" ያዳነን በቅዱስም አጠራር የጠራን እግዚአብሔር ነውና፥ ይህም እንደ ራሱ አሳብና ጸጋ መጠን ነው እንጂ እንደ ሥራችን መጠን አይደለም፤ ይህም ጸጋ ከዘላለም ዘመናት በፊት በክርስቶስ ኢየሱስ ተሰጠን፥
(2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1:9)
➫ እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤
(ወደ ቲቶ 3:5)
➫#እግዚአብሔር_የማዳንን_መንገድ_እንዴት አዘጋጀ?
➫ አንዱን ልጅ ኢየሱስን ለዓለም ሁሉ ኃጢአት እንዲሞት በማድረጉ።👇
➫ዓለም በልጁ እንዲድን ነው እንጂ፥ በዓለም እንዲፈርድ እግዚአብሔር ወደ ዓለም አልላከውምና።"(የዮሐንስ ወንጌል 3:17)
#ይህንን_መዳን_እንዴት_መቀበል_እንችላለን?👇
➻ይህንን መዳን መቀበል የሚንችለው በእምነት ብቻ ቢሆንም እንድናምን የምያደርገንን ወንጌል መስማት አለብን።
✔ እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፤
(ወደ ኤፌሶን ሰዎች 1:13)
➫#ኢየሱስ_እንደሚያድን የተሰበክነውን ወንጌል ከሰማን በኋላ በሙሉ ልባችን ካመንን በዛው ቅጽበት ድነናል(ጸድቀናል)::
➫በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና።
(ወደ ሮሜ ሰዎች 1:16)
👉 ስጠቀለል:- #አንድ_ሰው_ጌታን_ለመቀበል_ከወሰነ_ምን_ማድረግ_አለበት?
1.በአዳም አማከኝነት የወረሰውን ኃጢአት አምኖ መናዘዝ አለበት፦
➫እንግዲህ ከጌታ ፊት የመጽናናት ዘመን እንድትመጣላችሁ አስቀድሞም ለእናንተ የመረጠውን ኢየሱስ ክርስቶስን እንዲልክላችሁ፥ ኃጢአታችሁ ይደመሰስ ዘንድ ንስሐ ግቡ ተመለሱም።
(የሐዋርያት ሥራ 3:19-20)
2. ኢየሱስን ሕይወቱ ላይ ጌታ አድርጎ መቀበል አለበት፦
➫ ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤"(ወደ ሮሜ ሰዎች 10:9)
ዶ/ር መንግስቱ ለማ 🙌...ፀጋው ይብዛልህ ❤
ክፍል አምስት
#ለመዳናችን_የሆነው_ነገር_ይህ_ነው ፡፡
ገላ 1:4
የሰው ጆሮ እንደ ባለቤቱ ሊሰማ የሚወደው ነገር አለው ።ሁሉ ሁሉን መስማት አይወድም ምናልባትም ሁሉንም መስማት ለሁሉ አይጠቅምም ። ነገር ግን ለመዳኛችን የሆነ ነገር ይህ ነው ሲባል ሰው ጆሮውን አቁሞ መስማት አለበት ፡፡ ምክንያቱም መዳን ለሰው ልጆች ሁሉ የሚያስፈልግ ነውና ፡፡ መፅሐፍ ሁሉ ኃጢያት ሰርተዋል ይላል ። ለእዚህ ነው ጳውሎስ መዳናቹ የተሰራው እንዲህ ነው የሚለን ፡፡
ጳውሎስ በመግቢያ ሰላምታ ውስጥ በዘመኑ በጥቅሉ የሚያስተምረውን ሀሳብ በአንድ ቁጥር ውስጥ ጠቅጥቆ ይናገዋል ፡፡ ጳውሎስ የአዳኛችንን ስራ አያወሳስበውም ግልፅ ነው፡፡ ለሚሰሙት እንደሚገባቸው እንደዛ ያስረዳቸዋል ። ብዙዎቻችን ይሄን ፈለግ መከተል ይገባናል ፡፡ ሰዎች የምንሰብከውን እንዲረዱልን የተቻለ ጥረት ማድግ ይገባናል እንጂ ማወሳሰብ አይጠበቅብንም !!
ጳውሎስ እንዲህ ይላል
‹‹ክፉ ከሆነ ከአሁኑ ዓለም ያድነን ዘንድ እንደ አምላካችንና እንደ አባታችን ፈቃድ ስለ ኃጢአታችን ራሱን ሰጠ።››
በእዚህ ቁጥር ውስጥ ሶሰት ዋና ዋና ጉዳዮች ይነሳሉ ፡፡
1ኛ ክፉ ከሆነው አለም ያድነን ዘንድ ‹‹that he might deliver us from this present evil world››
ይህ ክፉ አለም ማነው ?
ምሁራን ይህንን ቃል በሁለት መንገድ የሚመለከቱት ሲሆን እኛ ይህንን ከመመለሳችን በፊት የጳውሎስ አላማ በገላቲያ መፅሀፍ ውስጥ ማስታወስ አለብን።
ይህም በክርስቶስ የተገኘው የመዳን ጉዳይ ላይ ጥያቄ ያስነሱ ከይሁዳ የመጡ ወንድሞች ግን የሐሰት አስተማሪዎች ላይ (ለመዳን መገረዝና እና የሙሴን ሕግ መጠበቅ ያስፈልጋል ያሉ) የስህተት ትምህታቸውን የማጋለጥ ስራ መስራት እና ትክክለኛውን ወንጌል ን ማስታወስ ነው ፡፡
ስለዚህ ክርስቶስ በአብ ፍቃድ ራሱን በመስጠት ከእዚህ ክፉ አለም "this present evil world" ያድነን ዘንድ ወዷል፡፡
ይሄንን ቃል በሁለት መንገድ ምሁራኖች ይረዱታል The phrase "this present evil world" can be understood in a couple of ways
🔸The moral and spiritual corruption of the world
🔸 The age or era dominated by evil
የአለም ስነ ምግባራዊ እና መንፈሳዊ ብልሹነት (The moral and spiritual corruption of the world ) ብዙዎች የሚስማሙት በመሆኑ ይህን አቀርባለው ፡፡
ጳውሎስ እየተናገረ ያለው ከእዚህ ክፉ አለም ያድነን ዘንድ ሲል ከክርስቶስ የተነሳ
🔸በኃጢያት ምንያንት ከተበላሸው ከእዚህ አለም በማዳን ደግሞም
🔸 ከእግዚአብሄር በተቃራኒ በመቆም በተፃራሪነት ካለው የሕይወት ስርአት አላቆ
🔸ለኃጢያት መከፈል ያለበት የመስዋት ክፍያን በመክፈል
🔸ከእግዚአብሄር ጋር ህብረት እንዲኖረን ስለ ተደረገበት ጉዳይ እና
🔸ከእዚህ የተዋረደው በኃጢያት ምክንያት ከተሰበረው የህይወት ስርአት ተላቀን
🔸በአዲስ የሕይወት ስርዓት ከአምላካችን ጋር እንደገና የተቋረጠውን የሕይወት ስርዓት በማስጀመር ስለ ገባንበት አለም እና ህብረት ስለመጀመራች የሚያወራ ነው ፡፡
‹‹Paul is highlighting the fallen state of the world in terms of its moral and spiritual condition. The world, in its rebellion against God, is characterized by sin, brokenness, and separation from God. Jesus' sacrifice aims to rescue humanity from this state of corruption and bring them into a restored relationship with God››
2ኛ እንደ አምላካችን እና እንደ አባታችን ፍቃድ
በእዚህ ክፍል አባታችን እና አምለካችን ተብሎ የተጠራው እግዚአብሄር አብ ነው ፡፡ ይህ አባትና አምላክ ልጆች ሊያደርገን ወዶ ልጁን መስጠት ፍቃዱ ሆኗል ፡፡ እንዴት ያለ ፍቅር ነው በሚያስብል ሁኔታ ልጁን በመስጠት ፍቅሩን አብራርቷል ፡፡
ዮሐንስ በመልዕክቱ እንዲህ ነው የሚለን
‹‹ በዚህ የእግዚአብሔር ፍቅር በእኛ ዘንድ ተገለጠ፥ በእርሱ በኩል በሕይወት እንኖር ዘንድ እግዚአብሔር አንድ ልጁን ወደ ዓለም ልኮታልና።ፍቅርም እንደዚህ ነው፤ እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተስሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔርን እንደ ወደድነው አይደለም።›› 1ኛ ዮሃ 4፡9-10
ለምን ልጁን ላከው ለምን ልጁን ሰጠን ?
🔸እኛ በህይወት እንኖር ዘንድ
እንዴት ሊልክልን ቻለ ?
🔸 ስለወደደን
የተላከበት ምክንያት ምንድነው ?
🔸ስለ ኃጢያታችን ማስተሰርያ እንዲሆነን
ይህ ክፍል የሚነግረን አባትችን እና አምላካችንን ፈቅዶ ልጁን ለእኛ መስጠቱንና የእርሱን ንፁህ ፍቅር ነው ፡፡
3. ስለ ሐጢያታችን ራሱን ሰጠ
ጳውሎስ በሰላምታ ውስጥ ሌላ የሚነግረን ነገር ኢየሱስ ራሱን መስጠቱን ነው ፡፡ አብ ልጁን ስለ እኛ ፍቅር ግድ ብሎት ለመስጠት ፍቃደኛ ሆኖ ፍቅሩን ገልጧል ወልደ እግዚአብሄር ኢየሱስ ክርስቶስም ስለ እኛ መዳን ራሱን ለመስጠት ፍቅሩን አሳይቷል ፡፡
ወደ እዚህ ምድር በመምጣት በስጋ በመገለጥ የሚታረድ በግ ሆነልን ታርዶ አዳነን ሞቶ ሕይወት ሰጠን በሸላቾች ፊት ዝም ብሎ ወደ አብ ፊት አቀረበን ርቀን የነበርን በእርሱ ሆነን ቀረብን ። ከሞት መቅሰፍት እንድንድን የሞት መቅሰፍትን ተቀበለልን !!
ሐዋሪያው ዮሃንስ በወንጌል መፅሐፉም በራዕይ መፅሐፍ ውስጥም ይህንን እውነት ይነግረናል ፡፡
‹‹መጽሐፉን ትወስድ ዘንድ ማኅተሞቹንም ትፈታ ዘንድ ይገባሃል፥ ታርደሃልና፥ በደምህም ለእግዚአብሔር ከነገድ ሁሉ ከቋንቋም ሁሉ ከወገንም ሁሉ ከሕዝብም ሁሉ ሰዎችን ዋጅተህ ለአምላካችን መንግሥትና ካህናት ይሆኑ ዘንድ አደረግሃቸው›› ራዕ 5፡9-10
‹‹እነሆ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ።›› ዮሃ 1፡29 ይላል ፡፡
ኢየሱስ በራሱ አንደበት እንዲህ ሲናገር ደግሞ እንሰማዋለን ፡፡
‹‹ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።›› ዮሃ 3፡14-16
ስለዚህ በድነታችን ወስጥ ያለውን የአብና የወልድን ስራ በእዚህ ክፍል እናያለን፡፡ ይህም እንዴት አይነት መፈቀር ነው ያስብላል፡፡ የሰው እጅ የለሌበት የመለኮት የማዳን አቅም የተገለጠበት ክርስቶስ በማመን የሚገን የዘላለም ህይወት የተቸረን እንዴት ብንፈቀር ነው ፡፡
ለመዳናችን ይህ ሆኗል
🔸አብ ልጁን ለመስጠት ፍቃዱ ሆኗል
🔸ወልድ ራሱን ለመስጠት ፈቅዶ አድርጎታል ።
ወገኖቼ በእዚህ ማረፍ እና መደሰት ይሁንልን ፡፡ ስለተወደዳችሁ ደስ ይበላችሁ አሜን !!!
ፀጋ ይብዛላችሁ
ይቀጥላል .......
በግሩም ድፋቅ❤
#ኑ፥ በነፃ ብሉ🙌
🙌🙌🙌🙌🙌🙌🙌
➾ያለ ምንም ድካም
➾ያለ ምንም ገንዘብ.....እንዲሁ በነፃ.....የተሰጠን የሕይወት እንጀራ ኢየሱስ ነው🙌 አሜን🙌
#ስለዚህ #ኑ፥ በነፃ ብሉ🙌
👇👇👇
#ምሳሌ 9
¹ ጥበብ ቤትዋን ሠራች፥ ሰባቱንም ምሰሶችዋን አቆመች።
² ፍሪዳዋን አረደች፥ የወይን ጠጅዋን ደባለቀች፥ ማዕድዋን አዘጋጀች።
³ ባሪያዎችዋን ልካ በከተማይቱ ከፍተኛ ስፍራ ላይ ጠራች፦
⁴ አላዋቂ የሆነ ወደዚህ ፈቀቅ ይበል፤ አእምሮ የጐደላቸውንም እንዲህ አለች፦
⁵ ኑ፥ እንጀራዬን ብሉ፥ የደባለቅሁትንም የወይን ጠጅ ጠጡ።
⁶ አላዋቂነትን ትታችሁ በሕይወት ኑሩ፥ በማስተዋልም መንገድ ሂዱ።
#እናንተ_የተጠማችሁ ሁሉ፥ ወደ ውኃ ኑ፥ ገንዘብም የሌላችሁ ኑና ግዙ ብሉም፤ ኑ ያለ ገንዘብም ያለ ዋጋም የወይን ጠጅና ወተት ግዙ።
— ኢሳይያስ 55፥1
ዮሐንስ 6
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁴⁸ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ።
⁴⁹ አባቶቻችሁ በምድረ በዳ መና በሉ ሞቱም፤
⁵⁰ ሰው ከእርሱ በልቶ እንዳይሞት ከሰማይ አሁን የወረደ እንጀራ ይህ ነው።
⁵¹ ከሰማይ የወረደ ሕያው እንጀራ እኔ ነኝ፤ ሰው ከዚህ እንጀራ ቢበላ ለዘላለም ይኖራል፤ እኔም ስለ ዓለም ሕይወት የምሰጠው እንጀራ ሥጋዬ ነው።
⁵² እንግዲህ አይሁድ፦ ይህ ሰው ሥጋውን ልንበላ ይሰጠን ዘንድ እንዴት ይችላል? ብለው እርስ በርሳቸው ተከራከሩ።
⁵³ ስለዚህ ኢየሱስ እንዲህ አላቸው፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ የሰውን ልጅ ሥጋ ካልበላችሁ ደሙንም ካልጠጣችሁ በራሳችሁ ሕይወት የላችሁም።
⁵⁴ ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፥ እኔም በመጨረሻው ቀን አስነሣዋለሁ።
⁵⁵ ሥጋዬ እውነተኛ መብል ደሜም እውነተኛ መጠጥ ነውና።
⁵⁶ ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ በእኔ ይኖራል እኔም በእርሱ እኖራለሁ።
#ኢየሱስ_ክርስቶስ በነፃ የተሰጠን የሕይወት እንጀራ ነው🙌
#ያለ ምንም ገንዘብ ከዚህ እንጀራ የሚበላ ለዘላለም ይኖራል🙌
#ሥጋውን የሚበላ ደሙንም የሚጠጣ ለዘላለም ይኖራል ያ ማለት በክርስቶስ ማመንን እንጅ የሰውን ደሙን መጠጣትን እና መብላት እና መጠጣትን አይደለም።
ፀጋው ይብዛላችሁ🙌🙌
AJEBA EMMANUEL UNITED CHURCH
►ወንድም ጥጋቡ አብርሃም 👈
