en
Feedback
Ethiopian Education//የኢትዮጵያ ትምህርት

Ethiopian Education//የኢትዮጵያ ትምህርት

Open in Telegram

ቻናሉን Join 👉https://t.me/mnistryofeducation ሀሳብ ለሀሳብ መለዋወጫ 👇👇👇👇 https://t.me/ethiopiancomunity

Show more
1 197
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
https://t.me/notcoin_bot?start=rp_34604495 🎁 +2.5k Notcoin as a first-time gift 🎁🎁🎁 +50k Notcoin if you have Telegram Premium @PremiumBot

የትምህርት ሚኒስቴር በአማራ ክልል ስላሉ ዩንቨርሲቲዎች የወሰነውን ውሳኔ መልሶ እንዲያጤነው የአማራ ተማሪዎች ማህበር ጠየቀ‼️ በአማራ ክልል የሚገኙ አስሩም የመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከጥ
የትምህርት ሚኒስቴር በአማራ ክልል ስላሉ ዩንቨርሲቲዎች የወሰነውን ውሳኔ መልሶ እንዲያጤነው የአማራ ተማሪዎች ማህበር ጠየቀ‼️ በአማራ ክልል የሚገኙ አስሩም የመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ እንዲጀምሩ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ ይታወሳል፡፡ ሚኒስቴሩ ይህንን ይበል እንጂ በክልሉ ያለው አሁናዊ ሁኔታ መደበኛ የመማር ማስተማር ስራዎች ለመስራት ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት አስቻይ አለመሆኑ ይገለጻል፡፡ የአማራ ክልል ተማሪዎች ማህበር በበኩሉ በክልሉ ያለው የፀጥታ ችግር ባለበት እንደቀጠለ መሆኑ እየታወቀ የትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ይጀምሩ ማለቱ ትክክል አይደለም  ውሳኔውን መልሶ እንዲያጤነው ይገባል ሲል ጠይቋል፡፡ የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አግማስ በየነ ተማሪዎቹ ለደህንነታቸው ዋስትና የሚሰጣቸው አካል በሌለበት ሁኔታ ወደ ተመደቡበት ትምህርት ተቋም መሄድ አዳጋች ነዉ ሲሉም አክለዋል፡፡ ከምንም ነገር በላይ የተማሪዎቹን ደህንነት መጠበቅ የሚቀድም በመሆኑ  ማህበሩ እንደ ተቋም ከሚኒስቴሩና ከትምህርት ተቋማት ጋር በመነጋገር ውሳኔውን ለማስቀልበስ የበኩሉን ጥረት እንደሚያደርግ አቶ አግማስ ገልጸዋል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ባሳለፍነው ሃሙስ ውሳኔውን ያሳለፈው ከክልሉ ኮማንድፖስት፣ የጸጥታ አደረጃጀቶችና የሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ካደረገ በኋላ መሆኑን ገልጿል። ከክልሉ ዩንቨርስቲዎች መካከል አንዱ የሆነው የባህር ዳር ዩንቨርሲም ተማሪዎቹ ሲመጡ ለደህንነታቸው ሃላፊነት መውሰድ ያለባቸው እራሳቸው ተማሪዎቹ እንደሆኑ በይፋ መግለጹ ይታወሳል፡፡ ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

በሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ተቋማዊ ለማድረግ የአምስት ዓመት ፕሮጀክት እየተተገበረ ነው። ትምህርት ሚኒስቴር ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን፣ ከአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ
በሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ተቋማዊ ለማድረግ የአምስት ዓመት ፕሮጀክት እየተተገበረ ነው። ትምህርት ሚኒስቴር ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን፣ ከአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ፣ ከሻያሾኔ እና ከሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመሆን "ኢ-ለርኒግ ከፍተኛ ትምህርትን ለማጎልበት" (e-SHE) የተሰኘ የአምስት ዓመት ፕሮጀክት እየተገበረ ይገኛል። ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ተቋማዊ ለማድረግና ለማጎልበት ግብ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል። ፕሮጀክቱ በአምስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት (አዲስ አበባ፣ ጅማ፣ ሀዋሳ፣ ድሬዳዋ እና ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲዎች) የዲጂታል ትምህርት የሚዘጋጅባቸው መልቲ-ሚድያ ስቱዲዮች እንዲገነቡ ያደርጋል። በፕሮጀክቱ የአምስት ዓመት ቆይታ 35 ሺህ መምህራን እና 800 ሺህ ተማሪዎች የዲጂታል ትምህርት አቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን ይወስዳሉ ተብሏል። ፕሮጀክቱ ሁለት ሞዴል የዲጂታል ኮርሶች ለማዘጋጀት እንደሚሠራም ተመላክቷል። በፕሮጀክቱ አማካኝነት የተዘጋጀው የኢ-ለርኒግ ትምህርት ፖሊሲ እና መመሪያ ተጠናቆ፥ ፖሊሲው በትምህርት ሚኒስቴር እንዲፀድቅ ሆኗል፡፡ ከአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የዲጂታል ትምህርት አዘገጃጀትና አሰጣጥን የተመለከተ ስልጠና ለመምህራን በመስጠት ላይ መሆኑም ተገልጿል። ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የዲጂታል ትምህርት እንዲሰጡ የሚያስችላቸው የLearning Management System (LMS) እና Student Information System (SIS) በመዘርጋት ላይ ነው ተብሏል። የዲጂታል ትምህርት ማስጀመሪያ የሚሆኑ ሁለት ሞዴል ኮርሶች ዝግጅት መጠናቀቁን ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል። #MoE @atc_news

የሥራና ክህሎት ሚኒስትር የሆኑት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የTVET የመቁረጫ ነጥብን ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳስታወቁት፣ ዜጎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚመጡት መ
+1
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር የሆኑት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የTVET የመቁረጫ ነጥብን ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳስታወቁት፣ ዜጎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚመጡት መሄጃ ስላጡ ሳይሆን ያላቸውን እምቅ አቅም አውጥተው መጠቀም እንዲችሉ ነው። ይህም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለዜጎች ዕድል ፈጣሪ አቅሞች እና ተጨማሪ አማራጭ የሚሰጡ ተቋማት ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡ ከባለፈው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ መሰረት ከዚህ ቀደም እስከ ደረጃ 5 ብቻ ተገድቦ የነበረው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የእድገት መሰላል እስከ ደረጃ 8 ድረስ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ 💥ይህም ፖሊሲው ደረጃ ስድስትን ከመጀመሪያ ድግሪ፣ ደረጃ ሰባትን ከማስተርስ እንዲሁም ደረጃ ስምንትን ከዶክትሬት ዲግሪ ትይዩ እንዲሆን አድርጓል፡፡ 💥በዚህ ዓመት የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ መግባት ቢፈልጉ በደረጃ 6 ገብተው መሰልጠን እንደሚያስችላቸው አመላክተዋል፡፡ በወጣው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ⚡️ደረጃ አንድ እና ሁለት 110,015 ⚡️በደረጃ ሦሰት እና አራት 412,557 ⚡️በደረጃ አምስት 110,015 ⚡️በደረጃ ስድስት ደግሞ 2000 የሚሆኑ ሰልጣኞችን ለቀመበል ዝግጅት ተደርጓል። 💥የ2016 የስልጠና ዘመን የተዘጋጀው መቁረጫ ነጥብ የ2015 ትምህርት እና የ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12 ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ላይ ተግባራዊ ይሆናል፡፡ 💥ከ2014 ዓ.ም በፊት ለነበሩ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ደግሞ በስልጠና ዘመኑ በነበረው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ይስተናገዳሉ፡፡ [ምስሎቹን ይመልከቱ] ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

በአዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር መመሪያ መሠረት 💥የ6ኛ ክፍል ክልላዊ የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር ሁኔታ ⚡️ በሁሉም የ
በአዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር መመሪያ መሠረት 💥የ6ኛ ክፍል ክልላዊ የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር ሁኔታ ⚡️ በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች 50% እና በላይ ያገኘ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛወራል፡፡ ⚡️ በ1 አንኳር ባልሆነ የትምህርት ዓይነት ከ50% በታች ውጤት ያመጣ ተማሪ አማካይ ውጤት 51% ካገኘ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛወራል፡፡ ⚡️ በ2 አንኳር ባልሆኑ የትምህርት ዓይነቶች ከ50% በታች ውጤት ያመጣ ተማሪ አማካይ ውጤት 52% ካገኘ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛወራል፡፡ ⚡️ በ3 አንኳር ያልሆኑ የትምህርት ዓይነቶች ከ50% በታች ውጤት ያመጣ ተማሪ 54% ካገኘ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛወራል፡፡ ⚡️ በአንኳር የትምህርት አይነቶች 50% እና በላይ ያላመጣ ተማሪ ወደ ቀጣዩ ክፍል አይዛወርም፡፡ [ ምስሉን ይመልከቱ ‼️] ➡️መመሪያው ከዚህ ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል የተባለ ሲሆን ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያው ተግባራዊ መደረግ የሚጀምርበትን ወር እና ቀን ለጊዜው አልተገለፀም። ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

“በጸጥታ ችግር ምክንያት 310 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ኾነዋል” የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ አሳሰበ። በሰላም መደፍረስ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የኾኑ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ለመመለስ በትኩረት መሥራታ እንደሚገባ የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ አሳሰበ። ከመስከረም ጀምሮ የትምህርት ዘመኑ የመማር ማስተማር ሂደቱ መጀመሩ ይታወቃል። የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ታደሰ ሸዋፈራው በሰጡን መረጃ “በጸጥታ ችግር ምክንያት በዞኑ 310 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ኾነዋል” ብለዋል። በአንደኛ ደረጃ ትምህር ቤት መማር የነበረባቸው 219 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ናቸው። በተመሳሳይ በሁለተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች መማር የነበረባቸው 57 ሺህ ተማሪዎች የመማር እድል አላገኙም። 33 ሺህ የቅድመ መደበኛ ተማሪዎችም ወደ ትምህት ቤት አልሄዱም። በአጠቃላይ በዘንድሮው የመማር ማስተማር ጅማሮ 500 ትምህርት ቤቶች ከመማር ማስተማር ተግባር ውጪ ናቸው። አንድ ትምህርት ቤት ደግሞ የተማሪዎች ምዝገባ እንኳን አላደረገም። የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ሂደት ውስጥ በርካታ ውስንነቶች መኖራቸው ይታወቃል። ከነዚህ ውስንነቶች መካከል የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ አናሳ መኾን፣ በሽፋንም ይሁን በጥራት የትምህርት መሠረተ ልማት በሚፈለገው ደረጃ አለመሟላት፣ የግብዓት እጥረት እንዲሁም በልዩ ልዩ መልኩ ሊገለጽ የሚችል የፍላጎት ማነስ ተጠቃሽ ናቸው። በተጠቀሱት እና ተያያዥ ችግሮች ምክንያት በየትምህርት ክፍሎቹ የሚመዘገበው ውጤት አመርቂ አይደለም። ወደ ቀጣዩ የትምህርት ደረጃ የማለፍ ምጣኔው አናሳ እየኾነ ስለመምጣቱም ከሰሞኑ ይፋ በተደረገው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መረዳት ይቻላል። አሁን ላይ በጸጥታ ችግሩ ምክንያት ታዳጊዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ደግሞ ችግሩን ‘በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ’ አድርጎታል። ባለሙያዎች በነጻነት ተንቀሳቅሰው የትምህርት ዘርፉን መደገፍ አለመቻላቸውንም አቶ ታደሰ ነግረውናል። “የሁሉም ነገር መሰረቱ ሰላም ነው” ያሉት ኀላፊው ሰላም የጠፋበት አካባቢ ከልማት እና ከእድገት የተነጠለ መኾኑ አይቀሬ ስለመኾኑ አስገንዝበዋል። ስለዚህ ከምንም ነገር ቅድሚያ ለሰላም መስራት ይገባል ነው ያሉት። የሰላምን ዋጋ በውል በመገንዘብ ስለሰላም እንሥራ፤ ተሻጋሪ አስተሳሰብ ያላቸውን ሀገር ተረካቢ ልጆች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱም ሁላችንም ጥረት እናድርግ ሲሉ ኀላፊው ጥሪ አቅርበዋል። #አሚኮ ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የከፍተኛ ትምህርት ማለፊያ ነጥብ ያመጡትንና ነባር ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተናገድ እንደሚችል አስታውቋል። በዩኒቨርሲቲው የሪጅስትራርና አልሙናይ ዳ
በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የከፍተኛ ትምህርት ማለፊያ ነጥብ ያመጡትንና ነባር ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተናገድ እንደሚችል አስታውቋል። በዩኒቨርሲቲው የሪጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክተር ገዛኸኝ አሰፋ (ዶ/ር ) ፣ የወሎ ዩኒቨርሲቲ የአይሲቲ ዳይሬክተር አቶ ጌታቸው ዋሴ እና በዩኒቨርሲቲው የቤተ ሙከራዎች አደረጃጀት ኮሚቴ ሰብሳቢና የኬሚስትሪ መምህር ዶ/ር ፈቃዱ ቸኮል እንደገለጹት ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ለመቀበል በሰው ሃይል፣ በቤተ ሙከራ፣ በቤተ መጻህፍት፣ በአይሲቲ መሰረተ ልማት እና በዘመናዊ የመማሪያ ክፍሎችን ዝግጅት ለመማር ማስተማሩ ምቹ ሁኔታዎች መሟላታቸውን ጠቅሰው አዲስ ተማሪዎች ወሎ ዩኒቨርሲቲን ቢመርጡ ብቁና ተወዳዳሪ ሆነው እንደሚወጡ ያላቸውን ሙሉ እምነት ገልጸዋል። የወሎ ዩኒቨርሲቲ የተማሪዎች አገልግሎት ዳይሬክተር አቶ ታምራት አበበ በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ለመቀበል በተማሪዎች መኝታ ክፍል፣ በምግብ ቤት እና በተማሪዎች ክሊኒክ በኩል አደረጃጀቱን በሰው ሃይል፣ በቁሳቁስና በአሰራር የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። በወሎ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት አወል ሰይድ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ ዩኒቨርሲቲው የተግባር ዩኒቨርሲቲ በመሆኑ ተማሪዎችን ለመቀበል ሲዘጋጅ በሰው ሃይል፣ በቤተ ሙከራ፣ በቤተ መጻህፍት፣ በመማሪያ ክፍል ዝግጅትና በሌሎችም አደረጃጀቶች የተሟላ መሆኑን ገልጸው ተማሪዎች በእውቀትም በክህሎትም ብቁና ተውዳዳሪ እንዲሆኑ በሚያስችል ደረጃ ላይ ያለ ዩኒቨርሲቲ መሆኑን ጠቁመዋል። ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

#የዩኒቨርስቲ ምደባ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ የተሰጠ ማብራሪያ የተማሪ ምደባ መስፈርቶች፡- 1. 1000 ለ
#የዩኒቨርስቲ ምደባ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ የተሰጠ ማብራሪያ የተማሪ ምደባ መስፈርቶች፡- 1. 1000 ለሚሆኑ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች፡- የምደባ ስርዓቱ በተፈጥሮም ሆነ በማህበራዊ ሳይንስ መስኮች 1000 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በመጀመሪያ የዩኒቨርስቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸው ምደባ የሚካሄድ ይሆናል። 2. ውጤት፡- የምደባ ስርዓቱ እያንዳንዱ ተማሪ ያስመዘገበውን አጠቃላይ ውጤት በምደባ ስርዓት ሂደት ውስጥ መለያ አድርጎ ይጠቀማል፡፡የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ሌሎች ተፈጻሚ የሚሆኑ ህግና ደንቦችን ባልጣሰ መልኩ ምርጫቸውን በመጠበቅ ረገድ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡ 3. የዩኒቨርሲቲ ምርጫ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የቅበላ አቅም ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ተማሪዎች 46 ዩኒቨርሲቲዎች ለምርጫ ቀርበውላቸዋል፡፡ መረጃው የተሰበሰበው https://portal.etherenet.edu.et ላይ ነው፡፡ 4. በተማሪዎች የተመረጡ ተቋማት ያላቸው የትምህርት ፕሮግራሞች ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች እና የተመረጡት ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የትምህርት ፕሮግራም መሰረት ያደረገ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ 5. ጾታ ፡- በተቋማት የጾታ ተዋጽኦን ለመጠበቅ በሚኖረው የምደባ ስርዓት የጾታ ተዋጽኦና ሚዛን እንዲጠበቅ ተደርጓል፣ እስከ ተራ ቁጥር 11 የተዘረዘረውን ሙሉ ማብራርያ ለማግኘት👇 Click ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

"በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ ያሉ ችግሮችን በግልፅ ተነጋግሮ በጋራ መፍታት ይገባል" ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለመምህራን ማህበር አባላት በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከ
"በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ ያሉ ችግሮችን በግልፅ ተነጋግሮ በጋራ መፍታት ይገባል" ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ለመምህራን ማህበር አባላት በሶማሌ ክልል ጅግጅጋ ከተማ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት፤ በትምህርት ሥርዓቱ ውስጥ ያሉ ችግሮችን በግልፅ ተነጋግሮ በጋራ መፍታት ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። "እንደ ትምህርት ሴክተር የትምህርት ሥርዓቱ ችግር ውስጥ ገብቷል" ያሉ ሲሆን፤ ይህንንም ችግር መቅረፍ ግዴታ መሆኑን አንስተዋል። "ባለፉት ኹለት ዓመታት በ12ኛ ክፍል ፈተና ያገኘነው ውጤት ምን ያህል የትምህርት ሥርዓቱ ችግር ያለበት መሆኑን ያሳየ ነው" ያሉት ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ችግሩን ሊፈታ የሚችል መፍትሄ ማስቀመጥና መሥራት ያስፈልጋል ብለዋል። በተለይም ጥራት ያለው ትምህርት አለማቅረብ፣ የፖለቲካና ትምህርት መጋባት የትምህርት አመራሩ የሚመደበው በብቃቱ ሳይሆን ለፖለቲካው ባለው ወገንተኝነት መሆኑ፣ ትምህርቱ በክልላዊነት መታጠሩ እና አጠቃላይ በሀገር ውስጥ የተፈጠረው የሞራል ውድቀት  የትምህርት ስርዓቱ ዋነኛ ችግሮች መሆናቸውን አንስተዋል። "በመሆኑም የትምህርት ሥርዓቱን በትክክል ለመቀየር እነዚህን ስብራቶች ከመሠረቱ ማስተካከል ይገባል" ሲሉ ተናግረዋል። በዚህም የግብረገብ ትምህርትን ከታች ጀምሮ መሥጠት፣ የትምህርት ቤቶችን መሠረተ ልማት ማሻሻል፣ ለትምህርት ቤት ርዕሳነ መምህራን የተለየ የሥልጠና ፕሮግራም አዘጋጅቶ መሥጠት፣ ለመምህራን ስልጠና ከትምህርት ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ አምስት ዩኒቨርሲቲዎች የትምህርት ኮሌጅ እንዲከፍቱ የማድረግ ሥራ እየተሠራ መሆኑንም አንስተዋል።    

ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የሲስኮ (CISCO NETWORKING) አካዳሚ ስልጠና የማስጀመር ፕሮግራም አካሄደ። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጁ ዳይሬክቶሬት ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር
+4
ጂንካ ዩኒቨርሲቲ የሲስኮ (CISCO NETWORKING) አካዳሚ ስልጠና የማስጀመር ፕሮግራም አካሄደ። የጂንካ ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽን ቴክኖሎጁ ዳይሬክቶሬት ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በሲስኮ ኔትዎርኪንግ አካዳሚ ስልጠና ለመስጠት ሰልጣኞችን ሲመዘግብ ቆይቶ በዛሬው ዕለት የማስጀመሪያ ፕሮግራም አካሂዷል። በስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራሙን ላይ እንደተገለፀው ተመጣጣኝ በሆነ ወጪ ስልጠናውን በማግኘት የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ክህሎት ክፍተቶችን ለመሙላት እንደሚያግዝና አሁን ላይ በዓለማችን በስፋት እየተፈፀመ ከሚገኘው የሳይበር ጥቃት ለመጠበቅና የራሳችንንም መረጃ ከመሰል ጥቃት ለመከላከል ይህ ስልጠና ጉልህ ሚና የሚጫወት ከመሆኑም ባሻገር ከስልጠናው በኋላ የሚገኘው ሰርትፊኬትም የስራ ዕድል ተፈላጊነትን ከፍ እንደሚያደርግ ተገልጿል። ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

የእቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅና ሰጠ‼️ የእቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ ትምህርት ቤት በ 2015 ዓ. ም የ
+2
የእቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ ትምህርት ቤት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች እውቅና ሰጠ‼️ የእቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ ትምህርት ቤት በ 2015 ዓ. ም የ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት በማምጣት ላለፉ ተማሪዎች የእውቅናና ሽኝት መርሃ ግብር አካሂደዋል :: የእቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህርት ወ /ሮ ሃና ፀጋዬ ለተማሪዎች መምህራንና ወላጆች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን የእውቅና መድረኩ መዘጋጀትም በ2016 ሀገር አቀፍ ፈተናውን ለሚወስዱ ተማሪዎች ልምድ ለማካፈል እንደሚጠቅምና ትምህርት ቤቱም በ 2016 ዓ. ም ሁሉንም ተማሪ በከፍተኛ ውጤት ለማሳለፍ በቂ ዝግጅት ለማድረግ እንደሚረዳ ተናግረዋል :: ወ /ሮ ሃና ተማሪዎች ከአንዱ የሕይወት ምእራፍ ወደቀጣዩ የሕይወት ምእራፍ መሸጋገራቸው ሳያዘናጋቸው በዚህ ትምህርት ቤት ያሳዩ የነበረውን ስነ-ምግባር ይዘው በዩኒቨርስቲ በሚገጥማችው ፈተና እየፀኑ ኢትዮጵያን የሚረከቡ ሴቶች መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል :: አያይዘውም በአራት ዓመት የትምህርት ቤቱ ቆይታቸው ላሳዩት መልካም ስነ-ምግባር እና ላገኙት ከፍተኛ ውጤት ምስጋና አቅርበዋል፡፡ መምህራንና ወላጆችም ለተገኝው ስኬት የነበራቸው አስተዋፅኦ ከፍተኛ እንደነበር አስታውሰዉ ሲያደርጉ ለነበረው ድጋፍና ክትትል ምስጋና አቅርበዋል :: ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

#መረጃ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከተፈተኑት ተማሪዎች መካከል 164 ሺ የሚሆኑ ተማሪዎች የአቅም ማሻሻያ ወይም ሬሚዳል የሚወስዱ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር ገለፀ፡፡ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት 👇👇👇👇👇👇👇 https://youtu.be/37Woeiyaxgs?si=qHSU0l-FHIdTWSzS

የቴክኒክና ሙያ ተቋማት 600 ሺህ ተማሪዎችን ለመቀበል ተዘጋጅተዋል፡፡ 12ኛ ክፍል ካጠናቀቁ ተማሪዎች ውስጥ በዘንድሮው ዓመት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚገቡ 600 ሺህ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት 600 ሺህ ተማሪዎችን ለመቀበል ተዘጋጅተዋል፡፡ 12ኛ ክፍል ካጠናቀቁ ተማሪዎች ውስጥ በዘንድሮው ዓመት በቴክኒክና ሙያ ተቋማት የሚገቡ 600 ሺህ ተማሪዎችን ለመቀበል ዝግጅት መደረጉን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታውቋል። የትምህርት ተቋማቱ ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ የ2016 ዓ.ም የቴክኒክና ሙያ ሠልጣኞችን እንደሚቀበሉ በሚኒስቴሩ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ለኢፕድ ተናግረዋል። በዘንድሮው ዓመት 600 ሺህ ተማሪዎችን ተቀብሎ ለማሠልጠን የሚያስችል በቂ የትምህርት ግብዓት ዝግጅት እየተደረገ ነው ብለዋል። በቴክኒክና ሙያ በመደበኛ ፕሮግራም ከሚሰለጥኑ በተጨማሪ በአጫጭር ስልጠናዎች ሁለት ሚሊዮን ዜጎች ስልጠና ለመስጠት መታቀዱንም ገልጸዋል። በኢትዮጵያ ከ700 በላይ የመንግሥት እና ከ900 በላይ የግል የቴክኒክና ሙያ ትምህርት ተቋማት እንዳሉ የኢፕድ ዘገባ ጠቁሟል።