cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Ethiopian Education//የኢትዮጵያ ትምህርት

ቻናሉን Join 👉https://t.me/mnistryofeducation ሀሳብ ለሀሳብ መለዋወጫ 👇👇👇👇 https://t.me/ethiopiancomunity

Show more
Advertising posts
1 197
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+1430 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

https://t.me/notcoin_bot?start=rp_34604495 🎁 +2.5k Notcoin as a first-time gift 🎁🎁🎁 +50k Notcoin if you have Telegram Premium @PremiumBot
Show all...
Notcoin

Probably nothing @notcoin

👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
የትምህርት ሚኒስቴር በአማራ ክልል ስላሉ ዩንቨርሲቲዎች የወሰነውን ውሳኔ መልሶ እንዲያጤነው የአማራ ተማሪዎች ማህበር ጠየቀ‼️ በአማራ ክልል የሚገኙ አስሩም የመንግሥት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከጥር 1 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ባሉት ሁለት ሳምንታት መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ እንዲጀምሩ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ ይታወሳል፡፡ ሚኒስቴሩ ይህንን ይበል እንጂ በክልሉ ያለው አሁናዊ ሁኔታ መደበኛ የመማር ማስተማር ስራዎች ለመስራት ባለው የፀጥታ ችግር ምክንያት አስቻይ አለመሆኑ ይገለጻል፡፡ የአማራ ክልል ተማሪዎች ማህበር በበኩሉ በክልሉ ያለው የፀጥታ ችግር ባለበት እንደቀጠለ መሆኑ እየታወቀ የትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ይጀምሩ ማለቱ ትክክል አይደለም  ውሳኔውን መልሶ እንዲያጤነው ይገባል ሲል ጠይቋል፡፡ የማህበሩ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አግማስ በየነ ተማሪዎቹ ለደህንነታቸው ዋስትና የሚሰጣቸው አካል በሌለበት ሁኔታ ወደ ተመደቡበት ትምህርት ተቋም መሄድ አዳጋች ነዉ ሲሉም አክለዋል፡፡ ከምንም ነገር በላይ የተማሪዎቹን ደህንነት መጠበቅ የሚቀድም በመሆኑ  ማህበሩ እንደ ተቋም ከሚኒስቴሩና ከትምህርት ተቋማት ጋር በመነጋገር ውሳኔውን ለማስቀልበስ የበኩሉን ጥረት እንደሚያደርግ አቶ አግማስ ገልጸዋል፡፡ የትምህርት ሚኒስቴር ባሳለፍነው ሃሙስ ውሳኔውን ያሳለፈው ከክልሉ ኮማንድፖስት፣ የጸጥታ አደረጃጀቶችና የሚመለከታቸዉ አካላት ጋር ተከታታይ ውይይቶችን ካደረገ በኋላ መሆኑን ገልጿል። ከክልሉ ዩንቨርስቲዎች መካከል አንዱ የሆነው የባህር ዳር ዩንቨርሲም ተማሪዎቹ ሲመጡ ለደህንነታቸው ሃላፊነት መውሰድ ያለባቸው እራሳቸው ተማሪዎቹ እንደሆኑ በይፋ መግለጹ ይታወሳል፡፡ ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news
Show all...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
በሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ተቋማዊ ለማድረግ የአምስት ዓመት ፕሮጀክት እየተተገበረ ነው። ትምህርት ሚኒስቴር ከማስተርካርድ ፋውንዴሽን፣ ከአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ፣ ከሻያሾኔ እና ከሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመሆን "ኢ-ለርኒግ ከፍተኛ ትምህርትን ለማጎልበት" (e-SHE) የተሰኘ የአምስት ዓመት ፕሮጀክት እየተገበረ ይገኛል። ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የዲጂታል ትምህርትን ተቋማዊ ለማድረግና ለማጎልበት ግብ ያደረገ መሆኑ ተገልጿል። ፕሮጀክቱ በአምስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት (አዲስ አበባ፣ ጅማ፣ ሀዋሳ፣ ድሬዳዋ እና ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲዎች) የዲጂታል ትምህርት የሚዘጋጅባቸው መልቲ-ሚድያ ስቱዲዮች እንዲገነቡ ያደርጋል። በፕሮጀክቱ የአምስት ዓመት ቆይታ 35 ሺህ መምህራን እና 800 ሺህ ተማሪዎች የዲጂታል ትምህርት አቅም ግንባታ ሥልጠናዎችን ይወስዳሉ ተብሏል። ፕሮጀክቱ ሁለት ሞዴል የዲጂታል ኮርሶች ለማዘጋጀት እንደሚሠራም ተመላክቷል። በፕሮጀክቱ አማካኝነት የተዘጋጀው የኢ-ለርኒግ ትምህርት ፖሊሲ እና መመሪያ ተጠናቆ፥ ፖሊሲው በትምህርት ሚኒስቴር እንዲፀድቅ ሆኗል፡፡ ከአሪዞና ስቴት ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የዲጂታል ትምህርት አዘገጃጀትና አሰጣጥን የተመለከተ ስልጠና ለመምህራን በመስጠት ላይ መሆኑም ተገልጿል። ከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የዲጂታል ትምህርት እንዲሰጡ የሚያስችላቸው የLearning Management System (LMS) እና Student Information System (SIS) በመዘርጋት ላይ ነው ተብሏል። የዲጂታል ትምህርት ማስጀመሪያ የሚሆኑ ሁለት ሞዴል ኮርሶች ዝግጅት መጠናቀቁን ከትምህርት ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል። #MoE @atc_news
Show all...
👍 4
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር የሆኑት ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል የTVET የመቁረጫ ነጥብን ይፋ ለማድረግ በተዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንዳስታወቁት፣ ዜጎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት የሚመጡት መሄጃ ስላጡ ሳይሆን ያላቸውን እምቅ አቅም አውጥተው መጠቀም እንዲችሉ ነው። ይህም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ለዜጎች ዕድል ፈጣሪ አቅሞች እና ተጨማሪ አማራጭ የሚሰጡ ተቋማት ያደርጋቸዋል ብለዋል፡፡ ከባለፈው ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ እየተደረገ ባለው አዲሱ የትምህርትና ሥልጠና ፖሊሲ መሰረት ከዚህ ቀደም እስከ ደረጃ 5 ብቻ ተገድቦ የነበረው የቴክኒክና ሙያ ስልጠና የእድገት መሰላል እስከ ደረጃ 8 ድረስ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ 💥ይህም ፖሊሲው ደረጃ ስድስትን ከመጀመሪያ ድግሪ፣ ደረጃ ሰባትን ከማስተርስ እንዲሁም ደረጃ ስምንትን ከዶክትሬት ዲግሪ ትይዩ እንዲሆን አድርጓል፡፡ 💥በዚህ ዓመት የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ነጥብ ያመጡ ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ መግባት ቢፈልጉ በደረጃ 6 ገብተው መሰልጠን እንደሚያስችላቸው አመላክተዋል፡፡ በወጣው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ⚡️ደረጃ አንድ እና ሁለት 110,015 ⚡️በደረጃ ሦሰት እና አራት 412,557 ⚡️በደረጃ አምስት 110,015 ⚡️በደረጃ ስድስት ደግሞ 2000 የሚሆኑ ሰልጣኞችን ለቀመበል ዝግጅት ተደርጓል። 💥የ2016 የስልጠና ዘመን የተዘጋጀው መቁረጫ ነጥብ የ2015 ትምህርት እና የ2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12 ኛ ክፍል ማጠቃለያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ላይ ተግባራዊ ይሆናል፡፡ 💥ከ2014 ዓ.ም በፊት ለነበሩ የ12ኛ ክፍል ተፈታኞች ደግሞ በስልጠና ዘመኑ በነበረው መቁረጫ ነጥብ መሰረት ይስተናገዳሉ፡፡ [ምስሎቹን ይመልከቱ] ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
በአዲሱ የትምህርት ሚኒስቴር የአጠቃላይ ትምህርት የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር መመሪያ መሠረት 💥የ6ኛ ክፍል ክልላዊ የተማሪዎች ምዘና እና የክፍል ክፍል ዝውውር ሁኔታ ⚡️ በሁሉም የትምህርት ዓይነቶች 50% እና በላይ ያገኘ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛወራል፡፡ ⚡️ በ1 አንኳር ባልሆነ የትምህርት ዓይነት ከ50% በታች ውጤት ያመጣ ተማሪ አማካይ ውጤት 51% ካገኘ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛወራል፡፡ ⚡️ በ2 አንኳር ባልሆኑ የትምህርት ዓይነቶች ከ50% በታች ውጤት ያመጣ ተማሪ አማካይ ውጤት 52% ካገኘ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛወራል፡፡ ⚡️ በ3 አንኳር ያልሆኑ የትምህርት ዓይነቶች ከ50% በታች ውጤት ያመጣ ተማሪ 54% ካገኘ ወደ ቀጣዩ ክፍል ይዛወራል፡፡ ⚡️ በአንኳር የትምህርት አይነቶች 50% እና በላይ ያላመጣ ተማሪ ወደ ቀጣዩ ክፍል አይዛወርም፡፡ [ ምስሉን ይመልከቱ ‼️] ➡️መመሪያው ከዚህ ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል የተባለ ሲሆን ትምህርት ሚኒስቴር መመሪያው ተግባራዊ መደረግ የሚጀምርበትን ወር እና ቀን ለጊዜው አልተገለፀም። ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news
Show all...
“በጸጥታ ችግር ምክንያት 310 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ኾነዋል” የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ አሳሰበ። በሰላም መደፍረስ ምክንያት ከትምህርት ገበታ ውጪ የኾኑ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት ለመመለስ በትኩረት መሥራታ እንደሚገባ የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ አሳሰበ። ከመስከረም ጀምሮ የትምህርት ዘመኑ የመማር ማስተማር ሂደቱ መጀመሩ ይታወቃል። የሰሜን ሸዋ ዞን ትምህርት መምሪያ ኀላፊ ታደሰ ሸዋፈራው በሰጡን መረጃ “በጸጥታ ችግር ምክንያት በዞኑ 310 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ኾነዋል” ብለዋል። በአንደኛ ደረጃ ትምህር ቤት መማር የነበረባቸው 219 ሺህ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ ናቸው። በተመሳሳይ በሁለተኛና መሰናዶ ትምህርት ቤቶች መማር የነበረባቸው 57 ሺህ ተማሪዎች የመማር እድል አላገኙም። 33 ሺህ የቅድመ መደበኛ ተማሪዎችም ወደ ትምህት ቤት አልሄዱም። በአጠቃላይ በዘንድሮው የመማር ማስተማር ጅማሮ 500 ትምህርት ቤቶች ከመማር ማስተማር ተግባር ውጪ ናቸው። አንድ ትምህርት ቤት ደግሞ የተማሪዎች ምዝገባ እንኳን አላደረገም። የትምህርት ጥራትን በማረጋገጥ ሂደት ውስጥ በርካታ ውስንነቶች መኖራቸው ይታወቃል። ከነዚህ ውስንነቶች መካከል የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ አናሳ መኾን፣ በሽፋንም ይሁን በጥራት የትምህርት መሠረተ ልማት በሚፈለገው ደረጃ አለመሟላት፣ የግብዓት እጥረት እንዲሁም በልዩ ልዩ መልኩ ሊገለጽ የሚችል የፍላጎት ማነስ ተጠቃሽ ናቸው። በተጠቀሱት እና ተያያዥ ችግሮች ምክንያት በየትምህርት ክፍሎቹ የሚመዘገበው ውጤት አመርቂ አይደለም። ወደ ቀጣዩ የትምህርት ደረጃ የማለፍ ምጣኔው አናሳ እየኾነ ስለመምጣቱም ከሰሞኑ ይፋ በተደረገው የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት መረዳት ይቻላል። አሁን ላይ በጸጥታ ችግሩ ምክንያት ታዳጊዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸው ደግሞ ችግሩን ‘በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ’ አድርጎታል። ባለሙያዎች በነጻነት ተንቀሳቅሰው የትምህርት ዘርፉን መደገፍ አለመቻላቸውንም አቶ ታደሰ ነግረውናል። “የሁሉም ነገር መሰረቱ ሰላም ነው” ያሉት ኀላፊው ሰላም የጠፋበት አካባቢ ከልማት እና ከእድገት የተነጠለ መኾኑ አይቀሬ ስለመኾኑ አስገንዝበዋል። ስለዚህ ከምንም ነገር ቅድሚያ ለሰላም መስራት ይገባል ነው ያሉት። የሰላምን ዋጋ በውል በመገንዘብ ስለሰላም እንሥራ፤ ተሻጋሪ አስተሳሰብ ያላቸውን ሀገር ተረካቢ ልጆች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱም ሁላችንም ጥረት እናድርግ ሲሉ ኀላፊው ጥሪ አቅርበዋል። #አሚኮ ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news
Show all...
👍 3
Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.