cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Bilaluna Edris (Xuqal.X.Qafarey)

♡_ወደ መልካም ነገር ያመላከተ ሰው የሰራ ሰውን አጅር ያህል ያገኛል"(አመላካች የሰሪውን ምንዳ ያገኛል)(ﷺ) « ከናንተም ወደ በጎ ነገር የሚጠሩ ፣ በመልካም ስራም የሚያዙ ከክፉ ነገርም የሚከለክሉ ሕዝቦች ይኑሩ» ﷻ                  ቁርኣን[ 3:104 ] መወያያ ግሩፓችን ☞ https://t.me/+1qmNqy265XoyNGY0

Show more
Advertising posts
449
Subscribers
+224 hours
+107 days
+4630 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
ለተባበራችሁ ወንድም እና እህቶች ሁሉ አላህ ምንዳችሁን በሰፊው ይክፈላችሁ እናመሰግናለን
681Loading...
02
በስም ሳይሆን በመሆን፤በምላስ ሳይሆን በተግባር እንዴት ወንድ እንደሚኾን ያሳዩ ድምቅ መሪ።ሰዎች ግማሾቹ በዐረባዊ ብሔረተኝነት፤ሌሎቹንም በቡድናዊ ወገንተኝነት ተቆላልፈው በታሰሩበት ሰዓት ፐርሺያነታቸውና የሺዓ ቡድን ተከታይነታቸው ዐረብና የሱና ተከታይ የሆኑት የገዛ ወንድሞቻቸውን ከመርዳት እንደማያግዳቸው ያሳዩ ድንቅ ህዝቦች ሐገር መሪ! ሰይድ ኢብራሂም ከስማቸው ድርሻቸውን የወሰዱ ናቸው።በአንዱ ሞት የማይሞት የኡመት ስም ነው! አሏህ በሰፊው ራሕመቱ ይቀበሎት ሰይድ ኢብራሂም ረኢሲ የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
772Loading...
03
«አንድ ሰው  ከሚኖረው መልካም ነገራት ሁሉ  በላጩ በመከራ የማይንበረከክ ልብን ማግኘት  ዋነኛው ነው» ©أدهم شرقاوي
771Loading...
04
የአፋልጉኝ ጥሪ...... በአፋር ክልል ከወላጆቹ ጋር በሎጊያ ከተማ የሚኖረው ህፃን አፍረሂም ሙሀመድ አብዱ ዛሬ ጠዋት አካባቢ ወላጆቹ ለመልእክት ወደ ሱቅ ልከውት እስካሁን አልተመለሰም። ህፃን አፍረሂም ሙሀመድን ያየ ካለ ከታች ባለው ስልክ ቁጥር (+251910090080)ደውላችሁ ብታሳውቁን ወሮታውን ከፋይ ነን። ቤተሰቦቹ ሼር ሼር ሼር
781Loading...
05
#BREAKING የኢራኑ ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ፣የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሁሰይን አሚር አብዱላሂ እና አብሯቸው የነበረው የልዑካን ቡድን በሙሉ በሄሊኮፕተር አደጋው መሞታቸውን የኢራን መንግስት ቴሌቭዥን አስታውቋል! #አልጀዚራ የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
963Loading...
06
🇮🇷🇺🇸 የአሜሪካ አየር ኃይል ካርጎ የሆነው C-17 ግዙፍ ወታደራዊ አይሮፕላን ከዓመት በላይ ጊዜ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ አዘርባጃን ባኩ በዛሬው ዕለት ማረፉ ተሰምቷል።   የአሜሪካው ወታደራዊ ካርጎ የኢራኑ ፕሬዝዳንት ራይሲ የተሳፈረበት ሄሊኮፕተር አዘርባጃንን ከመልቀቁ እና ከተከሰከሰበት ጊዜ ጋር መገጣጠሙ ጥያቄዎችን እየፈጠረ ይገኛል። #Ethiopia #Raisi #Iran #Helicoptercrash #SearchOperation #RescueOperation የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
952Loading...
07
▪️የኢራኑ ፕሬዝዳንት ራይሲ ከሄልኮፕተር አደጋው ጥቂት ቀደም ብሎ የነበሩበትን የሚያሳይ ቪዲዮ፤ እንዲሁም     - ከአደጋው በኋላ ለአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የሄልኮፕተር ፍለጋ ስራቸውን አስቸጋሪ ያደረገው የአየር ሁኔታ #Ethiopia #Raisi #Iran #Helicoptercrash #SearchOperation #RescueOperation የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
932Loading...
08
“የኢራኑ ፕሬዝዳንት ሄሊኮፕተር የወደቀችው በመጥፎ የአየር ሁኔታ ምክንያት ሲሆን ተሳፋሪዎቹ መቁሰላቸውን ወይም መሞታቸውን ማረጋገጥ አልተቻለም። በሄሊኮፕተሩ ላይ የተሳፈሩት ሰዎች ሞተዋል ወይም ቆስለዋል የሚሉ ዘገባዎች ያልተረጋገጡ ስለሆኑ አስተማማኝ አይደሉም!” #መህርአጄንሲ(ኢራን)
782Loading...
09
“በአስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እና በቀላሉ ሊደረስበት በማይችል ተራራማ አካባቢ የፍለጋው ስራ ቀጥሏል! - ተጨማሪ የነፍስ አድን ቡድኖች ወደ አደጋው ቦታ እየላክን ነው!” የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ! #አልጀዚራ
742Loading...
10
በምስራቅ አዘርባጃን ግዛት አደጋ በደረሰባት ሄሊኮፕተር ላይ የኢራኑ ፕሬዝዳንት ከውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ እና ከበርካታ ባለስልጣናት ጋር #የመጨረሻ እይታ! #አልጀዚራ
763Loading...
11
የኢራን ባለስልጣን ለሮይተርስ እንደተናገሩት የሄሊኮፕተር አደጋውን ተከትሎ የፕሬዚዳንቱ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ህይወት አደጋ ላይ ነው። #አልጀዚራ
711Loading...
12
#BREAKING! የኢራኑን ፕሬዝደንት ጭኖ በነበረ ኮንቮይ ላይ የነበረ ሄሊኮፕተር አደጋ ደረሰበት! #ኢራን ቲቪ
741Loading...
13
Media files
801Loading...
14
ኢና ሊላህ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን ! በጎንደር በግፍ የተገደሉት የመስጂድ ኢማም ሸይኽ ሲራጅ አብድሬ እኚህ ናቸዉ! በአማራ ክልል በማዕከላዊ ጎንደር ደንቢያ ወረዳ አየንባ ቀበሌ የመስጂድ ኢማም የሆኑት ሸይኽ ሲራጅ አብድሬ በግፍ ተገድለዋል:: አላህ(ሱ.ወ) ይዘንላቸዉ። አሚን🤲
933Loading...
15
በአላህ አምናችሁ፣በሱ እርግጠኛ ሆናችሁ ተኙ። እሱ በአንዲት ምሽት ብዙ ነገር ይቀይራል። ብዙ ብዙ ችግራችሁ ተፈትቶ የምታድሩበት ምሽት ይሁን 🤗 የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
953Loading...
16
Media files
892Loading...
17
#ለፈገግታ ✍ሚስት እቤት ቁጭ ብላ ለባለቤቷ text አደረገች🤳 "ከቢሮ ስትወጣ እግረመንገድህን ከጉሊት አትክልት ይዘህ መምጣትህን እንዳትረሳ፡ ሳራም ሰላም እያለችህ ነው ባል--"ሳራ ደግሞ ማናት?" ሚስት--"ዝም ብዬ ነው ባክህ ሚሴጁን ማየትህን ለማረጋገጥ ነው ባል ተበሳጭቶ ትንሽ ካሰበ በኋላ text አደረገ፡ "ግን እኮ እኔ ከሳራ ጋ ነው ያለሁት፡አንቺ ስለየትኛዋ ሳራ ነው ያወራሽው?" ሚስት--"የት ነው ያለሀው?" ባል---"ጉሊቱ ጋ ነዋ" ሚስት---"አሁኑኑ መጣሁ" ከ10 ደቂቃ በኋላ፡ ሚስት---"የቱ ጋ ነህ ጉሊቱ ጋ ደርሻለሁ" ባል--" ምን ጥሩ ነዉ ቢሮ ነኝ በቃ የፈለግሽውን አትክልት ገዝተሽ ቤት ሂጂ ማታ መጣው"😂😜 የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
1103Loading...
18
ቱርክ ወደ መስጊድነት የቀየረችው ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ቱርክ ወደ መስጊድነት የተቀየረችውን ጥንታዊት የቾራ ቤተ ክርስቲያን ለእስልምና እምነት ተከተዮች ክፍት አድርጋለች። ቤተ ክርስቲያኒቱ ለ70 ዓመታት በሙዝየምነት ስታገለግል የቆየች ሲሆን፤ በፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ውሳኔ ነው ወደ መስጊደነት ተለውጣ ክፍት የተደረገችው። ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ቤተከስርቲያኒቷ ወደ መስጊደነት እንድትለወጥ ውሳኔ ያሳለፉት በፈረንጆች 2020 ሲሆን፤ በእድሳት ላይ ቆይታ ነው ባሳለፍነው ሳምት ለእስልምና እምነት ተከተዮች ክፍት የተደረገችው። ቾረሰ ቤተ ክርስቲን በ4ኛው ክፍለ ዘመን የተገነባች ሲሆን፤ በኦቶማን ቱርክ ዘመን ወደ መስጊነነት ተቀይራ ቆይታለች፤ ከ1945 ጀምሮ ደግሞ ለ70 ዓመታት ሙዚየም ሆና ቆይታለች። ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ጥንዊ ቤተ ክርስቲያን ወደ መስጊድ ሲለውጠ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ ሲሆን፤ ከዚህ ቀደም በዓለም ታዋቂ የነበረች ሃጊያ ሶፊያ ቤተ ክርስቲያንን ወደ መስጊድነት እንዲለወጥ አድርገዋል። Via Alain Amharic የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
742Loading...
19
ለራሷ ዱዓ ማድረግ አስታውሳ አታውቅም። ለልጆቿ እንጂ።በልጅነት ወቅታቸውም ትልቅ ሆነዉም ለልጆቿ ብላ ራሷን የረሳች ከእናት ዉጪ ማን አለ? ❤
714Loading...
20
Media files
771Loading...
21
Media files
771Loading...
22
ብቻውን ሲዋጋ ውሎ ተሰዋ።  አራት ጥሎ ወደቀ።  ኢናሊላሂወኢናኢለይሂ ራጁኡን በጎንደር  በወገራ ወረዳ  ጉንትር ቀበሌ  አቶ ካሳው ሲሳይ አብድቃድር ለረጅም ሥዓት ከተዋጋ በሗላ   ከቀኑ በስምንት ሰዓት  ተሠዉቷል፡፡ ቦታ እየቀያየረ አላስጠጋ ብሎ ለረዥም ሰአት የተዋጋ ሲሆን በወቅቱ የነበረው መሪያቸውን ጨምሮ አራት ፋኖ ጥሎ ጥይት ሲጨርስ ተሰዋ።  ፋኖ በወሰደው የበቀል ርምጃ    1. አንድ ቤት ሙሉ ንብረት እንደያዘ ተቃጥሏል    2.400ሽ ብር የሚገመት ሁለት ክላሽ ኮፕ መሣሪያ    3.50 ሽ የሚገመት አምሥት የፍየል ሙክት    4. 500ሽ የሚገመት ጤፍ ፡ እና አብሽ     5.160ሽ ብር የሚገመቱ ሁለት በሬዎች ፡፡ በአጠቃላይ 1,110,000 ሽ ብር የተቃጠለውን ቤቱና ንብረቱን ሣይጨምር ዘርፈዋል፡፡ Via Adugnaw Muche የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
763Loading...
23
ኢና ሊላህ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን ! ከጎንደር ከተማ ወደ መተማ ስንሄድ በማእከላዊ ጎንደር ደንቢያ ወረዳ አየንባ ቀበሌ ሸኽ ሲራጅ የመስጅዱ ኢማም መግሪብ ሰላት ሰግደዉ ሲወጡ በታጣቂዎች ተይዘዉ ከሄዱ በሃላ በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ደብድበዉ ገድለዋቸዋል ። ሸኽ ሲራጅ በዛዉ መስጅ ለረጅም አመት ደረሳዎችን እስከዛሬዋ እለት ያቀሩ የነበሩ ሲሆን መግሪብን አሰግደዉ ሲወጡ ታጣቂዎቹ እየጎተቱ የወሰዷቸዉ መሆኑና ይህን የሀገር ሽማግሌ የሁሉ አባት የሆኑት የመስጅድ ታላቁን ሸኽ ገድለዉ ጥለዋቸዉ እንደሄዱ ሰማን ። በተፈጠረዉ ነገር በጣም እያዘንኩ ሸኻችን አሏህ ከሸሂዶች ተርታ እንዲያደርጋቸዉ እየለመንኩ ለቤተሰቦቻቸዉ መፅናናትን እመኛለሁ ። ©Abdurahman Sultan የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
712Loading...
24
ሀገራዊ ምክክሩ ሙስሊሙን ያገለለ የተሳታፊ ልየታ እንደተደረገበት ተገለፀ! … (ሀሩን ሚድያ፦ግንቦት8/2016፤ አዲስ አበባ ) … በኢትዮጲያ በመጪው ለሚካሄደው ሀገራዊ ምክክር የሙስሊሙ ቁጥር አነሳ በመሆኑ የተሳታፊዎች ልየታ  በድጋሚ እንዲካሄድ እና በሙስሊሙ በኩል የቀረቡ አጀንዳዎች በሀገራዊ ምክክሩ እንዲካተቱ  የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ጥሪ አቀረበ። … ጠቅላይ ምክር ቤቱ ባቀረበው ጥያቄ የሙስሊሞች ተሳትፎ በሕዝባችን ቁጥር ልክ መሆን ያለበት በመሆኑ የተሳታፊዎችና የአወያዮች ቁጥር በዚሁ መሠረት በኮሚሽኑ "የአካታችነት መርህ መሠረት ጠ/ም/ቤቱ ያቀረበውን የሕዝበ ሙስሊሙ የምክክር እጀንዳዎች ለጉባኤው ለማሰማት፤ ለማብራራት የሚችሉ ተገቢ ቁጥር ያላቸው ሙስሊም ተወካዮች እንዲካተቱ ይቻል ዘንድ የህዝብ ጥያቄዎች ከፍተኛ እየሆነብን በመምጣቱ ሥብጥሩ በፍትሃዊነት እንደገና እንዲቃኝ ለሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የበላይ ጠባቂ ለሆኑት  ለፕሮፌሰር መስፍን አርአያ በፃፈው ደብዳቤ ጠይቋል። … በኢትዮጵያ የተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ መግባባት ለመፍጠር ይችላል የተባለው የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዋጅ ተቋቁሞ የተለያዩ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱ የሚታወስ ሲሆን  ኮሚሽኑ ከትግራይ ክልል ውጪ እና ግጭት ባለባቸው የአማራ እና የኦሮሚያ ክልልች አንዳንድ አካባቢዎችን ሳያካትት በ10 ክልሎችን እና የከተማ አስተዳደሮች ለምክክሩ የሚሳተፉ አካላትን ልየታ ቢያካሂድም የሙስሊሙ ቁጥር አነስተኛ መሆኑ ተገልጿል፡፡ … የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ተወካዮች ከሀገራዊ ምክክሩ "3"ኮሚሽነሮች ጋር  ውይይት ማድረጋቸው የተገለፀ ሲሆን በባለሙያ በተሰጠ መግለጫ ላይም  በተሳታፊና በአወያይ ደረጃ የሙስሊሞችን ተሳትፎ እንዲነገረን ብንጠይቅም ከምክክር ኮሚሽኑ ምላሽ እንዳልተሰጠ በሰጠው መግለጫ ላይ አስታውቋል፡፡ … ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ ውሳኔውን በድጋሚ እንዲያጤነው እና በኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አማካኝነት የቀረቡ የመስሊሙ አጃንዳዋች እንዲካተቱ እና ህዝበ ሙስሊሙም በቁጥሩ ልክ ተሳታፊ እንዲሆን ጥሪ ቀርቧል። … ©ሀሩን ሚድያ የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
632Loading...
25
Media files
681Loading...
26
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በጎንደር ከተማ እየሰጠ ባለው ስልጠና ላይ ሙስሊሞች እንዳይሳተፉ መከልከሉ ተገለፀ! ... (ሀሩን ሚዲያ፦ግንቦት 9/2016) … የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በጎንደር ክላስተር በአጀንዳ ማሰባሰብና ምክክር ላይ የሚሳተፉ የማህበረሰብ አባላትን ለመመልመል የሚያግዙ ተባባሪ አካላት ስልጠና እየሰጠ ሲሆን በጉባኤው ላይ ለመሳተፍ የመጡ ሙስሊሞችን እንዳይገቡ መከልከሉን የሀሩን ሚድያ ምንጮች ገልፀውልናል፡፡ … የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በጎንደር ከተማ እየሰጠ ባለው ስልጠና አስመልክቶ "ሀሩን ሚድያ" ጉዳዩን አስመልክቶ ስልክ ደውልን ባጣራነው መረጃ መሠረት የደቡብ ጎንደር ደብረታቦር ከተማ መጅሊስ አመራሮች ስልጠናው ላይ ለመሳተፍ ወደቦታው ቢያቀኑም ከበር እንዳይገቡ እንደተከለከሉ አንስተዋል። ... ስልጠናውን እየሰጡ ያሉት የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን አመራሮች ምልመላ ያደረጉት ከክልሉ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ እንደሆነ በመግለፅ የክልሉ መጅሊስ ወክሏቸው ለመሳተፍ የመጡ ሙስሊሞችን አናስገባም ማለታቸውን ለሀሩን ሚድያ ተናግረዋል። … በጎንደር ከተማ እየተሰጠ በሚገኘው የጎንደር ክላስተር ተባባሪ አካላት ስልጠና ከ75 ወረዳዎች የተውጣጡ ከ500 በላይ ሰልጣኞች እየተሳተፉ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ነገር ግን የሙስሊሙ ቁጥር አነሳ መሆኑን እና የክልሉ መጅሊስ ባላወቀው መልኩ እንደተደረገ ተገልጿል፡፡ … ሀሩን ሚድያ ያነጋገራቸው አካላት እንደገለፁት ሙስሊሙን ያላሳተፈ ምክክር ውጤታማ አይሆንም በማለት ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ እየሄደበት ያለው መንገድ አግባብ ባለመሆኑ ሙስሊሙን እንዲያካትት ጥሪ አቅርበዋል። … ©ሀሩን ሚድያ የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
841Loading...
27
https://www.facebook.com/100057258774767/posts/966385415280075/?mibextid=AQBXeECoIFSgMqhe
701Loading...
28
አላህ ሆይ በየቀኑ ራሣቸዉን ገምግመው ከሚታረሙት አድርገን። ከነፍሳችን ተንኮል ባንተ እንጠበቃለን። ከባህሪያችን ክፋትም አንተው ጠብቀን
841Loading...
29
«አላህ ሆይ! መንገዳችንን ምሪት ወዳለበት፣ ጓደኝነታችንን ውዴታ ወዳለበት፣ ልባችንንም ደስታ ወዳለበት አድርግልን!»
983Loading...
30
Media files
941Loading...
31
የሚሽነሪዉ ሙሀመድ ሱሩር ማን ነዉ ? ቢስሚላህ ! ክፍል 3 ሙሀመድ ሱሩር WAMI የሚባል ድርጅት ሀላፊ የነበረዉ አል-አሚን ዛይድን የህክምና መሳሪያ እንዲሟላለት በጠየቀዉ መሰረት ሌሎች አባቶችም ተባብረዉ አስፈላጊ የተባሉት ነገሮች ተሟሉለት ። ህዝቡ በህክምና ክፍያዉ ማማረር ጀምሯል ሚስቱ ዘይነባ ( ስሟን ካልተሳሳትኩ ) ዉጭ ባለዉ ስብእናና ቤት ዉስት በምታየዉ ነገር በጣም ተጎድታለች ለምታዉቀዉ ሰዉ ሁኔታዉን ብታማክርም ለጊዜዉ ሰሚ አላገኘችም ። የመርከዝ ተማሪዎች ዉስጥ የሙሀመድ ሱሩርን አስመሳይነት በድፍረት ያጋለጠዉ ወንድሜ አህመድ ሙሀመድ ሳኒ ነበር ለሱ ምስክር የሆንኩት እኔ ነበርኩ ። ከዛም የጀመዓዉ መከፋፈል አንድ መስመር ያዘ እሱም ማስረጃ አምጡ የሚል ነበር ሁሉም በዚህ ተስማማ ወንድሜ አህመድ ሙሀመድ ሳኒም ማስረጃ ይዞ ቀረበ ምስክርነት ተሰማ ( ያዉ መለስተኛ ፍርድ ቤት በሉት ) የሚስቱ አቤቱታ ፣ የመርከዝ ልጆችም ፣ በህክምና ተበደልኩ የሚሉት የከተማዉ ሰዎችም ወደ አንድ ምእራፍ ላይ ደረሱ ። እስካሁን የሰራቸዉን ወንጀሎች አንድ ባንድ አልጠቀስኩም የዚህ ፅሁፍ አላማ አጠቃላይ ማንነቱን ማሳየትና ወደፊት በሀሩን ሚዲያ እንደ አስፈላጊነቱ ስለሚቀርብ ። በመጨረሻም ሙሀመድ ሱሩር በወልዲያ ህዝብ እንኳን ዳዒ ሊሆን ቁርአን እንዳልቀራ ተረጋገጠ ህክምናም መርፌ ከመዉጋት የዘለለ እዉቀት እንደሌለዉም አረጋገጥን ። ለእስልምና ብየ በሁስኒ ሙባረክ ( በጊዜዉ የግብፅ መሪ ) የነበሩትን የመግደል ሙከራ አድርገሃል ተብየ ታስሬ ነበር በሚል ከእስር ቤት ነፃ የተባልኩበት ወረቀት ብሎ ያሳየን ወረቀት የሌላ ሰዉ ስም መሆኑን ያጋለጠዉ አህመድ ሙሀመድ ሳኒ ነበር እሱም ይሀ ሌላ መጠሪያ ስሜ ነዉ ብሎ ያታለለንን አስታዉሳለሁ ። ሚስቱ ዘይነባ የዲን ሰዉ እንዳልሆነና አጭበርባሪ መሆኑን ሁሉም ሰዉ ሲረዳ ከብዙ ስቃይና በደል ትምህርቷን አቋርጣ ከዚህ ዉርደት አድስ አበባ ሄዳ የቤት ሰራተኛ ሆና መግባቷን ሰምቻለሁ ከዛ በሗላ ያለችበትን ሁኔታ አላዉቅም ። ስለሁኔታዋ የሚያዉቅ ካለ በዉስጥ መስመር ይፃፍልኝ ። ሚሽነሪዉ ሙሀመድ ሱሩር የወልዲያ ጊዜዉን ጨረሰ አሁን ከወልዲያ 50 ኪ.ሜ የምትርቀዉ የዉቦች ሀገር ቆቦ ከተማ በተለየ ማጭበርበሪያ ገባ የታላላቅ ሸኾችን አጠማጠም ጠምጥሞ ፉቅራነትን ተላብሶ ማምታታት ጀመረ ። የማስታዉሰዉ ወልድያ መጀመሪያ የመጣ አካባቢ እኔንና ወንድሜ ኢንጅነር ሙሀመድ ጀዉሀርን ቆቦ ከተማ ይዞን ሄዶ ነበር ለምሳ አንድ ምግብ ቤት ይዞን ገባ ። አስተናጋጅ ፣- ምን ልታዘዝ እኔና ወንድሜ ፣- ፓስታ መኮረኒ ( ለኛ ብርቅ ነበር ) አስተናጋጅ ፣- የፆም ነዉ የፍስግ ሚሽነሪዉ ፣- የፍስግ አድርጊላቸዉ ( በጊዜዉ የፆምና የፍስግ አናዉቅም የተህፊዝ ቅጥቅጦች ዉጭ የማናዉቅ ነበርን ) ። ምግቡ ቀረበ መብላት እንደጀመርን ስጋዉ ሰተት ብሎ ወደ ጉሮሮ እኛም ደነገጥን ሊያረጋጋን ሞከረ አንደኛችን አስታወክን ። ከባድ ወንጀል እንተፈፀመብን ተናገርን ። ቆቦ ለወልዲያ ቅርብ ስለነበር በወሬ ወሬ የቆቦ ሰዉ ትንሽ ጊዜ ቢጭበረበርም በጊዜ አሰናበተዉ ። ከትንሽ ጊዜ በሓላ ኮምቦልቻ ገብቶ ተመሳሳይ ማጭበርበር እየሰራ በህክምናዉ ላይ ስህተት ሰራ በዚህም ምክኒያት ታስሮ ነበር የሚል ሰምቻለሁ ። ኮምቦልቻ ለሚሽነሪዉ ሙሀመድ ሱሩር ከወሎ ምድር የመጨረሻዉ ሆነች ከዛም ተረኛዋ አድስ አበባ ላይ የሆነዉን አሏህ ይወቅ ። ለመሆኑ ሚሽነሪዉ ሙሀመድ ሱሩር ተልእኮዉ ምን ነበር እንደ ተባለዉ የገንዘብ ፍላጎት ወይንስ ተልእኮ ነበር የፈፀመዉ የሚለዉ ከተቻለ በሀሩን ሚዲያ ከሌሎች ወንድሞች ጋር እመለስበታለሁ ። ሙሀመድ ሱሩር የየጁ ተወላጅ ነዉ ቤተሰቦቹን መጥቀስ አልፈለኩም ምናልባት አካባቢዉን ከማወቁ አንፃር ተመልሶ በግልፅ የሚሽነሪ ስራ ይሰራ ይሆን ? አሏሁ አዕለም ። የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
961Loading...
32
Media files
832Loading...
33
የደጋጎች እናት፣ የኡሑድ ዘመቻ ዕለት የረሱሉ (ሰዐወ) ጋሻ፣ ኑሰይባ አል-ማዚኒያ ኡሙ ዑማራ (ረዐ) ጊዜው መካ ውስጥ ኢስላም ላይ የጦር ፍላፃ በተመዘዘበት ነበር፡፡ ከመዲና አንድ ልዑክ አስራ ሁለት ሰዎችን አካቶ ለሐጅ ስርዓት ወደ መካ ይንቀሳቀሳል፡፡ እግረ-መንገድም አላህን በማምለክና በርሱም ማጋራትን በመተው፣ እርሳቸውን ልጆቻቸውንና ሴቶቻቸውን ከሚከላከሉት አደጋ ሊከላከሏቸው ለመልዕክተኛው (ሰዐወ) የመጀመሪያውን የዓቀባ ቃል-ኪዳን ይፈፅማሉ፡፡ በሚቀጥለው የሐጅ ዓመት የዓቀባ ቃል-ኪዳን ላይ ደግሞ አንድ ሕፃን ልጅ ያለበት ሰባ ሁለት ወንዶችና ሁለት እንሰቶች ያሉበት ልዑክ መካን ረፈጠ፡፡ አንደኛዋ ሴት የዛሬዋ እንግዳችን ኑሰይባ ቢንት ከዕብ አል-ማዚኒያ አል-አንሷሪያ ናት፡፡ እነሆ ከመዲና ነዋሪዎች ወደ ኢስላም ከገቡት የቀደምቶቹን ማዕረግ ልታገኝ፣ በሕይወትም እስካለች ድረስ ከኢስላምና ነብያችን እየተከላከለች ልትኖር የሴቶች ዝንተ-ዓለማዊ ናሙና ለመሆን በቃች፡፡ የኡሑድ ዘመቻ ዕለት ከባለቤቷና ልጆቿ ጋር ዘማቾችን ልታበረታታና ቁስላቸውን ለማከም ነይታ ወጣች፡፡ እንደሚታወቀው ኡሑድ የሙሽሪኮች አሸናፊነት የታየበት፣ ብዙ ሶሐባ ሸሂድ የሆነበትና የድል ሚዛኑ ወደነርሱ ያጋደለበት ዕለት ነበር፡፡ በዚህ መሃልም ‹‹ሙሐመድ ተገደለ›› የሚለው ጩኸት ወደ ኑሰይባ ጆሮ ደረሰ፡፡ ከተቀመጠችበት ተነሳች፣ የውሃ ኮዳዋንና ቦርሳዋን ወርውራ ሰይፏን አነገበች፡፡ ልጆችና ባሏን ጠርታ ሕይወትን ከአንዲት ትንኝ ክንፍ አሳንሰው ያዩ አማኞችን አስከትላ ነብያችንን (ሰዐወ) በጀግና ሞገስ ለመጠበቅና ለመከላለከል ትፈልጋቸው ገባች፡፡ አግኝታቸውም ስትከላከልና ስትዋጋ ወደርሳቸው ከተወረወሩት ቀስቶች እንዲሁም ከሚቃጡ ሰይፎች ገላዋ ላይ አስራ ሶስት ያህሉ አረፉባት፡፡ ትከሻዋ ላይም ከባድ ጉዳት ስለደረሰባት እጇ ፓራላይዝ ሆነ፡፡ ነብያችን (ሰዐወ) ሰለርሷ አንዲህ ብለው ነበር ‹‹ወደ ቀኝም ይሁን ግራ ስዞር ከኔ ስትከላከልና ስትጋደል ነበር የማያት፡፡›› ታዲያ ነብያችንም (ሰዐወ) በግርምት ‹ምንኛ የተባረከ ቤተሰብ ነው፤ አላህ በረከትን ያውርድላችሁ› ብለው ዱዓ አደረጉላቸው፡፡ ኑሰይባም ‹የአላህ መልዕክተኛ ሆይ በጀነትም አንድንጎራበቶት ዱዓ አድርጉልን› አለቻቸው፡፡ ለርሷና ለቤተሰቦቿ የሚከተለውን ዱዓ አደረጉ ‹‹ አላህ ሆይ በጀነት ጎረቤቶቼ አድርግልኝ፡፡›› ለነገሩ ቤተሰቧ አስገራሚ ነበር፡፡ ከላይ ሰባ ሁለት ሆነው የሁለተኛውን ዐቀባ ቃል ኪዳን ከገቡት ውስጥ አንድ ህፃን ያልነውና በጥንጥዬ እጁ ለረሱሉ(ሰዐወ) ቃሉን ያሳለፈው ልጅ ዛሬ ጎርምሷል፡፡ ያኔ በሕፃንነቱ ወደ ኢስላም ለመግባት በአባቱ እቅፍ ትላልቆቹን እንደተስተካከለው ዛሬ ደግሞ ወደ ሐሰተኛው ሙሰይለማ ቀዬ የነብያችንን (ሰዐወ) ማስጠንቀቂያ ያዘለ ደብዳቤ ይዞ የሚሄድ መልዕክተኛ ሊሆን ነው፡፡ የኑሰይባ ልጅ ሲሆን ስሙም ሐቢብ ቢን ዘይድ አል-አንሷሪ (ረዐ) ነው፡፡ ምን ይገጥመው ይሆን? ሐሰተኛው ሙሰይለማ ፊት ምን ሊያደርገኝ ይችላል የሚል ስጋት ሳያሳስበው ደብዳቤውን ይዞ በሙስሊም ወጣት ሞገስ ቆመ፡፡ ሙሰይለማም ብዙ ሰው በተሰበሰበበት ይህ ወጣት በከባድ ሰንሰለት ታስሮ ይቀርብ ዘንድ አዘዘ፡፡ አስከትሎም ‹‹ ሙሐመድ የአላህ መልዕክተኛ እንደሆነ ትመሰክራለህ?›› አለው፡፡ ሐቢብም ‹‹አዎ እመሰክራለሁ›› አለው፡፡ ‹‹እኔስ የአላህ መልዕክተኛ እንደሆንኩ ትመሰክራለህ?›› አለው፡፡ ‹‹ጆሮዬ የምትለውን ለመስማት አይችልም፡፡ ደንቆሮ ነኝ፡፡›› አለው፡፡ ያ ውሸታም ሙሰይለማ ቁጣው ገነፈለ፡፡ ስጋውን እየቆረጠ እንዲቀጣው ገራፊውን አዘዘው፡፡ ከሰውነቱ ላይ ስጋ እየተቆረጠ መሬት ላይ ወደቀ፡፡ ሙሰይለማ ጥያቄውን ደጋገመ፡፡ ያ ወጣትም መልሱን ያለምንም መለሳለስ ደጋገመለት፡፡ ገራፊውም በተመሳሳይ ስጋውን አየቦጫጨቀ መሬት ላይ ይጥል ነበር፡፡ ያ ለጋ ወጣት በአላህ መንገድ፣ በረሱሉ ክብር መንገድ ላይ በምላስና ልቡ ስማቸውን እየደጋገመ ሰማዕት ሆነ፡፡ የሞቱ ዜና ለዚያች የኢስላምና መልዕክተኛው (ሰዐወ) ደጀን ለፅኑዋ አንዲሁም ለትዕግስት ተምሳሌቷ ኑሰይባ ደረሳት፡፡ ጉንጮቿን አልቧጠጠችም፣ በቁጭትና ሐዘን ተኮራምታ አልተበሰከሰከችም፡፡ አንደውም በኩራት ‹‹ ለዚህ መሰል ቀን ነው ያዘጋጀሁት፡፡ አላህ ዘንድም እተሳሰበዋለሁ፡፡ በአላህ ይሁንብኝ ሙሰይለማን ባገኘውና መግደል ብችል ሴት ልጆቹን ጉንጭ አስቧጥጣቸው ነበር፡፡›› አለች፡፡ የየማማ ዘመቻ ቀን እንደ ተቆጣ አንበሳ የአላህን ጠላት ሙሰይለማን ፍለጋ ሰልፎችን አየሰነጣጠቀች ትሄዳለች፡፡ ነገርግን ቀደም ብሎ በወሕሺይ ተገድሎ ስለነበር በደም ተነክሮ አገኘቺው፡፡ ምን ሊሰማት አንደሚችል ገምቱ፡፡ የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
1041Loading...
34
የ1445/2016/2024..ሀጅ ስነስርአት ክንውን 30 ቀናት ብቻ ቀርተውታል ኢላሂ እኛንም ወፍቀን 🥹 🤲 #Hajj #Hajj1445 #Hajj2024
861Loading...
Photo unavailableShow in Telegram
ለተባበራችሁ ወንድም እና እህቶች ሁሉ አላህ ምንዳችሁን በሰፊው ይክፈላችሁ እናመሰግናለን
Show all...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
በስም ሳይሆን በመሆን፤በምላስ ሳይሆን በተግባር እንዴት ወንድ እንደሚኾን ያሳዩ ድምቅ መሪ።ሰዎች ግማሾቹ በዐረባዊ ብሔረተኝነት፤ሌሎቹንም በቡድናዊ ወገንተኝነት ተቆላልፈው በታሰሩበት ሰዓት ፐርሺያነታቸውና የሺዓ ቡድን ተከታይነታቸው ዐረብና የሱና ተከታይ የሆኑት የገዛ ወንድሞቻቸውን ከመርዳት እንደማያግዳቸው ያሳዩ ድንቅ ህዝቦች ሐገር መሪ! ሰይድ ኢብራሂም ከስማቸው ድርሻቸውን የወሰዱ ናቸው።በአንዱ ሞት የማይሞት የኡመት ስም ነው! አሏህ በሰፊው ራሕመቱ ይቀበሎት ሰይድ ኢብራሂም ረኢሲ የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
Show all...
👍 3 1
«አንድ ሰው  ከሚኖረው መልካም ነገራት ሁሉ  በላጩ በመከራ የማይንበረከክ ልብን ማግኘት  ዋነኛው ነው» ©أدهم شرقاوي
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
የአፋልጉኝ ጥሪ...... በአፋር ክልል ከወላጆቹ ጋር በሎጊያ ከተማ የሚኖረው ህፃን አፍረሂም ሙሀመድ አብዱ ዛሬ ጠዋት አካባቢ ወላጆቹ ለመልእክት ወደ ሱቅ ልከውት እስካሁን አልተመለሰም። ህፃን አፍረሂም ሙሀመድን ያየ ካለ ከታች ባለው ስልክ ቁጥር (+251910090080)ደውላችሁ ብታሳውቁን ወሮታውን ከፋይ ነን። ቤተሰቦቹ ሼር ሼር ሼር
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
#BREAKING የኢራኑ ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ፣የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ሁሰይን አሚር አብዱላሂ እና አብሯቸው የነበረው የልዑካን ቡድን በሙሉ በሄሊኮፕተር አደጋው መሞታቸውን የኢራን መንግስት ቴሌቭዥን አስታውቋል! #አልጀዚራ የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
🇮🇷🇺🇸 የአሜሪካ አየር ኃይል ካርጎ የሆነው C-17 ግዙፍ ወታደራዊ አይሮፕላን ከዓመት በላይ ጊዜ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ አዘርባጃን ባኩ በዛሬው ዕለት ማረፉ ተሰምቷል።   የአሜሪካው ወታደራዊ ካርጎ የኢራኑ ፕሬዝዳንት ራይሲ የተሳፈረበት ሄሊኮፕተር አዘርባጃንን ከመልቀቁ እና ከተከሰከሰበት ጊዜ ጋር መገጣጠሙ ጥያቄዎችን እየፈጠረ ይገኛል። #Ethiopia #Raisi #Iran #Helicoptercrash #SearchOperation #RescueOperation የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
Show all...
▪️የኢራኑ ፕሬዝዳንት ራይሲ ከሄልኮፕተር አደጋው ጥቂት ቀደም ብሎ የነበሩበትን የሚያሳይ ቪዲዮ፤ እንዲሁም     - ከአደጋው በኋላ ለአደጋ ጊዜ ሰራተኞች የሄልኮፕተር ፍለጋ ስራቸውን አስቸጋሪ ያደረገው የአየር ሁኔታ #Ethiopia #Raisi #Iran #Helicoptercrash #SearchOperation #RescueOperation የቴሌግራም ቻናሌን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ @ https://t.me/Xuqal
Show all...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
የኢራኑ ፕሬዝዳንት ሄሊኮፕተር የወደቀችው በመጥፎ የአየር ሁኔታ ምክንያት ሲሆን ተሳፋሪዎቹ መቁሰላቸውን ወይም መሞታቸውን ማረጋገጥ አልተቻለም። በሄሊኮፕተሩ ላይ የተሳፈሩት ሰዎች ሞተዋል ወይም ቆስለዋል የሚሉ ዘገባዎች ያልተረጋገጡ ስለሆኑ አስተማማኝ አይደሉም!” #መህርአጄንሲ(ኢራን)
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
“በአስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እና በቀላሉ ሊደረስበት በማይችል ተራራማ አካባቢ የፍለጋው ስራ ቀጥሏል! - ተጨማሪ የነፍስ አድን ቡድኖች ወደ አደጋው ቦታ እየላክን ነው!” የኢራን መንግስት ቃል አቀባይ! #አልጀዚራ
Show all...
00:38
Video unavailableShow in Telegram
በምስራቅ አዘርባጃን ግዛት አደጋ በደረሰባት ሄሊኮፕተር ላይ የኢራኑ ፕሬዝዳንት ከውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ እና ከበርካታ ባለስልጣናት ጋር #የመጨረሻ እይታ! #አልጀዚራ
Show all...