Ethio Space (ኢትዮ ጠፈር)
Closed channel
ሰለ ሌሎች ዓለማላቶች እና አስትሮኖሚ ሳይንስ ስታስብ በሰዎች መካከል ያሉት የጎሳ ,የብሔር ,የሐይማኖት ልዩነቶች እንዲውም የአገር ልዩነቶች ለአንት ተራ ነገሮች ይሆናሉ ምክንያቱም እራስክን የምታነፃፅረው በሌሎች አለማት ላይ ይኖራሉ ተብለው ከሚታሰቡ ልዩ ፍጥሮች ጋር ይሆናል ሰለዚህ አንት ሰው ከሆነክ በቂ ነው ምክንያቱም ሰው መሆንክ በራሱ በቂ ማንነት.. @unverseand 👈ለcross
Show more1 981
Subscribers
No data24 hours
-127 days
-4330 days
Posts Archive
ናሳ ‘ድንቅነሽ’ በተባለች መንኮራኩሩ አማካኝነት በአስትሮይድ ዙሪያ አዲስ ጨረቃ ማግኘቱን አስታወቀ።
በዚህ ሳምንት ድንቅነሽ (ሉሲ) በተባለችው የናሳ የጠፈር መንኮራኩር የተጎበኘችው ንዑስ ፕላኔት (አስትሮይድ) ሳይንቲስቶችን ያስደነቀ አዲስ ጨረቃ እንዳላት ታውቋል።
ጨረቃዋ የተገኘችው ከማርስ ባሻገር ባለው ዋና ንዑስ ፕላኔት ቀለበት ውስጥ 480 ሚሊዮን ኪሎ ሜትር ርቆ ሲሆን፣ መንኮራኩሯ 435 ኪሎ ሜትር ያህል ርቀት ላይ የሚገኙ ተነባባሪ አካላትን ምስል አንስታ ወደ ምድር ልካለች።
መንኮራኩሯ ወደ ምድር በላከቻቸው መረጃዎች እና ምስሎች ላይ የጨረቃዋ መሻገሪያ ግማሽ ኪሎ ሜትር ብቻ እንደሆነ ተረጋግጧል።
ናሳ መንኮራኩሯን ወደ ጠፈር የላከው በጁፒተር አቅራቢያ የሚገኙ ሚስጥራዊ የሆኑ ንዑሳን ፕላኔቶች ላይ ምርምር ለማድረግ ሲሆን፣ ድንቅነሽ የላከችው የአዲሷ ጨረቃ ምስል የዚሁ ምርምር ውጤት እንደሆነ ኤቢሲ ኒውስ ዘግቧል።
እ.አ.አ በ2021 የተጀመረው ይህ የናሳ ምርምር በ2027 “ትሮጃን” ከሚባሉት ንዑሳን ፕላኔቶች መካከል የመጀመሪያው ላይ ለመድረስ ቢያንስ ለስድስት ዓመታት ምርምር እንደሚያደርግ የተገለጸ ሲሆን፣ ሊደረስባቸው የታቀዱ ንዑሳን ፕላኔቶች ቁጥር ከ7 ወደ 11 ከፍ ማለቱንም በዘገባው ተጠቅሷል።
ናሳ "ድንቅነሽ ማለት በአማርኛ ቋንቋ 'አስገራሚ' ማለት መሆኑን እና በ1970ዎቹ በኢትዮጵያ የተገኘችው የ3.2 ሚሊዮን ዓመት ዕድሜ ያላት ‘ሉሲ’ አማርኛ ስም በመሆኑ መንኮራኩሯ በዚህ ስም ተሰይማለች" በማለት ስለ መንኮራኩሯ ስያሜ ገልጿል።
የናሳ መሪ ሳይንቲስት የሆኑት ሃል ሌቪሰን አዲሱን ግኝት አስመልክተው በሰጡት መግለጫ "ድንቅነሽ ከስሟ ጋር ተስማምታለች፤ ይህ በጣም አስደናቂ ነው" ብለዋል።
ለአምስት ወራት ሕዋ ላይ የቆዩ የቻይና ጠፈርተኞች ወደ ምድር ተመለሱ
****
ሦስት ጠፈርተኞች በሕዋ ላይ በሚገኘው የቻይና የጠፈር ማዕከል ውስጥ አምስት ወራትን ካሳለፉ በኋላ ወደ ምድር ተመልሰዋል።
በሸንዙ 16 መንኮራኩር ወደ መሬት የተመለሱት ሶስቱ ቻይናውያን ጠፈርተኞች በሕዋ ላይ በቆዩበት ወቅት ፍሬያማ የምርምር ጊዜ ማሳለፋቸው ተገልጿል።
ጠፈርተኞቹ ለ154 ቀናት በሕዋ ላይ የቆዩ ሲሆን በቆይታቸውም፤ የጤና፣ ቴክኖሎጂ እና ምህንድስናን ጨምሮ በድምሩ በ70 ያህል ዘርፎች ሙከራዎች ማድረጋቸውን ዥንዋ ዘግቧል።
የቻይና ስፔስ ኤጀንሲ የዚህ ተልዕኮ መሳካት ለቀጣይ የጠፈር ምርምር መርሃ ግብሮች እድገትና የጠፈር ቴክኖሎጂዎች ፈጠራ ጥሩ መሰረት መጣሉን ገልጿል።
Repost from የአለም ጋለሪ
ፎሬክስ ትሬዴንግ አዋጭ እና ሕጋዊ የኦንላይን ስራ መሆኑን ያውቃሉ ?
ብዙዎች የተቀየሩበት ፎሬክስ ትሬዲንግ ገለሰቦች ባላሀብቶች ባንኮች እና የመንግስት መስሪያ ቤቶች ተሳታፊዎች ናቸው ለዚህም ነው ሕጋዊ እና የማይጠፍ የኦንላይን ስራ የሆነው።
ለበለጠ መረጃ ይቀላቀሉን👇👇👇👇👇👇
https://t.me/+Yk2NmnkNxCtmMzk8
https://t.me/+Yk2NmnkNxCtmMzk8
ዛሬ ምሽት ከፊል የጨረቃ ግርዶሽ ይኖራል ተባለ።
ዛሬ ምሽት ጥቅምት 17/2016 ዓ.ም የጨረቃ የተወሰነ ከፊል አካል የመሬት ጥላ ሲያርፍበት እንደሚሸፈን የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ይህ ክስተት ከፊል የጨረቃ ግርዶሽ ሲባል ግርዶሹ በሁሉም የአፍሪካ ክፍል የሚይታይ እንደሆነ ከስፔስ ሳይንስና ጂኦስፓሻል ኢንስቲትዩት የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክት ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ገልጿል።
ከፊል ግርዶሹ ከምሽቱ 4:35 ጀምሮ ምሽት 5:53 ላይ የሚያበቃ እንደሆነ ሲገለፅ 6 በመቶ የሆነው ዋናው ግርዶሽ ምሽት 5:14 ላይ እንደሚታይና ግርዶሹን ያለ ምንም መሳርያ በዓይን ብቻ የሚታይ እንዲሁም ቴሌስኮፕ እና ባይኑክላር ተጠቅሞም ማየት እንደሚቻል ተገልጿል።
የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር በመጀመሪያ ጨረቃ በመሬት ድብዝዝ ጥላ ወይም ፔኑምብራ ውስጥ ትገባለች ያለ ሲሆን ይሄም በጣም የደበዘዘ ስለሚሆን በባዶ ዓይን እንዳማይታይ ገልጾ በመቀጠል ጸሊም ጥላ ወይም አምብራ በሚባለው ከፊል ግርዶሽ ውስጥ ትገባለች ብሏል።
በዋናው ግርዶሽ ቅፅበት ወቅት የጨረቃ 12 ፐርሰንት አካሏ ብቻ የተጋረደ እንደሚሆንም የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚንስቴር ገልጿል።
እኛ ከምንገኝበት ምድር 111 የብርሃን ዓመት ረቀት ላይ 2-18b የሚል ስያሜ የተሰጠው እጅግ አስገራሚ ፕላኔት ይገኛል ፕላኔቱ ፈሳሽ ውሃ እና ተራራማ ስፍራዎች በውስጡ እንደሚገኝ በጥናት የተረጋገጠ ሲሆን ምንአልባትም ይህኛው ፕላኔት ከሰው ልጅ ወጣ ያሉ ፉጥሮች እየኖሩበት ሊሆን እንደሚችል የዘርፉ ባለሞያዎች ይሞግታሉ።
ምንጭ - ከአለም Gallery
ሰለኤልያኖች እና ከኤልያኖች ጋር የተደረገውን ቃለመጠየቅ ለማየት👇👇
https://www.youtube.com/playlist?list=PLL84IYkPmzk1ZA0sySTE6_bK_JnQau5WJ
🌕 ብርሀን ከፀሀይ የላይኛው ክፍል ወደ ምድር ለመድረስ 8 ደቂቃ ከ22 ሰኮንድ ይፈጅበታል ! ብርሀኑ የተላከው ከፀሀይ የውስጠኛው ክፍል (core) ቢሆን ግን ብርሀኑ ምድር ላይ ለመድረስ 100,000 አመታትን ይፈጅበታል !
ኢትዮጵያ ወደ ህዋ የላከቻቸው ሳተላይቶች ስራ አቆሙ
ኢትዮጵያ የተለያዩ ሳይንሳዊ ስራዎችን ለመከወን ያግዟታል ተብለው ወደ ህዋ የመጠቁ ሁለቱ ሳተላይቶች ስራ አቁመዋል ተባለ። የስራ ጊዜያቸውን ጨርሰው የሚወገዱበት ጊዜ ስለደረሰ ሌሎች ሳተላይቶች ላይ ጉዳት በማያደርስ መልኩ ለማስወገድ እየተሰራ መሆኑ ተገልፇል።
አዲስ ሳታላይት አልምቶ ለማምጠቅም እየተሰራ መሆኑን የኢንኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ለህዝብ ተወካዮች ተናግሯል። ከዚህ ቀደም ወደ ሳተላይት የመጠቁት ምን ፋይዳ አስገኙ የሚለው እንዳልተገለፀ ነው ሸገር ሬዲዮ የዘገበው።
🔮 እኛ የሰው ልጆች ነን...!!!
በአጋጣሚ ለምርምር ከዚህ ካለንበት ሚልክዌይ ጋልክሲ ወጣቹ እንበል ባጋጣሚ ምርምር እያደረጋቹ እያለ ከሌላ ጋልክሲ የመጣ ኤሌይን ወይም ልዩ ፍጡር አጋጠማቹ አጋጣሚ ሁኖ መግባባት ቻላቹ እንበል ነገረ ግን በድንገት ከየት እንደመጣቹ ቢጠይቃቹ ምንድነው መልሳችሁ።
እኔ ግን የምለው ከሚልክዌይ ጋልክሲ ከ ስርአተ ፀሀይ ፕላኔቶች አንዷ የሆነችው "EARTH" ከምትባለው ፕላኔት ነው የመጣሁት የምለው ምክንያቱም ሀገሬንም ሆነ ብሔሬን ብነግረው ስለማይገባው ሰው መሆኔ ግን ይገባዋል ስለዚህ ወገኖቼ ከምንም ነገር ሰውነት ይበልጣል።
በሥርዓት ፀሐይ ውስጥ ከብረት ወደተሰራው ሚስጥራዊ ዓለም የተጓዘችው አሳሽ መንኮራኩር
***
የአሜሪካ የጠፈር ኤጀንሲ (ናሳ) በሥርዓት ፀሐይ ውስጥ ካሉት ያልተለመዱ የህዋ አካላት አብዛኛው ስሪቱ ከብረት የተዋቀረውን የአስትሮይድ ዓለም ለማጥናት አዲስ አሳሽ መንኮራኩር ወደ ጠፈር አምጥቋል፡፡
“16 Psyche“ የሚል ስያሜ ያለው ሚስጥራዊው የአስትሮይድ ዓለም ከዚህ በፊት በተደረጉ የቴሌስኮፒክ ምልከታዎች 60 በመቶው ከብረት እና ኒኬል የተሰራ መሆኑ ተጠቅሷል።
ወደ ብረቱ አለም እንድትጓዝ የተላከችው አሳሽ መንኮራኩር አርብ ዕለት ፍሎሪዳ ከሚገኘው ኬፕ ካናቬራል የጠፈር ማዕከል መምጠቋ ነው የተገለጸው።
አሳሽ መንኮራኩሯ በሚቀጥሉት ስድስት አመታት ውስጥ ወደ 2.2 ቢሊዮን ማይል (3.6 ቢሊዮን ኪሎ ሜትር) በመጓዝ በማርስ ምህዋር መካከል ባለው ዋናው የአስትሮይድ ቀበቶ ውጫዊ ክፍል ላይ ወደሚገኘው የጠፈር አለት እንደምትደርስ እና ምርምሯን እንደምትጀምርም ተመራማሪዎች ገልፀዋል፡፡
እንደሚታወቀው አስትሮይዶች በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ትንንሽ አለማት ወይም ፕላኔቶች ሲሆኑ አብዛኛውን ጊዜም በማርስ እና በጁፒተር መካከል ሆነው በራሳቸው ምህዋር ፀሐይን የሚዞሩ ናቸው።
አስትሮይዶች በመጠን ከ 6ሜትር እስከ 940 ኪሎሜትር የሚረዝሙ ሲሆን በቅርፅ፣ በያዙት መአድን፣ በመጠን እና በሚያንጸባርቁት ቀለም ይለያያሉ፡፡
አስትሮይዶች የሚዞሩበት ምህዋር የአስትሮይድ ቀበቶ (Asteroid belt) የሚባል ሲሆን፤ በዚህ ቀበቶ ውስጥም በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ አስትሮይዶች ይገኛሉ ተብሎ ይታሰባል።
አስትሮይዶች ለምድር በጣም ከቀረቡ በስበት ሀይል ተስበው የመሬትን ተደራራቢ የከባቢ አየር ክልል (atmosphere layers) ጥሰው ሊገቡ የሚችሉ ሲሆን፤ ለዚህም ምሳሌ የሚሆነው እንደአውሮፓውያኑ አቆጣጠር በየካቲት 15, 2013 በሩስያ ቼልያቢንስክ ውስጥ የተከሰተው ትልቁ የአስትሮይድ ጥቃት ነው።
ይህ 20 ሜትር የሚረዝመው አስትሮይድ ባዶ ሜዳ ላይ ያረፈ ቢሆንም የንዝረት ሞገዱ ብዙ ኪሎሜትሮችን አካሎ እንደነበር በጊዜው ወተው የነበሩ ዘገባዎች አሳይተዋል።
በጥቃቱ ከ 1200 በላይ ሰዎች ተጎድተው የነበረ ሲሆን በአካባዊ በሚኖሩ ሰዎች ንብረት ላይም ውድመት ደርሶ እንደነበር የቢቢሲ ዘገባ አስታውሷል።
በታሪክ ተጠቅሶ እንደሚገኘው በጣም ትልቅ የተባሉት አስትሮይዶች ምድራችንን የሚመቷት በ 1ሺህ አመት አንድ ግዜ ብቻ ቢሆንም ትንንሾቹ አስትሮዶች በተደጋጋሚ ሊታዩ እንደሚችሉ የስነ-ፈለግ ተመራማሪዎች ያስረዳሉ፡፡
እስካሁን ድረስ የሰው ልጅ ማየት የቻለው 5% የሚሆነውን የአፅናፍ አለም(universes) ክፍል ነው ሌላው ክፍል ምን እንደሆነ በግልፅ አይታወቀም
በምድራችን ከተፈጠሩ እንስሳት እንደ ሻርክ ታጋሽ እና ጠንካራ እንስሳ የለም ሻርክ በዚ ምድርላይ ከዳይኖሠር በፊት መኖር የጀመረ ሲሆን ከተፈጠረም 400 ሚሊየን አመታትን አስቆጥሩአል ! ይህ ማለት ሳተርን ቀለበቷን ከማጥለቁአ ከ 300ሚሊየን አመት በፊት ሻርክ በምድር ውቅያኖሶቻችን ውስጥ ይንቀዋለል ነበር ማለት ነው ! 😁
Gj-1214B
NASA በ 2009 ያገኘው ፕላኔት ሲሆን በ 2017 የተረጋገጠ ከ ፀሀይ 48 የ ብርሀን አመት ርቆ የሚገኝ በውሀ የተሸፈነ ፕላኔት ነው !
እስካሁን በተደረገው ጥናት ደረቃማ ስፍራ አልተገኘም !
