en
Feedback
Save Amhara Fano 💚💛❤️

Save Amhara Fano 💚💛❤️

Open in Telegram

የተቀደሰን ነገር በእግሩ ለሚረግጥ ፥ ተመልሶም ያጎረሰውን እጅ ለሚናከስ ርኩስ መጫወቻ የማይሆን የነቃ ማህበረሰብ እስክንፈጥር ድረስ ብዕራችን አይነጥፍም።

Show more
794
Subscribers
No data24 hours
+17 days
+530 days
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+5
in 0 channels
August '26
+30
in 1 channels
Get PRO
July '26
+23
in 1 channels
Get PRO
June '26
+8
in 1 channels
Get PRO
May '26
+6
in 0 channels
Get PRO
April '26
+7
in 1 channels
Get PRO
March '26
+3
in 0 channels
Get PRO
February '26
+6
in 0 channels
Get PRO
January '26
+8
in 0 channels
Get PRO
December '25
+4
in 0 channels
Get PRO
November '25
+6
in 0 channels
Get PRO
October '25
+6
in 0 channels
Get PRO
September '25
+11
in 0 channels
Get PRO
August '25
+13
in 0 channels
Get PRO
July '25
+40
in 2 channels
Get PRO
June '25
+8
in 0 channels
Get PRO
May '25
+26
in 1 channels
Get PRO
April '25
+14
in 0 channels
Get PRO
March '25
+9
in 0 channels
Get PRO
February '25
+29
in 2 channels
Get PRO
January '25
+16
in 0 channels
Get PRO
December '24
+20
in 0 channels
Get PRO
November '24
+12
in 0 channels
Get PRO
October '24
+28
in 1 channels
Get PRO
September '24
+45
in 1 channels
Get PRO
August '24
+235
in 0 channels
Get PRO
July '24
+573
in 3 channels
Get PRO
June '24
+339
in 3 channels
Get PRO
May '24
+17
in 2 channels
Get PRO
April '24
+15
in 0 channels
Get PRO
March '24
+24
in 0 channels
Get PRO
February '24
+288
in 0 channels
Get PRO
January '24
+165
in 0 channels
Get PRO
December '23
+103
in 1 channels
Get PRO
November '23
+77
in 0 channels
Get PRO
October '23
+298
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
09 September+2
08 September0
07 September0
06 September+1
05 September0
04 September0
03 September+2
02 September0
01 September0
Channel Posts
ከብሬ ጭሷ ሿሿዎች መካከል የማልዘነጋቸው...! እኤአ Augest 14/2015 ልክ የዛሬ 10 አመት መሆኑ ነው። ብሬ ጭሷ '' የአርበኛች ግንቦት ሰባት የነፃነት ሀይሎች ፣ በዛሬው እለት ከትግሉ ደጋ
ከብሬ ጭሷ ሿሿዎች መካከል የማልዘነጋቸው...! እኤአ Augest 14/2015 ልክ የዛሬ 10 አመት መሆኑ ነው። ብሬ ጭሷ '' የአርበኛች ግንቦት ሰባት የነፃነት ሀይሎች ፣ በዛሬው እለት ከትግሉ ደጋፊ ሀገር 33 Mine Resistant Ambush Protected (MRAP vehicles) ካሚዮሎች እና በርካታ ሌሎች መሳሪያወች ድጋፍ ተደርጎልን ፣ ከወደብ በማጓጓዝ ወደትግል ሜዳ አስገብተናል።'' የሚል ዜና ከዚህ ምስል ጋር አሰራጭታ ፌሽታ በፌሽታ ያደረገችብንን ሿሿ መቼም አልረሳውም። ይሄን ምስል ስንቴ እንደፖሰትኩት የምናውቀው እኔና ያኔ እንደዛሬው አክቲቪስት ባልበዛበት ጊዜ የነበርን ወዳጆች ብቻ ነን!😁 ሁለተኛው ሞኝ የሆንበት ሿሿ ደግሞ - ብርአምጡ ነጋ '' በ6 ወር ውስጥ ትግሉን እናጠናቅቃለን'' ባለበት ሰሞን ፥ ይችን ግንባሯ ላይ 7 ቁጥር የተፃፈባት ጥጃ ምስል በተዋኒያኑ በኩል አሰራጭቶ '' ይኸው ፈጣሪ ራሱ ዘመኑ የግንቦት-7 መሆኑን በተአምር እያሳየ ነው'' ብለን የተጃጃልነውን መጃጃል መቼም አልረሳውም! አሰብ ሆኖ እንደነፍሰጡር '' ሚጥሚጣ አማረኝ ፣ አምጣልኝ'' እያለ ከባቲና ከኮምቦልቻ የሚያመላልስለት አንድ ወዳጄ ፣ በተገናኘን ቁጥር ''ምነው ያኔ ሚጥሚጣው ላይ ማላታይን ጨምሬ ገላግዬው በነበረ'' እያለ ይቆጫል!😁 ብሬንታ ጭሷ '' ሿሿ ትችያለሽ'' አይገልፀውምኮ!😁

2
አጫጭር የሶማሊያ የሱዳን የየመን መረጃዎች ሶማሊያ፦የባይዶአ ውጊያ፡ የ8ኛ ብርጌድ አዛዥ ቆስለው ወደ ሞቃዲሾ ተወሰዱ ባይዶአ — በባይዶአ በነበረው ከባድ ውጊያ የሶማሊያ ብሔራዊ ሠራዊት 60ኛ ክፍለ ጦር የ8ኛ ብርጌድ አዛዥ አብዱሌ ኢሳቅ ኢብራሂም በመቆሰላቸው ለአስቸኳይ ሕክምና ወደ ሞቃዲሾ ዲግፌር ሆስፒታል ተወሰዱ። ውጊያው በአዴን ማዶቤን በሚደግፉ የፌደራል ኃይሎች እና ለአብዲአዚዝ ላፍታጋሬን ታማኝ በሆኑት የዳራዊሽ ኃይሎች መካከል የተካሄደ ነው። በዶሎው እና ባይዶአ ከባድ ጥቃት ተፈጸመ፤ ደቡብ ምዕራብ ክልል ቱርክን ከሰሰ በሶማሊያ ዶሎው ወረዳ በሚገኘው የቀድሞው የማረሚያ ቤቶች አዛዥ ጄኔራል ማሃድ አብዲራህማን (ሹብ) መኖሪያ ቤት ላይ በተፈጸመ የአየር ጥቃት በርካታ ሰዎች ሲቆስሉ የቤት ሰራተኛ የሆነች አንዲት ኢትዮጵያዊት ህይወቷ አልፏል። ቦሳሶ ለሱዳኑ RSF የጦር መሳሪያ እና ተዋጊዎች ማስተላለፊያ ነጥብ መሆኗ ተገለጸ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ባወጣው አዲስ ሪፖርት በፑንትላንድ የምትገኘውን የቦሳሶ ወደብ ለሱዳኑ ፈጣን ደጋፊ ኃይል (RSF) የሚላኩ ተዋጊዎችን፣ የኮሎምቢያ ተዋዋዮችን እና የጦር መሣሪያዎችን ለማስተላለፍ የሚያገለግል ቁልፍ የመሸጋገሪያ ቦታ አድርጎ ለይቷታል። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት የአፍሪካ እና የአረብ ጉዳዮች አማካሪ ማስዑድ ቡሉስ ለቢቢሲ በሰጡት መግለጫ፣ የጎረቤት ሀገራትን ጨምሮ ቢያንስ 12 ሀገራት በሱዳን ለሚገኙ ተዋጊ ወገኖች ከፍተኛ የጦር መሳሪያ እና የሎጅስቲክስ ድጋፍ እያቀረቡ እንደሚገኙ ይፋ አድርገዋል። ቡሉስ የሀገራቱን ስም ለመጥራት ባይፈቅዱም፣ ሁኔታው በቅርብ ሳምንታት ውስጥ አደገኛ ደረጃ ላይ መድረሱን ጠቁመዋል። አሜሪካ በሱዳን ሙሉ ግዛት ላይ የጦር መሳሪያ እገዳ እንዲጣል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤትን ለማሳመን እየሰራች መሆኑንም አረጋግጠዋል። የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ አባላት በታኢዝ ተማረኩ፤ ከ130 በላይ የሁቲ ተዋጊዎች ተገደሉ ታኢዝ — የየመን ሠራዊት በታኢዝ ግንባር በነበረው ውጊያ የኢራን አብዮታዊ ዘበኛ አባላትን መማረኩንና ከ130 በላይ የሁቲ ተዋጊዎችን መግደሉን አስታወቀ። በሌላ በኩል ሁቲዎች ከባጅልና ቃናዊስ አራት ባሊስቲክ ሚሳኤሎችን የተኮሱ ሲሆን፣ ሰንዓ በኃይሎች በመከበቧ ምክንያት የኤሌክትሪክ አገልግሎት ማቋረጣቸው ተዘግቧል።
112
3
ይህ የፊርማ ማሰባሰብ ሂደት ተጠናቆ በስም ለተዘረዘሩት አለምአቀፍ ተቋማት አጀንዳ ሆኖ ይቀርብ ዘንድ የእናንተ ፊርማ እጅግ ወሳኝ ነው! ከስር ያለውን 👇 ሊንክ በመጫን ይፈርሙ! https://www.change.org/p/protect-amhara-civilians-in-ethiopia-investigate-the-east-wollega-zone-massacres?recruiter=1123915011&recruited_by_id=36eb5270-b6e1-11ea-b571-a1eeaa7d5a82&utm_source=share_petition&utm_campaign=share_petition&utm_term=starter_onboarding_share_personal&utm_medium=mobileNativeShare&share_id=8qhqHJjsr6
99
4
በራሱ አማራጭ መንገድ አንድ ሆኖ የማያውቅ ሁሉ ፣ በሌሎች አንድነትና ትብብር ውስጥ ገብቶ ሀሳብ የመስጠት የሞራል ልዕልና የለውም! የሰላማዊ ትግሉ ካምፕ ላይ ሰንፎ ፤ ተግባብቶና በአንድነት ተሰልፎ ተፅዕኖ መፍጠር አቅቶት ፥ ተስፋ ቆርጦ በየሰርጣ ሰርጡ የተቀመጠው ሁሉ ፥ የሰላም በሮች ሲዘጉባቸው የትጥቅ ትግል አማራጭን ተከትለው እየታገሉ ያሉ የነፃነት ሀይሎችን ፣ 24/7 ሲያብጠለጥል ውሎ ማደርን ስራው አድርጎታል! ገራሚ ነውኮ! ወይ የራሴ የሚሉት አማራጭ ላይ በርትተው ለውጥ ለማምጣት አይንቀሳቀሱ ፤ ወይ ከአገዛዙ ጋር አይደመሩ ፥ በሌሎች አማራጭ መንገድ ላይ እየተደነቀሩ እኚኚ ማለት ብቻ!😉 በሰላማዊ ትግሉ አንድ መሆን ያልቻለውና ብልፅግና አንቦ ውሃ ሆኖበት የበታተነው የከሸፈ ሀይል ፣ ሌላ ስራ ሲያጣ በአፈሙዝ እየታገሉ ስላሉ ሀይሎች አንድነትና ትብብር ሲተነትን ውሎ ያነጋል! ''እኔ አውቅላችኃለሁ'' እያለ መሰገጡ እንጂ መተንተኑና ሀሳብ መስጠቱኮ ባልከፋ ነበር! ''ወይ አይሰሩ ወይ አያሰሩ'' አለ ዘፋኝ!😁
105
5
''በታጣቂ'' ስም ያደራጀውን PLC ይዞ ከኤርትራ 1 ኪ.ሜትር ሳይንቀሳቀስ ሩጫውን በመገበር ያጠናቀቀው ብርአምጡ ነጋ ፤ "ህወሓት እና ፋኖ ተስማምተው 10 ኪሎ ሜትር እንኳን አብረው መሄድ አይችሉም+1
''በታጣቂ'' ስም ያደራጀውን PLC ይዞ ከኤርትራ 1 ኪ.ሜትር ሳይንቀሳቀስ ሩጫውን በመገበር ያጠናቀቀው ብርአምጡ ነጋ ፤ "ህወሓት እና ፋኖ ተስማምተው 10 ኪሎ ሜትር እንኳን አብረው መሄድ አይችሉም!'' ብሎ የማውራቱን የሞራል ልዕልና ከወዴት አገኘው?😉 የልጥ ፓርቲ ሊቀመንበርኮ ቀልዱ አይጠገብም!😁
115
6
alert ‼️ ጥንቃቄ 🔔 በምስራቅ ወለጋ ኪረሙ ወረዳ በበርካታ ቀበሌዎች ላይ አዲስ የጥቃትና የዘረፋ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ታውቋል የኦሮሚያ የፀጥታ አካላት ካደራጇቸው ዘራፊ ቡድኖች ጋር ከኪረሙ
alert ‼️ ጥንቃቄ 🔔 በምስራቅ ወለጋ ኪረሙ ወረዳ በበርካታ ቀበሌዎች ላይ አዲስ የጥቃትና የዘረፋ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ታውቋል የኦሮሚያ የፀጥታ አካላት ካደራጇቸው ዘራፊ ቡድኖች ጋር ከኪረሙ ከተማ በመነሳት በተለያዩ አቅራቢያ በሚገኙ የዐማራ መንደሮችና ቀበሌዎች ላይ አዲስ የጥቃትና የዘረፋ እንቅስቃሴ ለማካሄድ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን የመረጃ ምንጮች ጠቁመዋል። እንደ ምንጮቹ ዘገባ፣ ይህ የዘረፋና የጥቃት ዝግጅት ያነጣጠረባቸው ቀበሌዎች፦ * ሀሮ አዲስ አለም፣ * ኖሌ ገብርኤል፣ * ስደን፣ * ቦቃ፣ * ነጭሎ፣ * ወዴሳ ዲማ እና ሌሎች አቅራቢያ የሚገኙ ቀበሌዎች እንደሆኑ ታውቋል። በአካባቢው የሚገኙ ነዋሪዎችና የመረጃ ምንጮች እንደሚሉት፣ ከኪረሙ ከተማ ተነስተው ጥቃት ለማድረስ የሚዘጋጁት አካላት በእነዚህ ቀበሌዎች ላይ ከፍተኛ የንብረት ዘረፋና ውድመት ለማድረስ አቅደው እየተንቀሳቀሱ በመሆናቸው የአካባቢው ነዋሪዎች አስፈላጊ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል:: (ከቦታው የተላከ) በማጋራት መረጃውን ተደራሽ ያድርጉ።
196
7
በድጋሚ ለማስታወስ ያህል! በአማራ የህልውና ትግል ዙሪያ ያላችሁ ተቋማት ፣ ጋዜጠኞች ፣ አንቂዎች ፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና ሌሎችም ፤ ላለፉት አመታት በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈፀሙና እየተፈፀሙ
በድጋሚ ለማስታወስ ያህል! በአማራ የህልውና ትግል ዙሪያ ያላችሁ ተቋማት ፣ ጋዜጠኞች ፣ አንቂዎች ፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች እና ሌሎችም ፤ ላለፉት አመታት በአማራ ህዝብ ላይ የሚፈፀሙና እየተፈፀሙ ያሉ ጭፍ- ጨፋ ዎችን ፣ ግድያዎችን ፣ የአስገድዶ የመድፈር ወንጀሎችን ፣ ቶርቸርና አግቶ መሰወር ፣ ማፈናቀል ፣ ንብረት የማውደም ድርጊቶችን አንድ በአንድ ከዝርዝር አስረጂ ጋር አጠናቅሮ የመያዝ ባህላችንን ማዳበር ያስፈልጋል! እንደፕሮጀክት ተይዞ መሰራትም ይኖርበታል። በዚህ ረገድ በተበታተነ መልኩ አንዳንድ ስራዎችን ለመስራት እየተሞከረ ቢሆንም መናበብና በአንድ ቋት መረጃዎች ተደራጅተው የሚቀመጡበት ሁኔታ መፈጠር መቻል አለበት! ይህንን ሂደትም አፋብን እንደተቋም በባለቤትነት ማስተባበር ባለድርሻ አካላትን ማሳተፍና ሂደቱንም መከታተል መቻል ይኖርበታል ብዬ አስባለሁ!
184
8
ወንድማችን '' ምዕራባውያን በአብዛኛው በኢትዮጵያ ጉዳይ አሳስቧቸው ፈጣን መግለጫ የሚሰጡትና ጫና የሚያሳድሩት ከአማራ ውጭ ባሉ ኮዞች ነው። ይህ ለምን የሆነ ይመስልሃል?'' የሚል ጥያቄ ጠይቆኛል። በእኔ መረዳት ልክ በሚከተሉት 5 ምክንያቶች የመጣ ተዳማሪ ውጤት ይመስለኛል። 1ኛ. ዘመናትን የተሻገረ ትርክት አለመቀየሩ - ፋሽስት ጣሊያን '' አማራውን በጦርነት ማንበርከክ አይቻልም። ኢትዮጵያውያንን ቅኝ ለመግዛትና ለማንበርከክ ሌሎች ህዝቦች በአማራው ላይ እንዲነሱበት ማድረግ ነው!'' ብለው በነሮማን ፕሮቸስካ አማራውን ፀረ-ዴሞክራሲ ፣ ጨቋኝ የሆነ አስተሳሰብ ያለው ማህበረሰብ እንደሆነ በማድረግ ሀሰተኛ ትርክ ፅፈው ፥ በተለያዩ ቋንቋዎች አስተርጉመው ለየኤንባሲዎቹና ቆንስላዎቹ ያሰራጩበት እውነታ ለዚህ አንዱ ማሳያ ነው። 2ኛ. የአማራው ኢሊት ስንፍና - ከሀገር ውስጥ እስከ ውጭ ሀይሎች በአማራ ህዝብ ላይ ጥላቻና ሀሰተኛ ትርክትን እየፈጠሩ መፅሐፍት ሲፅፉ ፣ አርቲክሎችን ሲያሳትሙ ፣ ... '' ኧረ ይሄ ፍፁም ስህተት ነው'' ብለው ለማረምና የተዛባውን ለማስተካከል ከመትጋት ይልቅ ከእነኚህ ሀይሎች ጋር አብረው ሲላላኩና ሲደግፉ ፣ ገሚሶቹም በዝምታ ሲመለከቱ የኖሩ በመሆናቸው የመጣ ነው። 3ኛ. ምንም እንኳ በቅርብ የሚታዩ አበረታች መነሳሳቶች ቢኖሩም በተለያዩ የአለም ክፍሎች የሚኖሩ የአማራ ልጆች (ምሁራን) በተደራጀና በተቀናጀ መልኩ የሀገራትና የተቋማትን በራፍ አንኳኩተው ማስከፈት ፣ ተፅዕኖ የሚፈጥር የዲፕሎማሲ ስራ መስራትና የአማራን ህዝብ ሁለንተናዊ ገፅታ ማጉላት ባለመቻላቸው የተፈጠረ ነው! 4ኛ. ባለፉት አራት አስርት አመታት ውስጥ የአማራ ህዝብ በሀገረ-መንግስቱ ውስጥ የነበረው ተፅዕኖ ውስንነትና አማራውን ወከልነው ያሉት አካላትም ከተላላኪነትና እጅ አስታጣቢነት የዘለለ የአማራውን ኮዝና ሁለንተናዊ ፍላጎት የማስረዳት ሚና ያልነበራቸው መሆኑም ቀላል የማይባል ተፅዕኖ ነበረው። 5ኛ. የአማራው የህልውና ትግል በውስጣዊና አውራጃዊ ፈተና እየተፈተነ የሚገኝ ፣ እንደፖለቲካ ማህበረሰብ በጋራ አጀንዳዎቹ ላይ የጋራ አስተሳሰብ መገንባትና ለነዚያ የጋራ አጀንዳዎቹ የሚመጥን ፣ የተፅዕኖ ደረጃው ላቅ ያለ ተቋማዊ የትግል ስርአት ውስጥ ፈጥኖ መግባት አለመቻሉም የራሱ የሆነ ድርሻ አለው። መስራት ያለብንም በእነዚህ ሰፊ ዝርዝር ጉዳዮች ባሏቸው መሰረታዊ ጭብጦች ላይ መሆን አለበት!
181
9
''ብሔራዊ ምክክር'' የተሰኘውና ለ40 ተከታታይ ቀናት የተላለፈው አገዛዛዊ ድራማ ለአማራ ህዝብ የሚከተሉት 3 ጠቀሜታዎች ነበሩት። - ኦህ-Dead ለአማራ ህዝብ ያለውን ጫፍ የረገጠ ጥላቻና ዘረኝነት በሚገባ እንዲመለከት አድርጎታል። ይህ ሂደት ላለፉት 8 አመታት ከዚህ አገዛዝ ጋር ተሰልፈው በገዛ ህዝባቸው ላይ የእልቂትና የመከራ ድግስ አጋፋሪ የነበሩ ከአብራኩ የወጡ አመራሮች ጭምር እየተጓዙበት ያለውን አደገኛ መንገድ በገሀድ እንዲመለከቱ ያስቻለም ነበር። - ላለፉት አስርት አመታት የአማራን ህዝብ መዋቅራዊ በመሆነ መልኩ ለማጥቃት ጥቅም ላይ ይውሉ የነበሩት የጥላቻ ትርክቶች ፣ በከፍተኛ ደረጃ ታድሰውና ጎልብተው እንዲሁም አዳዲስ ፈርጆች ተጨምረውላቸው ስርአታዊና መዋቅራዊ በሆነ መልኩ መቀጠላቸውን አረጋግጦለታል። - በእልቂትና በደም መፋሰስ ላይ የተገነባው ይህ አገዛዝ - ሀገሪቱንና ህዝቧን ምን አይነት አደጋ ውስጥ እንደከተተ ብሎም ይህን ስርአታዊ አደጋ ለመቀልበስ ብቸኛው የመፍትሔ አቅጣጫ ምን እንደሆነ በቅጡ እንዲረዳ አስችሎታል። አብዛሀኛው ህዝባችን ይህን አስረጂ የማያሻው ነባራዊ እውነታ መረዳቱ ደግሞ ፣ ለህልውና ትግላችን ከፍተኛ አቅም የሚፈጥር የንቃት ደወል ነው!
209
10
ግራ መጋባታችንን በ3 ምሳሌዎች ላሳይህ! ✅'' አፋብን የ5 አመት የትግል ስትራቴጂክ ዕቅድ ገምግሞ አፀደቀ!'' የሚል ዜና ቢወጣ ከሚሰጡ አስተያየቶች ጥቂቶቹ ፦👇 '' እኛ በዚህ ክረምት ያልቃል ስንል ጭራሽ 5 አመት ? '' '' ህዝባችን የተራዘመ ጦርነት መቋቋም አይችልም!'' '' ምን ማለት ነው ይሄ እንዴት የረዥም ጊዜ እቅድ ታቅዳላችሁ?'' '' ተስፋችሁን ቁረጡ በሉና..😉'' ወዘተ የሚል ይገኝበታል። ✅'' አፋብን አንባገነኑን አገዛዝ በአጭር ጊዜ ለማስወገድ በኢትዮጵያ ሰማይ ስር ካሉ ተመሳሳይ ፀረ-አገዛዝ ትግል ከሚያደርጉ ኃይሎች ጋር ትብብርና ጥምረት ፈጠረ'' የሚል ዜና ሲወጣ ከሚጎርፉት በለቅሶ የታጀቡ አስተያየቶች መካከል ደግሞ ፦👇 '' በቃ ትግሉን ሸጣችሁት ማለት ነው ?'' '' ጭራሽ ከወያኔ ጋር ትብብር ትፈጥራላችሁ?'' '' መቼም ከኦLA ጋር አይደለም አብራችሁ መስራት ጎን ለጎንም መጓዝ የለባችሁም!'' '' ያ ሁሉ አማራ ካለቀበት የጉሙዝ ሀይሎች ጋር ተባበራችሁ ከምንባል ሞታችንን እንመርጣለን'' '' ብቻችሁን ካልሆነ በስተቀር የማንም ጥገኛ ሆናችሁ ኢትዮጵያ ነፃ አትወጣም'' '' ዱሮም ብለን ነበር። ባልተቀደሰ ጋብቻ ትግሉን ለወያኔና ሻዕቢያ ሸጡት'' '' ከህወሓት ፣ ከኦLA ፣ ከኦጋዴን ፣ ከጉሙዝ ፣ ከአፋር ፣ ...ኃይሎች ጋር አይሁን እንጂ መተባበሩ ጥሩ ነው!😉'' ወዘተ ይሉሃል። ✅'' አፋብን የአማራ ህልውና የሚከበረውም ሆነ ጥቅምና ፍላጎቶቹ የሚጠበቁት ራሱን የቻለ ሀገር ሲሆን መሆኑን አስታወቀ'' የሚል ዜና ቢመጣ ደግሞ ፦ '' አማራው ሀገሩ ኢትዮጵያ ናት'' '' ጭራሽ ልትገነጥሉት ነው ?'' '' የሻዕቢያና የግብፅን እቅድ እያስፈፀማችሁ ነው!'' '' አባቶቻችን ያቀኗትን ሀገር ለማን ሰጥታችሁ ታፈገፍጋላችሁ?'' '' ከሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች ጋር ተባብራችሁ ሀገርን ነፃ ማድረግ እንጂ የምን ሀገር ምስረታ ነው!'' '' ይሄ ፀረ- አማራ አካሄድ ነው!'' ወዘተ የሚል የሚዲያ ጩኸት ይቀልጥልሃል! የተቋምም ሆነ የኤሊት ሚና ህዝቡ የሚፈልገውን ብቻ ሳይሆን በዋናነት የሚያስፈልገውን ነገር ፣ በእውቀት ፣ በመርህና በአሰራር ለይቶ ያንን ለማሳካትና እውን ለማድረግ አቅዶ መታገል ነው! ተቋማዊነት ይለምልም!
356
11
No text...
282
12
#ኢትዮጵያዊ ነን” በሚለው ብዙኃንና “ኢትዮጵያዊ አይደለንም” በሚሉ ኦነጋውያን መካከል የሚካሄደው “አገራዊ ምክክር ጉባዔ” #ቢቢሲ ስለ ምክክር ኮሚሽን ተብዮው መሰንበቻ ዛሬ ያወጣው ዘገባ፣ መድረኩን በየዋህነት “አገራዊ ምክክር” የሚደረግበት ገለልተኛ መድረክ ነው ብለው ለሚያምኑት ሁሉ፣ በውስጡ እየተፈጸመ ያለውን ዐቢይ አሕመድ መር ኦነጋዊ ሸፍጥ ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይ ነው። #ዘገባው እንደሚያሳየው፣ ምክክር ተብዮው እየተደረገ ያለው “ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ነን፤ አዲስ አበባም የኢትዮጵያ ዋና ከተማና፣ በአስተዳደሯም ራሷን የቻለች የሁሉም ኢትዮጵያውያን የፌዴራል ከተማ ትሁን” በሚሉ ብዙኃን ኢትዮጵያውያን እና “አዲስ አበባ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ሳትሆን የኦሮሞ ብቻ ናት፤ ስለሆነም የኦሮሚያ አካል መሆን አለባት” የሚል አቋም በያዙ፣ ኢትዮጵያዊ አይደለንም በሚሉ ኦነጋውያን መካከል ነው። በእነዚህ ሁለት አቋሞች መካከል ያለው ልዩነት ተራ የሐሳብ ልዩነት ሳይሆን፣ መሠረታዊ የሀገር ማንነት ጥያቄ ነው። #ከሁሉም ይበልጥ አስገራሚው ደግሞ፣ “አዲስ አበባ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ሳትሆን የኦሮሞ ብቻ ናት፤ ስለሆነም የኦሮሚያ አካል መሆን አለባት” የሚል አቋም የሚያራምዱትን፣ ኢትዮጵያዊ አይደለንም የሚሉትን የኦነጋውያን ቡድን የሚመራው፣ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትርነት የተሰየመው ዐቢይ አሕመድ የሚባለው ጉድ መሆኑ ነው። #በሌላው ዓለም፣ የአንድ ሀገር መሪ ዋናው ተግባር የዚያችን ሀገር የጋራ መሠረት፣ የጋራ ዋና ከተማና የጋራ ማንነት ማጠናከር ነው። ዐቢይ አሕመድ የሚባለው ኦነጋዊ ጉድ ግን፣ በጠቅላይ ሚኒስትርነት ተሰይሞ የሚገዘግዛትን አገር “አላውቅሽም” ብሎ፣ “ኢትዮጵያዊ አይደለንም፤ አዲስ አበባ የሁሉም ኢትዮጵያውያን ሳትሆን የኦሮሞ ብቻ ናት፤ ስለሆነም የኦሮሚያ አካል መሆን አለባት” የሚለውን ኦነጋዊ ቡድን ይመራል። #መስፍን አርአያ የሚባለው የዐቢይ አሕመድ ከዳም በተደጋጋሚ ኮሚሽኑ “ተመካካሪዎች የሚመካከሩበት መድረክ ነው” ሲል ይሰማል። ይህ ከሆነ ታዲያ፣ “አዲስ አበባ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ርዕሰ ከተማ መሆኗን ዕውቅና ይሰጣት” የሚለው ጉዳይ፣ ከታች ጀምሮ በተካሄደው ምክክር ተብዮው ያልተነሳ፣ ያልተወያዩበትና “ተመካካሪዎቹ” ያልጠየቁት ጉዳይ ሆኖ ሳለ፣ ድንገት “ከበላይ የመጣ ሐሳብ” ተብሎ በቃለ ጉባኤ ውስጥ እንዴት እንዲገባ ተደረገ? #በእውነቱ ይህ ብቻ የምክክር ተብዮውን ኦነጋዊ ማጭበርበሪያ መሆኑን ለማሳየት ከበቂ በላይ ነው። ከታች ያልተነሳን ጉዳይ ዐቢይ አሕመድ ከላይ ስላወረደው ብቻ፣ ተመካካሪዎቹ ተብዮዎች ያልጠየቁትን እንደጠየቁ አስመስሎ፣ ያልተወያዩበትን እንደተወያዩበት አድርጎ በቃለ ጉባኤ ማስፈር ምክክር አይደለም። ይህ አብነት የሚያሳየው ምክክር ኮሚሽን ተብዮው ምድረካ ኦነጋዊ የማይጠረቃ ፍላጎትን በሕዝብ ስም ለማስፈጸም የተዘረጋ ኦነጋዊ ማጭበርበሪያ ስለመሆኑ በተደጋጋሚ የተናገርነውን የሚያረጋግጥ ብቻ ነው። #የነ ዐቢይ አሕመድ ኦነጋዊ ቲያትር በዚህ ብቻ አያበቃም። አብዛኞቹ “ተመካካሪዎች” አዲስ አበባ ራሷን የቻለች የፌዴራል ከተማ ትሁን ሲሉ፣ ጥቂቶቹ ደግሞ የኦሮሚያ ትሁን ማለታቸውን የቢቢሲ ዘገባ ያሳያል። ይህ እውነታ “አብዛኞቹ እንዲህ አሉ፣ ጥቂቶቹ ደግሞ እንዲህ አሉ” ተብሎ በቃለ ጉባኤ እንዲሰፍር ሲባል ግን፣ “አብዛኞቹ” እና “የተወሰኑ” የሚሉት ቃላት እንዲጠፉና ሁለቱም “አማራጭ አንድ፣ አማራጭ ሁለት” ተብለው እንዲመዘገቡ ተደርጓል። #ይህ ተራ የቃላት ምርጫ አይደለም። ይህ ብዙኃኑን ከቃለ ጉባኤ ላይ የማጥፋት፣ ጥቂቶችን ወደ ብዙኃን ደረጃ የማሳደግ፣ እውነተኛውን የድምፅ ሚዛን ደብቆ የጥቂቶቹን ፍላጎት ሕዝባዊ አማራጭ አስመስሎ የማቅረብ ኦነጋዊ አሻጥር ነው። #ቁጥርን አጥፍቶ፣ የብዙኃኑንና የጥቂቶቹን ልዩነት ደብቆ፣ ሁለቱንም እኩል “አማራጭ” ብሎ መመዝገብ እውነታን መዝግቦ ማስቀመጥ አይደለም፤ እውነታን ቀይሮ ለተፈለገው ፖለቲካዊ ውጤት ማመቻቸት ነው። መስፍን አርአያ “ሁሉም ነገር በቃለ ጉባኤ ተይዟል” የሚለን ሆዳም ስለኾነ እንጂ ቁጥር እየተደበቀ፣ የብዙኃኑና የጥቂቶቹ ልዩነት እየተፋቀ፣ ሁለቱ እኩል አማራጭ እየተደረጉ ከተጻፈ፣ የእውነታ መዝገብ ሳይሆን እውነታ የተጣመመበት ድሪቶ መሆኑ ጠፍቶት አይደለም። #ከዚህ በተጨማሪ፣ ቢቢሲ ባቀረበው ዘገባ መሠረት፣ “አጠናቃሪዎች” የተባሉት ሰዎች ራሳቸው እንደ ተመካካሪ ሆነው ኦነጋዊ ሐሳብ እንደሚሰጡ፣ “ይህ መሆን አለበት” ብለው እንደሚከራከሩ መስፍን አርአያ ራሱ አምኗል። ኦነጋዊ ፍላጎታቸውን በተመካካሪው ላይ እንዲጭኑ የተሰማሩ ኦነጋውያንን መስፍን አርአያ የሚባለው ጉድ ግን እንደ ባለሙያ ነው የሚቆጥራቸው። #የኦሮሞ ባለሥልጣናት በአካልና በስልክ ጭምር ጫና ለመፍጠርና ጣልቃ ለመግባት ሞክረዋል የሚል አቤቱታ በተሳታፊው ሁሉ ቀርቧል። ከታች ያልተነሳ አጀንዳ “ከበላይ” እየወረደ፣ አጠናቃሪዎች ከአጠናቃሪነት ወጥተው ተከራካሪ እየሆኑ፣ በባለሙያነት ስም ኦነጋዊ ፍላጎትን እየጫኑ፣ ባለሥልጣናትም ጫና ያደርጋሉ የሚል ቅሬታ እየቀረበበት ያለው የመስፍን አርአያ ኮሚሽን አሁን መጠየቅ ያለበት “ሂደቱ ችግር አለበት ወይ?” የሚል ሳይሆን፣ “ከዚህ ውስጥ ምክክር ሊባል የሚችል የቀረው ምንድን ነው?” የሚል ነው። #ይህ ሁሉ አንድ ላይ ሲታይ፣ ምክክር ኮሚሽን ተብዮው የሕዝብን ፍላጎት በገለልተኝነት የሚመዘግብ መድረክ ሳይሆን፣ ቀድሞ የተያዘን ኦነጋዊ አጀንዳ በ“ሕዝባዊ ምክክር” ማኅተም ለማጽደቅ የተዘጋጀ መሣሪያ መሆኑን ነው። ከታች ያልመጣን ከላይ አውርዶ፣ ያልተባለን እንደተባለ ጽፎ፣ የብዙኃኑን ድምፅ አጥፍቶ፣ የጥቂቶቹን ፍላጎት ከብዙኃኑ ጋር እኩል አማራጭ አድርጎ ማቅረብ ከሆነ፣ ይህንን “ምክክር” ማለት ለቃሉ ራሱ ስድብ ነው።
295
13
#ከመርማሪ ኮሚሽን እስከ ምክክር ኮሚሽን፡ ኦነጋውያን ላለፉት ኀምሳ ዓመታት ጠባብ የፖለቲካ ፍላጎታቸውን በሕዝብ ላይ ለመጫን የተጠቀሙባቸው ተለዋዋጭ ስልቶች! 👇 https://drive.google.com/file/d/1iN-EKqd3ZsjyMl_cxcAGp8m5B9wZgmzZ/view?usp=sharing
227
14
♦ ማስታወሻ ደብተራችሁን አውጡ! – እነ ጸጋዬ አራርሳ ያመለጣቸው የ16ኛው ክፍለ ዘመን የታሪክ ትምህርት 😁 1. የኦሮሞ ህዝብ መነሻና ጥንታዊ መኖሪያ ፤ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን ታላቅ የህዝብ እንቅስቃሴና ፍልሰት በፊት፣ የኦሮሞ ህዝብ ዋና መገኛ ግዛት በደቡባዊ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ቦታዎች እና በሰሜን ኬንያ አዋሳኝ ስምጥ ሸለቆ አካባቢዎች ነበረ። የመሃል ማዕከሉ "ማዳ ወላቡ" (በአሁኑ የባሌና ቦረና አዋሳኝ) በመባል ይታወቃል። የጎሳ አደረጃጀት ፤ ቦረና (በደቡብና ደቡብ ምዕራብ) እና ባሬንቱ (በደቡብ ምስራቅ) የኑሮ ዘይቤ ፤ በዋነኝነት ከብት አርቢ የነበረና ህይወቱ ከግጦሽ መሬትና ከዝናብ ዑደት ጋር የተቆራኘ ነበረ። 2. የ16ኛው ክፍለ ዘመን የኦሮሞ መስፋፋት (Oromo Expansion / Movement) ከ1520ዎቹ ጀምሮ በክርስቲያኑ የኢትዮጵያ መንግሥት እና በአዳል ሱልጣኔት (በአህመድ ግራኝ) መካከል በነበረው አውዳሚ ጦርነት ሳቢያ የተፈጠረውን የኃይል ክፍተት በመጠቀም፣ የኦሮሞ ህዝብ እንቅስቃሴ በሶስት ዋና ዋና አቅጣጫዎች ተካሄዷል ። ሀ. ወደ መካከለኛውና ምዕራብ ኢትዮጵያ የመጫ እና የቱለማ ቅርንጫፎች ወደ ሸዋ፣ ወለጋ፣ ኢሉባቦር፣ ጂማ እና ከፋ አካባቢዎች። ለ. ወደ ምስራቅ ኢትዮጵ ፤ የባሬንቱ ወገኖች (ኢቱ እና ሀምባና) ወደ ሐረርጌ እና አርሲ። ሐ. ወደ ሰሜን ኢትዮጵያ ፤ የወሎ እና የጁ ኦሮሞዎች መካከለኛው ሸዋን አቋርጠው እስከ ወሎ፣ ደቡብ ትግራይ እና ጎንደር አዋሳኝ። 3.በOromo Expansion / Movement የማህበራዊና ስነ-ህዝብ ለውጦች (የጠፉና የተዋሃዱ ብሔሮች ፤ የማስፋፋት ሂደቱ በየ8 ዓመቱ በሚካሄደው የገዳ "ሉባ" ዘመቻ እንዲሁም በባህላዊ ውህደት ስርዓቶች (ሞጋሳ እና ጉዲፈቻ) አማካኝነት ተከናወነ። በዚህ ሳቢያ የሚከተሉት ጥንታዊ ህዝቦችና መንግሥታት ታሪካዊ ህልውናቸውን አጥተዋል ወይም በማህበረሰቡ ውስጥ ቀልጠዋል፦ ሀ. ጋፋት ፤ በአባይ ወንዝ ዙሪያና በምስራቅ ጎጃም/ወለጋ ይኖሩ የነበሩ ሲሆን፣ በሂደት ቋንቋቸውና ማንነታቸው ጠፍቷል ። ለ. የዳሞት መንግሥት ፤ ህዝቡ ወደ ሰሜን (ጎጃም) ለመሰደድ ተገዷል፤ የቀረውም በኦሮሞ ማንነት ውስጥ ቀልጧል ። ሐ. ፈጠጋር እና ጋንጅ ፤ በመካከለኛውና ምስራቅ ኢትዮጵያ (ሸዋና አርሲ) የነበሩ ህዝቦች ሲሆኑ፣ በሞጋሳ ስርዓት ተዋህደዋል። መ. የእንጅናርያ መንግሥት፤ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የነበረ ባለጸጋ የኦሞቲክ/ሲዳማ መንግሥት ሲሆን፣ በሊሙ ኦሮሞዎች እንቅስቃሴ ፈርሷል። ሠ. ሐዲያ እና ሲዳማ ፤ ሰፊ ግዛታቸውን ያጡ ሲሆን፣ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ህዝባቸው በሞጋሳ ስርዓት ተዋህዷል ። 4. ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በፊት የአዲስ አበባ (በረራ) ገጽታ ፦ አሁን አዲስ አበባ የምትባለው ስፍራ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በፊት በታሪክ ማህደሮች "በረራ" በሚል ስም የምትታወቅ የኢትዮጵያ ነገሥታት (የሰሎሞናዊው ሥርወ-መንግሥት) ዋና ከተማና የንግድ ማዕከል ነበረች። እንደ አፄ ዳዊት፣ አፄ ይስሐቅ እና አፄ ዘርአ ያዕቆብ ያሉ ነገሥታት ቤተ-መንግሥት የሰሩበት ስፍራ ነበረች። በጊዜው በአካባቢው ይኖሩ የነበሩት ነባር ህዝቦች፦ የአማራ ህዝብ ፤ የመካከለኛው ሸዋ የክርስቲያኑ መንግሥት እምብርት በመሆኑ በስፋት ይኖርበት ነበር። የጋፋት፣ የጉራጌ እና የአገው ህዝቦች በአሁኑ አዲስ አበባ እና ዙሪያዋ ባሉ የሸዋ ክፍሎች ከጥንት ጀምሮ ይኖሩ የነበሩ ሴማዊና ኩሻዊ ቋንቋ ተናጋሪዎች ነበሩ። ማጠቃለያ ! የታሪክ ድርሳናት እንደሚያስረዱት፣ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን የታላቁ ህዝቦች እንቅስቃሴ በፊት አሁን አዲስ አበባ የምትባለው "በረራ" አማራ፣ ጋፋት፣ ጉራጌ እና አገው ህዝቦች ይኖሩባት የነበረች ታሪካዊ ቦታ እንጂ የኦሮሞ ህዝብ ነባር መኖሪያ አልነበረችም። እርግጥ ነው፣ የወቅቱ የፖለቲካ ተንታኞች ይህን የታሪክ ሂደት አይፈልጉትም ፤ አሁን ባለው ህገ-መንግስት መመራት አለብን የሚል ሙግት ያቀርባሉ፤ ሆኖም የታሪክ እውነታውን መካድ ግን ፈጽሞ አይቻልም ፤ ለዘላቂ መፍትሄ መሰረት አይሆንም። የታሪክ ድርሳናት ማጣቀሻዎች (Sources) • Prof. Richard Pankhurst – "The Ethiopian Borderlands" (1997) • Prof. Taddesse Tamrat – "Church and State in Ethiopia (1270-1527)" • Abba Bahrey – "Zenahu Galla" (1593) • Prof. Mohammed Hassen – "The Oromo of Ethiopia: A History 1570-1860" • Ulrich Braukämper – "Islamic History and Culture in Southern Ethiopia" • Prof. Getachew Haile –"የአባ ባሕርይ ድርሳናት"
262
15
No text...
192
16
የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ቴዎድሮ ሩዝቬልት(Theodore Roosevelt) አንድ ዝነኛ አባባል አላቸው ይህም "ለድርድር ወይም ለውይይት ከመቀመጥህ በፊት ከአጠገብህ ጠብደል ዱላ መኖሩን ማረጋገጥ አለብህ" የሚል ነው ብዙ ሰዎች ቀደም ብሎ ስለ ምክክር ኮሚሽኑ ሲነገራቸው ፈጽሞ መቀበል አልፈለጉም ነበር። ማዕከላዊ ስልጣን እና ጉልበት ያልያዘ የትኛውም ኃይል በየትኛውም መንገድ ጥቅሙን ለማስከበር አይደለም በግለሰብ ደረጃ የመከበር ዕድል እንደሌለው ግልጽ ነው። ምክክር ኮሚሽኑ "የቄጠማ ምርኩዝ" ከመሆን ያለፈ ምንም ለውጥ እንደማያመጣ አቋም ወስዶ አርፎ መቀመጥ የነበረበት አንድ ሰው ዛሬ እሳት ለብሶ እሳት ጎርሶ የኦህዴድ ባለስልጣናት እኮ ክብራችን ነኩት እያለ ፀጉሩን እየነጨ ነው። ከአምስት ዓመታት በፊት አዲስአበባ እንዳትገባ ኬላ ላይ ሲመልሱህ እነ መራራ ጉድና አዲስ አበባ በሮችን እንዘጋለን ሲሉህ ጃዋር መሐመድ ዱላ ይዞ ድሃ በቆጠበው ገንዘብ የተሰራ ቤት እየሰበረ በመኪና ጭኖ እያመጣ ሲያስገባ አዲስ አበባ እርባና ቢስ ከተማ እናደርጋታለን በማለት ሽመልስ አብዲሳ ሲያቅራራ አስከትሎም ሸገር ብሎ አዲስአበባን በሲባጎ ገመድ ሸምቀቆ ውስጥ ሲያስገባት ኮሪደር ልማት በሚል ውጫዊ የልማት ገፅታ ወስጠ ማኅበረሰባዊ ስሪቱ ሲበጠስ ከተማው መዋቅር 60% ሲነጠቅ ያልታየህ ወዳጄ ዛሬ አንድ የኦህዴድ ባለጊዜ ባለ ስልጣን"ቀነዓ ያደታ" ምክክር ኮሚሽኑ ላይ የተከበሩ ፕሮፌሰር አዋረደ ተሳደበ አስጠነቀቀ በሚል ለቅሶ ብታላዝን ሙሾ ብታወርድ የሚለወጥ ነገር የለም። ሩዝቬልት እንዳለው ከአጠገቤ ምን አለ ነው ብለህ መጠየቅ ያለብህ!? ይሄ ምክክር ኮሚሽን ከወጣበት ገንዘብ ከፈሰሰው ጉልበት ከወጣው የሰው ሐብት ይልቅ ያስገኘው አንድ ትልቅ ጥቅም ኦህዴድ-ብልጽግና በራሱ ድግስ ዕራቁቱን የታዬበት ጥቂትም ቢሆን በደንብ ያላወቁት እንዲያውቁት መሆኑ ነው።
241
17
+2
No text...
215
18
These three evil sprited Eritreans are the ones who steered Oromo nationalism and prevented reconciliation with Ethiopia! 1) Professor Asmarom Legesse (They dubbed him *Abba Gada* because he wrote—under the guise of anthropology and the like—criticizing his own country and people.) This professor spent his time writing based on the false, anti-Ethiopian propaganda of Ciurletti—Mussolini’s chief fascist "scholar" and advisor on East Africa. 2) Tesfaye Gebreab (They trusted him and even erected a monument in his honor because he wrote falsehoods while disparaging his own people.) 3) Dr. Samuel Kifle (He is steering them toward irreconcilable hatred under the guise of "consultation.") Asmarom Legesse and his ilk did this from abroad, citing fascist anti-Ethiopian propaganda to drive a wedge between Oromo nationalism and Ethiopia. Dr. Samuel, meanwhile, has been doing so from within Addis Ababa University, operating from the halls where "consultations" and similar forums take place.
182
19
የኦሮሚያው ፓብሎ ኤስኮባር...! '' መከላከያና ልዩ ሀይል ወደወረዳው ሲገባ ነፍጠኛን ከዚህ አካባቢ አፅ-ዱ-ልኝ እያለ በነፍስ ወከፍ እስከ 70ሺህ ብር የሚከፍለው ፤ የአርሷደሩ ማዳበሪያ ሲመጣ በቀጥታ የሚረከበውና በውድ የሚሸጠው ፤ ባለሀብቶችን እያስፈረጀ በማሳሰር ከፍተኛ ገንዘብ የሚቀበለው ፤ ማሳገትና ማስገደል ዋና የገቢ ምንጩ የሆነለት ፣ ከኖኖ እስከ ወሊሶ ፤ ከዳርጌ እስከ ወልቂጤ እንደመንግስት የሚቆጠረው ፤ ሰማዩም ምድሩም የኔ ነው ያለ ፤ በቀጠናው ለሚፈፀመው እያንዳንዱ እልቂት እጁ ያለበት ፥ ስልጣን ሳይኖረው ባለስልጣናትን እንደፈለገ የሚያሽከረክረው ፣ ልክ እንደሲሲሊ ማፊያዎች ሁሉ አደገኛ የወንጀል ቡድኖች ያሉት ፥ አረመኔው ፣ ጨካኙ የኦሮሚያው ፓብሎ ኤስኮባር .....!'' ስለዚህ አደገኛ ሰው ማንነትና ዝርዝር መረጃዎችን አጠናቅረን እንመለሳለን! በቀንም ሆነ በጨለማ የፈፀማችሁት እልቂትና ግፍ ሁሉ ከማንም የተሰወረ አይደለም! በግፍ የተጨፈጨፉ ወገኖቻችንን ነፍስ ይማር!😥
148
20
+1
No text...
134