247
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-230 days
Posts Archive
247
“I have delayed too much in loving You, O You indescribable Beauty”.
(Saint Augustine)
«የማትገለጽ ውበት ሆይ ፤ እጅግ ዘግይቼ ወደድኩህ።»
📖:-Tears in spiritual life
247
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል
በወርኀ ጳጉሜን ከሚታሰቡ እና ከሚከበሩ በዓላት መካከል በየዓመቱ ጳጕሜን ፫ ቀን የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት በልዩ ልዩ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ይከበራል፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል በዓሉ የሚከበርባቸው ምክንያቶችም ሁለት ናቸው፤ እነርሱም አንደኛው በዓለ ሢመቱን ምክንያት በማድረግ ሲኾን፣ ሁለተኛው ደግሞ ቅዳሴ ቤቱ ነው፡፡ ‹ሩፋኤል› የሚለው የስሙ ትርጓሜ ‹ደስ የሚያሰኝ፣ ቸር፣ መሐሪ፣ ቅን የዋህ› ማለት ነው፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ያለ ማቋረጥ ፈጣሪያቸው ልዑል እግዚአብሔርን ከሚያመሰግኑ ቅዱሳን መላእክት አንዱ ነው፡፡ ‹‹ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ›› እንዲል (ጦቢት ፲፪፥፲፭)፡፡
የሰው ልጆች ከተያዙበት የኀጢአት ቍስል ይፈወሱ ዘንድ በአማላጅነቱና በጸሎቱ የማይለይ መልአክ ነው፡፡ ‹‹በበሽታ ዅሉ ላይ በሰው ልጆችም ቍስል ላይ የተሾመው ቅዱስ ሩፋኤል ነው›› በማለት ሄኖክ ከእግዚአብሔር መልአክ ያገኘውን የምስክርነት ቃል ጽፏል (ሄኖክ ፲፥፲፫)፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል በሰውነታችን ላይ የሚወጣውን ደዌም ኾነ ቍስል ይፈውስ ዘንድ ከልዑል እግዚአብሔር ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡ ‹‹በሰው ቍስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው›› እንዳለ ሄኖክ፡፡ ለቈሰሉ ፈውስን የሚያሰጣቸው፤ ላረገዙ ሴቶች ረዳታቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ሴት በፀነሰችበት ወቅት ቅዱስ ሩፋኤል አይለያትም፡፡ ሕፃኑ (ኗ በማኅፀን እያለ (ች) ተሥዕሎተ መልክዕ (በሥላሴ አርአያ መልኩ /ኳ/ መሳል) ከጀመረበት ቀን አንሥቶ እስከሚወለድበት ቀን ድረስ ቅዱስ ሩፋኤል በጥበቃው አይለያቸውም፡፡ በመውለጃቸው ቀን ሴቶች ከሚደርስባቸው ጭንቀትና ሕመም ስሙን ጠርተው ይማጸኑታል፡፡ ፈታሔ ማኅፀን ነውና ቅዱስ ሩፋኤልም ጭንቀታቸውን ያቀልላቸዋል፡፡(ሄኖክ ፮፥፫)
አስማንድዮስ የተባለ ጋኔን በወለተ ራጉኤል ላይ አድሮ ባሎቿን እየገደለ ቢያሰቃያት ቅዱስ ሩፋኤል ጋኔኑን አስጨንቆ አስወጥቶላታል (ጦቢት ፫፥፰-፲፯)፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ‹‹ዳግመኛም እግዚአብሔር ሩፋኤልን፣ አዛዝኤልን እጁን እግሩን አስረህ በጨለማ ውስጥ ጣለው አለው›› ተብሎ እንደ ተጻፈ (ሄኖክ ፫፥፭-፯)፡፡ ለቃየን ልጆች ሰይፍና ሾተል መሥራትን፣ የምንዝር ጌጥ ማጌጥን፣ መቀንደብን ያስተማረ አዛዝኤል የተባለውን ጋኔን በእሳት ሰይፍ እየቀጣ በረቂቅ አስሮ ወደ ጥልቁ የጣለው ይኸው መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ነው (ሄኖክ ፪፥፲፰)፡፡ የጦቢትን ልጁ ጦቢያን በሰው አምሳል ተገልጦ ከተራዳው በኋላ ወደ ሰማይ በሚያርግበት ጊዜ ራሱን ሲገልጥ ‹‹የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረ ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ አላቸው›› (ጦቢት ፲፪፥፲፭)፡፡
በቅዱስ ሩፋኤል ተራዳዒነት ከተደረጉ ተአምራት መካከል በእስክንድርያ አቅራቢያ በምትገኝ ደሴት በታነጸች ቤተ ክርስቲያኑ ያደረገው ተአምር አንደኛው ነው፡፡ በመጽሐፈ ስንክሳር እና በድርሳነ ሩፋኤል እንደ ተጻፈው ብዙ ምእመናን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ፈጽማ ተናወጠች፤ ያቺ ደሴት በታላቅ አንበሪ ጀርባ ላይ የቆመች ናትና፡፡ የሰዎች ብዛትም በከበደው ጊዜ ዓሣ አንበሪው ቤተ ክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሣሣው፡፡ ምእመናኑም ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሔር በከበረ መልአክ ሩፋኤል ስም ጮኹ፡፡ ያን ጊዜ ቅዱስ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በጦሩ ወግቶ ‹‹እግዚአብሔር አዝዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጥ ጸጥ ብለህ ቁም!›› ባለው ጊዜ አንበሪው ጸጥ ብሎ ቆሟል፡፡ በውስጧም ድንቆች ተአምራቶች ተገልጠዋል፡፡ ለሕሙማንም ፈውስ ሆኗል፤ የቅዱስ ሩፋኤል ተራዳዒነት አይለየን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
247
Tears in spiritual life (ዕንባ በመንፈሳዊ ህይወት) አሪፍ ተደርጎ በአማርኛ ተተርኳል ።
YouTube:ማርቃል ተራኪ Markal teraki
Link 👇
http://sharevideo1.com/v/anJxcG5rNlN1R3c=?t=ytb&f=co
247
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
በዓለ ቅዱስ ሩፋኤል
በወርኀ ጳጉሜን ከሚታሰቡ እና ከሚከበሩ በዓላት መካከል በየዓመቱ ጳጕሜን ፫ ቀን የሊቀ መላእክት የቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል በመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት በልዩ ልዩ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ይከበራል፡፡ የቅዱስ ሩፋኤል በዓሉ የሚከበርባቸው ምክንያቶችም ሁለት ናቸው፤ እነርሱም አንደኛው በዓለ ሢመቱን ምክንያት በማድረግ ሲኾን፣ ሁለተኛው ደግሞ ቅዳሴ ቤቱ ነው፡፡ ‹ሩፋኤል› የሚለው የስሙ ትርጓሜ ‹ደስ የሚያሰኝ፣ ቸር፣ መሐሪ፣ ቅን የዋህ› ማለት ነው፡፡ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል ያለ ማቋረጥ ፈጣሪያቸው ልዑል እግዚአብሔርን ከሚያመሰግኑ ቅዱሳን መላእክት አንዱ ነው፡፡ ‹‹ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ›› እንዲል (ጦቢት ፲፪፥፲፭)፡፡
የሰው ልጆች ከተያዙበት የኀጢአት ቍስል ይፈወሱ ዘንድ በአማላጅነቱና በጸሎቱ የማይለይ መልአክ ነው፡፡ ‹‹በበሽታ ዅሉ ላይ በሰው ልጆችም ቍስል ላይ የተሾመው ቅዱስ ሩፋኤል ነው›› በማለት ሄኖክ ከእግዚአብሔር መልአክ ያገኘውን የምስክርነት ቃል ጽፏል (ሄኖክ ፲፥፲፫)፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል በሰውነታችን ላይ የሚወጣውን ደዌም ኾነ ቍስል ይፈውስ ዘንድ ከልዑል እግዚአብሔር ሥልጣን ተሰጥቶታል፡፡ ‹‹በሰው ቍስል ላይ የተሾመ ከከበሩ መላእክት አንዱ ቅዱስ ሩፋኤል ነው›› እንዳለ ሄኖክ፡፡ ለቈሰሉ ፈውስን የሚያሰጣቸው፤ ላረገዙ ሴቶች ረዳታቸው ቅዱስ ሩፋኤል ነው፡፡ ሴት በፀነሰችበት ወቅት ቅዱስ ሩፋኤል አይለያትም፡፡ ሕፃኑ (ኗ በማኅፀን እያለ (ች) ተሥዕሎተ መልክዕ (በሥላሴ አርአያ መልኩ /ኳ/ መሳል) ከጀመረበት ቀን አንሥቶ እስከሚወለድበት ቀን ድረስ ቅዱስ ሩፋኤል በጥበቃው አይለያቸውም፡፡ በመውለጃቸው ቀን ሴቶች ከሚደርስባቸው ጭንቀትና ሕመም ስሙን ጠርተው ይማጸኑታል፡፡ ፈታሔ ማኅፀን ነውና ቅዱስ ሩፋኤልም ጭንቀታቸውን ያቀልላቸዋል፡፡(ሄኖክ ፮፥፫)
አስማንድዮስ የተባለ ጋኔን በወለተ ራጉኤል ላይ አድሮ ባሎቿን እየገደለ ቢያሰቃያት ቅዱስ ሩፋኤል ጋኔኑን አስጨንቆ አስወጥቶላታል (ጦቢት ፫፥፰-፲፯)፡፡ ቅዱስ ሩፋኤል ‹‹ዳግመኛም እግዚአብሔር ሩፋኤልን፣ አዛዝኤልን እጁን እግሩን አስረህ በጨለማ ውስጥ ጣለው አለው›› ተብሎ እንደ ተጻፈ (ሄኖክ ፫፥፭-፯)፡፡ ለቃየን ልጆች ሰይፍና ሾተል መሥራትን፣ የምንዝር ጌጥ ማጌጥን፣ መቀንደብን ያስተማረ አዛዝኤል የተባለውን ጋኔን በእሳት ሰይፍ እየቀጣ በረቂቅ አስሮ ወደ ጥልቁ የጣለው ይኸው መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ነው (ሄኖክ ፪፥፲፰)፡፡ የጦቢትን ልጁ ጦቢያን በሰው አምሳል ተገልጦ ከተራዳው በኋላ ወደ ሰማይ በሚያርግበት ጊዜ ራሱን ሲገልጥ ‹‹የቅዱሳንን ጸሎት ከሚያሳርጉ ወደ ከበረ ወደ ገነነ ወደ እግዚአብሔር ጌትነትም ከሚያገቡ ከከበሩ ከሰባቱ አለቆች አንዱ አለቃ እኔ ሩፋኤል ነኝ አላቸው›› (ጦቢት ፲፪፥፲፭)፡፡
በቅዱስ ሩፋኤል ተራዳዒነት ከተደረጉ ተአምራት መካከል በእስክንድርያ አቅራቢያ በምትገኝ ደሴት በታነጸች ቤተ ክርስቲያኑ ያደረገው ተአምር አንደኛው ነው፡፡ በመጽሐፈ ስንክሳር እና በድርሳነ ሩፋኤል እንደ ተጻፈው ብዙ ምእመናን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ፈጽማ ተናወጠች፤ ያቺ ደሴት በታላቅ አንበሪ ጀርባ ላይ የቆመች ናትና፡፡ የሰዎች ብዛትም በከበደው ጊዜ ዓሣ አንበሪው ቤተ ክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሣሣው፡፡ ምእመናኑም ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሔር በከበረ መልአክ ሩፋኤል ስም ጮኹ፡፡ ያን ጊዜ ቅዱስ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በጦሩ ወግቶ ‹‹እግዚአብሔር አዝዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጥ ጸጥ ብለህ ቁም!›› ባለው ጊዜ አንበሪው ጸጥ ብሎ ቆሟል፡፡ በውስጧም ድንቆች ተአምራቶች ተገልጠዋል፡፡ ለሕሙማንም ፈውስ ሆኗል፤ የቅዱስ ሩፋኤል ተራዳዒነት አይለየን፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
247
She did not have any words to say, or dare to say, so she spoke with her tears.(Luke 7:38).
📖:-Tears in spiritual life
እርሷ የምትናገረው ቃል አልነበራትም፤ አንዳች ለማለትም አልደፈረችም። ስለዚህ በእንባዋ ተናገረች።
247
He weeps in reverence whilst sensing his unworthiness to be in the presence of God. He weeps in front of the altar or the sanctuary whilst feeling the reverence of the place, or he weeps during Holy Communion also for the same feeling of reverence. He wept in love of God Who accepted him and has not dealt with him according to his sins and weaknesses.
እርሱ በአምላክ ፊት ለመቆም የማይገባው መሆኑን እየተሰማው፣ በአክብሮትና በፍርሃተ እግዚአብሔር ያለቅሳል። የቦታው ቅድስናና አስፈሪ ክብር እየተሰማው በመሠዊያው ወይም በቅድስተ ቅዱሳኑ ፊት ያለቅሳል። በዚሁ የአክብሮት ስሜት ምክንያት በቅዱስ ቁርባን ጊዜም ያለቅሳል።
እግዚአብሔር ተቀብሎት፣ እንደ ኃጢአቱና እንደ ድካሙ ሳይፈርድበት በምሕረት ስለተቀበለው ከእግዚአብሔር ፍቅር የተነሣ ያለቅሳል።
📖:- Tears in spiritual life
247
He weeps in reverence whilst sensing his unworthiness to be in the presence of God. He weeps in front of the altar or the sanctuary whilst feeling the reverence of the place, or he weeps during Holy Communion also for the same feeling of reverence. He wept in love of God Who accepted him and has not dealt with him according to his sins and weaknesses.
እርሱ በአምላክ ፊት ለመቆም የማይገባው መሆኑን እየተሰማው፣ በአክብሮትና በፍርሃተ እግዚአብሔር ያለቅሳል። የቦታው ቅድስናና አስፈሪ ክብር እየተሰማው በመሠዊያው ወይም በቅድስተ ቅዱሳኑ ፊት ያለቅሳል። በዚሁ የአክብሮት ስሜት ምክንያት በቅዱስ ቁርባን ጊዜም ያለቅሳል።
እግዚአብሔር ተቀብሎት፣ እንደ ኃጢአቱና እንደ ድካሙ ሳይፈርድበት በምሕረት ስለተቀበለው ከእግዚአብሔር ፍቅር የተነሣ ያለቅሳል።
📖:- Tears in spiritual life
247
የነቢዩ ዳዊት እንባ ፦
ከታች የተጠቀሱ መዝሙራት ንጉሡ ምን ያህል ልቡ እንደተሰበረ እና እንደተጸጸተ ያሳያሉ።
«በጩኸቴ ደክሚያለሁ፤ ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ፥ በዕንባዬም መኝታዬን አርሳለሁ።»
(መዝሙር 6፥6)
ደግሞም እንዲህ ይላል፦
«አለቀስኩ ነፍሴንም በጾም አደከምኋት፤ ማቅንም ለበስሁ።»
(መዝሙር 69፥10-11)
እንዲሁም፦
«ከጩኸቴ ድምፅ የተነሣ አጥንቶቼ ከቆዳዬ ጋር ተጣበቁ… አመድ እንደ እህል በልችያለሁና፥ መጠጤንም ከዕንባዬ ጋር ቀላቀልሁ።»
መዝሙር 102፥5, 9
📖 :-Tears in spiritual life
በተጨማሪም:-
« ተቸግሬአለሁና አቤቱ ምራኝ ዓይኔም ከኃዘን የተነሣ ተፈጀች፥ ነፍሴም ሆዴም።
10 ሕይወቴ በኅዘን አልቃለችና፥ ዓመታቴም በልቅሶ ጩኸት ኃይሌ በችግር ደከመ፥ አጥንቶቼም ተነዋወጡ።(መዝ 31:9)
«እንባዬ በቀንና በሌሊት ምግብ ሆነኝ።(መዝ 42:3)
«ሕግህን አልጠበቅሁምና የውሃ ጅረት ከዓይኖቼ ፈሰሰ።(መዝ 119:136)
......
እነዚህንና ሌሎችንም የዳዊት መዝሙራት ደጋግሞ ማንበብና ማሰላሰል፤ በነቢዩ ስም መማጸን፣ንጉሡን መወዳጀት(ወር በገባ 23 ይዘከራል) ዕንባን ለማግኘት አንዱ መፍትሄ ነው።
247
....“Give me, Lord, fountains of many tears to weep over my pride, anger, harshness, impurity, negligence and over the many sins of my tongue, heart and mind. Also, for my lack of love of your people, for my lack of seriousness in my spirituality, and for my carelessness in keeping your laws. Give me also fountains of many tears to weep for my lack of love.”
“አቤቱ ጌታዬ፣ በትዕቢቴ፣ በቁጣዬ፣ በጨካኝነቴ፣ በርኵሰቴ፣ በቸልተኝነቴ እና በምላሴ፣ በልቤና በአእምሮዬ በሠራኋቸው ብዙ ኃጢአቶች ላይ እንዳለቅስ የብዙ እንባ ምንጮችን ስጠኝ።
እንዲሁም ሕዝብህን በፍቅር ስለማልወዳቸው፣ በመንፈሳዊ ሕይወቴ ንዝህላል ስለሆንኩ፣ ሕጎችህንም ለመጠበቅ ስለማልተጋ እንዳለቅስ የብዙ እንባ ምንጮችን ስጠኝ።
ከዚህም በላይ፣ ፍቅር ስለሌለኝ እንዳለቅስ የብዙ እንባ ምንጮችን ስጠኝ።”
📖 :-Tears in spiritual life
247
A Couplet:"The Psalter of David, whose sayings are as stones, Doth crush the passions as they were another Goliath."
የዳዊት መዝሙራት እንደ ዳዊት ወንጭፍ ናቸው ዳዊት ጎልያድን እንደጣለባቸው ድንጋዮች የበረቱ የሐጢአት ግንቦችን ያፈርሳሉ።
የልብ ውስጥ ጎልያድ የተባሉ የርኩሰት ሐሳቦችንም ያደቅቃሉ።
247
8 አብርሃም የተባለው ርስት አድርጎ ሊቀበለው ወዳለው ስፍራ ለመውጣት በእምነት ታዘዘ፥ ወዴትም እንደሚሄድ ሳያውቅ ወጣ። ✍️:ዕብራውያን 11:8
ነሐሴ 28 የአባቶቻችን የአብርሃም፣ይስሐቅና ያዕቆብ መታሰቢያቸው ነው።
በረከታቸው ይደርብን።
247
“Give me, Lord, fountains of many tears as you did in the past to the sinful woman” and “Make me worthy to shed my tears on your feet, which took me to the right path and offer you the best of perfumes. Grant me to live pure and repentant...”
“ጌታዬ ሆይ፣ በአንድ ወቅት ለኃጢአተኛይቱ ሴት እንደሰጠሃት የብዙ እንባ ምንጮችን ስጠኝ። በቀኝ መንገድ የመራኝን ቡሩካት እግሮችህን በእንባዬ ለማጠብና ከሁሉ የተሻለውን ሽቶ ለአንተ ለማቅረብ የተገባሁ አድርገኝ። በንጽሕናና በንስሐ እንድኖር ስጠኝ…”
📖 :-Tears in spiritual life
247
"ዕንባ በመንፈሳዊ ሕይወት" (Tears in Spiritual Life) 📖
የ117ኛው የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የቤተክርስቲያን መብራት በሆኑት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ የተደረሰ፣ ክርስቲያኖች በጸሎትና በንስሐ ሕይወታቸው ውስጥ ስላላቸው የዕንባ መንፈሳዊ ሚስጥርና ጥቅም የሚያስተምር ጥልቅ መጽሐፍ ነው።
በመጽሐፉ ውስጥ የተብራሩት ዋና ዋና የመንፈሳዊ ዕንባ ዓይነቶችና ጥቅሞች የሚከተሉት ናቸው፦
1. የንስሐ ዕንባ (የኃጢአት መጸጸቻ)
ሰው ስለሠራው ኃጢአት አዝኖና ልቡ ተሰባብሮ የሚያፈሰው ዕንባ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኛል።
ይህ ዕንባ ልብን ከበደል ያጠራል፤ ወደ እግዚአብሔር ምሕረትም ይመራል።
2. የፍቅርና የናፍቆት ዕንባ
አማኝ ክርስቲያን ወደ ፈጣሪው ያለውን ጥልቅ ፍቅርና መናፈቅ ለመግለጽ የሚያፈሰው ዕንባ ነው።
በጸሎት ጊዜ ከመንፈሳዊ መጋደልና ከልብ መነካት የሚመነጭ የናፍቆትና የፍቅር ዕንባ ነው።
3. የጭንቅና የልመና ዕንባ
ሰው በችግር፣ በፈተና ወይም በጭንቀት ጊዜ ረዳት አጥቶ ወደ እግዚአብሔር ብቻ ሲጮኽ የሚፈስ ዕንባ ነው።
እግዚአብሔር የሰዎችን የችግር ለቅሶና ጩኸት ሰምቶ ፈጣን ምላሽ ይሰጣል።
4. ስለ ሌሎች ማልቀስ (የመራራት ዕንባ)
ቅዱሳን ስለ ሌሎች ሰዎች መዳን፣ ስለ ሕመምተኞችና ስለ ዓለም ሰላም የሚያለቅሱት ዕንባ ነው።
ይህ የፍቅር መገለጫና የክርስቶስን የርኅራኄ መንገድ መከተል ነው።
ዋናው መልእክት፦
አቡነ ሺኖዳ በመጽሐፋቸው ዕንባ ከዓይን የሚፈስ ተራ ፈሳሽ ሳይሆን "የነፍስ ጸሎት" እና ልብን ለጸጋ የሚያዘጋጅ መንፈሳዊ መሣሪያ መሆኑን ያስተምራሉ።
✍️:አጋራችን AI ላይ ጥቂት ጣል ተደርጎበት
247
Abba Noah asked Saint Macarius, “Tell me a word of benefit.” The old man said to him, “flee from men”. Abba Noah then asked him, “What do you mean my Father by fleeing from men?” The old man then said, “Stay in your cell and weep for your sins”.
✍️:-Tears in spiritual life
247
ዲያቆን አቤል ካሳሁን ስለ ራዕየ ኒፎን 📖
"በሁሉ ጎዳና ምሳሌ የሚሆን፣ በተለይ ለዚህኛው ትውልድ ቅርብ የሆነ እና ወድቆ በመነሣት ውስጥ ያለውን ተስፋ ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ አንድ ቅዱስ ወደ ሕይወታችሁ የምትጨምሩበትን መጽሐፍ ልጋብዛችሁ? ይኸው “ራእየ ኒፎን” በቀሲስ ታምራት ውቤ።
ቀሲስ ታምራት ውቤ ይህን ድንቅ መጽሐፍ በመተርጎማቸው፣ ቅድስና ርቆ እንደ ተሰቀለ ውብ ፍሬ እያጓጓ የማይደረስበት ለሚመስለን ለዛሬ ክርስቲያኖች፣ ዛፉን ዘንበል አድርጎ ፍሬውን የማቅረብ ያህል ነው ድርሻቸውን ተወጥተዋል። ደግሞ የአተረጓጎም ለዛው፣ እና የቋንቋው ውበት ደግሞ አስደናቂ ነው። አንዴ ካነሡት አስቀምጡኝ አይልም።"
