cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

መልሕዕቅ️ የዐማራ ልሣን ( Anchor Voice Of Amhara)

እንኳን ደህና መጡ⚓️ ይህ መልህቅ(የአማራ ልሣን) የቴሌግራም ገፅ ነው❗️ 💲የመልህቅ(የአማራ ልሣን)ቤተሰብ ሰለሆኑ ደስብሎናል። አማራ የጎደለባት ኢትዮጵያ ደካማ እንደሆነች ሸዋ የጎደለበት አማራነትም ደካማ ነው። ✔️ፈጣን ✔️ትኩስ ✔️ወቅታዊ እና ✔️ወሳኝ መረጃዎችን እንደወረዱ በቅፅበት ፥ በትኩሱ እናደርሳለን❗️ ይወዳጁን ፤ በእርግጥም ይወዱታል❗️ የአማራ ልሣን@Kingofshewa

Show more
Advertising posts
1 723
Subscribers
+2624 hours
+647 days
+19130 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ ናደው ክፍለ ጦር! የኮማንዶ ሳይንስን ጥንቅቅ አድርገው የጨረሱ ፀያይም ግስሎች!
Show all...
Repost from N/a
እንዴት አመሻትሁ ቤተሰብ ወደ ዩቱባችን ገባ ገባ በማለት ቃኙት በዛዉም ሰብስክራይብ አይለያችሁ። https://www.youtube.com/@metekelmedia-ev5tm
Show all...
metekel media

በመተከል አማራ በመሆናቸዉ ብቻ በግፍ ተጨፍጭፈዉ በጅምላ መቃብር በግሊደር ለተቀበሩ አማራ ወገኖቻችን መታሰቢያ የሚሆን የዩቱብ ቻናል ።

Repost from N/a
ሰላም እንዴት ዋላችሁ የሚዲያ ቤተሰቦቻችን የተቀረፀ ንፁህ የጉዞ ቪዲዮ ካላችሁ ለዩቱብ ማልበሻ ላኩልን። እናመሰግናለን። በዚህ፦ @Eiehshau
Show all...
አስቸኳይ አስቸኳይ - ምስራቅ ጎጃም! ወደ ደጀን ከተማ ለስብሰባ ሂደው የነበሩና "ስራ አጥ፣ ግንበኛ ወዘተ" የሚል መታወቂያ የያዙት የምስራቅ ጎጃም ዞን የወረዳ አመራሮች ለትናንት አስበውት የነበረውን ጉዞ በመሰረዝ ለዛሬ ሐምሌ 08/2016 ዓም ለጉዞ በመዘጋጀት ላይ መሆናቸው ታውቋል። የአካባቢው ቀጠና ፋኖዎቻችን ዝግጁ! መረጃው ይዛመት ይዳረስ!
Show all...
Photo unavailableShow in Telegram
በርካታ ወራት የበዛ ጠንካራ እና ትንሽ መታረም የሚገባቸው ነገሮች ነበሩህ ነገር ግን ትግል ነው እና ዱላ ቅብብሎሹ ይቀጥላል የሰራኃው መልካም ነገር ላይ ተጨማሪ ግብዓት እየተስተካከለ ይቀጥላል። የዕድሜ እና ልምድ ተመልክቶ የሰረሃው አመዛኝ በመሆኑ ትውልዱ አብርክቶህን አይረሳም ማርሸት ፀሃዮ የትግሉን ዳይሜሽን በፕሮፓጋንዳ እና ሚዲያ ብልጫ በማሳየት ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክተሃል እና እናመሰግናለን። በርታ ቀጣዮ የትግል መንገድ ብዙ ይጠበቃል በተለይም በሚዲያው።
Show all...
ሰበር ዜና! በወልድያ ከተማ በሚገኝ አንድ ፖሊስ ጣቢያ ላይ በተፈፀመ ጥቃት ስድስት የፖሊስ አባላት ሲገደሉ አምስቱ ተማርከው መወሰዳቸው ተሰማ! የሰሜን ወሎ ዞን ዋና መቀመጫ በሆነችው ወልድያ ከተማ 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ላይ አዳሩን በተፈፀመ ጥቃት በቁጥር ስድስት የፖሊስና የአድማ ብተና አባላት ሲገደሉ አምስቱ ደግሞ ተማርከው መወሰዳቸውን የአማራ ድምፅ ሚዲያ ጥቃቱን የፈፀሙ የፋኖ አባላትና አመራሮችን እንዲሁም የከተማዋ ነዋሪዎችን በማነጋገር ለማረጋገጥ ችሏል። ሙት እና ምርኮኛ ከሆኑት የአድማ ብተናና የፖሊስ አባላት በተጨማሪ ሰባት የጣቢያው አባላት ቆስለው ወደ ሕክምና የተወሰዱ ሲሆን ከነዚህ መካከል ሦስቱ በጠና ታመው ወደ ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል መላካቸውን ነው የአይን እማኞች ለጣቢያችን የገለፁት። ጥቃቱ የተፈፀመው ትናንት ሐምሌ 07/2016 ዓ/ም ለዛሬ አጥቢያ ለሊት 7:00 ጀምሮ እስከ 9 ሰዓት ባለው ነው የተባለ ሲሆን ጥቃቱን የፈፀሙት የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ብርጌድ ፋኖዎች መሆናቸውንም ለማረጋገጥ ተችሏል። በከተማዋ ራስ አሊ ክ/ከተማ ስር የሚገኘው 2ኛ ፖሊስ ጣቢያ ላይ በተፈፀመው ጥቃት ሙትና ቁስለኛ እንዲሁም ምርኮኛ ከሆኑ የአድማ ብተናና ፖሊስ አባላት በተጨማሪ አንድ የፖሊስ ጣቢያው ተሽከርካሪ መውደሙንም  የራስ አሊ ክ/ከተማ ነዋሪዎች ተናግረዋል። በዚህ ጥቃት አራት ስታር ሽጉጥን ጨምሮ 25 የሚደርስ ክላሽንኮቭ መሣሪያና በርካታ ቁጥር ያለው ተተኳሽ የማረኩት የፋኖ አባላቱ፡ የማረኩትን መሣሪያ በማረኳቸው የፖሊስ አባላት አሸክመው ከተማዋን ለቀው መውጣታቸው ታውቋል። ከቆሰሉት ሰባት የፖሊስ አባላት መካከል ወደ ደሴ ሪፈራል ሆስፒታል ሪፈር የተባሉት ሦስቱ የፖሊስ አባላት ክፉኛ በመጎዳታቸው የመትረፍ እድላቸው አነስተኛ ነው ሲሉ ሁኔታውን በቅርብ ርቀት ሁነው ሲከታተሉ የነበሩ የክ/ከተማዋ ነዋሪዎች ተናግረዋል። "በፖሊስ ጣቢያው ላይ ጥቃቱ ሲፈፀም ዝም ብላችሁ ተመልክታችኋል፡ ለምን አባሎቻችንን አላገዛችሁም?" በሚል ዛሬ እረፋዱን ለእስር የተዳረጉ በርካታ የራስ አሊ ክ/ከተማ ነዋሪዎች መኖራቸውም ታውቋል። የአማራ ድምፅ ሚዲያ
Show all...
👍 5
የጉና ክፍለ ጦር ደብረታቦር ከተማ የደህንነቱን መዋቅር በማጠናከር ሰርጉ በመግባት ደብረ ታቦር ከተማ ላይ ሲዝናኑ አደሩ ። የክፍለ ጦሩ መሪ ሜጀር ጀኔራል አምሳሉ ማዘንጊያም  አማካኝነት የተመራ አደረጃጀት ደብረታቦር ከተማ ምሸት 1 30 ሳዓት ላይ ገብተዉ ኦፕሪሽናቸዉን አሳክተዉ ወተዋል ። ወደ ፋኖ ለመቀላቀል ያሰቡ የአገዛዙ ወታደሮች አልመቻቸዉ ብሎ ነበር ግን በሜጀር ጀኔራል አምሳሉ ማዘንጊያ በሱ መሪነት ከተማ ድረስ ዘልቆ በመግባት የኦሮሞ  አንቦ ከተማ ተወልዶ ያደገዉን አምሳ አለቃ ዮሀንስ ሀይሉን ከነሙሉ ትጥቃቸዉ  ማወጣታቸዉን በክፍለ ጦሩ መሪ አረጋግጠናል ። አምሳ አለቃ  ዮሀኒስ ሀይሉ ይባላል የክፍለ ጦሩ ማሀዲስ  የነበሩ አባላት ናቸዉ  አሁን ላይ በጉና ክፍለ ጦር እያገለገሉ ያሉ ጀግኖች ናቸዉ ። ከአገዛዙ ወታደሮችም ወደ ፋኖ የተቀላቀሉ ከራሳቸዉ አንደበት  እኛ ከአምሳሉ ጋር መሆነችን ደስ ብሎናል ተመችቶ ነዉ የያዘን ሜ/ጀኔራል አምሳሉ ማለት  የእናት ጉያ ነዉ በማለት አድንቀዋል ።  የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑት አምሳ አለቃ ዩሀኒስ ሀይሉ  አገዛዙ በወታደሩ ላይ በደል እየፈፀመ ነዉ እኛ ህዝብ አንወጋም ስንል እየተረሽን ነዉ ወታደሩም እየተረሸነ አልቋል እኛ አገር ነዉ የምንጠብቅ እንጅ ህዝብን ለመጨፍጨፍ አይደለም። ወታደር የሆነዉ ትናንት ከትግሬ ጋር ተጋደልን ዛሬ ደግሞ ከአማራ ጋር ተጋደልን ነገ ደግሞ ከኦሮሞ ጋር ያለመግጠማችን ምንም ዋስትና የለነም ስለዚህ ፋኖን መቀላቀል ብቸኛዉ አማራጭ ስለሆነ ተቀላቅያለዉ ብሏል ።
Show all...
👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
በላይነህ ሰጥአርጌ ተስፋ ብርጌድ- ከሰም ክፍለ ጦር- የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ በትናንትናው ዕለት በረኸት ወረዳ ውስጥ በአራት ግምባር ሲፋለም ውሎ አምሽቷል:: በ 04፣ 05 ፣ 06 እና 07 ቀበሌዎች በኩል በሜካናይዝድ ጦር የታገዘ እግረኛ የጠላት ኃይል የከፈተውን ጥቃት በረኸኞቹ በደንብ ቀልብሰዋል:: አሁን ላይ ቀጠናው ውስጥ ቀይ ቦኔት ቆልሎ ከሚንቀሳቀሰው ኮማንዶ ይልቅ ፎጣ የጠመጠመ በረኸኛ ነው የሚያስፈራው ጠላት የስነ ልቦና የበላይነቱ ተወስዶበታል። አሁን መከላከያን የሚፈራ አማራ የለም የፋኖዎች ግዳጅ የመፈፀም ብቃት እና ወታደራዊ ዲስፕሊናቸው አኩሪ ነው። የሚያፈገፍግ ፋኖ የለም፤ ጠላት ግን ተኩስ ሲከፈት እንደ ሰንበት ዳቦ ወዲያው ነው የሚቆራረሰው:: ባለ ቀይ ቦኔቱ ናድ ናድ ሲል አይቆይም። ቀጥ ብሎ 1 ሰአት የሚዋጋ ጠላት የለም። የመጣው ሲበተን ከሗላ ሌላ ይመጣል። በረኸት ወረዳ ውስጥ ትናንት የሆነውም ይህ ነው። ሲመላለሱ ነው የዋሉት። እጅግ በጣም ብዙ ሰራዊት በቡልጋ ግምባር ተሰማርቷል ግን በረኸኞች በጥይት እየቆሉት ነው። ብዛቱን ወደነዋል እያሉ ነው። ለምን ሲባሉ በደንብ ያስታጥቀናል ነው መልሳቸው። ምስል: (የተስፋ ብርጌድ ሻለቃ አንድ ሻምበል 3 ፋኖዎች)
Show all...
የአማራ ፋኖ ሸዋ ዕዝ የናደው ክፍለጦር ወደ አማራ ክልል ደራ ወረዳ ዘልቆ ገብቶ የነበረን ሸኔ በሚባል የሚታወቅ የሽመልስ አብዲሳ መልዕክተኛ ኃይል 67 አባላቱን አፈር አቅምሰውታል። ይህ ሴቶችና ህጻናት ላይ የሚበረታ ሹሩቤ፣ ከወንዶቹ ፊት ግን መቆም እንዳልተቻለው ቤተልሔም አስራት ካጋራችው መረጃ መረዳት ይቻላል።
Show all...
👍 5
Show all...
ሰበር መረጃ ሰበር ሰበር የፍርድበቱ ጉድ፡ የሽዋ ገድል

Choose a Different Plan

Your current plan allows analytics for only 5 channels. To get more, please choose a different plan.