cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Merkato Media

#merkato_media #መርካቶ_ሚድያ በዚህ ቻናል ለኢትዮጵያ ፍቅር ሰላም አንድነት ስለ ፍትህ የምናወራበት ድምፅ ላጡ ድምፅ የምንሆንበት ቻናል ነው። ''We testify about the Truth ''

Show more
Advertising posts
7 323
Subscribers
-524 hours
-367 days
-28230 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
መንግሥት የመንግሥት ሠራተኞች ቅጥርና ምደባ የአገሪቱን ብሄረሰቦች ብዝኀነትና የጾታና የአካል ጉዳተኞችን ተዋጽዖ የጠበቀ እንዲኾን የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል። ምክር ቤቱ፣ በረቂቅ አዋጁ ላይ ትናንት ተወያይቷል። ረቂቅ አዋጁ፣ በመንግሥት ሠራተኞች ደሞዝ ጭማሪ፣ ደሞዝ እርከን፣ ክፍያና ጥቅማጥቅሞች ላይ ማሻሻያ እንዳደረገም ተገልጧል። የአነሳ ብሄረሰቦችና የማኅበረሰብ ክፍሎች በመንግሥት መስሪያ ቤቶች በቅጥር፣ ምደባ፣ ዝውውር፣ በሥራ ደረጃ እድገት፣ በትምህርትና ሥልጠና ረገድ ተጨማሪ መንግሥታዊ ድጋፍ እንዲደረግላቸውም ረቂቅ አዋጁ ይደነግጋል። ምክር ቤቱ፣ ረቂቅ አዋጁን ጉዳዩ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል። [ዋዜማ]
2 1483Loading...
02
ዋቻሞ ዩኒቨርስቲ🙆‼️ በሀድያ ዞን ዋቻሞ ዩኒቨርስቲ ለአንድ የዩኒቨርስቲው የፋይናንስ ቡድን መሪ የ790 ቀን አበል እንዲሁም ለሌላኛው የፋይናንስ የቡድን መሪ ደግሞ በስድስት ወራት ውስጥ ብቻ የ1,469 ቀን (1,056,854 ብር) አበል እንደተከፈላቸው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሰነድ ማስረጃዎችን፣ጥቆማዎችን እና መመሪያዎችን በማጣቀስ ምርመራ አድርጎ ውጤቱን ይፋ አድርጓል። ሌላም የዩኒቨርስቲው ፋይናንስ ሳያውቅ 1.4 ቢሊዮን ብር ለኦክስጅን ማምረቻ በሚል በህገወጥ መንገድ መንቀሳቀሱን እና ፍቃድ የሌለው የኮንስትራክሽን ድርጅት ግንባታውን እንዲሰራ ያለ ጨረታ እንደተሰጠው በምርመራ ውጤቱ ተገልጿል። በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተመሳሳይ ምርመራ ቢደረግ ከዚህም በላይ የሙስና ወንጀል እንደሚገኝ እሙን ነው። @sheger_press @sheger_press
2 7494Loading...
03
የ2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መርሐግብር ይፋ ሆኗል፡፡ መርሐግብሩ ከትግራይ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱም የከተማ አስተዳደሮች በወረቀት እና በበይነ መረብ ፈተናውን ለሚወስዱ ተፈታኞች እንደሚያገለግል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና:— ✔ከሐምሌ 3-5/2016 ዓ.ም ለማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ✔ከሐምሌ 9-11/2016 ዓ.ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ይሰጣል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት @sheger_press @sheger_press
3 5436Loading...
04
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ በአፋርና ሱማሌ ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች በአፋር እና ኢሳ ጎሳዎች መካከል በሚያጋጥሙ ግጭቶች ሳቢያ ከ38 ሺህ በላይ ዜጎች አፋር ክልል ውስጥ በሦስት ወረዳዎች መፈናቀላቸውን ባካባቢው ባደረገው ጉብኝት ማረጋገጡን አስታውቋል። የኹለቱ ጎሳዎች ታጣቂዎች ባብዛኛው ግጭት ውስጥ የሚገቡት፣ በአፋር ክልል ገቢ ረሱ ዞን እና በሱማሌ ክልል ሲቲ ዞን አጎራባች አካባቢዎች ሲኾን፣ በተለይ በተያዘው ዓመት ተደጋጋሚ ግጭቶች ተካሂደዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ በኹለቱ ጎሳዎች መካከል በተደጋጋሚ የሚካሄደውን ግጭት ለመፍታት ከሳምንታት በፊት አሸማጋይ ኮሚቴ ማቋቋሙ አይዘነጋም። ኾኖም የጎሳ ግጭቱ እስካለፈው ሳምንት ድረስ ቀጥሎ እንደነበር ተሰምቷል። @merkato_media
4 2801Loading...
05
ታሰረ ‼️ በቲክቶክ የማህበራዊ ትስስር ገፅ መሌ ፌዳው በሚል ስም የምናውቀው የፌደራል ፖሊስ አባል መለሰ ብርሃኑ መታሰሩ ተሰምቷል። የፖሊስ አባሉ የታሰረበት ምክንያት የመከላከያን የክብር ልብስ ለብሶ የሰራዊቱን ስም የሚያጎድፍ ቪድዮ ሰርቷል በሚል ሲሆን ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርቦ ዋስትና ሳይፈቀድለት ቀጠሮ እንደተሰጠበት እንደቀረ ታውቋል። @sheger_press @sheger_press
4 8982Loading...
06
ባለፉት ጥቂት ቀናት በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን መራዊ ከተማ በፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግሥት ኃይሎች መካከል ግጭቶች እንደተካሄዱ ዋዜማ ከምንጮች ሰምታለች። በግጭቱ ሳቢያ፣ የክልሉን ዋና ከተማ ባሕርዳርን ከምሥራቅ ጎጃም ዞን ዋና መቀመጫ ደብረማርቆስ ጋር የሚያገናኘው መንገድ ለተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ተዘግቶ እንደነበር ተሰምቷል። በተመሳሳይ፣ በሰሜን ወሎ ዞን ውርጌሳ ከተማ እና አካባቢዋ በኹለቱ ወገኖች መካከል ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ግጭት እንደተካሄደ ምንጮች ተናግረዋል። @merkato_media @merkato_media
5 8200Loading...
07
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል የሕወሃት ኃይሎች ከሱዳን ጦር ሠራዊት ጋር ወግነው እየተዋጉ ነው በማለት ያቀረበውን ውንጀላ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስተባብሏል። የፈጥኖ ደራሹን ኃይል ውንጀላ "በጥብቅ እንደሚያወግዝ" የገለጠው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ይህን ውንጀላ ያሰማው ዓለማቀፍ ድጋፍ ለማግኘት ሲል ነው በማለት አጣጥሎታል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ሕወሃት የፖለቲካ ፓርቲ በመኾኑ "የታጠቀ ኃይል ወይም ሚሊሺያ የለውም" በማለትም ምላሽ ሰጥቷል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ አያይዞም፣ ሱዳን በትግራዩ ጦርነት ወቅት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የክልሉን ስደተኞች ያስጠለለች እንደመኾኗ ትግራይ በሱዳን የውስጥ ጉዳይ የምትገባበት ምክንያት ሊኖራት አይችልም ብሏል። ኹለቱ ወገኖች ጦርነቱን ከሚያባብሱ ንግግሮች እንዲቆጠቡና ጦርነቱን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ጠይቋል። @merkato_media @merkato_media
5 4841Loading...
08
ለመላው የመርካቶ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ   እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። በዓሉ የሰላም ፣ የደስታ ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ  ይሆን ዘንድ እየተመኘን በዓሉን ስናከብር ዓቅመ ደካሞችን በመርዳት ይሆን ዘንድ በትህትና እንጠይቃለን። መልካም በዓል @merkato_media @merkato_media
5 7120Loading...
09
ተፈታ‼️ ልጅ ያሬድ ተፈቷል💇‍♂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ክብር የሚነካ ቃላት ተናገሮ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበረው ልጅ ያሬድ በዛሬው ዕለት ተፈቷል። @sheger_press @sheger_press
5 6402Loading...
10
ጌታቸው ረዳ‼️ "በየጊዜው ወጣቶች የምገብርበት የጦርነት ምዕራፍ መዘጋት አለበት " - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በኩል ዛሬ መልዕክት አሰራጭተው ነበር። በዚህም ፤ " የህዝባችን ሁለንተናዊ መብትና ጥቅም ከማረጋገጥና አስተማማኝ ከማድረግ የሚቀድም ሌላ አጀንዳ የለንም " ብለዋል። " የህዝባችን ጥቅምና መብት የሚያረጋግጥ መንገድ ሁሉ እንጓዘዋለን " ያሉት አቶ ጌታቸው " ጉዞው እንዲሳካ የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው " ሲሉ አክለዋል። ፕሬዜዳንቱ ፤ " ከሚገባው በላይ ያበረከተ ህዝብ በቅንነትና ታማኝነት ማገለገል ይገባል " ሲሉም ገልጸዋል። " ህዝቡ ከጦርነትና ጦርነት ወለድ ችግሮች በማላቀቅ ወደ አስተማማኝ ሰላም እንዲሸጋገር መስራት ይገባል " ሲሉም አስገንዝበዋል። አቶ ጌታቸው ረዳ  ፤ " በየጊዜው ትኩስ ሃይል የሆኑትን ወጣቶች የምንገብርበት የጦርነት ምዕራፍ ተዘግቶ ፤ የልማትና የእድገት ፍላጎታችን እንዲሳካ መስራት አለብን " ብለዋል። (Tikvah)
5 9323Loading...
11
የ2016 ዓ.ም የሪሚዲያል ፈተና መቼ ይሰጣል ? እንደ ትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ፤ የ2016 ዓ/ም የሪሚዲያል ተማሪዎች ፈተና በሰኔ ወር መጀመሪያ ይሰጣል። ፈተናው ለ15 ቀናት በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት እየተሠራ ነው። ከ70 በመቶ የሚዘጋጀው ፈተና በኦንላይንና በወረቀት ወይም በጥብቅ ቁጥጥር በወረቀት ይሰጣል ተብሏል። ባለፈው ዓመት የተፈጠረውን ችግር ለመቅረፍ የሪሚዲያል ፈተናውን በሁሉም የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ለመስጠት ታቅዶ እየተሰራበት ነው። ዘንድሮ 32,500 ተማሪዎች 50 በመቶ በላይ ውጤት በማምጣት በቀጥታ ዩኒቨርሲቲ ገብተው መደበኛ ትምህርት እየተከታተሉ ሲሆን ከ78 ሺህ በላይ ተማሪዎች ደግሞ በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ሪሚዲያል ትምህርት እየወሰዱ እንደሚገኙ ሚኒስቴሩ ለኢፕድ ከሰጠው መረጃ ተመልክተናል። በሌላ በኩል ፤ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተመደቡ የሬሜዲያ ተማሪዎች ከታህሳስ ወር ጀምሮ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ቢሆንም በባህርዳር ዩኒቨርሲቲ የሪሚዲያል ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የተመደቡ ተማሪዎች እስካሁን ጥሪ አልተደረገላቸውም። @Addis_News
5 4941Loading...
12
እግር ኳስ በኢትዮጵያ ተዓምራቱ እንደቀጠለ ነው። ይህ ክስተት ጎል አግብተው ደስታቸውን እየገለፁ ይመስላል ግን አይደለም ዳኛውን ከበው እያናገሩት ነው። አንዱ ተጨዋች ለማናገር ሜዳው ሁላ አልበቃውም ተጨዋች ላይ ወጥቶ ነው የሚያናግረው።
7 2234Loading...
13
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለሆሳዕና በዓል በሰላም አደረሳችሁ፡፡
6 7974Loading...
14
ኢትዮጵያ ፤ የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እቅድ እንዳላትና ለእርሱም እየሰራች ነዉ ተባለ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አመታት የአፍሪካ ዋንጫ ውድድርን እንድታዘጋጅ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጄላ መርዳሳ መናገራቸውን ዳጉ ጆርናል ታዝቧል። የአፍሪካ ዋንጫን እ.ኤ.አ በ 2029 ወይም በ2031 ለማዘጋጀት እየሰራን ነው ያሉት ሚኒስትሩ ለእቅዱ መሳካትም ቢያንስ ስድስት ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ካፍ ከዚህ በፊት ያልነበሩ አዳዲስ መስፈርቶችን በማስቀመጡ ኢትዮጵያ አንድም ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም እንዳይኖራት አድርጓል ሲሉም አቶ ቀጀላ መርዳሳ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የካፍን ደረጃ የሚመጥኑ ስታዲየሞች የሌላት በመሆኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ረዘም ላሉ ጊዜያት ከሀገሩ ዉጪ ለመጫወት ተገድዶ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። የዉድድሩ አዘጋጅ ሀገራት ቢያንስ ስድስት ስታዲየሞችን እንዲያዘጋጁ ካፍ ቢያዝም ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ ምን ያህል ዝግጁ ናት የሚለዉ ግን አጠያያቂ ነዉ። Via ዋልታ
7 4002Loading...
15
በልዩ ቅናሽ ኦርጅናል ስልኮች ይሸምቱ Brand #Samsung A15- 4 ram 128 GB - 16,500 A05 -4 ram 64 GB - 11,500 A34- 6ram 128 GB - 28,000 A54- 8ram 256GB - 38,000 S24 Ultra -12 ram - 512 GB -126,000 ይደውሉልን 👉 0913366506 Telegram @Birukepromo ተጨማሪ እቃዎችን ለመሸመት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ👇👇 https://t.me/bura_collection
6 3722Loading...
16
አዲስ አበባ፤ ተኝተዉ በነበሩ ሰዎች ላይ ቤት ተደርምሶ ሰባት ሰዎች ሞቱ ዛሬ ለሊት ሊነጋ ሲል 11 ሰኣት አከባቢ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 በተለምዶ ጠሮ መስጊድ በሚባል አከባቢ በደረሰ የቤት መፍረስ አደጋ የሰባት ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡ ለአደጋው መንስኤ የሆነው በጎረቤት የተከማቸው ለቤት ግንባታ የሚውል ከፍተኛ መጠን ያለው አፈርና ድንጋይ ከመሬት እየወጣ ካለው ግንባታ ጋር ተደርምሶ መኖሪያ ቤቶች ላይ በማረፉ በጠዋት ተኙ የነበሩ ሰባት ሰዎች አንዳቸውም በህይወት መውጣት ሳይችሉ በዚያው አልቀዋል፡፡ አፈርና በግንባታ ላይ ያለው ድንጋይ ተደርምሶባቸው ያለቁት የአንድ ቤተሰብ አባላት እና ጎረቤታቸው ነው ተብሏል፡፡ እድሜያቸው ከ11፤ 12፣ 25 እና 28 የሆኑ አራት ሴቶች እንዲሁም እድሜያቸው የ4፣ የ12 እና የ30 ዓመት እድሜ ያላቸው ሶስት ወንዶች ባጠቃላይም ሰባት ሰዎች በተኙበት ቤትን የደረመሰባቸው የአፈር እና የድንጋይ ክምር አንዳቸውም በህይወት እንዳይወጡ አድርጓል፡፡ የአደጋውን ዝርዝር ጉዳይ ፖሊስ እያጣራ መሆኑን ያስረዱት የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ ኮሚሽናቸው ያደረገው የህይወት አድን ሙከሪያ ከቦታው አመቺ አለመሆን ጋር ተያይዞ ሳይሳካ መቅረቱን አስረድተዋል፡፡ ቦታው ላይ ደርሶ አደጋውን የተመለከተው የአዲስ አበባው ዘጋቢችን ከላይ ወደ ታች የተደረመሰው የአፈር ክምችትና ግንብ ስር የወጡ የሰው አስከሬን የመቅበር እና ቤት ላይ የተደረመሰውን አፈርና ድንጋይ የማንሳት ስራ በአከባቢው ህብረተሰብ ስከወን ነበር ብሏል፡፡ በቦታው ላይ ከነበሩ የሟቾች ጎረቤት መካከል አቶ አሊ አማን የተባሉ የአይን እማኝ ጎረቤት በሌሊቱ ተነስተው የደረሱት የድንጋይ መደርመስ ከፍተኛ ድምጽ በመስማት ነው ብለዋል፡፡
5 6652Loading...
17
ስለ ጊዜ..... ኒዉዬርክ ከካሊፎርኒያ በ 3 ሰዓት ትቀድማለች ነገር ግን ይህ ካሊፎርኒያን ቀርፋፋ አያደርጋትም ምክንያቱም የራሷ ጊዜ አላትና ፡፡ አንዳንድ ሰዉ በ22 አመቱ ይመረቃል ነገር ግን ጥሩ ስራ ለመያዝ 5 አመት ይፈጅበታል፡፡ አንዳንዱ በ25 አመቱ የድርጅት ሃላፊ ሆኖ በ5ዐ አመቱ ሲሞት ሌላዉ በ50 ዓመቱ ሃላፊ ሆኖ እስከ 9ዐ ዓመት ይኖራል፡፡ ኦባማ በ55 ዓመቱ ኘሬዝዳንትነቱን ጨረሰ ነገር ግን ትራምፕ በ7ዐ ዓመቱ ኘሬዝዳንትነቱን ጀመረ! ይሄ ትራምፕን ኀላ ቀር አያደርገዉም፡፡ ጊዜ በሕይወታችን ወሳኝ ነገር ነዉ ፡፡ ፈጣሪ በጊዜዉ ሁሉን ነገር ዉብ ያደርጋል ስለዚህ.... ከሁሉ በኋላ የቀረን ወይም ወደፊት የቀደምን አይምሰለን ሁሉም ሰዉ የራሱ የሆነ የኑሮ ሩጫና የተፈጠረበት አላማ አለዉ! ሁላችንም የራሳችን የሆነ የጊዜ ክልል አለን! Dr. Mihret Debebe
4 54921Loading...
18
ሰውዬው ተገኝተዋል ኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ለገጣፎ አቅራቢያ 44 ማዞሪያ ጅዳ ኩራ በተባለ ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸው ታውቋል። እኝህ ሰው በተደበደቡ፣በተበደሉ፣ጥቃት በደረሰባቸው እንደት ሊታሰሩ ቻሉ ለሚለው ምላሽ አልተገኘም። በወቅቱ እሳቸውን ከፍ ዝቅ እያደረኩ ርካሽ የዘረኝነት ተግባር ሲፈፅሙባቸው የነበሩ ወጣቶች ተሰብስበው መታሰራቸውም ተሰምቷል።(wasu) @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
6 1233Loading...
19
የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ እንዳስታወቀው፤ "በኢትዮጵያ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት ከ5 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጪ ናቸው።"
5 9370Loading...
20
"እስራኤል በወታደሮቿ ላይ የሚጣልን ማዕቀብ ትታገላለች" - ኒታንያሁ አሜሪካ በእስራኤል ወታደሮች ላይ ማዕቀብ ለመጣል እያቀደች መሆኗ ዘግቦ ነበር። እንደ South China Morning Post ዘገባ አሜሪካ እጥለዋለሁ ያለችው ማዕቀብ በዌስት ባንክ የሰፈሩ የጦር አባላት ላይ ነው። "የተፈፀመ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የለም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ኒታንያሁ በበኩላቸው፣"በእስራኤል የጦር አባላት ላይ የሚጣልን የትኛውንም ማዕቀብ እታገላለሁ" ብለዋል። @thiqahEth
7 0620Loading...
21
ጥቆማ‼️ ታላቅ ቅናሽ ይዞ የመጣው የራሳችን የሆነው bura collection የገበያ መድረክ አሁንኑ የቴሌግራም ቻናላችን በመቀላቀል ኦርጅናል እቃዎችን ይሸምቱ👇👇 ኦርጅናል አልባሳቶችና ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች ሁሉንም ዕቃ ባንድ ላይ የሚያገኙበት የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ👇👇 https://t.me/bura_collection https://t.me/bura_collection የፈለጉትን እቃ የሚያገኙበት
4310Loading...
22
ኢራን አፋጣኝ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ እቅድ የላትም ሲሉ አንድ የኢራን ባለስልጣን ተናገሩ አንድ የኢራን ከፍተኛ ባለስልጣን ለሮይተርስ የዜና ወኪል እንደተናገሩት "ኢራን በእስራኤል ላይ አፋጣኝ የበቀል እርምጃ ለመውሰድ እቅድ የላትም" ሲሉ እስራኤል በኢራን ኢስፋሃን ከተማ ላይ ጥቃት መሰንዘሯ ተከትሎ ተናግረዋል፡፡ ሁለት የአሜሪካ ባለስልጣናት ጥቃቱ ከእስራኤል የመጣ መሆኑን ለመገናኛ ብዙሃን ቢናገሩም እስራኤል ኃላፊነቱን ለመዉሰድ ወዲያዉ መግለጫ አላወጣችም ነበር።አንድ ኢራናዊ ተንታኝ ለኢራን መንግስት ቲቪ እንደተናገሩት "በኢስፋሃን በአየር መከላከያ የተተኮሱ ሚኒ ሰው አልባ አውሮፕላኖች ወደ ኢራን ውስጥ ሰርጎ ገቦች ገብተዋል" በማለት እስራኤል ጥቃቱን ፈጽማለች የሚለውን ዘገባ አሳንሰዉ ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል እስራኤል በኢራን ላይ የበቀል ጥቃት መፈጸሙን ተከትሎ ዩናይትድ ስቴትስ በእስራኤል ለሚገኙ የኤምባሲ ሰራተኞቿ እና ቤተሰቦቻቸው “ከከፍተኛ ጥንቃቄ የተነሳ” የጉዞ ገድብ ጥላለች።ኤምባሲው ሰራተኞቹ ከታላቋ ቴል አቪቭ ክልል ውጭ  ወደ ሄርዝሊያ ፣ ኔታንያ እና ዩሁዳን ጨምሮ ወደ እየሩሳሌም እና ቢየር ሼቫ አካባቢዎች እንዳይጓዙ አስጠንቅቋል፡፡
6 2180Loading...
23
ሶሻል ሚዲያ ይሺጡ ይግዙ ✔️የቴሌግራም ግሩፕ እና ቻናል ✔️የዩትዩብ ቻናል ✔️የፌስቡክ ፔጅ ✔️የቲክቶክ ገፅ መግዛት እና መሸጥ የምትፈልጉ አናግሩን ሁሉም እኛ ጋር አለ።     @ethio_sellerr @birukpromo ላይ አናግሩን በስልክ ቁጥራችን 0946159797 ይደዉሉንን::
5 1900Loading...
24
መረጃ‼️ የአለም የባሎች ቀን በአለም ዙሪያ እየተከበረ ይገኛል ።
5 6525Loading...
25
በአዲስ አበባ ከተማ በተገነቡ ማዕከላት ከመደበኛው ገበያ የጤፍ ዋጋ ላይ የ3 ሺ ብር ቅናሽ እንዳለው ተገለፀ በአዲስ አበባ ከተማ ተገንብተው አምራችን ከሸማቾች የሚያገናኙ ሶስት ማዕከላት ሙሉ በሙሉ ስራ መጀመራቸውን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታውቋል። ቢሮው አሁን ላይ በዋነኛነት የገበያ ማዕከላት ላይ ትኩረት አድርጎ እየሰራ እንደሚገኝ ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን የተናገሩት የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ የኮምኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ ከ3.3 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ ተደርጎባቸው እንደተገነቡ ተናግረዋል። ከተማ አስተዳደሩ በእነዚህ ማዕከላት አምራቾችን ሙሉ በሙሉ አስገብቶ ለሸማቾች ከማሳ የተሰበሰቡ ምርቶችን በቅናሽ ዋጋ እያቀረበ ነው ብለዋል።እነዚህ ማዕከላት በሸማቹ እና በአምራቹ መሀል የነበረውን ህገ ወጥ ደላላን መስበር የቻለ ነው። ከዋጋም አኳያ ከእሁድ ገበያ አንፃር የተሻሉ መሆናቸውን ገልፀዋል።ምርቶች በበቂ ሁኔታ በገበያ ማዕከላት ቢገቡም ህብረተሰቡ ስለ ማዕከላቱ በቂ ግንዛቤ ስሌለው የሚበላሹ  ምርቶች አሉ በተለይ ደግሞ  የአትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶች ብልሽት እንደሚገጥማቸው ተናግረዋል። ሸማቹ ወደ እነዚህ ማዕከላት በመምጣት ሁሉንም ምርቶች በአንድ እንዲሁም በቅናሽ ዋጋ ማግኘት እንደሚችል ገልፀዋል።ከመደበኛ ገበያዎች የጤፍ ዋጋ በእነዚህ ማዕከላት ውስጥ የ3ሺ ብር ቅናሽ እንዳለው አንስተዋል። እንዲሁም አትክልት እና ፍራፍሬ ምርቶችም ከእሁድ ገበያው ቅናሽ እንዳለውም አቶ ሰውነት አየለ ጨምረው ለብስራት ሬድዮና ቴሌቭዥን ተናግረዋል። ማዕከላቱ በኮልፌ ፣በአቃቂ እና በለሚ ኩራ ክፍለ ከተሞች ይገኛሉ ተብሏል። ዳጉ_ጆርናል
5 9253Loading...
26
m14 Samsung 📱 ✔️6ram ✔️128 GB 📌ዋጋ=16500 @ethio_sellerr    @Birukepromo            ላይ  ያናግሩን። በስልክ ቁጥራችን 0946159797 ይደዉሉልን ። አዲስአበባ ያሉበት እናደርሳለን 🛵🚵 ክፍለሀገር በፖስታ ይደርሷታል።📩📮 ተጨማሪ እቃዎችን ለመሸመት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ👇👇 https://t.me/bura_collection
4 1410Loading...
27
#Update የ " ቲክቶክ " እገዳ በኪርጊስታን ተግባራዊ ሆነ። ኪርጊስታን " ቲክቶክ " በመላ ሀገሪቱ  እንዲታገድ ውሳኔ ማስለፏ ይታወሳል በዚሁ ውሳኔ መሰረት የቴሌኮም አገልግሎት የሚሰጡ ድርጅቶች ትዕዛዙን ወደ መፈጸም #እርምጃ ገብተዋል። በሀገሪቱ " ቲክቶክ " መስራት እንዳቆመም ተነግሯል። ሰዎች መተግበሪያውን ሲከፍቱን የሚያገኙት መልዕክት " Unable to load, please try again." የሚል ነው። ውሳኔው በሀገሪቱ ብሔራዊ ደህንነት መ/ቤት የተላለፈ ነው። የኪርጊስታን ዲጂታል ሚኒስቴር ቲክቶክን የሚያስተዳድረው ' ባይት ዳንስ ' ኩባንያ ፥ " #የልጆችን ፦ - አእምሯዊ፣ - አካላዊ፣ - መንፈሳዊ እና #ሥነምግባራዊ እድገትን ለመጠበቅ በህግ የተዘረዘሩ ህጋዊ መስፈርቶችን ማክበር አልቻለም " ብሏል። በዚህም ምክንያት " ቲክቶክ " በሀገሪቱ እንዳይሰራ ተደርጓል። ውሳኔው የተቃወሙ አካላት ይህ ተገቢ እንዳልሆነ በመግለጽ ገደቡ እንዲነሳ ጠይቀዋል። ከገደብ ይልቅ ቁጥጥር ይደረግበት ብለዋል። ከዚህ ቀደም የኪርጊስታን የባህል፣ ወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ፥ " ቲክቶክ " የተሰኘው መተግበሪያ ለልጆች አእምሯዊ እድገት እና አጠቃላይ ደህንነት ጠንቅ እየሆነ ነው " ማለቱ ይታወሳል። መተግበሪያው #ህጻናት እጅግ ጎጂ ሊሆኑ የሚችሉ ይዘቶችን እንዳያገኙ ለመከላከል በቂ #መቆጣጠሪያ እንደሌለው ነበር የገለጸው። በተጨማሪም ለተጠቃሚዎቹ ትክክለኛ የዕድሜ ማረጋገጫ እርምጃዎች እንደለለው እና ተጠቃሚዎችን በአጫጭር የቪዲዮ ክሊፖች ወደ ምናባዊ ግዛት በመሳብ #ሱስ የሚያስይዝ ይዘት እንዳለው አስረድቶ ነበር። ሚኒስቴሩ " ቲክቶክ " በወጣቱ ትውልድ ደህንነት ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳለው በአጠቃላይም ለትውልዱ ጠንቅ እየሆነ እንደመጣ አሳውቆ ነበር። በሌላ በኩል ፤ አሜሪካ ውስጥ ከመረጃ ደህንነት ጋር በተያያዘ መተግበሪያው እንዲታገድ ከፍተኛ ግፊት እየተደረገ ሲሆን  " ቲክቶክ " ከቻይናው ኩባንያ ካልተፋታ / አሜሪካ የምትቆጣጠረው አይነት ካልሆነ በመላ ሀገሪቱ መታገድ ዕጣ ፋንታ ሊገጥመው ይችላል ተብሏል። via tikvahethiopia @merkato_media
4 1931Loading...
28
በአሜሪካ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን (የኦሮሞ እና የትግራይና ማኅበረሰብ) አባላት ጦርነት እንዲቆም የሚጠይቅ ሰልፍ አካሄዱ‼️ ዋሺንግተን ዲሲ አካባቢ የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያ የኦሮሞ ማኅበረሰብ አባላት፣ የኦነግ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ የነበሩት የአቶ በቴ ዑርጌሳ ግድያን የሚቃወም ሰልፍ እና የሻማ ማብራት ሥነሥርዐት አከናወኑ። ኢትዮጵያ ውስጥ በኦሮሞ ተወላጆች ላይ ይደርሳል ያሉትን ግድያ ተቃውመው ጦርነት እንዲቆም ጠይቀዋል። በሌላ በኩል በዚሁ አካባቢ ሰልፍ ያደረጉት ትውልደ ኢትዮጵያ የትግራይ ተወላጆች፣ ጦርነት እንዲቆም፣ የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሙሉ ለሙሉ እንዲከበር እና ተገቢው ርዳታ ወደ ክልሉ እንዲገባ የሚጠይቅ ሰልፍ አካሂደዋል ሲል የአሜሪካ ድምፅ ዘገባ ያመላክታል። @merkato_media
4 3270Loading...
29
የቻይና ከተሞች እየሰመጡ ነው❗️ ከቻይና ዋና ዋና ከተሞች ግማሽ ያህሉ ላይ የመስመጥ አደጋ መጋረጡ ተሰምቷል።  በበሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰዎች በተለይ የባህር ከፍታ ሲጨምር ለጎርፍ አደጋ እየተጋለጡ ነው ሲል በአገር አቀፍ ደረጃ የወጣው የሳተላይት መረጃ  አመልክቷል። በሳይንስ ጆርናል የታተመው ይኸው ጥናት 45 በመቶው የቻይና የከተማ መሬት በአመት ከ3 ሚሊ ሜትር በላይ በፍጥነት እየሰመጠ ነው ያለ ሲሆን 16 በመቶው ደግሞ በዓመት ከ10 ሚሊ ሜትር በላይ መስመጡን ገልጿል።  በከተሞቹ የሚገኙ በርካታ ሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች  ምክንያት መሆናቸውን ሮይተርስ በዘገባው አመልክቷል።
4 1215Loading...
30
🛒ታላቅ ቅናሺ ከሸገር ገበያ📣 ✔️m13 Samsung 📱 ✔️4ram ✔️64Gb         ዋጋ 13200 እዚህ ላይ ያግኙን 👇👇                   @ethio_sellerr አዲስአበባ ያሉበት እናደርሳለን 🛵🚵 ክፍለሀገር በፖስታ ይደርሷታል።📩📮
3 9201Loading...
31
ልጁን ከእነ ህይወቷ ለመቅበር የሞከረው ወላጅ አባት #Ethiopia | የአንድ አመት ልጁን ከእነ ህይወቷ ለመቅበር የሞከረው ወላጅ አባት በቁጥጥር ስር ማዋሉን በቤንች ሸኮ ዞን የሰሜን ቤንች ወረዳ ፖሊስ አስታወቀ፡፡ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በቤንች ሸኮ ዞን የሰሜን ቤንች ወረዳ ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፒክተር አለማየሁ አማረ ለክልሉ ፖሊስ የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን እንደገለፁት በወረዳው ኮሶል ቀጭን መንደር ሚያዚያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ላይ በባልና ሚስት መካከል በተፈጠረው ፀብ ምክንያት የወንጀል ድርጊቱን ለመፈፀም ሙከራ ማድረጉን አስረድተዋል፡፡ አዛዡ አክለውም በባልና ሚስት መካከል በተፈጠረ ጊዜያዊ ፀብ እናት የአንድ ዓመት ሴት ህፃን ልጅ ጥላ በመጥፋቷ ወላጅ አባት ቲቲዮስ ኪያግላስ የተባለው ተጠርጣሪ የአንድ ዓመት ህፃን ልጁ እያለቀሰች ስታስቸግረዉ በሁኔታው ተበሳጭቶ የአንድ አመት ልጁን በህይወት ለመቅበር ጉድጓድ ሲያዘጋጅ የተመለከቱ የአከባቢው ነዋሪዎች ለፖሊስ ጥቆማ ይሰጣሉ፡፡ ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ተጠርጣሪውን ጉድጓድ እየቆፈረ እያለ በቁጥጥር ስር እንዲውል በማድረግ ህፃኗን ጉዳት ሳይደርስባት መታደግ መቻሉንና በተጠርጣሪው ላይ ምርመራ እየተጣራበት እንደሚገኝ አስረድተዋል፡፡ ፖሊስ የህፃኗን ወላጅ እናቷን እያፈላለገ ሲሆን ህፃኗ በአሁን ሰዓት ሰሜን ቤንች ወረዳ ፖሊ እንክብካቤ እያደረገላት እንደሚገኝ የገለፀት ፖሊስ አዛዡ በቤተሰብ መካካል አለመግባባቶች በሚፈጠሩበት ወቅት ችግሩን በመነጋገር መፍታት ይገባል ሲሉ ፖሊስ አዛዡ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል ሲል የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነትና ኮሚንኬሽን መረጃ ያመለክታል።
4 2204Loading...
Photo unavailableShow in Telegram
መንግሥት የመንግሥት ሠራተኞች ቅጥርና ምደባ የአገሪቱን ብሄረሰቦች ብዝኀነትና የጾታና የአካል ጉዳተኞችን ተዋጽዖ የጠበቀ እንዲኾን የሚያስገድድ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርቧል። ምክር ቤቱ፣ በረቂቅ አዋጁ ላይ ትናንት ተወያይቷል። ረቂቅ አዋጁ፣ በመንግሥት ሠራተኞች ደሞዝ ጭማሪ፣ ደሞዝ እርከን፣ ክፍያና ጥቅማጥቅሞች ላይ ማሻሻያ እንዳደረገም ተገልጧል። የአነሳ ብሄረሰቦችና የማኅበረሰብ ክፍሎች በመንግሥት መስሪያ ቤቶች በቅጥር፣ ምደባ፣ ዝውውር፣ በሥራ ደረጃ እድገት፣ በትምህርትና ሥልጠና ረገድ ተጨማሪ መንግሥታዊ ድጋፍ እንዲደረግላቸውም ረቂቅ አዋጁ ይደነግጋል። ምክር ቤቱ፣ ረቂቅ አዋጁን ጉዳዩ ለሚመለከተው ቋሚ ኮሚቴ መርቶታል። [ዋዜማ]
Show all...
👍 7👎 5
Photo unavailableShow in Telegram
ዋቻሞ ዩኒቨርስቲ🙆‼️ በሀድያ ዞን ዋቻሞ ዩኒቨርስቲ ለአንድ የዩኒቨርስቲው የፋይናንስ ቡድን መሪ የ790 ቀን አበል እንዲሁም ለሌላኛው የፋይናንስ የቡድን መሪ ደግሞ በስድስት ወራት ውስጥ ብቻ የ1,469 ቀን (1,056,854 ብር) አበል እንደተከፈላቸው ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሰነድ ማስረጃዎችን፣ጥቆማዎችን እና መመሪያዎችን በማጣቀስ ምርመራ አድርጎ ውጤቱን ይፋ አድርጓል። ሌላም የዩኒቨርስቲው ፋይናንስ ሳያውቅ 1.4 ቢሊዮን ብር ለኦክስጅን ማምረቻ በሚል በህገወጥ መንገድ መንቀሳቀሱን እና ፍቃድ የሌለው የኮንስትራክሽን ድርጅት ግንባታውን እንዲሰራ ያለ ጨረታ እንደተሰጠው በምርመራ ውጤቱ ተገልጿል። በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎችም ተመሳሳይ ምርመራ ቢደረግ ከዚህም በላይ የሙስና ወንጀል እንደሚገኝ እሙን ነው። @sheger_press @sheger_press
Show all...
👍 21 1
Photo unavailableShow in Telegram
2016 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና መርሐግብር ይፋ ሆኗል፡፡ መርሐግብሩ ከትግራይ ክልል ውጪ በሁሉም ክልሎች እና በሁለቱም የከተማ አስተዳደሮች በወረቀት እና በበይነ መረብ ፈተናውን ለሚወስዱ ተፈታኞች እንደሚያገለግል የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል። የ2016 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና:— ✔ከሐምሌ 3-5/2016 ዓ.ም ለማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ✔ከሐምሌ 9-11/2016 ዓ.ም ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ይሰጣል። የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት @sheger_press @sheger_press
Show all...
👍 5
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ በአፋርና ሱማሌ ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች በአፋር እና ኢሳ ጎሳዎች መካከል በሚያጋጥሙ ግጭቶች ሳቢያ ከ38 ሺህ በላይ ዜጎች አፋር ክልል ውስጥ በሦስት ወረዳዎች መፈናቀላቸውን ባካባቢው ባደረገው ጉብኝት ማረጋገጡን አስታውቋል። የኹለቱ ጎሳዎች ታጣቂዎች ባብዛኛው ግጭት ውስጥ የሚገቡት፣ በአፋር ክልል ገቢ ረሱ ዞን እና በሱማሌ ክልል ሲቲ ዞን አጎራባች አካባቢዎች ሲኾን፣ በተለይ በተያዘው ዓመት ተደጋጋሚ ግጭቶች ተካሂደዋል። የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት፣ በኹለቱ ጎሳዎች መካከል በተደጋጋሚ የሚካሄደውን ግጭት ለመፍታት ከሳምንታት በፊት አሸማጋይ ኮሚቴ ማቋቋሙ አይዘነጋም። ኾኖም የጎሳ ግጭቱ እስካለፈው ሳምንት ድረስ ቀጥሎ እንደነበር ተሰምቷል። @merkato_media
Show all...
👍 11
Photo unavailableShow in Telegram
ታሰረ ‼️ በቲክቶክ የማህበራዊ ትስስር ገፅ መሌ ፌዳው በሚል ስም የምናውቀው የፌደራል ፖሊስ አባል መለሰ ብርሃኑ መታሰሩ ተሰምቷል። የፖሊስ አባሉ የታሰረበት ምክንያት የመከላከያን የክብር ልብስ ለብሶ የሰራዊቱን ስም የሚያጎድፍ ቪድዮ ሰርቷል በሚል ሲሆን ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርቦ ዋስትና ሳይፈቀድለት ቀጠሮ እንደተሰጠበት እንደቀረ ታውቋል። @sheger_press @sheger_press
Show all...
👍 17😁 6😢 3
ባለፉት ጥቂት ቀናት በአማራ ክልል ምዕራብ ጎጃም ዞን መራዊ ከተማ በፋኖ ታጣቂዎች እና በመንግሥት ኃይሎች መካከል ግጭቶች እንደተካሄዱ ዋዜማ ከምንጮች ሰምታለች። በግጭቱ ሳቢያ፣ የክልሉን ዋና ከተማ ባሕርዳርን ከምሥራቅ ጎጃም ዞን ዋና መቀመጫ ደብረማርቆስ ጋር የሚያገናኘው መንገድ ለተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ተዘግቶ እንደነበር ተሰምቷል። በተመሳሳይ፣ በሰሜን ወሎ ዞን ውርጌሳ ከተማ እና አካባቢዋ በኹለቱ ወገኖች መካከል ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ግጭት እንደተካሄደ ምንጮች ተናግረዋል። @merkato_media @merkato_media
Show all...
👍 12
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል የሕወሃት ኃይሎች ከሱዳን ጦር ሠራዊት ጋር ወግነው እየተዋጉ ነው በማለት ያቀረበውን ውንጀላ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አስተባብሏል። የፈጥኖ ደራሹን ኃይል ውንጀላ "በጥብቅ እንደሚያወግዝ" የገለጠው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ይህን ውንጀላ ያሰማው ዓለማቀፍ ድጋፍ ለማግኘት ሲል ነው በማለት አጣጥሎታል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ሕወሃት የፖለቲካ ፓርቲ በመኾኑ "የታጠቀ ኃይል ወይም ሚሊሺያ የለውም" በማለትም ምላሽ ሰጥቷል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ አያይዞም፣ ሱዳን በትግራዩ ጦርነት ወቅት በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ የክልሉን ስደተኞች ያስጠለለች እንደመኾኗ ትግራይ በሱዳን የውስጥ ጉዳይ የምትገባበት ምክንያት ሊኖራት አይችልም ብሏል። ኹለቱ ወገኖች ጦርነቱን ከሚያባብሱ ንግግሮች እንዲቆጠቡና ጦርነቱን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱም ጊዜያዊ አስተዳደሩ ጠይቋል። @merkato_media @merkato_media
Show all...
👍 7
ለመላው የመርካቶ የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ   እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። በዓሉ የሰላም ፣ የደስታ ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ  ይሆን ዘንድ እየተመኘን በዓሉን ስናከብር ዓቅመ ደካሞችን በመርዳት ይሆን ዘንድ በትህትና እንጠይቃለን። መልካም በዓል @merkato_media @merkato_media
Show all...
👍 19 2
Photo unavailableShow in Telegram
ተፈታ‼️ ልጅ ያሬድ ተፈቷል💇‍♂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ክብር የሚነካ ቃላት ተናገሮ ማረሚያ ቤት በእስር ላይ የነበረው ልጅ ያሬድ በዛሬው ዕለት ተፈቷል። @sheger_press @sheger_press
Show all...
👎 33👍 7🖕 1
Photo unavailableShow in Telegram
ጌታቸው ረዳ‼️ "በየጊዜው ወጣቶች የምገብርበት የጦርነት ምዕራፍ መዘጋት አለበት " - አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ በኩል ዛሬ መልዕክት አሰራጭተው ነበር። በዚህም ፤ " የህዝባችን ሁለንተናዊ መብትና ጥቅም ከማረጋገጥና አስተማማኝ ከማድረግ የሚቀድም ሌላ አጀንዳ የለንም " ብለዋል። " የህዝባችን ጥቅምና መብት የሚያረጋግጥ መንገድ ሁሉ እንጓዘዋለን " ያሉት አቶ ጌታቸው " ጉዞው እንዲሳካ የህዝቡ ተሳትፎ ወሳኝ ነው " ሲሉ አክለዋል። ፕሬዜዳንቱ ፤ " ከሚገባው በላይ ያበረከተ ህዝብ በቅንነትና ታማኝነት ማገለገል ይገባል " ሲሉም ገልጸዋል። " ህዝቡ ከጦርነትና ጦርነት ወለድ ችግሮች በማላቀቅ ወደ አስተማማኝ ሰላም እንዲሸጋገር መስራት ይገባል " ሲሉም አስገንዝበዋል። አቶ ጌታቸው ረዳ  ፤ " በየጊዜው ትኩስ ሃይል የሆኑትን ወጣቶች የምንገብርበት የጦርነት ምዕራፍ ተዘግቶ ፤ የልማትና የእድገት ፍላጎታችን እንዲሳካ መስራት አለብን " ብለዋል። (Tikvah)
Show all...
😁 18👍 15🕊 3👎 2