Merkato Media
#merkato_media #መርካቶ_ሚድያ በዚህ ቻናል ለኢትዮጵያ ፍቅር ሰላም አንድነት ስለ ፍትህ የምናወራበት ድምፅ ላጡ ድምፅ የምንሆንበት ቻናል ነው። ''We testify about the Truth ''
Show more7 455Subscribers
-1624 hours
-697 days
-20730 days
- Subscribers
- Post coverage
- ER - engagement ratio
Data loading in progress...
Subscriber growth rate
Data loading in progress...
እግር ኳስ በኢትዮጵያ ተዓምራቱ እንደቀጠለ ነው።
ይህ ክስተት ጎል አግብተው ደስታቸውን እየገለፁ ይመስላል ግን አይደለም ዳኛውን ከበው እያናገሩት ነው። አንዱ ተጨዋች ለማናገር ሜዳው ሁላ አልበቃውም ተጨዋች ላይ ወጥቶ ነው የሚያናግረው።
😁 7👍 5💔 1
ኢትዮጵያ ፤ የአፍሪካ ዋንጫ ለማዘጋጀት እቅድ እንዳላትና ለእርሱም እየሰራች ነዉ ተባለ
ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አመታት የአፍሪካ ዋንጫ ውድድርን እንድታዘጋጅ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጄላ መርዳሳ መናገራቸውን ዳጉ ጆርናል ታዝቧል።
የአፍሪካ ዋንጫን እ.ኤ.አ በ 2029 ወይም በ2031 ለማዘጋጀት እየሰራን ነው ያሉት ሚኒስትሩ ለእቅዱ መሳካትም ቢያንስ ስድስት ደረጃቸውን የጠበቁ ስታዲየሞች አስፈላጊ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
ካፍ ከዚህ በፊት ያልነበሩ አዳዲስ መስፈርቶችን በማስቀመጡ ኢትዮጵያ አንድም ደረጃውን የጠበቀ ስታዲየም እንዳይኖራት አድርጓል ሲሉም አቶ ቀጀላ መርዳሳ አስረድተዋል። ኢትዮጵያ የካፍን ደረጃ የሚመጥኑ ስታዲየሞች የሌላት በመሆኑ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ረዘም ላሉ ጊዜያት ከሀገሩ ዉጪ ለመጫወት ተገድዶ የነበረ መሆኑ ይታወቃል።
የዉድድሩ አዘጋጅ ሀገራት ቢያንስ ስድስት ስታዲየሞችን እንዲያዘጋጁ ካፍ ቢያዝም ኢትዮጵያ በዚህ ረገድ ምን ያህል ዝግጁ ናት የሚለዉ ግን አጠያያቂ ነዉ።
Via ዋልታ
🤣 20👍 12
በልዩ ቅናሽ ኦርጅናል ስልኮች ይሸምቱ
Brand #Samsung
A15- 4 ram 128 GB - 16,500
A05 -4 ram 64 GB - 11,500
A34- 6ram 128 GB - 28,000
A54- 8ram 256GB - 38,000
S24 Ultra -12 ram - 512 GB -126,000
ይደውሉልን 👉 0913366506
Telegram @Birukepromo
ተጨማሪ እቃዎችን ለመሸመት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ👇👇
https://t.me/bura_collection
👍 4😁 1
አዲስ አበባ፤ ተኝተዉ በነበሩ ሰዎች ላይ ቤት ተደርምሶ ሰባት ሰዎች ሞቱ
ዛሬ ለሊት ሊነጋ ሲል 11 ሰኣት አከባቢ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 12 በተለምዶ ጠሮ መስጊድ በሚባል አከባቢ በደረሰ የቤት መፍረስ አደጋ የሰባት ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡
ለአደጋው መንስኤ የሆነው በጎረቤት የተከማቸው ለቤት ግንባታ የሚውል ከፍተኛ መጠን ያለው አፈርና ድንጋይ ከመሬት እየወጣ ካለው ግንባታ ጋር ተደርምሶ መኖሪያ ቤቶች ላይ በማረፉ በጠዋት ተኙ የነበሩ ሰባት ሰዎች አንዳቸውም በህይወት መውጣት ሳይችሉ በዚያው አልቀዋል፡፡
አፈርና በግንባታ ላይ ያለው ድንጋይ ተደርምሶባቸው ያለቁት የአንድ ቤተሰብ አባላት እና ጎረቤታቸው ነው ተብሏል፡፡ እድሜያቸው ከ11፤ 12፣ 25 እና 28 የሆኑ አራት ሴቶች እንዲሁም እድሜያቸው የ4፣ የ12 እና የ30 ዓመት እድሜ ያላቸው ሶስት ወንዶች ባጠቃላይም ሰባት ሰዎች በተኙበት ቤትን የደረመሰባቸው የአፈር እና የድንጋይ ክምር አንዳቸውም በህይወት እንዳይወጡ አድርጓል፡፡
የአደጋውን ዝርዝር ጉዳይ ፖሊስ እያጣራ መሆኑን ያስረዱት የአዲስ አበባ አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ ኮሚሽናቸው ያደረገው የህይወት አድን ሙከሪያ ከቦታው አመቺ አለመሆን ጋር ተያይዞ ሳይሳካ መቅረቱን አስረድተዋል፡፡ ቦታው ላይ ደርሶ አደጋውን የተመለከተው የአዲስ አበባው ዘጋቢችን ከላይ ወደ ታች የተደረመሰው የአፈር ክምችትና ግንብ ስር የወጡ የሰው አስከሬን የመቅበር እና ቤት ላይ የተደረመሰውን አፈርና ድንጋይ የማንሳት ስራ በአከባቢው ህብረተሰብ ስከወን ነበር ብሏል፡፡
በቦታው ላይ ከነበሩ የሟቾች ጎረቤት መካከል አቶ አሊ አማን የተባሉ የአይን እማኝ ጎረቤት በሌሊቱ ተነስተው የደረሱት የድንጋይ መደርመስ ከፍተኛ ድምጽ በመስማት ነው ብለዋል፡፡
👍 6😭 3❤ 2😢 1
ስለ ጊዜ.....
ኒዉዬርክ ከካሊፎርኒያ በ 3 ሰዓት ትቀድማለች ነገር ግን ይህ ካሊፎርኒያን ቀርፋፋ አያደርጋትም ምክንያቱም የራሷ ጊዜ አላትና ፡፡
አንዳንድ ሰዉ በ22 አመቱ ይመረቃል ነገር ግን ጥሩ ስራ ለመያዝ 5 አመት ይፈጅበታል፡፡
አንዳንዱ በ25 አመቱ የድርጅት ሃላፊ ሆኖ በ5ዐ አመቱ ሲሞት ሌላዉ በ50 ዓመቱ ሃላፊ ሆኖ እስከ 9ዐ ዓመት ይኖራል፡፡
ኦባማ በ55 ዓመቱ ኘሬዝዳንትነቱን ጨረሰ ነገር ግን ትራምፕ በ7ዐ ዓመቱ ኘሬዝዳንትነቱን ጀመረ! ይሄ ትራምፕን ኀላ ቀር አያደርገዉም፡፡
ጊዜ በሕይወታችን ወሳኝ ነገር ነዉ ፡፡ ፈጣሪ በጊዜዉ ሁሉን ነገር ዉብ ያደርጋል
ስለዚህ.... ከሁሉ በኋላ የቀረን ወይም ወደፊት የቀደምን አይምሰለን ሁሉም ሰዉ የራሱ የሆነ የኑሮ ሩጫና የተፈጠረበት አላማ አለዉ! ሁላችንም የራሳችን የሆነ የጊዜ ክልል አለን!
Dr. Mihret Debebe
👍 37👏 3👎 1
ሰውዬው ተገኝተዋል
ኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ለገጣፎ አቅራቢያ 44 ማዞሪያ ጅዳ ኩራ በተባለ ፖሊስ ጣቢያ መታሰራቸው ታውቋል።
እኝህ ሰው በተደበደቡ፣በተበደሉ፣ጥቃት በደረሰባቸው እንደት ሊታሰሩ ቻሉ ለሚለው ምላሽ አልተገኘም።
በወቅቱ እሳቸውን ከፍ ዝቅ እያደረኩ ርካሽ የዘረኝነት ተግባር ሲፈፅሙባቸው የነበሩ ወጣቶች ተሰብስበው መታሰራቸውም ተሰምቷል።(wasu)
@ethio_mereja_news
@ethio_mereja_news
👍 9
የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ እንዳስታወቀው፤ "በኢትዮጵያ በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ ችግሮች ምክንያት ከ5 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው ውጪ ናቸው።"
👎 17👍 4😁 1
"እስራኤል በወታደሮቿ ላይ የሚጣልን ማዕቀብ ትታገላለች" - ኒታንያሁ
አሜሪካ በእስራኤል ወታደሮች ላይ ማዕቀብ ለመጣል እያቀደች መሆኗ ዘግቦ ነበር።
እንደ South China Morning Post ዘገባ አሜሪካ እጥለዋለሁ ያለችው ማዕቀብ በዌስት ባንክ የሰፈሩ የጦር አባላት ላይ ነው።
"የተፈፀመ የሰብዓዊ መብት ጥሰት የለም" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ኒታንያሁ በበኩላቸው፣"በእስራኤል የጦር አባላት ላይ የሚጣልን የትኛውንም ማዕቀብ እታገላለሁ" ብለዋል።
@thiqahEth
👍 12❤ 2👎 1
ጥቆማ‼️
ታላቅ ቅናሽ ይዞ የመጣው የራሳችን የሆነው bura collection የገበያ መድረክ አሁንኑ የቴሌግራም ቻናላችን በመቀላቀል ኦርጅናል እቃዎችን ይሸምቱ👇👇
ኦርጅናል አልባሳቶችና
ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች
ሁሉንም ዕቃ ባንድ ላይ የሚያገኙበት የቴሌግራም ቻናላችን ይቀላቀሉ👇👇
https://t.me/bura_collection
https://t.me/bura_collection
የፈለጉትን እቃ የሚያገኙበት