en
Feedback
Bashewam Primary & Junior School 1-8

Bashewam Primary & Junior School 1-8

Open in Telegram

Bashewam School Grade 1-8

Show more
2 749
Subscribers
+624 hours
+367 days
+4630 days
Posts Archive
photo content

photo content

የመኪና አደጋ ሕይወቱን የቀማው ታዳጊ ብስክሌተኛ!😭 #maleda: በአዲስ አበባ ከተማ የብስክሌት ስፖርት ውስጥ ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት የነበረው ታዳጊው ቤካ ወ/ኪዳን በደረሰበት አሳዛኝ የመኪና አደጋ ሕይወቱ አለፈ። ታዳጊው ቤካ ወ/ኪዳን ትናንት ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በብስክሌት ላይ እያለ በደረሰበት ከባድ የትራፊክ አደጋ ነው ሕይወቱ ሊያልፍ የቻለው። የአባቱን ፈለግ በመከተል ወደ ብስክሌት ስፖርት የገባው ቤካ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደረጃ በሚዘጋጁ ልዩ ልዩ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ውጤታማ መሆን የቻለ ስፖርተኛ ነበር። በዚሁ ዓመት በአዳማ ከተማ በተካሄደው ሀገር አቀፍ የታዳጊዎች የምዘና ውድድር ላይም የከተማ አስተዳደሩን ወክሎ በመሳተፍ ደማቅ አፈጻጸም አሳይቶ ነበር። ይህን ባለ ብዙ ህልም ታዳጊ ብስክሌት እየነዳ ሳለ የትራፊክ አደጋ ገጭቶት ህልሙን እስከወዲያኛው ቀማው ። ልብ ይሰብራል። ዛሬ ቤካን የቀማን አደጋ ነገ ሌላ ህይወት እንዳይቀማ፣ አሽከርካሪዎች ሆይ በመንገድ ላይ ለባለብስክሌቶችና ለእግረኞች ያለንን አክብሮትና ጥንቃቄ እናሳድግ። በሕይወት ውስጥ ሁለተኛ ዕድል የለምና።የማለዳ ቤተሰቦች በቤካ ድንገተኛ ህልፈት እጅግ አዝነናል። ለቤተሰቦቹ፣ ለስፖርቱ ማኅበረሰብ እና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛለን።ቤካ ፤ነፍስህን ይማር፣ እግዚአብሔር በገነት ያኑርህ!🙏💔

ተማሪ ቤካ ወ/ኪዳን  በትናትናው እለት በቀን 04/10/2018 ዓ. ም እጅግ አሳዛኝ በሆነ ክስተት በሞት ተለይቶናል። ተማሪው በዚህ ዓመት የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልቀቂያ ፈተና (ሚንስትሪ) ለመፈተን ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቆ👉 Orientation ለመዉሰድ በቀጠሮ የተለያየን ቢሆንም በጋጠመዉ ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ህይወቱ አልፋል። ተማሪው በትምህርት ቤት በነበረው ባህሪ ተወዳጅ እና ምስጉን የነበረ ሲሆን በሀገር ደረጃም ተሰፋ የተጣለበት ጎብዝ ብስክሌተኛ ነበር። የባሽዋም ት/ቤት ማህበረሰብ በዉዱ ተማሪያችን በቤካ ወ/ኪዳን እጅግ አስደንጋጭ እና ድንገተኛ ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ የሃዘን ስሜት እየገለፅን👉 ቸሩ እግዚአብሔር ነብሱን በአፀደ ገነት እድያኖርልንና ለመላው ቤተሰቡ እና ጕደኞቹ መፅናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን።

photo content

photo content

photo content

photo content

ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ:: በቅድሚያ እንኳን በሰላም አደረሳችሁ እያልን አርብ ሰኔ 05/10/2018ዓ.ም በሚክሊላንድ ት/ቤት የመፈተኛ ጣቢያ:- 1.👉ለ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከ4:00 - 600 ሰዓት 2.👉ለ 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከ7:30 ጀምሮ በጣቢያ ኃላፊዎች እና ሱፕርቫዘሮች ኦረንቴሽን የሚሰጥ ስለሆነ አንድ ላይ በጋራ ለመሄድ አንዲመች በባሽዋም ት/ቤት :- 👉6ኛ ክፍሎች ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት በባሽዋም ት/ቤት 👉8ኛ ክፍሎች 7:00 ሰዓት ላይ ከቻላችሁ ሚክሊላንድ ት/ቤት ካልሆነ ደግሞ ባሸዋም ት/ቤት መጥታችሁ አብረን መሄድ የሚቻል መሆኑን እየገለፅን ሁላችሁም በተጠቀሰው ሰዓት ዩኒፎርም ለብሳችሁ እንድትገኙ እናሳሰባለን::

photo content

photo content

photo content

photo content
+6

photo content

Grade 6th Exam Orientation

Bashewam Primary & Junior School 1-8 - Statistics & analytics of Telegram channel @bash2015