2 749
订阅者
+624 小时
+367 天
+4630 天
帖子存档
የመኪና አደጋ ሕይወቱን የቀማው ታዳጊ ብስክሌተኛ!😭
#maleda: በአዲስ አበባ ከተማ የብስክሌት ስፖርት ውስጥ ትልቅ ተስፋ ተጥሎበት የነበረው ታዳጊው ቤካ ወ/ኪዳን በደረሰበት አሳዛኝ የመኪና አደጋ ሕይወቱ አለፈ።
ታዳጊው ቤካ ወ/ኪዳን ትናንት ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም በብስክሌት ላይ እያለ በደረሰበት ከባድ የትራፊክ አደጋ ነው ሕይወቱ ሊያልፍ የቻለው።
የአባቱን ፈለግ በመከተል ወደ ብስክሌት ስፖርት የገባው ቤካ፣ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ደረጃ በሚዘጋጁ ልዩ ልዩ ውድድሮች ላይ በመሳተፍ ውጤታማ መሆን የቻለ ስፖርተኛ ነበር።
በዚሁ ዓመት በአዳማ ከተማ በተካሄደው ሀገር አቀፍ የታዳጊዎች የምዘና ውድድር ላይም የከተማ አስተዳደሩን ወክሎ በመሳተፍ ደማቅ አፈጻጸም አሳይቶ ነበር። ይህን ባለ ብዙ ህልም ታዳጊ ብስክሌት እየነዳ ሳለ የትራፊክ አደጋ ገጭቶት ህልሙን እስከወዲያኛው ቀማው ። ልብ ይሰብራል።
ዛሬ ቤካን የቀማን አደጋ ነገ ሌላ ህይወት እንዳይቀማ፣ አሽከርካሪዎች ሆይ በመንገድ ላይ ለባለብስክሌቶችና ለእግረኞች ያለንን አክብሮትና ጥንቃቄ እናሳድግ። በሕይወት ውስጥ ሁለተኛ ዕድል የለምና።የማለዳ ቤተሰቦች በቤካ ድንገተኛ ህልፈት እጅግ አዝነናል።
ለቤተሰቦቹ፣ ለስፖርቱ ማኅበረሰብ እና ለወዳጅ ዘመዶቹ መጽናናትን እንመኛለን።ቤካ ፤ነፍስህን ይማር፣ እግዚአብሔር በገነት ያኑርህ!🙏💔
ተማሪ ቤካ ወ/ኪዳን በትናትናው እለት በቀን 04/10/2018 ዓ. ም እጅግ አሳዛኝ በሆነ ክስተት በሞት ተለይቶናል።
ተማሪው በዚህ ዓመት የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልቀቂያ ፈተና (ሚንስትሪ) ለመፈተን ቅድመ ዝግጅቱን አጠናቆ👉 Orientation ለመዉሰድ በቀጠሮ የተለያየን ቢሆንም በጋጠመዉ ድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ህይወቱ አልፋል። ተማሪው በትምህርት ቤት በነበረው ባህሪ ተወዳጅ እና ምስጉን የነበረ ሲሆን በሀገር ደረጃም ተሰፋ የተጣለበት ጎብዝ ብስክሌተኛ ነበር።
የባሽዋም ት/ቤት ማህበረሰብ በዉዱ ተማሪያችን በቤካ ወ/ኪዳን እጅግ አስደንጋጭ እና ድንገተኛ ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ የሃዘን ስሜት እየገለፅን👉 ቸሩ እግዚአብሔር ነብሱን በአፀደ ገነት እድያኖርልንና ለመላው ቤተሰቡ እና ጕደኞቹ መፅናናትን እንዲሰጥልን እንመኛለን።
ለ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች በሙሉ::
በቅድሚያ እንኳን በሰላም አደረሳችሁ እያልን አርብ ሰኔ 05/10/2018ዓ.ም በሚክሊላንድ ት/ቤት የመፈተኛ ጣቢያ:-
1.👉ለ6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከ4:00 - 600 ሰዓት
2.👉ለ 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ከ7:30 ጀምሮ በጣቢያ ኃላፊዎች እና ሱፕርቫዘሮች ኦረንቴሽን የሚሰጥ ስለሆነ አንድ ላይ በጋራ ለመሄድ አንዲመች በባሽዋም ት/ቤት :-
👉6ኛ ክፍሎች ከጠዋቱ 3:00 ሰዓት በባሽዋም ት/ቤት
👉8ኛ ክፍሎች 7:00 ሰዓት ላይ ከቻላችሁ ሚክሊላንድ ት/ቤት ካልሆነ ደግሞ ባሸዋም ት/ቤት መጥታችሁ አብረን መሄድ የሚቻል መሆኑን እየገለፅን ሁላችሁም በተጠቀሰው ሰዓት ዩኒፎርም ለብሳችሁ እንድትገኙ እናሳሰባለን::
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
