en
Feedback
ተዋሕዶን እንወቅ።

ተዋሕዶን እንወቅ።

Open in Telegram

አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኲሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድኅነነ እምዕለት እኪት ወባልሐነ ውስተ መንሡት። ✝በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ✝ የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ጸሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማዕታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።

Show more
Buy Ad
2 372
Subscribers
-124 hours
-117 days
+330 days
Posts Archive
❝እንግዳ ሊመጣ ሲል ቤታችሁን እንደምታሰናዱ፥ ክርስቶስ ወደ እናንተ ሊመጣ ነውና፤ በጾም፥ በጸሎትና በንጽሕና ነፍሳችሁን አሰናዱ።❞ (ቅዱስ አምብሮስ ዘሚላን)
❝እንግዳ ሊመጣ ሲል ቤታችሁን እንደምታሰናዱ፥ ክርስቶስ ወደ እናንተ ሊመጣ ነውና፤ በጾም፥ በጸሎትና በንጽሕና ነፍሳችሁን አሰናዱ።❞ (ቅዱስ አምብሮስ ዘሚላን)

https://youtu.be/ybmxpG8ZRqw?si=7EVwxSO8DMZJ1LtS ❝በጽዮን ለሚኖር ለእግዚአብሔር ዘምሩ..❞

✥ አስማቲሁ ለጾም ✥ የነቢያት (የገና ጾም) ከኅዳር እኩሌታ (15) ጀምሮ የሚጾም ሲሆን ፍጻሜው ታህሳስ 29 በልደት በዓል ነው በዘመነ ዮሐንስ ግን ታህሳስ 28 የልደት በዓል ይከበራል። ይህን ጾም በዘመነ ብሉይ እና በዘመነ ሐዲስ ብዙ ቅዱሳን ጾመውታል ። ለጾሙ ከተሰጡት ስያሜዎች የተወሰኑትን እነሆ፦ 1, ጾመ አዳም ለአዳም የተነገረው ትንቢት ስለተፈጸመበት ይህንን ስያሜ አግኝቷል። አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገነት ከተባረረ በኋላ በፍጥረቱ ገዢ ኣድርጎ በገነት ያኖረኝን ፈጣሪዬን ትቼ የፍጡሩን ቃል ሰምቼ ትዕዛዝን አፍርሼ አሳዘንኩት ብሎ በፈጸመው በደል አዝኖ ተክዞ ፣ ጾመ ፣ ጸለየ ከልብ የሆነ ጸጸቱንም እንባውን በራሱ መፍረዱንም ዓይቶ እግዚአብሔር ተስፋ ድኅነት ሰጠው “በሐሙስ ዕለት ወበመንፈቃ ለዕለት እትወለድ እምወለተ ወለትከ ወእድህክ ውስተ መርህብከ ወእትቤዘወከ በመስቀልየ ወበሞትየ - በአምስት ቀን ተኩል (ማለት ከአምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን በኋላ) ከሰማየ ሰማያት ወርጄ ከድንግል ማርያም ተወልጄ በፈቃዴ ተገፍፌ ተገርፌ በዕለተ ኣርብ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅዬ ሥጋዬን ቆርሼ ደሜን አፍስሼ ሞቼ ተነስቼ አድንሃለሁ” ብሎ ቃል ኪዳን ገባለት አዳምም ‹‹በሐሙስ ዕለት›› ያለውን እንደ ተለመደው አቆጣጠር መስሎት እስከ ኣምስት ቀን ጠበቀ በኋላ ግን አምስት ሺህ አምስት መቶ ዘመን ሲፈጸም በፈቃዴ ተገርፌ በዕለተ አርብ በመልዕልተ መስቀል ተሰቅዬ ሥጋዬን ቆርሼ ደሜን አፍስሼ ሞቼ ተነስቼ አድንኃለው እንዳለው ተረድቶ ይህን ተስፋ በልቡናው ተሸክሞ ይኖር ነበር፡፡ ነጋዴ ስንቁን ይዞ እየበላ ከዚህ እስከዚያ ያደርሰኛል እያለ እንዲጓዝ በአጸደ ሥጋ በአጸደ ነፍስም ሳለ ጌታ እንዲህ ብሎኛል እና ይምረኛል እያለ ተስፋውን ኣጽንቶ ሲጠባበቅ ኖረ ለልጆቹም ሁሉ ነገረ፡፡ ትንቢት ተነገረ ሱባዬ ተቆጠረ፡፡ ፭ (5) ሺህ ፭፻ (500) ዘመን ሲፈጸምም የማያደርገውን የማይናገር የተናገረውንም የማያስቀር ጌታ‹‹ ቀን ቢደረስ አንባ ይፈርስ›› እንዲሉ ከዘመን ዘመን ከወሩ ወር ከዕለታቱ ዕለት ከሰዓቱ ሰዓት ሳይጎል በጽኑ ቀጠሮ የአዳም የልጅ ልጅ ከምትሆን ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ተወለደ፡፡ ገላ ፬፡፬ ስለዚህ ጾሙ ለአዳም የተሰጠው ተስፋ የተቆጠረው ሱባዔ ስለተፈጸመበት ‹‹ጾመ አዳም›› ይባላል፡፡ 2, ጾመ ነቢያት ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ስለተፈጸመበት ይህንን ስያሜ ኣግኝቷል፦ በየዘመናቱ የተነሱ ነቢያት እግዚአብሔር ወደፊት ሊያደርግ ያሰበውን በእምነት ዓይን እያዩ ምሥጢር ተገልጦላቸው የራቀው ቀርቦ የረቀቀው ገዝፎ እየተመለከቱ ትንቢት ተናገሩ፤ ያዩትን መልካም ነገር እንዲደርስላቸው ጾሙ ጸለዩ ፡፡ ነቢያት ስለመወለዱ፣ ወደ ግብጽ ስለመሰደዱ፣ በባህረ ዮርዳኖስ ስለመጠመቁ ብርሃን በሆነው ትምህርተ ወንጌል ጨለማን ዓለም ስለማብራቱ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ ስለመቀበሉ እና ስለመስቀሉ ስለትንሳኤው ስለ እርገቱ እና ስለዳግም ምጽኣቱ ትንቢት ተናግረው ኣላቆሙም፤ ለአዳም የተሰጠው ተስፋ ተገልጦላቸው ለተናገሩት ትንቢት ፍጻሜ እንዲያደርሳቸው ፈጣሪኣቸውን ተማጽነዋል በየዘመናቸው ‹‹ አንሰእ ኃይለከ ፈኑ እዴከ›› እያሉ ጮኹ በጾምና በጸሎትም ተወስነውም ሰው የሚሆንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራት እና በዓመታት ቆጠሩ ለምሳሌ ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሥጋዊው ትንቢት በተናገር በ446 ዓመት ጌታችን ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኖል ነቢያት ተስፋው በዘመናቸው ተፈጽሞ በዓይነ ሥጋ ለማየት ባይችሉም እግዚአብሔር ‹‹ አያደርገው አይናገር የተናገረውንም አያስቀር›› ብለው አምነው ከወዲሁ ተደሰቱ በዘመነ ሥጋዊ ቅርብ የነበሩት እነ ኢሳይያስ ጾሙ እንዴት መፈጸም እንዳለበት ተናግረዋል ትኢሳ 58፡1 በመሆኑ በጌታ ልደት ትንቢተ ነቢያት ስለተፈጸመበት ይህ ጾም ‹‹ጾመ ነቢያት›› ይባላል፡፡ የወልደ እግዚኣብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት ስለሆነም‹‹ጾመ ስብከት ›› ይባላል፡፡ 3, ጾመ ማርያም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ይህን ጾም ጾማዋለች ፡፡ ይህም ቅዱስ ገብርኤል ወልደ አምላክን ያለ ሰስሎተ ድንግልና (ድንግልና ያለማጣት) በግብረ መንፈስ ቅዱስ ጸንሳ እንደምትወልደው ካበሰራት በኋላ እመቤታችን ትሁት ናትና ምን ሠርቼ እወልደዋለሁ ብላ ጌታን ከመውለዷ አስቀድሞ ጾማዋለችና ‹‹ጾመ ማርያም›› ይባላል፡፡
JOIN @Applied_CHRISTIANITY

ጸምዐት ነፍስየ ለከ🥺 ❝አምላኬ፥ አምላኬ፥ ወደ አንተ እገሠግሣለሁ፤ ነፍሴ አንተን ተጠማች፥ ሥጋዬ አንተን እንዴት ናፈቀች።❞ (መዝ. 63፥1)

Repost from Gracious ✝
እመቤቴ ሆይ ለእኔም መልካሙን ስደት አስለምጂኝ። ስለ ልጅስ ስለወዳጅሽ ብለሽ የተሰደድሽ የክርስቶስ እናቱ እኔ ልጅሽን ተመልከቺኝ አንቺ ስለ ልጅሽ ተሰደድሽ እኔ ግን ከልጅሽ ተሰደድኩ። መልካሙን ስደ
እመቤቴ ሆይ ለእኔም መልካሙን ስደት አስለምጂኝ። ስለ ልጅስ ስለወዳጅሽ ብለሽ የተሰደድሽ የክርስቶስ እናቱ እኔ ልጅሽን ተመልከቺኝ አንቺ ስለ ልጅሽ ተሰደድሽ እኔ ግን ከልጅሽ ተሰደድኩ። መልካሙን ስደት ዘነጋሁት ክፉውን ስደት ግን ተያያዝኩት። ስለ ልጅሽ ሳይሆን ከልጅስ ተሰደድኩ ማዳኑንም ሁሉ ዘነጋሁት። እመቤቴ ሆይ ለእኔም መልካሙን ስደት አስለምጂኝ ከሃጢአት ሀገር ወደ እውነተኛ ሀገር ወዳቺ ቅዱስ ስደት እሰደድ ዘንድ ስጪኝ። ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ክፉን ስደት ከአንተ እርቄ እሰደድ ዘንድ ኀጢአቴ ግድ አለቺኝ ባዶ እግሬንም አስቀረቺኝ ለልቦናዬ(እግሮች) ንሰሃ የተባለ ቅዱስ መንገድን ሰራህለኝ ልመላለስበት ግን አልወደድሁምስለ እኔ በምድር እንደተሰደድህ እኔም ወደ አንተ እንድሰደድ ቅዱስ መሰደድን ስጠኝጌታዬ ሆይ ይህንንም ጊዜ ከሰጠኸንም ዘንድ መልካም የተመስጦ የፅሞና የንሰሐ ጊዜ አድርግልኝ። ከአንተ የምርቅበት ክፉ ስደት ሳይሆን ወደ አንተ የምቀርብበት ቅዱስ ስደትን እሰደድም ዘንድ ስጠኝ። “ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።”   — ማቴዎስ 5፥10

🎵#ኑ_እንቅረብ መጠራት ሳይመጣ ሥጋውን እንብላ ደሙንም እንጠጣ
ተወዳጆች ሆይ! ትዘምራላችሁ፡፡ [ከጸሎታቱ ትሳተፋላችሁ፡፡ ቅዳሴውን አስቀድሳችሁ] እምነታችሁን ትመሰክራላችሁ፡፡ ይህን ኹሉ አድርጋችሁ ስታበቁ ግን አትቆርቡም፡፡ ለምን? ከሰማያዊው ማዕድ የማትሳተፉት ለምንድን ነው? አንዳንዶቻችሁ፡- “እኔ ኃጢአተኛ ስለ ኾንሁ ልቆርብ አይገባኝም” ብላችኋል፡፡ እንዴ! እንደዚህ’ማ ካላችሁ ከመዝሙሩም፣ ከጸሎታቱም፣ ከቅዳሴውም ልትሳተፉ አይገባችሁማ! እስኪ ንገሩኝ! የንጉሥ ማዕድ በፊታችሁ አለ፡፡ መላእክት “ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ” እያሉ የሚያመሰግኑት የሚያገለግሉትም ማዕድ በፊታችሁ አለ፡፡ ንጉሡ በፊታችሁ አለ፡፡ ታዲያ እናንተ እንዲሁ ቁልጭልጭ እያላችሁ ትቆማላችሁን? ልብሳችሁ አድፎ ተዳድፎም ሳለ ምንም እንዳልተፈጠረ ኾናችሁ ወደ ቤታችሁ ትመለሳላችሁን? ወደ መንግሥተ ሰማያት፣ ወደ ሰማያዊው ንጉሥ ማዕድ ራሱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጠርቶን ሳለ ተዘጋጅተን እንደ መቅረብ ወደ ኋላ እንላለንን? እንደዚህ የምናደርግ ከኾነ ታዲያ ተስፋ ድኅነታችን ምንድን ነው? “መቅረብ ያልቻልኩት’ኮ” ብለን ደካማ መኾናችንን እንደ ሰበብ ማቅረብ አንችልም፡፡ ተፈጥሮአችንን እንደ ምክንያት ማቅረብ አንችልም፡፡ እንዳንቀርብ የሚያደርገን ደካማ መኾናችን አይደለም፡፡ አዎን ከሰማያዊው ማዕድ እንዳንሳተፍ የሚያደርገን እንዲሁ ሳንዘጋጅ ልል ዘሊላን ኾነን መቅረባችን እንጂ ሌላ ምንም ምክንያት አይደለም፡፡
ስለዚህ እማልዳችኋለሁ! [ንስሐ ገብተን እንደ ቸርነቱም ተዘጋጅተን] በፍርሐትና በረዓድ ኾነን [በግድ] እንቅረብ እንጂ “ኃጢአተኛ ስለ ኾንሁ” ብለን አንራቅ፡፡ [ከኃጢአት ኹሉ የሚያነጻን የክርስቶስ ደም እንጂ ኃጢአተኛ ነኝና አይገባኝም ብለን መራቃችን አይደለምና፡፡]
ክርስቶስ ዳግም ሲመጣ በድፍረት ወደ እርሱ መቅረብ ይቻለን ዘንድ ዛሬ በፍርሐትና በረዓድ ኾነን ወደ እርሱ እንቅረብ፡፡ ያኔ “ኑ እናንተ የአባቴ ብሩካን” ከሚላቸው ጋር ዕድል ፈንታችን ፅዋ ተርታችን በመንግሥተ ሰማያት ይኾን ዘንድ ዛሬ ወደ ሰማያዊው ማዕድ እንቅረብ፡፡ (በቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ገብረ እግዚአብሔር ኪደ እንደተረጎመው)

https://youtu.be/o8R3wowSXqk?si=5ZWKAdKdYoB62oPx በሸመገለም ጊዜ ከርሱ ፈቀቅ አይልም..

እግዚአብሔር ቢፈቅድና ቢወድ ከሕዳር 15 ጀምሮ ወደምንናፍቀው አምላካችን እቅፍ የሚያስጠጉን ፤ እግዚአብሔርን እንድንመስል የሚረዱን መንፈሳዊ ልምምዶችን በየሳምንቱ በጋራ እንለማመዳለን። በጾመ ነቢያት የምንጀምረው ይህንን ተግባራዊ ልምምድ እንዴት እንደምናከናውነው ሰሞኑን ሰፋ ያለ ማብራሪያ እሰጣችኋለሁ። እስከዚያው ይህንን መንፈሳዊ ልምምድ አብረን በዛ ብለን እንድንጀምረው ለወዳጆቻችሁ አጋሯቸው። በተግባራዊ ልምምዱ ቢካተት የምትሏቸው ነገሮች ካሉ ሀሳባችሁን መስማት እንሻለን። በቅዱሳን በአት በቤተ ክርስቲያን መኖርን ያድለን! @i_panagia

https://youtu.be/eR_njTYwa9A?si=UhkOdIlCMvnXt8zc Subscribe በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑን።

የ2018 የመጨረሻ የዘመነ ጽጌ ማኅሌት ግዕዙና አማርኛው
እነሆ የተወደደ የጽጌ ማኅሌት እነሆ ተፈጸመ፤ የሰማይና የምድር ንግሥት ሆይ! የተወደደው ልጅሽ ወደ እቅፍሽ እንደ ተጠጋ፣ አንቺም ወደ ማኅሌቱ ተጠጊ።
ወደ እግዚአብሔር ዙፋን የሚቀርብ ማኅሌት (ምስጋና) ያድርግልን። ሰናይ ማኅሌት!

የ2018 የመጨረሻ የዘመነ ጽጌ ማኅሌት ግዕዙና አማርኛው
እነሆ የተወደደ የጽጌ ማኅሌት እነሆ ተፈጸመ፤ የሰማይና የምድር ንግሥት ሆይ! የተወደደው ልጅሽ ወደ እቅፍሽ እንደ ተጠጋ፣ አንቺም ወደ ማኅሌቱ ተጠጊ።
ወደ እግዚአብሔር ዙፋን የሚቀርብ ማኅሌት (ምስጋና) ያድርግልን። ሰናይ ማኅሌት!

Repost from Gracious ✝
ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የአንተን ደስታ አድለኝ፡፡ ኀዘን የማያገኘው ደስታም አንተ ነህ። በሰውነቴ አገኘው ዘንድ ሰወነቴም ንጹሕ ሙዳይ ምርጥ ዕቃ ትሆን ዘንድ ልቡናዬም ማደሪያህ ትሆን ዘንድ ይህ
ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የአንተን ደስታ አድለኝ፡፡ ኀዘን የማያገኘው ደስታም አንተ ነህ። በሰውነቴ አገኘው ዘንድ ሰወነቴም ንጹሕ ሙዳይ ምርጥ ዕቃ ትሆን ዘንድ ልቡናዬም ማደሪያህ ትሆን ዘንድ ይህን እውነተኛ ደስታ ስጠኝ።

ይህን የYouTube ቻናል Subscribe በማድረግ ሁላችሁም ተቀላቀሉ፨ https://youtube.com/@kidanzeiyesus?si=FQi0ItGpo-VFUg9L
ይህን የYouTube ቻናል Subscribe በማድረግ ሁላችሁም ተቀላቀሉ፨ https://youtube.com/@kidanzeiyesus?si=FQi0ItGpo-VFUg9L

የጥቅምት 23 ሥርዓተ ማኅሌት በግእዝና በአማርኛ
በበጉ ደም ልብሶቻቸውን (ሰውነቶቻቸውን) ካጠቡ ጋራ የዘንባባ ዝንጣፊ ተሸክሜ ዳግመኛ አመሰግንሽ ዘንድ በመንግስቱ ውስጥ መቆምን አድዪኝ።
በሊቀ ሰማዕቱ በቅዱስ ጊዮርጊስ በረከት የምንጎበኝበት ማኅሌት ያድርግልን።

❝አምላኬ ሆይ አባቱን የረሳ ልጅ ሆኛለሁና ወዳንተ መልሰኝ! ብቸኛ ምርጫዬ አድርጌ እንድወድህ አንተ እርዳኝ!❞ 🥹🙏🏾

Repost from Timeless Truth
አብዛኞቻችን ምናልባትም ሁላችንም ብዙ መላቀቅ ፈልገን ያቃቱን ብዙ ሞክረን አልለቅም ያሉን ኃጢአቶች ይኖራሉ በተጨማሪ ደግሞ ብዙ እቅዶችን እያወጣን ግን እነሱን ማሳካት ላይ ደካማ እንሆናለን። እናም ከነዚህ ለመላቀቅ ብለን የተለያዩ ዘዴዎችን youtubeም ላይ ወይም ከመጽሐፍት በማንበብ በራሳችን ነገሮችን ለመቀየር ሞክረን ይሆናል ፣ ወይም እንዴት እንደምንላቀቅ ግራ ገብቶን ቁጭ ብለናል። እስኪ ይህንን ቃል አብረን እናንብበው “እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።” — ዮሐንስ 15፥5 እውን ለኃጢአቶች ለመላቀቅ ስንፈለግ ክርስቶስን ከኃጢአታችን አስበልጠነው ነው (እንዴ አዋ! አምላክን እንዴት ከኃጢአት ከጥፋት የበለጠ እንዴት አልወደውም ልንል እንችላለን...ግን የእውነት ሥራችን ይህንን ፍቅራችንን ያሳያል ወይስ በተቃራኒው ነው?). ..... የምንወዳቸውን ነገሮች ከክርስቶስ ሚለዩን ከሆነ ምን ያልህ ለመተው ፈቃደኛ ነን?.... በህይወታችን ውስጥ ምን ያህል ለአምላክ ቦታ እንሰጠዋለን? ህይወታችንን አምላክ እንዲመራልን አሳልፈን ሰጥተናል ወይስ እኛ እየመራነው ከበድ ሲለን ነው አምላክን አግዘኝ እያልን ያለነው?. ...እስኪ ወደ መፍትሔው እንሒድ እስኪ ለአምላክ ራሳችንን አሳልፈን ለመስጠት ዝግጁ እንሁን.... እስኪ አምላካችንን ብቸኛ ምርጫችን እስኪሆን ድረስ እንውደደው....በሁሉም ነገር ውስጥ እሱን እናስቀድም ለርሱ ሁሉን አሳልፈን እንስጥ....እነዚህን ነገሮች ራሱ ለማድረግ እንድንችል እስኪ በጸሎት ያለማቋረጥ ለሱ ታምነን እንጠይቀው ካሁኗ ሰዓት ጀምሮ "አምላኬ ሆይ አባቱን የረሳ ልጅ ሆኛለሁና ወዳንተ መልሰኝ ፣ ብቸኛ ምርጫዬ አድርጌ እንድወድህ አንተ እርዳኝ" እንበል....ያኔ አምላክ ሁሉን እንድንችል ያደርገናል ፣ አልለቀን ብሎ የነበረው ኃጢአት ሳናስበው ትቶን ውልቅ ይላል ፣ ጽፈን ማስቀመጥ የለመደብንን እቅድ ስንፍናችን እየተገፈፈ ማሳካት እንጀምራለን ይህ ሁሉ ሚሆነው ግን አምላክን ለሁሉም ነገር መጀመሪያ ማድረግን እስከመረጥ ነው አለበለዚያ ያለ እርሱ ምንም ነገር ማድረግ አንችልም። አምላክ በቸርነቱ እና በምህረቱ ይርዳን!

የጥቅምት 16 ሥርዓተ ማኅሌት
❝ማርያም ሆይ! ፍቅርሽን ለልቤ ያደለ፣ የቃል ኪዳንሽን ይቅርታም ከእኔ ያላራቀ አበባ ልጅሽ ይመስገን።❞
መልካም የምስጋና ሌሊት ተመኘንላችሁ።