ተዋሕዶን እንወቅ።
Open in Telegram
አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኲሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድኅነነ እምዕለት እኪት ወባልሐነ ውስተ መንሡት። ✝በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ✝ የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ጸሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማዕታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።
Show more2 372
Subscribers
-124 hours
-117 days
+330 days
Posts Archive
2 372
Repost from Gracious ✝
አቤቱ ተወዳጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ
የምንኮራበት ክብራችን ፡ የምንደምቅበት አክሊላችን አንተ ነህ ፤ ቀና ያልንብህ ትምክህታችን ፡ ያረፍንብህ ክንዳችን አንተ ነህ ፤ እግራችን እንዳይሰናከል የምትጠብቀን፡ እንዳንባዝን የምታረጋጋን አንተ ነህ፤
ጌታችን ሆይ ፦ ፍቅርህን የሚመስለው የለም፡፡ እንዳንወድቅ የምትጠብቀን ብንወድቅ የምታነሳን አንተ ነህ ፤ እንዳንደክም የምትራራልን ብንደክም የምታበረታን አንተ ነህ ፤ እንዳንታመም ባንተ እንታመናለን ብንታመምም ስላንተ ተስፋ አለን፤
ጌታችን ክርስቶስ ሆይ ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? እንዳንሰናከል መላእክቱን ስለእኛ አዘጋጀልህን ፡ ጠላቶች እንደበዙብን አይተህ ወዳጆችን አበዛኅልን ፤
ፈተናወቻችንን አይተህ መውጫውን ደግሞ አመላከትከን ፡ የቀደመውን ፍቅራችንን ብንቀንስ ያንተን ፍቅር አበዛህልን ፤
ጌታችን ክርስቶስ ሆይ ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ራቅንህ ፡ አንተ ወደኛ ቀረብክ፤ በግብራችን ናቅንህ አንተ ግን እኛን አከበርክ፤ ያለአንተ መኖር እንደማንችል ታውቃለህና ክፋታችንን ሳታይ ራራህልን ስንፍናችንን ሳታይ ቀረብከን ፤
ጌታችን ክርስቶስ ሆይ ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ተወዳጅ ሆይ ፦ እንዳንተ ያለ ለእኛ ማን አለን? ማንም የለንምና ክብራችንን አውቀን እንኖር ዘንድ አንተን ሳናስብ የምንውልበት ጊዜ አይኑረን፡፡
ክብርና ምስጋና ላንተ ይሁን፡፡
(ቅዳሴ ያዕቆብ ዘስሩግ)
2 372
Repost from ኪዳን ዘኢየሱስ
በዚህ ዓመት የጥምቀት በይረሙን (Paramoun) ወይም ጾመ ገሃድ ሦስት ቀን መሆኑን ላስታውሳችሁ።
ጥምቀት ሰኞ ስለሚውል አርብ ጸሐይ እስክትጠልቅ ይጾማል ፤ ቅዳሜ እና እሑድ ግን ምግብ ቢበላም ከእንስሳት ተዋጽኦዎች ይጾማል።
በይረሙን የሚጾመው የጥምቀት ዋዜማ ዕለት ቢሆንም የዘንድሮ ጥምቀት ሰኞ ነው የሚውለው ፣ በይረሙን ደግሞ strict አጽዋማት ከሚባሉት አንዱ ሆኖ ከአብይ ጾም ጋር ይደመራል የሚጾመውም ጸሐይ እስጠልቅ ነው (በኮፕቲክ ደግሞ ከዚህ በተጨማሪ በሌሎቹ አጽዋማውት የሚፈቀደው አሳም አይፈቀድም) ይህን ማድረግ ደግሞ በቅዳሜ እና እሑድ አይቻልም ስለዚህ ጾሙ 3 ቀን ይሆናል አርብ ጸሐይ እስክጠልቅ ይጾማል ቅዳሜ እና እሑድ ደግሞ ከጥሉላት ብቻ ይጾማል።
2 372
Repost from Philokalia
ሰውን ለመርዳት የተለየ ምክንያት አያስፈልግም።
ከላይ በምስሉ ላይ ምትመለከቷት እህታችን ቃልኪዳን ቶማስ ትባላለች የአጥንት ካንሰር ህመም አጋጥሟት በጽኑ ታማ ትገኛለች እናም ክርስቲያን ወገኖቻችን፣ እህታችንን በቻልነው አቅም እንደግፋት። ጸሎት እንኳን ዋጋ አላት።
እኔስ ብሆን? እንበል
ነጻነት አለሙ 1000348032651
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
❖ እንደምን ሰነበታችሁ ?
እግዚአብሔር ቢፈቅድ ብንኖር ዛሬ (ቅዳሜ) ማታ በዚሁ በቴሌግራም ቻናል Live ላይ የምንማር ይሆናል ።
1, በተረጋጋ እና ጸጥ ባለ ሁኔታ ማዳመጥ ። 2, ማስታወሻ በመያዝ መከታተል ። 3, ከትምህርቱ በኋላ የተረዳነውን ነገር በ comment መስጫ ላይ በትንሹ ማካፈል ። 4, የተማርነውን ትምህርት ጥቂትም ቢሆን ተግባራዊ ማድረግ ። 5, ሌሎች እህት ወንድሞችን መጋበዝ ! "ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ፤ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።" /ያዕ 1 ÷ 22/ ❖ #ተግባራዊ_ክርስትናን ከቅዱሳን ሕይወት ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን ! ❖
🕝 ከምሽቱ 3፡00 ይጠብቁን !
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 372
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
+4
እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ።
❝እነሆ ዛሬ ሰማያዊ ንጉሥ #በበረት_ተኛ። ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደውን ሰማያዊ ንጉሥ እረኞች አዩት፤ መላእክትም አመሰገኑት።❞
2 372
Repost from አምላከ ብርሀን
የእኛ ደብር ዲያቆናት ለቅዳሴ እና ለማህሌት የሚሆኑ ስክሪኖች ለመግዛት እየሞከሩ ነው .... በውነቱ እጅግ ደስ አለኝ ሀሳቡን ሰምቼ .... ቅዳሴው እና ማህሌቱ ግዕዙ እና አማርኛው እየተተረጎመ በማሳየት ሁሉንም አሳታፊ ለማድረግ ነው አላማው .... ለገና ለማድረሰ አስበው ነበር ገንዘቡ አልሞላም መሰል
ያው እናንተስ አትችሉም ... እንዳው መርዳት የሚችል ካለ ግን እስኪ ሞክሩ ...
Absyssinia : 244-155-855 በ3 ሰው ስም የተከፈተ ነው
እኔም ያቅሜን ሰጥቻለሁ የምር 😁
እስኪ ሌሎች ደብሮች ያላችሁ ዲያቆናት ፤ሰንበት ተማሪዎች ምናምን እንደዚህ አድርጉ የምር ፀዴ እኮ ነው
2 372
🔴 አባ ጳውሊ ለጥያቄዎቻቸው መልስ ያገኙ ዘንድ በእግዚአብሔር ፈቃድ ከሰይጣን ጋር ያደረጉት ቃለ መጠይቅ ነው ልብ ብለን እናድምጥ !
🚫 ማሳሰቢያ ፦ ይህ ታሪክ ተረት (ቀልድ) አይደለም እውነታ ነው !
"ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ፤ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።" /ያዕ 1 ÷ 22/ ❖11፡47 - ከሰዎች በአንዱ አድረህ በኃጢአት ትጥለው ዘንድ አጋዥ የሚሆንህ ምንድነው ? 13፡42 - ዓለማውያን ሰዎችን የምትፈትናቸው እንዴት ነወ ? 16፡00 - ሰዎች ነገርህን እንዴት አምነው ይቀበሉሀል ? የመልክህን ክርፊት አያውቁም ? 16፡38 - መልክህን መለዘጥ እንዴት ይቻልሀል ? 16፡54 - የማታውቀውን ምስጢር ማስመሰል እንዴት ይቻልሀል ? 17፡15 - የክርስቶስ ሰው መሆን እንዴት ተሰወረብህ ? 17፡34 - ክርስቶስ አምላክ መሆኑን ያወከው መች ነበር ? 17፡46 - ሰዎችን በማሳትህ ምን ትጠቀማለህ ? 18፡04 - በእውኑ ገሃነም የሚባል አንድ ቦታ አለ ? 18፡24 - አግዚአብሔር ይቅር እንዲልህ ለምን ንስሐ አትገባም ? 18፡57 - ለሰው በምትሀት የምታዩት በምን አምሳል ነው ? 19፡35 - ሰዎች አምላካቸውን እንዲክዱ የምታደርገው በምን መንገድ ነው ? 20፡40 - እናንተ አሳቾች እንደሆናችሁ ለሰው በምን ትታወቃላችሁ ? መጨረሻችሁስ እንዴት ነው ? 21፡15 - ሥጋው የደከመን ሽማግሌ በምን ትፈትኑታላችሁ ? 21፡51 - በገዳም ከሚኖሩት ጋር የምትዋጋው እንዴት ነው ? 23፡57 - መነኮሳት በምን ያሸንፉሀል ? 30፡00 - ከአዳም ልጆች የምትፈራቸው እና የማትፈራቸው አሉ ? 31፡37 - የማርያም ልጅ የምትለው ማንን ነው ? እርሱን ትፈራለህን ? 32፡38 - አንተን ያልበደሉህን ሰዎች እንዲህ የምትፈትናቸው ለምንድን ነው ?
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
❖ እንደምን ሰነበታችሁ ?
ከዚህ ቀደም "ለእግዚአብሔር ጊዜ ማጣት !" በሚል ርዕስ ከወንድማችን ብርሃነ ሥላሴ ጋር ለመማር ቀጠሮ ይዘን የነበረ ቢሆንም በተወሰኑ ጉዳዮች ምክንያት መዘግየቱ ይታወሳል ። በመሆኑም ፦ እግዚአብሔር ቢፈቅድ ብንኖር ዛሬ (ቅዳሜ) ማታ በዚሁ በቴሌግራም ቻናል Live ላይ የምንማር ይሆናል ። ወንድማችን አስቀድሞ እንዳሳወቀን በሰዓቱ ስንገናኝ አምስት ነገሮችን መተግበር አንዘንጋ ።
1, በተረጋጋ እና ጸጥ ባለ ሁኔታ ማዳመጥ ።
2, ማስታወሻ በመያዝ መከታተል ።
3, ከትምህርቱ በኋላ የተረዳችሁትን ነገር በ comment መስጫ ላይ በትንሹ ማካፈል ።
4, የተማራችሁትን ትምህርት ጥቂትም ቢሆን ተግባራዊ ማድረግ ።
5, ሌሎች እህት ወንድሞችን መጋበዝ !
"ቃሉን የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ፤ ራሳችሁን እያሳታችሁ የምትሰሙ ብቻ አትሁኑ።" /ያዕ 1 ÷ 22/ ❖ #ተግባራዊ_ክርስትናን ከቅዱሳን ሕይወት ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን ! ❖
🕝 ከምሽቱ 3፡00 ይጠብቁን !
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
+1
ይህ ኢየሩሳሌም የሚገኘው የቅዱስ ዳዊት መካነ መቃብር ነው ። ከበዓለ ዕረፍቱ ረድኤት በረከት ይክፈለን፤ በጸሎቱ ይማረን።
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 372
Repost from Gracious ✝
ካደረክልኝ አንፃር የእኔ በኀጢአት መውደቅ ምን ይባላል? በውስጤ ያለችው የኀጢአት ጣዕም አንተ ካቀመስከኝ የፍቅር ጣዕም እንዳትበልጥብኝ እለምንሃለሁ። ለእኔ አንተን መውደድ ሕይወቴ ከአንተም መራቅ ደግሞ ሞቴ ነው።አሁንስ በፈቃዴ ሳይሆን አንተው እራስህ ግድ እንድትለኝ እሻለሁ።እኔ በአንተ አንተም በእኔ ትኖርልኝ ዘንድ ናፍቆቴ ይህ ነው።
“ነፍሴን፦ መድኃኒትሽ እኔ ነኝ በላት።”
— መዝሙር 35፥3
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
« ጨካኙ ንጉሥ ሄሮድስ ሕጻኑ ክርስቶስን ሊገድለው የፈለገው ከ20 ወይም ከ30 ዓመት በኋላ በእኔ ላይ ይነግሳል ብሎ በማሰብ ነበር ። ነገር ግን ሄሮድስ ለመኖር የቀረው ዕድሜ 3 ዓመት ብቻ ነበር ። »
➱ አይገርምም ! እኛም ብዙ ተጨንቀን የክፋት ወጥመዶችን የምንዘረጋው ረጅም ዕድሜ የምንኖር እየመሰለን ነውኮ ።
እግዚአብሔር ይማረን ![ ታኅሣሥ 20 ቀን 2018 ዓ.ም ]
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 372
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
ከታኅሣሥ 7 እስከ ታኅሣሥ 26 ድረስ ያለው ዘመን ዘመነ ስብከት እየተባለ ይጠራል። ነቢያት የጌታን በሥጋ መምጣት በጥልቀት በትንቢትና በትምህርት መስበካቸውን ቤተክርስቲያን እያሰበች ሰውን ለማዳን ወደምድር የመጣውን አምላክ በተለየ ሁኔታ የምትሰብክበት ጊዜ ነው።
የዘመነ ስብከት የመጀመሪያው ሰንበት ደግሞ ስብከት እየተባለ ይጠራል። ስብከት አዲስ ዜናን መንገር ማለት ነው። በዚህ ዕለት የነብያትና የሐዋርያት ስብከት ክርስቶስ መሆኑ ይሰበካል።
“በመስቀል የተሰቀለውን መድኃኒታችን እርሱን እንሰብካለን።”
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
❖ እንደምን ሰነበታችሁ ?
እግዚአብሔር ቢፈቅድ ብንኖር ዛሬ ማታ (ቅዳሜ) በዚሁ በቴሌግራም ቻናል Live Stream የምንጀምር ይሆናል ። የትምህርቱ ርዕስ "ለእግዚአብሔር ጊዜ ማጣት" የሚል ነው ። በሰዓቱ ስንገናኝ አምስት ነገሮችን መተግበር አንዘንጋ ።
🕝 ከምሽቱ 3፡00
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
ታላቁ ዋርካ ወደቀ !
ሊቀ ብርሃናት የኔታ ይባቤ በላይ ( ዐራት ዐይና ) የፈለገ ብርሃን ናዳ ቅድስት ማርያምና ክብረ ደናግል ቅዱስ ላሊበላ አንድነት ገዳም የ፬ቱ መጻሕፍተ ትርጓሜ ጉባዔያት ፣ የቅኔና የአቡሻኽር ምስክር መምህርና የገዳሙ አበምኔት ባደረባቸው ሕመም ምክንያት ከዚኽ ዓለም አርፈዋል።
እጅግ ልብ ሰባሪ ነው የእውነት እንደ ዋርካ ብዙዎች የተጠለሉባቸው ፣ ለበርካታ ዓመታት ጉባዔ ዘርግተው በሺዎች የሚቆጠሩ ሊቃውንትን ያፈሩ ፣ እውነተኛ ገዳማዊ ፣ የልማት አባት ፣ የሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ጠበቃ ፣ ዓለምን የናቁ መናኝ ፣ የቤተ ክርስቲያን ምሰሶ ናቸው በእውነት ትተውን ሲሄዱ ልብ ይሰብራል።
ያ ተርጓሚው ሊቅ ያ የአቡሻኽሩ ጌታ የኔታ ይባቤ ወደ አምላካቸው ሂደዋል ለእኛ ይብላኝ እንጂ ።
" የኔታ ከወር በፊት ገዳሙንና ጉባዔ ቤቱን የሚመራ ሰው ፈልጉ በማለት የሀገረ ስብከቱን አመራሮች እንደተናገሩ መረጃዎች ይጠቁማሉ " እረፍታቸውን የተረዱ መናኝ አባት !
የኔታ የ፬ቱ መጻሕፍት አንድምታ ፣ የቅኔ እና ጥንቁቅ የአቡሻክር የምስክር መምህር ነበሩ። ከ40 ዓመት በላይ ወምበር ዘርግተው በርካታ ሊቃውንትን አፍርተዋል። የክብረ ደናግል ናዳ ማርያም ገዳምን ከምድረ በዳ ወደለም ወደታላቅ ገዳም የቀየሩ አበምኔት በተጋድሎ የጸኑ ገዳማዊ የትህትና አባት። ፊት አይተው የማያዳሉ መምህር ወመገስጽ ዘኢያደሉ ለገጽ የተባሉ የምግባር ሰው ሥርዓት ጠንቃቂ ነበሩ። መንፈስ ቅዱስ እንደገለጸላቸው የሚያርፉበትን ቀን ቀድመው ተናግረው ህዳር 22/2018 ዓ.ም አርፈው ወደ ወደዳቸው ፈጣሪ ሄደዋል ።
ሥርዓተ ቀብራቸው በ23/03/2018 ተፈጸመ ! ቅድስት በረከትዎ አትለየኝ !
(ከመጋቢት 27/1954 - ህዳር 22/2018 ዓ.ም)
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
✝ እንኳን ለእናታችን ጽዮን ማርያም ዓመታዊ በዓል አደረሰን አደረሰን ! ✝
❖- ታቦተ ጽዮን የዮርዳኖስን ባሕር የከፈለች (ኢያሱ 3፡14-17)
❖- ቅጽረ ኢያሪኮን ያፈረሰች (ኢያሱ 6፡1-21)
❖- ዳጎን የተባለ የፍልስጤማውያንን ጣዖት ሰባብራ ቆራርጣ የጣለች (1ኛ ሳሙ 5፡1-5)
❖- በድፍረት ሊነካ የሞከረውን ኦዛን የቀሰፈች (1ኛ ሳሙ 6፡6)
❖- በአቢዳራ ቤት ሦስት ወር ተቀምጣ ቤቱን በበረከት የመላች (2ሳሙ 6፡12)
❖- ቅዱስ ዳዊት የዘመረላት (2ኛ ሳሙ 6፡14)
❖- ጠቢቡ ሰሎሞን በቤተ መቅደስ በክብር ያኖራት (1ኛ ነገ 8፡1)
ሌላም እጅግ ብዙ ድንቅ ድንቅ ተኣምራትን ያደረገች የእግዚአብሔር የክብር መገለጫ ናት፡፡
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
🚫 ክርስቲያኖች እንንቃ !
የዘንድሮውን የታላቁ ሩጫን ፎቶ ሚዲያ ላይ ስመለከት በድንገት ብዙ ነገር አእምሮዬ ውስጥ ተመላለሰብኝ። እስቲ ከቀለሙ ጀምሮ ተመልከቱት ! በጦርነት ውስጥ ያገኙትን ደም መፋሰስንና ገሀነመ እሳትን ለመግለጽ የተጠቀሙበት ይመስላል። አጀንዳው ያልገባቸው ሰዎች ተሰብስበው ደም የመሰለ ቲሸርት ለብሰው የደም ጎርፍ መስለው 6 ኪሎን ሦስት ጊዜ እንዲዞሩ መደረጉ (ልብ እንበል 6 ኪሎን ሦስቴ ሲዞሩ) ትእይንቱና ሁኔታዎቹ ወደ 666 የሚወስዱ ምልክቶች ይመስላሉ።
መቼም የንጹሓንን ደም እየገበሩለት ያሉት ለዚሁ የአውሬው መንፈስም መሆኑ ግልጽ ነው።
እግዚአብሔር ይጠብቀን !
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 372
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
❝እንግዳ ሊመጣ ሲል ቤታችሁን እንደምታሰናዱ፥ ክርስቶስ ወደ እናንተ ሊመጣ ነውና፤ በጾም፥ በጸሎትና በንጽሕና ነፍሳችሁን አሰናዱ።❞ (ቅዱስ አምብሮስ ዘሚላን)
