ተዋሕዶን እንወቅ።
Open in Telegram
አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኲሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድኅነነ እምዕለት እኪት ወባልሐነ ውስተ መንሡት። ✝በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ✝ የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ጸሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማዕታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።
Show more2 372
Subscribers
-224 hours
-67 days
+530 days
Posts Archive
2 372
Repost from Gracious ✝
ወየው!!! ወዮታ አለብኝ ወየው ሊሉኝ ይገባል!!!ፍጥረታት ሁሉ ያንተን ክብር ይናገራሉ።እኔ ግን አንድ ቀንም በሕይወቴ ልገልጥህ አልወደድሁም!!
ወየው!!! ወዮታ አለብኝ ወየው ሊሉኝ ይገባል!!! ሰማያት ያንተን ስራ ይናገራሉ። እኔ ግን አንድ ቀንም በስራዬ ልገልጥህ አልወደድሁም!!
ወየው!!! ወዮታ አለብኝ ወየው ሊሉኝ ይገባል!!! አዕዋፋት ያንተን ልግስና ይናገራሉ። እኔ ግን አንድ ቀንም በልግስና በምፅዋት አንተን ልገልጥህ አልወደድሁም !!
ወየው!!! ወዮታ አለብኝ ወየው ሊሉኝ ይገባል!!!ቅዱሳንህ ያንተን ቅድስና ይናነራሉ።እኔ ግን አንድ ቀንም በቅድስና በንጽሕዬ አንተን ልገልጥህ አልወደድሁም !!
ወየው!!! ወዮታ አለብኝ ወየው ሊሉኝ ይገባል!!!ሰማዕታትህ ያንተን መልክ ይገልጣሉ።እኔ ግን በፈቃዴ መልኬን አደበዘዝኩ አንተም በእኔ አትታይም። አንተንም ልገልጥህ አልወደድሁም !!
“እኔ ምንኛ ጎስቋላ ሰው ነኝ! ለዚህ ሞት ከተሰጠ ሰውነት ማን ያድነኛል?”(ሮሜ 7፥24)
ማረኝ አቤቱ ማረኝ!!!
2 372
Repost from Theo-Sophia
ሁላችሁም ባሁኑ እሁድ እንዳትቀሩ በዚህ ሴሚስተር የመጀመሪያ መርሃ ግብር ስለሆነ ሁላችሁም ተጠራርታችሁ ኑ አንድ ሰው አንድ ሰው ይዞ ይምጣ ወገን እሁድ እንገናኝ
2 372
Repost from N/a
#ርዕስ ፦ አድዋ እና ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
- ቅዱስ ጊዮርጊስ ሆይ ከእኛ ወገን ነህን ?
- አድዋ እና ቅድስት ቤተ ክርስቲያን
- በአድዋ እንዴት ልናሸንፍ ቻልን ?
📖 መልካም ንባብ#Share
JOIN @RGB_METSHEFT
2 372
Repost from Gracious ✝
ምኩራብ
ጌታዬ የሚታይ ሰላምታ ያለኝ የማይታይ ሐሜት ታቅፌ ነዉ የሚታይ መልካምነት ያለኝ የማይታይ ክፋት ታቅፌ ነዉ በቤትህ ሺ ብሰግድ ዉጪ የወደቀዉን ወንድሜን አልፌ ነዉ በገነቱ ቤትህ የጠፋሁት አዳም በቅዱስ ቤትህ የጠፋሁት ድሪም ጅራፍ ብታነሳ ዛሬ እተርፍ ይሆን ?
2 372
Romans 12 አማ - ሮሜ
2: የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
የእውነተኛ ወዳጅ ምክር !
“ጠቢብ እነዚህን ከመስማት ጥበብን ይጨምራል፥ አስተዋይም መልካም ምክርን ገንዘቡ ያደርጋል።” [መጽሐፈ ምሳሌ 1÷5]"እውነተኛ ወዳጅ፥ ወዳጅ መሆኑ የሚታወቀው ጓደኛውን መገሠጽ ሲችል ነው፡፡" በእርግጥ ሁላችንም በየጊዜው ኃጢአት እንሰራለን፡፡ አብዛኞቻችን ደግሞ ኃጢአታችንን እንዳላየነው ሆነን ንስሐ ሳንገባም ለማለፍ እንጥራለን ፣ ለራሳችን ይቅርታ እንቸራለን፡፡ ወይም ደግሞ ምንም እንዳላጠፋ ሰው ለመምሰል እንሞክራለን ታዲያ በእንደዚህ ዓይነት ሰዓት እውነታውን በትክክል እናይ ዘንድ ዓይናችንን የሚከፍት እውነተኛ ወዳጅ ያስፈልገናል፡፡ እስኪ ራስህን መርምር ! ጓደኛህ እውነታውን እንዲያይ ታደርጋለህ? ፣ ጓደኛህ ኃጢአት ሰርቶ ሲያበቃ ለራሱ ይቅርታ ሲያደርግ ይቅርታው ትክክል እንዳልሆነ እንዲያውቅ ታደርግ ይሆን? ምናልባት እንዲህ እውነታውን ስትነግረው ጓደኛህ አለ አግባብ ሊቈጣህ ፣ ምን አገባህም ሊልህ ይችላል፡፡ ታዲያ ሲቈጣህ ለመታገሥ ዝግጁ ነህን? ወይስ ከዚህ በተቃራኒ የጓደኛህን ኃጢአት አይተህ እንዳላየህ ነው የምትሆነው? አየህ ጓደኛ ስንመርጥ ከእኛ ጋር እውነተኛ ወዳጅ ሊሆን የሚገባውን መምረጥ አለበት። ስንቆጣው ቁጣችንን ታግሶ የሚጸና ብቻ ሳይሆን እኛም ስናጠፋ የሚያርመን ሊሆን ይገባል፡፡ እንደዚህ ካልሆነ ጓደኝነታችን ጥቅም አይኖረውም ፤ ጓደኞዬ ነው ማለትም ከንቱ ነው። ነገር ግን ልናውቀው የሚገባን አንድ ነገር አለ ! ጓደኛችን በሚያጠፋበት ሰዓት ተግሣጽ አስመስለን እንዲሁ ክብሩን በሚነካ መልኩ ልንናገረው ፣ በሰው ፊት ልናዋርደው አይገባንም፡፡ ተግሣጻችን ሁልጊዜ እውነቱን ብቻ እንጂ የተጋነነና ሌላውን መልካምነቱን የሚክድ መሆን የለበትም፡፡ ጥፋቱን ስንነግረው ሁልጊዜ በቀና ልብ እንደምንነግረው እርግጠኛ መሆን አለብን፡፡ ይህን የምናደርገው ከፍቅራችን የተነሳ እንጂ ከቅናት ወይም ከንቀት እንዳልሆነ እንዲያውቅ ማድረግም አለብን ምክንያቱም እውነተኛ ወዳጅነት ማለት ይህ ነው ፡፡
መልካም ቀን 🕊
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 372
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
የዓብይ ጾም ሳምንታት ቅዳሴ መከታተያ ቅጽ እነሆ።
ከነገ ቅድስት ጀምረን ሁላችንም በጌታ ቀን በአማናዊው መስዋዕት በኢየሱስ ክርስቶስ ፊት ልንሰበሰብ ግድ ይለናል - በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም እንዲሰበስበን ለመማጸን።
ምንባባቱንና ምስባኩን አስቀድመን ቅዳሜ ማታ አንብበን እንሂድ፤ ቃሉ በልባችን እንዲሰርጽ።የበረከት ጾም ይሁንልን።
2 372
ጥሩ ወንድሞቻችን ናቸው ። አይደለም እንደዚህ አይነት ሀሳብ ቀርቶ ስንት ለእኛ የማይረቡን ረብሕ ጥቅም የማይሰጡን ቻናሎችን ሰብስክራይብ እናደርግ የለ..? በርትተው እንዲሠሩ ሰብስክራይብ እንዲሁም ሼር እናድርግ ... የአንድ ሰከንድ ሥራ ናት😊
2 372
Repost from Theo-Sophia
ሰላም ለእናንተ ይሁን፣ በቅርቡ YouTube ላይ ብዙ ነገሮችን አስበናል፣ የምንሰራው እንዲሁ ለአገልግሎት ስለሆነ እና ከብዙ ስራዎች ጎን ለጎን የሚሰራ ስለሆነ የሚቀሰቅስ እና የሚያበረታው የእናንተ ተሳትፎ ነው፣ ሃላፊነት ተሰምቶን በደንብ በዐብይ ጾሙ እንደንበረታበት ሄዳችሁ subscribe አድርጉ፣ Video ሲለቀቅም በአግባቡ ተከታተሉ (ቢያንስ 3K Subscribers እንዲኖሩ)። ኤቲይዝም፣ እስልምና፣ ፕሮቴስታንቲዝም ላይ እና ሌሎች ከነገረ ሃይማኖት ውጪ ያሉ ማህበራዊ እና ሕይወታዊ ነገሮችም ላይ ብዙ ለመስራት እና ማህበራችንን ለማሳደግ እንጥራለን፣ እናንተ share እና subscribe አድርጉ፣ የሚለቀቁትን videoዎች ደግሞ በአግባቡ ተከታተሉ።
https://youtube.com/@theo-sophia?si=aOSK_1U0aQTAUugL
2 372
Repost from Theo-Sophia
ከጎልጎታ ዜማ እንሰማ ዘንድ ጆሮአችንን እናዘንብል።
ብዙ ድምፆች ይሰማሉ።የሚሉትን የማያውቁ በቁጣ ይናገራሉ።ፈሪዎች እና ደንጋጦች በስላቅ ይጮሃሉ ዓመጽ በታላቅ ድምጽ ሊያሸንፍ ይታገላል።ወንበዴ በስድብ መዳንን ይጠይቃል።ዓለም እንደለመደችው በጩኸት፣ በችኮላ እና ያለ ማስተዋል ትናገራለች።
እነሆ ሌላ ድምጽ
“አባት ሆይ፣ ይቅር በላቸው።”
ገዳዮች በከበቡት ጊዜ በርህርሄ ይመልሳል።ይህ ምልጃ ብቻ አይደለም፤ የቀዘቀዘውን ልብ የሚያሞቅ እሳት ነው እንጂ።ፍቅር መውደድ ማቆም አይችልምና የሚገድሉትን ጭምር ወደዳቸው።ለእኛ የሚታየን የንጹህ ሰው ሞት ከኃይል ይልቅ መስዋዕትነትን የመረጠ የፍቅር ዜማ ነው።ወልድ ራሱን ይሰጣል፣ አብ ይቀበላል፣ መንፈስ ቅዱስም በወልድ ቁስል ከብዙ የግፍ ድምጾች መሐል ለህይወት ትርጉም ይሰጣል።እናም፣ ከእንጨትና ከቁስል፣ ዓለም አዲስ የሚሆንበት አብ በመንፈስ ቅዱስ የደረሰው መዝሙር ከጎልጎታ ይሰማል።
የዋህ ሆይ፣ በፍርሃት ሳይሆን በፍቅር ልቤ ከአንተ ጋር ትቸንከር።ጌታ ሆይ ነፍሴ መራራውን ጽዋ ከአንተ ጋር ትጠጣ።መሐሪ ሆይ በቁስሎችህ እታመም ዘንድ ስጠኝ።ንጹህ ሆይ መንፈሴ ካንተ ጋር ትጣበቅ።በመስቀል ላይ ላዘነብልከው ላንተ ራሳችንን እናነሳለን ከቸር አባትህ ጋር አዳኝ ከሆነ ከመንፈስ ቅዱስም ጋር ላንተ ምስጋና ይሁን እንላለን።
አሜን!
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
❖ ስለ ፍኖተ ቅዱሳን ማኅበር ለጠየቃችሁ ❖
ካልጨረሳችሁት ማንበብ አትጀምሩ !«ፍኖት» የሚለው ቃል ከግዕዝ ቋንቋ የመጣና አካላዊ መንገድን እንዲሁም በአንዳንድ አውድ ውስጥ የጉዞ መስመርን (race) የሚያመለክት ስም ነው። ትርጉሙ መንገድ፣ ጎዳና ማለት ነው። "ቅዱሳን" የሚለው ደግሞ የተለዩ ፣ የከበሩ ፣ የተመረጡ ማለት ነው ። ስለዚህ "" ፍኖተ ቅዱሳን "" ስንል የቅዱሳንን ተጋድሎ ፣ የጽድቅ ጉዞ ፣ በፈተና ማለፍን ፣ እስከ ሞት መታመንን ፣ ቁርጥ ዓላማ መያዝን ፣ እምነትን ፣ ጽናትን ፣ ጥረትን ፣ ትዕግስትን ከእነርሱ እንድንማር ይጋብዘናል ። በነገራችን ላይ የቅዱሳን ተጋድሎ የሚነገረን እንደ ታሪክ እንዲሁ ሰምተን እንድናልፈው አይደለም ። 1, ታሪካቸውን ከልቡ ለሚያዳምጥ እና ገድላቸውን ለሚያነበው ትልቅ በረከት አለው ። 2, ከቅዱሱ (ከቅድስቷ) ቃል ኪዳን በእምነት ተካፋይ መሆን ይቻላል ። 3, ቅዱሳኑ ክርስትናቸውን ያጸኑበት ፣ የጠበቁበትና ለሰማያዊ ክብር የበቁበትን መንገድ እንማርበታለን ትልቁ ጥቅማችን ይህ ነው ። በአሁን ጊዚ ቁጥራችን ቀላል የማይባል የተዋሕዶ ልጆች ሕይወተ ቅዱሳንን እንደ ተራ ታሪክ ወይ ጀምረን እንተወዋለን ምናልባትም በግዴለሽነት እናነበዋለን ደስ ሲለንም ምስሉ ላይ 'like' የምትለውን ተጭነን እናልፈዋለን ። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ በደንብ አንብበን "ወይ መታደል!" ብለን አድንቀን እናልፋለን ። በእውነቱ ማድነቃችን ጥሩ ነበር ነገር ግን ቅዱሳኑ ለዚህ ጽድቅ የበቁት የታደሉ ስለ ሆኑ ብቻ አይደለም ከእነርሱ የሚጠበቀውን ነገር በሚገባ ስለሰሩ ነው እንጂ እንደ እኛ ሥራ በመፍታት ቁጭ ብለው አይደለም ። እናስተውል እግዚአብሔር የሚያዳላ አምላክ አይደለም "እኔ ቅዱስ እንደሆንኩ እናንተም ቅዱሳን ሁኑ" /ዘሌ.19÷2 ፣ 1ጴጥ 1÷15/ ብሎ የተናገረው ለጥቂት ወይም ለተለዩ ሰዎች አይደለም በስሙ ለሚያምኑና ለተጠመቁ ክርስቲያንች ሁሉ ነው ። ስለሆነም እኛ ክርስቲያኖች በተለይ ወጣቶች ከቀደምቶቻችን ተገቢውን ትምሕርት ወስደን ልንጸና ፣ ልንበረታ ፣ ለቤተ ክርስቲያናችንም "አለሁልሽ" ልንላት ይገባል ዛሬ እናት ቤተ ክርስቲያን በተለይ በከተሞች የወላድ መካን እየሆነች ነው ። ቤተክርስቲያን ይህን ያህል ካህን ፣ ዲያቆን ፣ ሰንበት ተማሪና ወጣት አላት" ይባላል ውስጡ ሲፈተሽ ግን በትክክለኛ ቦታው የሚገኘው ከመቶው ስንቱ እንደ ሆነ ለመናገርም ያሳፍራል ። ታዲያ መፍትሔው ምንድነው ብንል:- እባካችሁ ከቅዱሳን ቀደምት ክርስቲያኖች መሥራት ያለብንን ቀስመን ከዘመኑ ጋር አዋሕደን (ዘመኑን ዋጅተን) ራሳችንን ፣ ቤተ ክርስቲያንንና አገራችንን እንደግፍ ካለንበት ያለማስተዋል አዘቅት እንውጣ ። ለዚህ ይረዳን ዘንድ በምናቋቁመው ማኅበር ላይ ተሳተፉ ስንል ብዙዎቻችሁ በውስጥ ጥያቄ እየጠየቃችሁ ነበር ከጥያቄው ውስጥ ግን በብዛት ገንዘቡ ላይ ትኩረት ማድረጋችሁ አስገርሞኛል ። በአሁን ሰዓትኮ 100 ብር ማለት ከአንድ ምሳ የማይዘል ምናልባትም ለትራንስፖርት የምናወጣው ወጪ ነው ። እሱን ተውትና ሶሻል ሚዲያ (TikTok , YouTube , Telegram , Instagram ...) ለመጠቀም በሳምንት ስንት ብር እናወጣለን ? መልሱን ለእናንተ ልተው...... ክፍያው ማኅበሩን ለማቋቋም የሚረዳን እንደሆነ እና በየወሩ ምንም አይነት ክፍያ እንደማንቀበል ቀድሜ አሳውቄአለው በይበልጥ ከላይ ያለውን Voice አድምጡ ። ስለዚህ ምክንያት ባናበዛ መልካም ነው ። ስንመዘገብ (ሙሉ ስም ፣ የክርስትና ስም ፣ ጾታ ፣ የሰፈር / የአገር ስም) መሙላት ይጠበቅብናል ። ሌላው ደግሞ ማኅበሩ በስሙ የተከፈተ አካውንት የለውም ምክንያቱም ያንን ለማድረግ አቅሙ አይፈቅድም ስዚህ ሲባል የእኔን የግል አካውንት ሙሉ በሙሉ ለማኅበሩ እንዲሆን ሰጥቻለው ገቢ የምታደርጉት በእርሱ በኩል ይሆናል ። ስትመዘገቡ የከፈላችሁበትን ደረሰኝ መላክ አትርሱ ምዝገባው ከተጠናቀቀ በኋላ ግን ማንንም የማናስተናገድ መሆኑን ከወዲሁ ለማሳወቁ እወዳለው ። እስከ አሁን ጥቂት ሰው ነው የተመዘገበው ። ምዝገባው እስከ የካቲት 15 ይቆያል ። በማኅበሩ ጉዳይ ይህ የመጨረሻ መልዕክቴ ነው የቀረውን (ዋናውን ጉዳይ) ከተመዘገቡት ጋር የምንቀጥል ይሆናል ። ለዚህ አገልግሎት ቁርጥ ልቡና እንዲኖረን አምላካችን እግዚአብሔር ይርዳን ። ለመመዝገብ ይህን ይጫኑ ! 👉 @Fnote_Kdusan 👈 ገንዘብ ለማስገባት ፦ 1000643268136 የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ - Alazar Seifu Geleta ✍ ብርሃነ ሥላሴ [ የካቲት 5 ቀን 2018 ]
2 372
Repost from አምላከ ብርሀን
ኧ ሰዎች ግን ንስሀ እየገባችሁ ነዋ ሰሞኑን ... ዓቢይ ፆም እየመጣ ነውኮ ... 8ቱንም ሳምንት ከቅዱስ ምስጢር እየተሳተፉ ለማሳለፍ ዝግጁ እንሁን እንጂ ... ቀኖናችሁን ምናምን ሰሞኑን ጨራርሱ
2 372
Repost from Gracious ✝
አንተን አፈላለጌን አሳምራት።
አንተን አፈላለጌን አሳምራት። በማትገኝበት እንዳልፈልግህ ያለትርፍም እንዳልደክም። እውነተኛ መልካምም መዐዛ ያለው እጣን ሆይ ያንን መዐዛህን አሸትተኝ እርሷን ተከትዬ ካለህበት እጠጋ ዘንድ የቅዱሳንንም(አንተን በመፈለግ የደከሟትን) ድካም እኔም እደክማት ዘንድ ስጠን። በዛች ድካማቸው አንተን እንዳገኙ አይቻለሁና።ኦ ሃያል ሁሉን የማትዘነጋ ነህ፤የማትሰለች ነህ። ያዩህ ሊያቅፉህ የተሽቀዳደሙልህ ነህ።ፍቅርህን በልቤ አፅናት ልለይህ እንኳን እስካይቻለኝ። በመስቀል እንደተቸነከርህ አንተነትህን በፍቅርህ ችንካር በልቤ ውስጥ ቸንክረው፡፡
እንድወድህም ግድ በለኝ።
2 372
Repost from Gracious ✝
....ነገረ ፡ ግን ፡ ቀን ፡ ሳለ ፡ የላከኝን ፡ ሥራ ፡ ልሠራ ፡ ይገባኛል ፤ አንድ ፡ ሰው ፡ ስንኳ ፡ ሥራ ፡ ሊሠራበት ፡ የማይቻለው ፡ ሌሊት ፡ ትመጣለችና።ዮሐንስ ወንጌል ምዕ 9 ፥ 4
2 372
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
የእግዚአብሔር መሐሪነት የታየባት ታላቋ ከተማ
ከጤግሮስ ወንዝ በስተ ምሥራቅ የምትገኝ የኢራቅ ከተማ በኾነችው ሞሱል የተከበበች አንድ ጥንታዊት ከተማ አለች - ነነዌ የምትባል። ታዲያ ይኽች ታላቅ ከተማ በነቢዩ በዮናስ ዘመን (በአማካኝ ከ773-755 ክ.ል.በ.) ‛ክፋቷ በእግዚአብሔር ፊት ወጣ።’ ነዋሪዎቿን ከክፋታቸው ይመልስ ዘንድም ዮናስ የተባለ ዕብራዊ ነቢይን ወደነርሱ ላከ፤ ዮናስ ግን የእግዚአብሔርን መሐሪነት ያውቅ ስለነበር ኮብልሎ ወደ ተርሴስ ለመሔድ በመርከብ ተሳፈረ።
በባሕር እያሉ ግን መርከቧ እንደተለመደው ጉዞዋን መቀጠል አልቻለችም፤ “እግዚአብሔርም በባሕሩ ላይ ታላቅ ነፋስን አመጣ፥ በባሕርም ላይ ታላቅ ማዕበል ሆነ፥ መርከቢቱም ልትሰበር ቀረበች።” መርከበኞቹ ተጨንቀው ባሉበት ጊዜ ዮናስ ተኝቶ ስለነበር አለቃቸው “እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ያስበን እንደ ኾነ ተነሥተኽ #አምላክኽን_ጥራ” አለው። በማን ምክንያት ይኽ ጭንቅ እንደመጣባቸው ለማወቅም ዕጣ ተጣጣሉ፤ ዕጣውም በዮናስ ላይ ወጣ። ዮናስም ማንነቱንና ለምን ወደ ተርሴስ እንደሚሔድ ነገራቸው፤ አስከትሎም “ይኽ ታላቅ ማዕበል በእኔ ምክንያት እንዳገኛችኹ አውቃለኹና አንሥታችኹ ወደ ባሕር ጣሉኝ፥ ባሕሩም ጸጥ ይልላችኋል” አላቸው። ዮናስንም ወደ ባሕሩ ጣሉት፤ ባሕሩም መናወጡን አቆመ። “እግዚአብሔርም ዮናስን የሚውጥ ታላቅ ዓሣ አሰናዳ፤ ዮናስም ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት በዓሣው ሆድ ውስጥ ነበረ።” [ሦስት ቀንም ከኾነው በኋላ] “እግዚአብሔርም ዓሣውን አዘዘው፥ እርሱም ዮናስን በየብስ ላይ ተፋው።” እግዚአብሔርም ዮናስን በድጋሚ “ተነሥተኽ ወደዚያች ወደ ታላቂቱ ከተማ ወደ ነነዌ ሒድ፥ የምነግርኽንም ስብከት ስበክላት አለው።” ዮናስም “በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ #ትገለበጣለች” ብሎ ጮኾ ተናገረ። “የነነዌ ሰዎችም በእግዚአብሔር አመኑ፤ ለጾምም አዋጅ ነገሩ፤ ከታላቅ እስከ ታናሽም ማቅ ለበሱ።” የነነዌ ንጉሥም “ከዙፋኑ ተነሥቶ መጐናጸፊያውን አወለቀ፤ ማቅም ለበሰ፥ በአመድም ላይ ተቀመጠ።” አዋጅንም አወጀ፤ ከሰው አንስቶ እስከ እንሰሳት ድረስ እንዲጾና ሰዎች ከክፋት መንገዳቸው እንዲመለሱ አስነገረ።“እኛ #እንዳንጠፋ እግዚአብሔር ተመልሶ ይጸጸት እንደ ኾነ፥ ከጽኑ ቍጣውም ይመለስ እንደ ኾነ ማን ያውቃል?” [ከሦስት የንስሐና የጾም ቀናት በኋላም] “እግዚአብሔር ከክፉ መንገዳቸው እንደተመለሱ ሥራቸውን አየ፤ እግዚአብሔርም ያደርግባቸው ዘንድ በተናገረው ክፉ ነገር ተጸጽቶ #አላደረገውም።” የነነዌ ሰዎች ላይ ትንሽ እንቆይባቸው እስቲ። “ነነዌ ትገለበጣለች” ሲል ‛ማን ነው የሚገለብጣት?’ ‛ለምን ትገለበጣለች?’ ‛ለመኾኑ አንተ ማን ነኽ?’ ’ዝም ብሎ ትገለበጣላችኹ ይባላል? መጀመሪያ ትምህርት አይቀድምም?’ አላሉም፡፡ ራሳቸውን እንጂ ሰባኪውንና ስብከቱን ለመገምገም ጊዜ አልነበራቸውም፡፡ “እግዚአብሔርን አመኑ፥ ለጾም አዋጅ ነገሩ፤ ከታላቁ ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ።” ነቢዩ ዮናስ ግን የነነዌ ሕዝብ በመማራቸው ‛ደስ አልተሰኘም።’ እግዚአብሔርም ዮናስን የርሱን ታላቅ ርኅሩኅነት ሊያሳየው ፈልጎ ለምልማ የደረቀችን ቅል አሳየው [ሙሉ ታሪኩን ትንቢተ ዮናስ ምዕራፍ አራት ላይ ይመልከቱ]።
“እግዚአብሔርም፦ አንተ ትበቅል ዘንድ ላልደከምኽባት ላላሳደግኻትም፥ በአንድ ሌሊት ለበቀለች፥ በአንድ ሌሊትም ለደረቀችው ቅል አዝነኻል። እኔስ ቀኛቸውንና ግራቸውን የማይለዩ ከመቶ ሀያ ሺኽ የሚበልጡ ሰዎችና ብዙ እንስሶች ላሉባት ለታላቂቱ ከተማ ለነነዌ #አላዝንምን? አለው።”እግዚአብሔር ለኛም እንደ ነነዌ ሕዝብ ለንስሐና ለጾም የፈጠነ ልብ ያድለን! ዓይነ ምሕረቱን ይመልስልን!
2 372
Repost from Gracious ✝
"የህይወት እናት ድንግል ማርያም ሆይ ትንሳኤሽ ሳይሆን ሞትሽ ይደንቀኛል፤ እርገትሽ ሳይሆን ወደ መቃብር መውረድሽ ይገርመኛል፤ የብርሃን እናት ድንግል ማርያም ሆይ ትወጂኛለሽን? ብየ አልጠይቅሽም ፍቅርን የወለድሽ አንቺ ለአለሙ ሁሉ ፍቅርሽ የበዛ ነውና፤ አትናፍቂኝምን? ብየም አልጠይቅሽም ዘወትር እኔን ለመጠበቅ ከጎኔ እንደማትለይ አውቃለሁኝና፤ ሆኖም እመቤቴ ሆይ፦ እንደ ቶማስ አይሽ ዘንድ በእጅጉ እጓጓለሁ የቶማስ ንፅህናና ቅድስና ግን የለኝም እንደ ዮሃንስ ከጎንሽ ልሆን እጓጓለሁ የዮሃንስ ፀጋ ግን የለኝም፤ እናቴ ሆይ፦ እንደ ኤልሳዕ የልቦናዬ አይን በርቶ ሰማያዊ ክብርሽን ላይ አልተቻለኝምና አዝናለሁ ኤልሳዕ በፀሎት ሃይል የግያዝን አይን እንዳበራ አንቺም አይኔን ታበሪልኝ ዘንድ ሃይልሽን በእኔ ላይ አበርቺ፡፡ ድንግል ሆይ፦ ይህን የምል የእምነት ማረጋገጫ ፈልጌ አይደለም በልጅሽ መሰረትነት የታነፅኩኝ በልጅሽ ስምም የተጠመቅኩኝ ነኝና፤ ነገር ግን ስለምትናፍቂኝ ይህን አልኩኝ ስለዚህም ነይ ነይ እምየ ማርያም እያልኩኝ እንደ እናቶቼም እለምንሻለሁ፡፡ የብርሃን ልብስሽን ለብሰሽ ነይ የክብር አክሊልሽን ደፍተሽ ነይ አንቺ ሱላማጢስ ሆይ ነይ እናይሽ ዘንድ ነይ፡፡"
2 372
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
“አቤቱ፥ ውሆች አዩህ ውሆችም አይተውኽ ፈሩ፤ ጥልቆች ተነዋወጡ፥ ውሆችም ጮሁ።” (መዝ. 77፥16)እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ አደረሳችሁ!
2 372
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
እኔ ንስሓን የምሰብክ ነኝ፡፡ እርሱ ግን ኃጢአትንና በደልን ሁሉ ይቅር የሚል ነው፡፡ በእሳትና በመንፈስ ቅዱስም ያጠምቃችኋል፡፡ የመለኮቱን ብርሃንም በላያችሁ ላይ ያወጣል፡፡እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን! ዛሬ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ካልዕ ድርሳን ስለ ጌታችን ጥምቀት ከጻፈው እና በሊቃውንት በመምህር ቃለጽድቅ ሕግነህ የተተረጎመው ድርሳነ ሠለስቱ ገጽ 89-103 የተቀነጨበ ጽሁፍ እናቀርብላችኋለን እነሆ ጌታ መጥቶ በዮርዳኖስ ወንዝ ዳር ከሰዎች እንደ አንዱ ቆመ፡፡ ዮሐንስም ባየው ጊዜ በታላቅ ቃል አሰምቶ እንዲህ አለ፦ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ ይህ ነው፡፡ ከእኔ በኋላ የሚመጣው እሱ ከእኔ ይበልጣል ያልኋችሁ ይህ ነው፡፡ ኃጢአታችንና በደላችንን ሁሉ ይቅር የሚል የእግዚአብሔር በግ ይህ ነው፡፡ ክርስቶስም መጥቶ ከእርሱ ይጠመቅ ዘንድ ራሱን ወደ አጥማቂው ዮሐንስ ጎንበስ አደረገ፡፡ ዮሐንስም የሚያደርገውን አይቶ ታላቅ ፍርሀትን ፈራ፡፡ ደነገጠ ተንቀጠቀጠም፡፡ እንዲህም አለው፡፡ እኔ ታጠምቀኝ ዘንድ እወዳለሁ፡፡ አንተ ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ ይህ ግብር ምንድን ነው? ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም መልሶ አንዲህ አለው፡፡ ዮሐንስ ሆይ እኔ በመለኮቴ ክብር የማደርገውን ሁሉ አውቃለሁና ሆይ ተወኝ፡፡ዮሐንስ ሆይ ትእዛዛትን ሁሉ እፈጽም ዘንድ ተወኝ፡፡ ያን ጊዜ ዮሐንስ ፈቃዱን ይፈጽም ዘንድ ተወው፡፡ ከዚህም በኋላ ወልድ ዋሕድ ወደ ዮርዳኖስ ወርዶ በውኃ መካከል ቆመ፡፡ ከጌታ ከግርማው ክብር የተነሣ በውኃው ውስጥ የሚንቀሳቀሰው ሁሉ ዝም አለ፡፡ከአውሎና ከነጎድጓድ ብዛት የተነሣ ድንቅ ነገር ሆነ፡፡ ዮሐንስም ታላቅ ድንጋጤን ደነገጠ፡፡ የእግዚአብሔር የሀብቱ ጸጋ ተገለጠ፡፡ ሰማይ ተከፈተ መንፈስ ቅዱስም በነጭ ርግብ አምሳል ወርዶ በተወደደ ልጁ ላይ ተቀመጠ፡፡ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው ሲል የአብ ቃልም ከሰማይ ተሰማ፡፡ በዚያ የቆሙ ሰዎችም ሰምተው ይህን ነገር ዕፁብ ዕፁብ አሉ፡፡ ለአብ ለወልድ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይሁን አሜን ለዘለዓለሙ ይሁን፡፡ መልካም በዓል! #ከቅዱሳን_አንደበት
