ተዋሕዶን እንወቅ።
Open in Telegram
አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኲሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድኅነነ እምዕለት እኪት ወባልሐነ ውስተ መንሡት። ✝በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ✝ የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ጸሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማዕታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።
Show more2 372
Subscribers
-224 hours
-67 days
+530 days
Posts Archive
2 372
Repost from አምላከ ብርሀን
ዳግመኛም በዚህች ቀን ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች በሊብያ ሀገር በእስላማዊ አሸባሪ IS እጅ ምስክርነታቸውን ፈፅመው ፤ ሀይማኖታቸውን ጠብቀውው ፤ የድል አክሊል ተቀዳጁ ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ፤ እኛንም በፀሎታቸው ይማረን ።
ሰላም ለክሙ በቃለ ማሕሌት ወእንዚራ
ምስለ ሰማዕታት ዘግብፅ መከራቲክሙ ዘሐብራ
ቅዱሳን ሰማዕታት ዘኦርቶዶክሳዊት ሐራ እፎ ክሕልክሙ ተዓግሶ ፅኑዕ መከራ
እስከ ክሳውዲክሙ በአይሲስ ተመትራ
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
🎧 Share , Subscribe በማድረግ አገልግሎቱን ይደግፉ ! ( ቤተ ዝማሬ Podcast )
YouTube https://youtu.be/v3ebjryGGYw?si=U7thirpPIWRei7fF
2 372
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
[ የሚኖር ክርስትና ]
✝ ምዕራፍ ፩/1
✥ ክፍል ፩/1 ፦ መንፈሳዊ እድገት !
https://youtu.be/v3ebjryGGYw?si=U7thirpPIWRei7fF
2 372
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
ክርስቶስ ተንሥአ በአማን ተንሥአ
✨ እንኳን አደረሳችሁ ✨
#ሰሙነ_ፋሲካ
ፋሲካ የሚለው ስም በአረማይክ /ፓስኻ/፣ በግሪክ /ፓስቃ/፣ በዕብራይስጥ /ፐሳኽ/ ሲሆን፤ ደስታ ፣ ማለፍ የሚሉ ትርጉሞች አሉ፞ት።
ከትንሣኤ ሌሊት ጀምሮ እስከ ዳግም ትንሣኤ ያለው ሳምንት
የፋሲካ ምሥጢር የተገለጠበት፤ ከግብፅ ወደ ምድረርስት ከሲኦል ወደ ገነት መሻገርን የሚያመላክት ሳምንት ነው።
ከትንሣኤ እሁድ በኋላ ያሉ ዕለታት ስያሜ፡-
ሰኞ- #ማዕዶት ይባላል፡- ማዕዶት ማለት መሻገር፣ ማለፍ ማለት ነው፡፡ በዚህ ዕለት በፋሲካችን በክርስቶስ ትንሣኤ ከድቅድቅ ጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃን፣ ከሞት ወደ ሕይወት፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ከሃሳር ወደ ክብር መሻገራችንን እናስባለን፡፡
ማክሰኞ- #ቶማስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቶማስ ጌታን አይቶ ማመኑ፤ ጌታዬና አምላኬ ብሎ መመስከሩ ይዘከራል፡፡ ዮሐ. 20፡27-29
ረቡዕ- #አልአዛር ይባላል፡- በዚህ ዕለት ትንሣኤና ሕይወት የሆነው
ጌታ ኢየሱስ አልአዛርን ከሞት እንዳስነሳው እናስባለን፡፡ ክርስቶስ የሞትን ስልጣን የሻረ የሕይወት ራስ፤ የመቃብርን ሥርዓት ያጠፋ ትንሣኤ፡ በድልም ያረገ ንጉሥ መሆኑን እንመሰክራለን፡፡
ሐሙስ- #አዳም_ሐሙስ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ለአዳም የተሰጠው ተስፋ እና የተገባለት ኪዳን እንደተፈጸመ አዳምና ልጆቹ ነጻ እንደወጣን እናስባለን፡፡
አርብ- #ቅድስት_ቤተክርስቲያን ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቤተክርስቲያን በክርስቶስ ሞትና ትንሣኤ ስለመመስረቷ ይሰበካል፡፡ ክርስቶስ ስለ እርሷ ራሱን አሳልፎ ሰጥቶ ቤዛ ሆኖ በደሙ አንጽቶ በትንሣኤው ድል ሰጥቶ እንዳከበራት ይነገራል፡፡ ቤተክርስቲያን ስንል ሕንፃውን ሳይሆን አማኞችን ነው፤ ክርስቶስ ለሕንፃ አልሞተምና፡፡
ቅዳሜ- #ቅዱሳት_አንስት ይባላል፡- በዚህ ዕለት ቅዱሳት አንስት የክርስቶስን አካል ሽቶ ለመቀባት ጨለማ አቋርጠው ወደ መቃብር መምጣታቸውና ትንሣኤውንም ቀድመው ማየታቸው ይሰበካል፡፡
እሁድ- #ዳግም_ትንሣኤ ይባላል፡- በዚህ ዕለት ክርስቶስ ለሦስተኛ ጊዜ ለደቀመዛሙርቱ ተገልጦ ሰላምን መስበኩ እና ሥልጣንን መስጠቱ ይሰበካል፡፡
2 372
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት...?
“ኢየሱስም መልሶ፦ ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት፥ በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ። ... ዮናስ በዓሣ አንባሪ ሆድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት እንደ ነበረ፥ እንዲሁ የሰው ልጅ በምድር ልብ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ይኖራል አላቸው።” (ዮሐ. 2፥19፤ ማቴ. 12፥40)
ጌታችን በከርሰ መቃብር የቆየው ከዓርብ አስራ አንድ ሰዓት በፊት ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ለእሑድ አጥቢያ ነው። ታዲያ ሦስት ቀን ከሦስት ሌሊት በከርሰ መቃብር አደረ ልንል እንችላለን?
ይኽን ጥያቄ ለመመለስ የዕብራውያንን የቀን አቆጣጠር መረዳት ያስፈልጋል። በኹለት መንገድ ሦስት ቀንና ሦስት ሌሊት ተደርጎ ሊቆጠር ይችላል።
1. በዕብራውያን አቆጣጠር አንድ ሌሊት የሚጀምረው ከዋዜማው 11 ሰዓት ጀምሮ ነው። ከአስራ አንድ ሰዓቱ በፊት ያሉት ሰዓቶች አንድ ሰዓትም ቢኾን እንደ አንድ መዓልትና ሌሊት ይቆጠራል። ጌታችን ደግሞ የተቀበረው ከአስራ አንድ ሰዓት በፊት ነው - አንድ ቀንና አንድ ሌሊት። ዓርብ ከሠርክ 11:00 ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ሠርክ 11:00 ድረስ - ከዓርብ ጋር ኹለት ቀንና ኹለት ሌሊት። ከላይ እንዳየነው አንድም ሰዓት ቢኾን እንደ አንድ መዓልትና ሌሊት ይቆጠራል፤ ከቅዳሜ ሠርክ 11:00 ጌታችን ከሞት እስከ ተነሣበት መንፈቀ ሌሊት ድረስ - ከዓርብና ከቅዳሜ ጋር በአንድ ላይ - ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ኾነ ማለት ነው።
2. ክርስቶስ በፈቃዱ የተሰቀለውና የሞተው በዕለተ ዓርብ ስለኾነ አቆጣጠሩ ከጠዋት 12 ሰዓት ይጀምራል - ከ12 ሰዓት እስከ 6 ሰዓት በምድር ላይ ብርሃን ነበር - አንድ ቀን። ከስድስት እስከ ዘጠኝ ሰዓት ደግሞ በምድር ላይ በምትሐት ያልኾነ እውነተኛ ጨለማ ነበር - አንድ ሌሊት። ከዓርብ ዘጠኝ ሰዓት እስከ 12 ሰዓት እንደገና ቀን ኾኗል - አንድ ቀን። ከማታ 12 ሰዓት እስከ ቅዳሜ ጠዋት 12 ሰዓት - አንድ ሌሊት። ከቅዳሜ ጠዋት እስከ ማታ እና ከማታ እስከ መንፈቀ ሌሊት - ከዓርብ ጠዋት ጀምሮ - ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ይኾናል።
“ነፍሴን ደግሞ አነሣት ዘንድ አኖራለሁና ስለዚህ አብ ይወደኛል። እኔ በፈቃዴ አኖራታለሁ እንጂ ከእኔ ማንም አይወስዳትም። ላኖራት ሥልጣን አለኝ ደግሞም ላነሣት ሥልጣን አለኝ።” (ዮሐ. 10፥17-18)
2 372
Repost from Theo-Sophia
ምድራዊ ነገሥታት ዝቅ ብለው ለመመልከት በወርቅ ዙፋን ላይ ይወጣሉ፤ ክርስቶስ ግን እኛን ከፍ ያደርግ ዘንድ በዕፀ መስቀል ዙፋን ላይ ወጣ። የጦር መሪዎች የጠላቶቻቸውን ደም በማፍሰስ ድል ያደርጋሉ፤ ክርስቶስ ግን የገዛ ደሙን በማፍሰስ ጠላታችንን እስከመጨረሻው ድል ነሳ። ዓለም ሁሉ የሚታዘዝለትን "ጌታ" ይለዋል፤ የሁሉ ጌታ ግን ምንም ሳይኖረው ሁሉን በማገልገል በፍቅር ጌታ ሆነን። የምድር ዳኞች ሕግን ለማጽናት በበደለኛው ላይ ይፈርዳሉ፤ የእግዚአብሔር ልጅ ግን በደለኛውን ለመቤዠት በራሱ ላይ ፈረደ። የጀግና ጉልበቱ እስራቱን በመበጠስ ጠላቱን በመደምሰስ ይታወቃል፤ የክርስቶስ ኃይል ግን ስለ ሰው ልጆች ፍቅር ታስሮ በመዋሉ ታወቀ። ሰዎች ምስጋናን ይሻሉ ክርስቶስ ግን የርኩሳንን ምራቅ ታገሰ።ድል አድራጊ በሬሳዎች ላይ ይቆማል ክርስቶስ ግን ከሰዎች እና ከኃጥአን መካከል ሞቶ ተገኘ በሞቱ ሬሳዎች ላይ ሳይሆን በሞት ላይ ተረማመደ ። ለእግዚአብሔር ልጅ ክብር እና ምስጋና ይገባዋል።
2 372
Repost from SSC ቅድመ ግቢ ጉባኤ
#ሰሙነ_ሕማማት
እንበለ ደዌ ወሕማም፥ እንበለ ፃማ ወድካም፥
አመ ከመ ዮም ያብጽሐነ ያብጽሕክሙ
ለብርሃነ ትንሣኤሁ እግዚአብሔር በፍስሓ ወበሰላም!
ያለ ደዌና ያለ ሕማም፥ ያለ ፃማና ያለ ድካም
እግዚአብሔር ለትንሣኤው ብርሃን እንደ ዛሬ ቀን
በደስታና በፍቅር በአንድነት ያድርሰን፤ ያድርሳችሁ!
2 372
Repost from Timeless Truth
ጌታ ሆይ እባክህ አሁን አድን
ያንን ምራቅ ያንን ግርፋት ያንን ዘለፋ የተቀበልክለትን ልጅ ፈጽሞ አልመስልምና ጌታ ሆይ እባክህን እኔን ከእኔ አሁን አድነኝ
እኔን ከቃላት በላይ እንደወደድከኝ ዘንግቼ ኃጢአትን በጥቂቱ እንኳን አልጠላሁምና ጌታ ሆይ እኔን ከእኔ አሁን አድነኝ
ነፍሱን ለእኔ አሳልፈህ የሰጠህ አባትነትህን በዘነጋ ኑሮ እየኖርኩ ዛሬም እንደ ልጅ ሳይሆን እንደ ጥቅመኛ ዛሬም የማስታውስህ ለጥቅሜ ነውና ጌታ ሆይ እኔን ከእኔ አድነኝ
ጌታ ሆይ ልጆችህ በኃጢአት የተያዝንበት ንስሐን የሸሸንበት ሕይወት ከሆነው ሥጋና ደምህ የራቅንበት ጊዜ ነውና ጌታ ሆይ እኛን ከእኛ አሁን አድነን
ጌታ ሆይ ልጆችህ ባለ ማመን ጥርጣሬ የተያዝንበት ከቤተክርስቲያን የራቅንበት በምንፍቅና በብዙ የተወሰድንበት ጊዜ ነውና ጌታ ሆይ እባክህ አሁን አድነን
ጌታ ሆይ በቤተክርስቲያንህ ውስጥ እውነትን የያዙ ዝም እንዲሉ የተደረጉበት ይልቁንም ልጆችህን መጠበቅ የተሳናቸው አሳልፈው የሚሰጧቸው እረኞችን ፊት የወጡበት ጊዜ ላይ ነንና አንተ መልካሙ እረኛ ጌታ ሆይ እባክህ ቤተክርስቲያንህን አስባት አሁን አድናት
ጌታ ሆይ ልጆችህ በግፍ ደማቸው የሚፈስበት ሁሉም ነገን የመኖሩን የማያውቅበት እጅግ ክፉ ጊዜ ላይ ነንና ደማቸው የፈሰሰውን ልጆችህን ጌታ ሆይ እባክህ ነፍሳቸውን አሳርፋት የሰላም ጌታ የሆንከው እባክህን ሰላምህን በመስጠት አሁን አድነን
ከፍጡራን ሁሉ የጌታን ሕማም እንዳንቺ ያየና እንደ አንደኛውና ብቸኛው ልጅሽ እንደመሆኑ እንዳንቺ ያለቀሰ የለምና እባክሽን እንደኛ ኃጢአት ሳይሆን እንደ ምህረቱ እንዲያድነን ማርያም ሆይ ለምኚልን
ዮሐንስ ሆይ ያንተን አይነት ከጌታ ጋር መጽናት የሚያስፈልጋቸው ልጆችህ በብዙ ማዕበል እየተናወጡ ነውና እባክህን ወደ ምትወደው ጌታ አሁን ያድነን ዘንድ ለምንልን
2 372
Repost from Gracious ✝
“የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።”
ኢሳይያስ 53፥3
2 372
እስቲ ዝም ብለን ይሄን አጭር ጸሎት የምንሠራውን የምናደርገውን ሁሉ እያፈጸምን እንጸልየው...
ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ [የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ] ሆይ እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ።
2 372
Repost from Z𝑒𝑙𝑎𝑙𝑒𝑚 A𝑙𝑒𝑚𝑎𝑦𝑒ℎ𝑢 || ዘለዓለም ዓለማየሁ
ቤተ ክርስቲያናችን የሐዋርያትን ትምህርት መያዟን፣ ሐዋርያት ባስተማሩበት ትምህርት ላይ መሰረት ማድረጓን ከምንረዳባቸው መንገዶች መካከል ከሐዋርያት እግር ስር ከተማሩና በሕይወትም በመጸሐፍም ክርስቶስን ከሰበኩ የሐዋርያት ደቀ መዛሙርት (ሐዋርያን አበው) ካስተማሩት ትምህርት ጋር አንድ መሆኑ ነው።
ይህንን የሐዋርያን አበው(Apostolic fathers) መጸሐፍ ወደ አማርኛ እጅግ ውብ በሆነ መንገድ ተተርጉሟል። ስለዚህ ሁላችንም መጸሐፉን ገዝተን ሕሊና አበውን ገንዘብ እናድርግ።
መጸሐፉን አንብባችሁ ስትጨርሱ በአበው ተጋድሎና ፍቅረ ክርስቶስ እየተደነቃችሁ ነፍሳችሁ የፈለገችው ክርስቶስን እንደምታገኙት አልጠራጠርም።
መጸሐፉ የፊታችን ረቡዕ ገበያ ላይ ይውላል።
Pre-order ስለተጀመረ ሁላችሁም ሳያልቅባችሁ አስቀድማችሁ እዘዙ።
መልካም ንባብ!
መጸሐፉን ለማዘዝ
https://t.me/Theo_Sophia_apology/922
2 372
Repost from Theo-Sophia
ስለዚህ ፍላጎታችሁን ታሳቀውቁን ዘንድ እነሆ poll። እስከ ነገ ማታ 4 ሰአት ድረስ ይቆያል።
2 372
Repost from Theo-Sophia
ስላረፈድን በእውነቱ በጣም ይቅርታ እንጠይቃለን ። ይህ ፖል ለእኛ በጣም አስፈላጊ ነው ፤ ምክንያቱም በዚህ ምርጫችሁ መሠረት ነው ቀጣይ የሚታተሙት መጻሕፍት ቁጥር የሚወሰውነው ። እና ደግሞ አሁን እዚህ ላይ ያላችሁ ሁላችሁም ቅድሚያ እንዲደርሳችሁ፣ እዚህ ያለውን ሰው ብዛት እና መግዛት የምትፈልጉትን መጠን ማወቅ ያስፈልገናል ። መጽሐፉ እንደሰማችሁት ለጥቂት ሰው ስለሆነ የሚታተመው የጀርባ ዋጋ አልወጣለትም ከዚህ የሚሸጠው ግን ለ አንድ መጽሐፍ 1200 ብር ነው በብዛት ለሚገዙ (በተለይ ናዝሬት ብዙ ሰው ጠይቆናል) እና እዚው ለምናቃቸው ተማሪዎች ምን አልባት ይቀንሳል ።
2 372
Repost from Theo-Sophia
እነሆ እገዛችሁ የሚስፈልግበት ቀን መጥቷል። ከመቼውም ጊዜ በላይ ለእኛ የምትተጉበት ጊዜ እና አገልግሎታችንም እንዲቀጥል የምታደርጉበት ጊዜ መጥቷል። ይህንን በምትችሉት ሁሉ Share አድርጉ፦ በፌስቡክ (Facebook)፣ በቴሌግራም ስቶሪ በግሩፖችና ቻናሎች፣ በኢንስታግራም ስቶሪ ፣ በቲክቶክ (TikTok)፣ በግል መልእክቶች ልባቸው ክፍት ለሆኑ ሰዎች ሊደርስ በሚችልበት በማንኛውም ስፍራ አድርሱ ዜናው በሁሉ ዘንድ እንዲሰማ እና እንዲወራ የሁሉንም ሰው ጆሮ ልንወር ይገባናል። የአባቶችን ጽሁፍ ሁሉም ሰው ሊያነበው ይገባል!።
2 372
Repost from ኑር አል-መሲሕ ዕቅበተ ክርስትና ☦️☦️☦️
ምሥጢረ ሥላሴ ቁ.1 (የምሥጢረ ሥላሴ መግቢያ)
https://youtu.be/BjwOLTJwGsA?si=PeAYFEKch_T9X5lC
ምሽት 12፡00 ይመልከቱ
2 372
Repost from Gracious ✝
“ወደ ክርስቶስ መቅረብ ማለት የሕይወትን ትክክለኛ መልክ እንድናይ የሚረዳን አዲስ ዓለም ውስጥ እንደ መግባት ነው፡፡ ይህ ደግሞ ከዓለም ሸሽተን የምንደበቅበት ሳይሆን፣ ይልቁንም ዓለማችንን በደንብና በጥልቀት ማየት የምንችልበት ልዩ ዕይታ ነው፡፡"
Fr Alexander Schmemann
"Do not conform to the pattern of this world, but be transformed by the renewing of your mind. Then you will be able to test and approve what God’s will is his good, pleasing and perfect will."
Romans 12:2
