ተዋሕዶን እንወቅ።
Open in Telegram
አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኲሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድኅነነ እምዕለት እኪት ወባልሐነ ውስተ መንሡት። ✝በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ✝ የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ጸሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማዕታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።
Show more2 373
Subscribers
-124 hours
-27 days
+630 days
Posts Archive
2 371
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
📖 ራእየ ኒፎን 2013 ዓ.ም
ከገጽ 222 - 228“በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሳለን ዘወትር ከምሥጢራት ሊካፈል ወደ ቤተ ክርስቲያን በመገሥገስ የሚተጋ ለጽድቁ ሥራ የሚጋደል አንድ ወጣት ወደ አባታቸን ቀርቦ “አባቴ ሆይ የዘለዓለም ሕይወት እንዳገኝ ምን ላድርግ?” ሲል ጠየቀው ፡፡ “ልጄ ንጹሕ ነፍስ ያለችህ ኾነህ ሳለህ በኃጢአት ከተበላሸ አንድ ሽማግሌ ምን የሚጠቅም ነገር አለና ትጠይቀኛለህ?” አለው ፡፡ “ምክንያቱም አባቴ የእግዚአብሔር ቃል “አባትህን ጠይቅ ይነግርሃል” ይላልና ፤ ከአንተ የሚጠቅመኝን ቃል ለመስማት ጠየቅሁህ ፡፡ እባክህ የማልጠቅም ከኾንሁ ከእኔ ፊትህን አትመልስብኝ ፡፡” “ለመመንኮስ አስበሃል ወይስ ለሰው ሁሉ የተፈቀደውን ሕይወት በመኖር ፈጣሪህን ደስ ለማሰኘት ነው ምኞትህ? በማለት ወጣቱን ጠየቀው ፡፡ “አባቴ ለጊዜው በዚህ እየኖርሁ ለየትኛው ሕይወት የተገባሁ እንደ ኾንሁ ራሴን መፈተን እፈልጋለሁ ፡፡ ከዚያ የእግዚአብሔር ፈቃድ ወደምትመራኝ እሄዳለሁ ፡፡” አለው ፡፡ እንግዲያውስ ልጄ በሰዎች መካከል የምትኖር ከኾነ በእነዚህ ነገሮች ዙሪያ ጥንቃቄ ልታደርግ ይገባሃል ፡፡ በማንም ላይ ትችትን አትሰንዝር ፤ በማንም አትሳለቅ ፤ ለመቆጣት አትቸኩል ፤ ማንንም አትናቅ ፣ እገሌና እገሌ በቅድስና ይኖራሉ ፤ እገሌና እገሌ ደግሞ በኃጢአት ተውጠዋል ብለህ ከመናገር ተጠንቀቅ ፡፡ ምክንያቱም “በማንም አትፍረድ” ማለት ይህ ነውና ፡፡ ሁሉንም ሰው በተመሳሳይ ሐሳብ በእኩል ወዳጅነት በንጹሕ ልቡና ተመልከት ፡፡ እንደ ክርስቶስ አድርገህ ተቀበላቸው ፡፡ በሰዎች ላይ የሚፈርድን ሰው ጆሮህን ከፍተህ አትስማው ፡፡ የበለጠ ግን በሚሰጠው ሐሳብ ተስማምተህ ደስተኛ እንዳትኾን ተጠንቀቅ ፤ አፍህንም ጠብቅ ፡፡ በሌላ አነጋገር ለመናገር የዘገየህ ለጸሎት ግን የምትፋጠን ኹን ፡፡ ምንም እንኳ እያደረገ ያለው ስሕተት ቢኾንም በሌሎች ሲፈርድ የሰማኸውን ሰውም በሕሊናህ እንዳትፈርድበት ተጠንቀቅ ፡፡ ከዚያ ይልቅ የራስህን ድክመት እያሰብክ በራስህ ላይ የምትፈርድ ኹን ፡፡” አለው ፡፡ “አባቴ አኹን የነገርከኝ ዘወትር ሳያቋርጡ በተጋድሎ ለሚኖሩ ነው ፡፡ የማልጠቅም እኔ እግዚአብሔርን እንዴት ደስ ማሰኘት እችላለሁ? በማለት የመከረውን ሁሉ በደንብ ከሰማ በኋላ ጠየቀው ፡፡ “ልጄ በብዙ ምኞትና የሥጋ ፈቃድ ለሚቃጠል ወጣት ንጽሕናንና ትሕትናን ከያዘ ተስፋ ያለው ነው ፡፡ በጸጋ እያደገ እስኪሄድም ጌታ እግዚአብሔር ከዚያ በላይ አይጠብቅበትም ፡፡ ስለዚህ ወጣትነትህን በንጽሕናና በትሕትና አስጊጠው ፡፡ ራስህን በትሕትና ከሁሉ በታች አዋርድ ፡፡ ይህን ካደረግህ በእውነት ከክርስቶስ ጋር ኅብረት ይኖርሃል ፡፡ በሕሊናህም በቅድስና ታላላቅ ቅዱሳን የደረሱበት ከፍታ ላይ እንደ ወጣህ አታስብ ፡፡ ይልቅስ ነፍሴ ሆይ በእግዚአብሔር ፊት የሚያቀርብሽ ምንም መልካም ሥራ የለሽም ፡፡ ዕለት ዕለት በክፋት ከአጋንንት እንኳ እየባስሽ ሄደሻል ፡፡ በፍርድ ቀን የሚጠብቅሽ ቅጣት ምን ያህል ይኾን? ወዮልሽ! በማለት ራስህን ውቀስ ፡፡ ጸሎት ስትጸልይም በዓለም ካሉት ኃጢአተኞች ሁሉ የከፋው ሰው ጸሎት እንደ ኾነ ቊጠር ፡፡ … አንድ ሰው ሲበድልህ ካየህ ስለ እርሱ ራስህን ውቀስ ፡፡ አንተን ሰው ቢሰድብህ፣ ቢተችህ፣ ቢሳለቅብህ፣ ፈጽሞ ቢያዋርድህ እንኳ በሕሊናህ ራስህን አዋርደህ በሕይወት እንኳ ለመቆየት የማይገባህ መኾንህን እመን ፡፡ ይቅርታና ድኅነት የሚመጡት እነዚህን ተከትሎ ነው ፡፡” አለው ፡፡ - .....እንዴት #አደራችሁ ? - .....እንዴት #አረፈዳችሁ ? - .....እንዴት #ዋላችሁ ? - .....እንዴት #አመሻችሁ ?
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 371
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
✝ እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ !
(በዋናነት ለ12ተኛ ክፍል ተፈታኞች የተዘጋጀ)
ነገ ማታ 3፡00 ሰዓት ይጠብቁን !
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 371
Repost from ቬነስያ
እግዚአብሔር ምን ያህል እንደሚወዳችሁ ላሳያችሁ? ይኸው...
ዛሬም በሕይወት አላችሁ!
እስኪ አስቡት... ስንት በደል፣ ስንት ድካምና ስህተት በውስጣችን እያየ፣ እርሱ ግን ሁሉንም በትዕግሥት አልፎ በቸርነቱ ያኖረናል።
በእውነት በኃጢአታችን ልክ ምድራዊ ፍርድ ቢሰጠን ኖሮ፣ ከቶ ማን ነፃ ይወጣ ነበር? ሁላችንም የሞት ፍርድ ወይም የእድሜ ልክ እስራት የሚገባን እስረኞች አልነበርንም?
በቃ ተወዳችኋል!
╭══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╮
ቬነስያ
╰══•:|★✧♡💝♡✧★|: ══╯
2 371
Repost from Timeless Truth
+2
4ኛው መጽሐፋችንን እንደጨረስን ለJimmy Akin Email አድርጌለት ነበር
ይህንን ስራችንን በሚድያዎቹ ሁሉ አጋርቶልናል [አሪፍ ስራ እንደሰራን ይሰማኛል]
ይህንን እየጻፍኩላችሁ Email መለሰልኝ እና ከነዚህ ስራዎቹ ባለፈ የትኛዎቹንም ስራዎቹን እንድተረጉም ፈቃዱን ሰቶኛል እግዚአብሔር ይመስገን🙏
2 371
Repost from Timeless Truth
4ኛ መጽሐፋችን ይኸው
ልክ እንደ "ወንጌላት" መጽሐፍ እዚህም ላይ አሪፍ ሐሳቦችን ታገኛላችሁ ብለን እናምናለን
ሐሳባችሁን አካፍሉን አንብቡትና
2 371
Repost from N/a
እዩትማ ናፋቂያችንን ✨🥺
አምላክ ሰውን ብሎ.........................ሲ..ን..ከ...ራ...ተ...ት።
ሰውኮ የእጁ ስራ ነው . . .እንደ ፍቅር የጸና ኃይል የትም የለም። አምላክን ፍቅር ከዙፋኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው ።
2 371
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
🔴 "" በክርስትና ሕይወት ጥንቃቄ ከጎደለን የሚገጥመን ይህ ነው ""
ተለቋል !
YouTube - https://youtu.be/L4QOUNTR9qQ?si=bU1rnRuh8u344nLh
2 371
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
✝ « ግንቦት 11 ቀን በዓሉ ለቅዱስ ያሬድ ማሕሌታይ » ✝
የቤተ ክርስቲያን ጌጥ የዜማ አባት የመጻሕፍት ትርጓሜ መምህር የቅኔ እና የሥነ መለኮት ሊቅ ማሕሌታይ ቅዱስ ያሬድ ደብረ ሐዊ በተባለ ቅዱስ መካን በምናኔ ለብዙ ዘመን ከኖረ በኃላ ሞት ሳይቀምስ በሰባ አምስት አመቱ የተሰወረው ግንቦት 11 ቀን ነው ።
በገድለ ቅዱስ ያሬድ ተጽፎ እንደምናገኘው በዘመኑ የነበሩ ሁሉ እንደ መበረቅ የሚደምቅ፣ ምሥጢሩ እንደ መስታወት የሚያንጸባርቅ ጥበብ የተሞላበትን ድንቅ ዜማውን ለመስማት ከህጻናት እስከ ንጉሡ ድረስ ይከቡት የነበረ ማሕሌታይ ነው ።
ንጉሥ ገብረ መስቀል ይህን ታላቅ ጣዕም ያለው ዜማ በሰማ ጊዜ ጫማውን ከእግሩ አልጨመረም ንግሥቲቱም አገልጋዮቿን ተወች ያንን ጥዑም ዜማ ትሰማ ዘንድ በአንድነት ሮጡ ጳጳሳት ካህናት የቤተ መንግሥቱ ወይዛዝርት ሹማምንት ወደ ቅዱስ ያሬድ መጡ ሲሰሙት ዋሉ፤ ከድምፀ ቃናው ጣዕም የተነሣ አጥንትን የሚያለመልም ልቡናን የሚያስደስት ነገር አግኝተዋልና፤ የቃሉን ድምፅ በሰሙ ጊዜ ሮጡ ወደ እርሱ ደረሱ ንጉሡም ንግሥቲቱም ከካህናቱ ጋር፣ ከመንግሥት ሹማምንትና ከሕዝቡ ጋር በመኾን ሲያዳምጡት ዋሉ እንዲል ገድለ ቅዱስ ያሬድ ።
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር ሆይ የክብርህ ምስጋና ሰማያትንና ምድርን የመላ ነው እያሉ በስማይ ከሚኖሩ ከቅዱሳን መላእክት የሰማሁት ዜማ ምን ይረቅ ምን ይጠልቅ እንደምን ያለ ረቂቅ ነው ለዚህ አንክሮ ይገባል እያለ በምስጋና ሥርዓታቸው ሲደነቅባቸው ከነበሩ ከቅዱሳን መላእክት ጋራ ሊያመስገን ከዚህ ዓለም መከራ እና ድካም ሊያርፍ ሞትን ሳይቀምስ ተሰወረ በድርሣነ ቅዱስ ዑራኤል የስኔ ወር ምንባብ ላይ "" ከሰው ዓይን ተሰወረ አኗኗሩም ከሰማይ መላእክት ጋር ሆነ "" እንዲል።
ተዓምረ ኢየሱስ የተሰኘው የቤተ ክርስቲያናችን መጽሐፍም ፦ "" ካህኑ ያሬድ ከዚህ ዓለም የሚለይበት ሰአት በደረሰ ጊዜ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ወዳጄ ሆይ ቀድሞ በሰማይ ያለ የመላእክትን ሥርዓት እንድታይ እና ወደ ምድር አስተላልፈህ ይህንኑ ዜማ እንድትመሠርት እንደ ወደድኩ ሁሉ አሁንም ከዚህ ዓለም በምትለይበት ሰዓት እኔ ዳግም ተመልሼ በምመጣበት ጊዜ ከካህናተ ሰማይና ሄሮድስ ደማቸውን ካፈሰሳቸው ህጻናት ጋር በደብረ ጽዮን ትዘምር ዘንድ ሰማያዊ የክብር አክሊል እና የብርሃን ልብስ ተዘጋጅቶልሃል ብሎት ወደ ሰማይ ዐረገ "" ሲል ሞትን ሳይቀምስ መሰወሩን ይገልጻል ።
የቅዱስ ያሬድ በረከት በሁላችን ይደር በምልጃው ሀገራችንን ከክፉ ነገር ይሰውርልን ። አሜን ፫
- .....እንዴት #አደራችሁ ?
- .....እንዴት #አረፈዳችሁ ?
- .....እንዴት #ዋላችሁ ?
- .....እንዴት #አመሻችሁ ?
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 371
Repost from Theo-Sophia
ይህንን story በማድረግ እና share በማድረግ ተባበሩን ። እንደሁል ጊዜው መልካም ፈቃዳችሁ እና ቀና ልቡናችሁ ያስፈልገናል ። ያልሰማ ሰው እንዳይኖር ሰምቶም ቸላ ያለ እናም ለመስጠት የሰሰተ እንዳይኖር የሰማ ሁሉ የአቅሙን እንዲያደርግ እና የነዳያንን ረሃብ እንድናስታግስ እንለምናችኋለን።
2 371
Repost from Theo-Sophia
+1
በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ተጀምሮ በ ቴዎሶፍያ የተጠናቀቀው ለብዙዎች መንፈሳዊ ህይወት በጣም ጠቃሚ የሆነው elements ቅጽ 1― ባህርያት እነሆ ደርሳ ለገበያ ውላለች ማስተዋወቅ እና ገዝታችሁ ማንበብ አትርሱ ።
2 371
Repost from Theo-Sophia
+1
በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ተጀምሮ በ ቴዎሶፍያ የተጠናቀቀው ለብዙዎች መንፈሳዊ ህይወት በጣም ጠቃሚ የሆነው elements ቅጽ 1― ባህርያት እነሆ ደርሳ ለገበያ ውላለች ማስተዋወቅ እና ገዝታችሁ ማንበብ አትርሱ ።
2 371
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
✝ አልጠበኩም !
ይህንን ሚድያ ከወንድሞች ጋር ስንጀምር እናንተን በምንም ነገር አላስቸገርናችሁም ። እንደ ሠርግ ደጋሽ የሚያስፈልገውን ሁሉ አሰናድተን ነው የጠበቅናችሁ ታዲያ ለምን ሰሀን አታነሱም ? ለምን አትመገቡም ? ካሜራ ፣ ማይክ ፣ መብራት ፣ የቀረጻ ቦታ.... ወዘተ እዚህ ባሉ አገልጋዮች ተሸፍኖ ተዘጋጀ እንጂ ከእናንተ ምንም አይነት የገንዘብ ድጋፍ አልጠየቅንም ። ይህም ሆኖ የጠበቅነውን ያህል አልሆነልንም ።
በዚህ አንድ ወር ውስጥ 94 ሰው ብቻ ነው ቤተሰብ የሆነው ። እዚህ ካለው ሰው አንጻር እኔ ይህን አልጠበኩም ። ከዚህ ቁጥር ውስጥ እንኳ ግማሽ ያህሉ በእኛ በኩል የተሰበሰቡ ናቸው ። ከዚህ በፊት በምንም አስቸግሬአችሁ አላውቅም ለወደፊቱም እንዲሁ ። ነገር ግን መርሐግብሩን አሰናድተው የሚያቀርቡላችሁ አገልጋዮች በብዙ የሚደክሙበት ፣ ከኪሳቸው ወጪ የሚያወጡበት ስለሆነ ቢያንስ ይህን ተረድታችሁ አገልግሎታቸው እንዲሰፋ ፣ በሥራቸውም እንዲጠነክሩ በሙሉ እጃችሁም ባይሆንላችሁ እንኳ በአንድ ጣታችሁ ብቻ Subscribe በማድረግ አግዟቸው ። ከተረዳችሁኝ ይህ ትልግ ድጋፍ ነው ። ሌሎች ቤተ እምነቶች ክህደታቸውን ፣ ኑፋቄአቸውን ፣ ተንኮላቸውን ለመዝራት በብዙ ይደጋገፋሉ እኛ ላይ ግን ምን አዚም እንደጣለብን ሁልጊዜ ጥያቄ ይሆንብኛል !?
...... ብቻ አደራ እንዳታሳፍሩኝ !
...... አይታችሁ ዝም አትበሉ !
...... አንድ ጣት ብቻ !
✝ በሉ አሻራችሁን አሳርፉ - https://youtube.com/@betezimarepodcast
2 371
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
🔴 የሚኖር ክርስትና ( ምዕራፍ ፩/1 )
✥ ክፍል ፫/3 ፦ ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ ጥቂት ጥረት እናድርግ !
መሉ ትምህርት ተለቋል !
YouTube - https://youtu.be/zKNQd_GN9Lg?si=a2tnQ0bu5GBOtrWC
2 371
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
✝ ፈቃድህ ይሁን !
✥ ክፍል ፪/2
መንገድ ዘግቼ የሚዘለውን ፣ በር ቆልፌ ሰብሮ የሚወጣውን ፣ እየለመንሁ የማይመለሰውን ነገር ሁሉ ፈቃድህ ይሁን ብሎ መተውን አስተምረኝ ። የእኔ መሻት ይህ ነው ፤ የሚሆነው ግን ተቃራኒ ነው ለምን ? በምልበት ሰዓት ፈቃድህ ይሁን ማለትን አስተምረኝ ። በበጎ አሳብ እንዳልቀጣ ፣ መራራትም ግርፋት እንዳይሆንብኝ ፈቃድህን ካላከበረ ፍቅር አድነኝ ። ሰው ቢኖር የእኔ ነው ብልም ቢሞት ግን ያንተ ብቻ ነው ። ቢኖርም ቢሞትም ላንተ ነውና ስለ ሰው አንተን እንዳልከስህ ፣ ስለ ወዳጆቼ ለምን ነካህብኝ እንዳልልህ እርዳኝ ።
የሆነውን ነገር ብቻ ሳይሆን የሚሆነውንም እንድቀበል ፣ መገረሜ ባንተ ብቻ እንዲሆን እለምንሃለሁ ። ብቻ ጌታ ሆይ የአቅሜን ሞክሬ አንባዬ አፈትልኮ ሲወጣ ፈቃድህ ይሁን ማለትን አስተምረኝ ። እኔ ምድርን እያየሁ ስከላከል ፣ አንተ ሰማይን ባየህለት ሰው ፈቃድህ ይሁን ማለትን አስተምረኝ ። ምንም ነገር ጥያቄ እንዳይሆንብኝ አንተ ሰው ሁነሃል ። ሰው እስከ መሆን ፍቅር ዝቅ ካደረገህ ለሰው የምታደርገው ሁሉ በጎ ነው ። እባክህን የጌታ ፈቃድ ይሁን ብሎ ዝም ማለትን አስተምረኝ ። አሜን !
ጌታ ሆይ ፈቃድህ ይሁን !.....ይቀጥላል - .....እንዴት #አደራችሁ ? - .....እንዴት #አረፈዳችሁ ? - .....እንዴት #ዋላችሁ ? - .....እንዴት #አመሻችሁ ?
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 371
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
✝ ፈቃድህ ይሁን !
✥ ክፍል ፩/1
“የጌታ ፈቃድ ይሁን ብለን ዝም አልን ።” /ሐዋ 21÷14/
ጌታ ሆይ የምወደው ፣ የምሰራው ሁሉ ያለ ችግር እንዲሆን መመኘቴ በእውነት ከንቱ ነው ። ወፍጮ ቤት ገብቶ ዱቄት ሳይነካው የሚወጣ ፣ በዚህ ዓለም ኑሮ መከራ ሳያገኘው የማያልፍ ማነው ? እኔ ግን የእኔ የምለው ሁሉ ያለ መከራ እንዲኖር እፈልጋለሁ ። ጌታዬ ሆይ መምከር እንጂ ማስገደድ በማልችልበት ዓለም ከጸሎት ጋር መምከርን ስጠኝ ። እኔ በቃል ብመክር አንተ ግን በሕይወት እያሳለፍህ መምከር የምትችል መምህር ነህና ላንተ ስፍራ መልቀቅን አስተምረኝ ። የሰው ልጅ በመጀመሪያ ምርጫው የኋላ ውጤቱ ይታወቃልና የማውቀው ነገር ፍርሃት እንዳይሆንብኝ ፣ የእኔ ለምላቸውም መምረጥ ባለመቻሌ እንዳላዝን እባክህ አስተምረኝ ።
ያልከው አይቀርምና መጨነቄ ፣ ሊሆን ያለው ይሆናልና መባዘኔ ከንቱ ነው ። ሁሉን ላንተ ሰጥቶ ማረፍ ይሁንልኝ ። ልመልሰው ያቃተኝን ፣ ልይዘው ስል ያመለጠኝን ሁሉ ፈቃድህ ይሁን ብዬ እንዳርፍበት እለምንሃለሁ ። ስለ ልጆቼ ፣ ስለ ትዳሬ ፣ ስለ አገልጋዮቼ ፈቃድህ ይሁን ማለትን አስተምረኝ ። ፈቃዴ ፈቃድህን ላይለውጠው ፣ መሻቴ ሰውን ከመልካም መንገዱ ላይመልሰው እንዲሁ መዋተትን ከእኔ አርቅ ። አገልጋዮቼ የተፈጠሩት ላንተ እንጂ ለእኔ አይደለም ፣ የእኔ በምላቸውም ላይ ፣ እኔ ካለኝ ዓላማ አንተ ያለህ ዓላማ ይበልጣል ። ጌታ ሆይ "ፈቃድህ ይሁን" ብዬ ማረፍን ስጠኝ !
..... ይቀጥላል
መልካም ዕለተ ሰንበት 🕊- .....እንዴት #አደራችሁ ? - .....እንዴት #አረፈዳችሁ ? - .....እንዴት #ዋላችሁ ? - .....እንዴት #አመሻችሁ ?
JOIN @Applied_CHRISTIANITY
2 371
Repost from መራኁት
እድሜዬ እየጨመረ ሲመጣ እና ነገሮችን እንዲሁም የገዛ ሕይወቴን ከድሮው በተለየ ማስተዋል ስጀመር፣ የኃጢአቴ ነገር ከአቅሜ በላይ መሆኑን ስረዳ ቤተክርስቲያን ውስጥ ዕለት ዕለት በቋሚነት የሚጸለዩ ጸሎቶች ቅዳሴ ብቻ፣ ኪዳን ብቻ፣ ፍትሐት ብቻ እንዳልሆኑ በደንብ እየገባኝ መጥቷል። it is personal! It is always about me. ሊቃውንቱ የሥነ ጽሑፍ ችሎታ ስላላቸው፣ ቅኔ ስለሚችሉ፣ ግጥም ስለሚሳካላቸው ወይ ደግሞ ፎርማሊቲ ለሟሟላት አልተሠሩም፣ ይልቁንም መንፈስ ቅዱስ ለኔ ስብራት መድኅን እንዲሆኑ ያዘጋጃቸው ናቸው።
እያንዳንዱ ቃል በልባችሁ አይከብድባችሁም? ውዳሴ አምላክን ስታነቡ ስለ ግል ሕይወታችሁ የተጻፈ ያህል አይሰማችሁም? ካህኑ "ኢትዝክር ለነ አበሳነ ዘትካት፣ ፍጡነ ይርከበነ ሣህልከ እግዚኦ" ብሎ አንጀት በሚያራራ ዜማ ሲያዜም ኡ! ኡ! ብሎ መጮኽ አያምራችሁም? የጌታን ምሕረቱን የራሳችሁንም ኃጢአት ስታስቡ፣ እናቱ ስትገርፈው መሄጃ ስለሌለው ቀሚሷን ይዞ በጉያዋ ተወሽቆ እንደሚያለቅስ ሕጻን ያለ ስሜት አይሰማችሁም?
ቢሆንላችሁ ቢሳካላችሁ ክርስቶስ ላይ ልጥፍ ብላችሁ ሌላ ምንም ምን ሳታስቡ፣ ሁለተኛ ምንም ኃጢአት ሳትሠሩ ጌታን ብቻ እያሰባችሁ መኖር አያምራችሁም🥹 ያንን ማድረግ አለመቻላችሁስ ልባችሁን ስብር ስብርብር አያደርገውም?
ቅዱስ ጳውሎስ በሲቃ "ለዚህ ለሞት ከተሰጠ ሥጋ ማን ያድነኛል?" ሲል እኔን እኔን ብላችሁ ደረታችሁን እየደቃችሁ ልታለቅሱለት አያምራችሁም? i know what you mean, i really really do ማለት አያሰኛችሁም? ከዛ ግን የርሱን ሩብ ያህል እንዳልተጋደላችሁ ስታስቡ ኀፍረት ፊታችሁን ሽምቅቅ አያደርገውም?
ነጠላ ያደረገ፣ የጸሎት መጽሐፍ የያዘ ሰው ባያችሁ ቁጥር፣ በማርያም ጸልይልኝ ማለት አያምራችሁም?
እንጃ
2 371
Repost from N/a
የሞት ሞቱን ተጎትቶ እየሄደ ስዕሏ ስር ተደፋ . . . ሊነግራት የፈለገው ብዙ ነገር አለው። ግን ስዕሏን ማየት ነፍሱን ሲያዘልላትና ሲያስፈነድቃት የነፍስ ማደርያ የሆነው ስጋ ሲሸነፍ እና እዳዘዘችው ሲሆን ገረመው።
ሊያወራት መጥቶ ገጿን ማየት እንዲኽ ጮቤ ሲያስረግጠው ደስ አለው።. . . .ዘለአለም አለሜን ምናለ አንቺን ብቻ እያየሁ መኖር ብችል ብሎ ተመኘ. . .
ጭካኔን እና ክፋትን ለመናት! ልቤን አስጨክኚልኝ ፣ ልቤን ክፉ አድርጊልኝ . . .አለ! ክፋትና ጭካኔን በልቡ ሞልታለት ሺ ዘመን እሷን እያየ ሰማይና ምድር ቢያልፉ አማረው።
የተቀደሰ ጭካኔ ፣ በአለም እና በሁለመናዋ ላይ ጥርስን ንክስ የሚያስደርግ ጭካኔን ለመናት። የተቀደሰን ክፋት ለአለም መሻቶች እንቢ አንቺማ ምትፈልጊው አልሰጥሽም አታቂም እንዴ እኔ እኮ ክፉ ነኝ ማለትን አሰኘው።
ምናለ ብሎ ብዙ ምናለዎችን በልቡ አሰበ።. . .አንዲት ጭካኔ አንዲትም ክፋትን ብቻ እለምንሻለሁ እነኚህም ለአለም መክፋትንና በአለም መጨከንን ነው. . . .ከዛማ ባርያሽ ሆኜ ዘላለም በተባለ ወሰን የለሽ የጊዜ ቀመር ውስጥ አንቺን ብቻ ሳይሽ ብኖር እላለሁ አለ. . . .
አሁን እንዳያት ነው . . .አይኑን ከእርሷ አላነሳም. . .በአይነ ስጋ ያዩዋትን ሰዎች እያሰበ ቀና። . . . .ልቡ ተንገበገበበት. . .ይኽን መንገብገብ ዘላለም ቢንገበገበው ወደደ. . . ይኽን መንገብገብ ከዛች ቅጽር እግሩ እንደወጣ አለም ውሃ እንደምቸልስበት ሲያውቅ ከፋው. . . . ." ዘላለም አታንገበግቢኝም? ዘላለም አታቃጥይኝም? ማንም ቸልሶ ማያጠፋው የፍቅርሽ እሳት መቼ ነው ሚነደኝ ግን?" እየጠየቃት ነው!
2 371
Repost from ተግባራዊ ክርስትና
🔴 የሚኖር ክርስትና ( ምዕራፍ ፩/1 )
✥ ክፍል ፩/1 ፦ ዓላማ !
https://youtu.be/DOwhqdQmkaA?si=1RKOTLUO2eZDlOjm
2 371
Repost from አምላከ ብርሀን
ዳግመኛም በዚህች ቀን ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች በሊብያ ሀገር በእስላማዊ አሸባሪ IS እጅ ምስክርነታቸውን ፈፅመው ፤ ሀይማኖታቸውን ጠብቀውው ፤ የድል አክሊል ተቀዳጁ ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ፤ እኛንም በፀሎታቸው ይማረን ።
ሰላም ለክሙ በቃለ ማሕሌት ወእንዚራ
ምስለ ሰማዕታት ዘግብፅ መከራቲክሙ ዘሐብራ
ቅዱሳን ሰማዕታት ዘኦርቶዶክሳዊት ሐራ እፎ ክሕልክሙ ተዓግሶ ፅኑዕ መከራ
እስከ ክሳውዲክሙ በአይሲስ ተመትራ
