cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

Secrets of Truth - 𝘽𝙮 𝙍𝙚𝙨𝙝𝙖𝙙

● ዲናችንና በሚመለከት ወቅታዊ መረጃዎችን ➶ Current information about Muslims and Islam 🔗 ሌሎችንም አንገብጋቢ ጉዳዮችን የምንተዋወስበት Channel ነው‼️ ➞ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አጠር ያሉ ስንኞች (በተለይም ስለ ፈለስጢን 🇵🇸) 🎯 አላማዬ:- የእውነትን ሚስጥሮች ማጋለጥ ነው‼️ #Free_Palestine 🇵🇸

Show more
Advertising posts
282
Subscribers
+124 hours
+27 days
-930 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

‏يوم القيامة تُجْزَى كل نفس بما كسبته من عمل، إن خيرًا فخير، وإن شرًّا فشرّ ﴿اليَومَ تُجزى كُلُّ نَفسٍ بِما كَسَبَت لا ظُلمَ اليَومَ إِنَّ اللَّهَ سَريعُ الحِسابِ﴾. تلاوة فضيلة الشيخ د. ‎#صلاح_البدير من صلاة المغرب السبت 18 شوال 1445هـ ما تيسر من سورة غافر 13-20 #المسجد_النبوي #الحرم_المدني #فروض_شوال_١٤٤٥ #مغربيات_شوال_١٤٤٥
Show all...
﴿فَليَعبُدوا رَبَّ هذَا البَيتِ﴾ تلاوة لسورتي التين وقريش للشيخ د. #بندر_بليلة | مغرب السبت 18-10-1445هـ #تسجيل_من_ساحات_الحرم #المسجد_الحرام #الحرم_المكي
Show all...
ተዋቂ ስትሆን ከሚያጨበጭቡልህ ሚሊዮን እጆች ይልቅ በውድቀትህ ጊዜ ልታነሳህ የተዘረጋች አንዲት እጅ እጅጉን በላጭ ነች!!! ስለዚህ ዛሬ ላይ በየትኛውም ሁኔታ ብንሆን የለኛ የሚያዝኑልንን፣ ከመጥፎ የሚከለክሉንና በጥሩ የሚያዙንን እጆች እንናቃቸው!
Show all...
أذان صلاة العصر من #المسجد_الحرام للمؤذن #ماجد_العباس 21 شوال 1445هـ
Show all...
أذان صلاة الظهر من #المسجد_الحرام للمؤذن #أحمد_خوجة 21 شوال 1445هـ
Show all...
⛅️የጠዋት መልዕክት - ቤተሰቦችህ የስራህን ክብደትና በቀንህ ላይ የሚያጋጥምህን ውጣ ውረድ አያውቁም ። - ስራህም የህይወትህንና የቤተሰብህን ሁኔታ አያውቅም ። - ጓደኞችህም ወዳጆችህም ጫንቃህ ላይ የተከመሩብህን ሀላፊነቶች ላይረዱ ይችላሉ። - የህይወትህም አጋር ካንተ ምንም መስፈርት የሌለውን ፍቅርና ትብብርን በተለያየ መልኩ ይጠብቃል ። ምንም ያህል ለማስረዳት ብትሞክር የምትጋፈጠውን ችግር ላይረዳህ ይችላል… 〰 በአጠቃላይ ማንም ሰው ከራስህ በላይ የሚረዳህ የለም ። ማንም ሰው የምታሳልፈውን መከራ በሙሉ ሊረዳህ አይችልም ። ለድካምህም ዋጋ የሚሰጥ ሰው ጥቂት ነው ። ስለዚህ… 🔖 አንተ ዝም ብለህ ጉዞህን ቀጥል … ማንም ሰው እንዲረዳህ አትጠብቅ… ⛅️⛅️ መልካም ንጋት⛅️⛅️ ✍🏻 ቢንት አብደላህ ይ🀄ላ🀄ሉን👇👇 share👇 ┏━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┓        @tolehaahmed ┗━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┛
Show all...
🌿🌿🌿🍃ጥቆማ 🍃🌿🌿🌿 ኢስላም ያለ አንድ ሰይፍ አውሮፓን እያጥለቀለቀ ነው ~ ኢስላም በአሁኑ ሰዓት በምእራቡ አለም በከፍተኛ ፍጥነት እየተስፋፋ ነው። ብሪታንያን እንደ ምሳሌ እንመልከት። መረጃዎቼን የወሰድኩት የኢስላም በሃገሪቱ በከፍተኛ ፍጥነት መስፋፋት እንቅልፍ የነሳው ፀሐፊ “ለንደን 500 ቤ/ክርስቲያናትን ዘግታ 423 አዳዲስ መስጂዶችን ከፈተች” በሚል ርእስ ከፃፈው አርቲክል ሲሆን በዚህ ድረ ገፅ ታገኙታላችሁ። http://yournewswire.com/london-churches-mosques/ ኢስላም ብሪታንያን እየዋጣት ነው ይላል የፅሁፉ ጭብጥ። ይህንን ለማሳየትም የተለያዩ መረጃዎችን ዘርዝሯል። ሀሳቡ ሲሰበሰብ የሚከተለውን ይመስላል:- በሂያት ዩናይትድ ቤ/ክ በግብፃውያን ኮሚዩኒቲ ተገዝቶ መስጂድ ሆኗል። ቅዱስ ጴጥሮስ ቤ/ክ “መዲና  መስጂድ” ተብሎ ተቀይሯል። ብሪክ ሌን መስጂድ ቀድሞ የሜተዲስት ቤ/ክ ነበር። ህንፃው ያለ ምክንያት አልተቀየረም። ህዝቡም እየተቀየረ ሆኖ እንጂ። አዎ የሰለምቴዎች ቁጥር በእጥፍ አድጓል። ፀሐፊው ዴይሊ ሜይልን አጣቅሶ እንደፃፈው በለንደን እምብርት ውስጥ በጥቂት ሜትሮች ርቀት ላይ ቤ/ክ እና መስጂድ ይገኛሉ። ይሄ ምንም አይደንቅም። የሚደንቀው 1,230 ሰዎችን ለማስተናገድ የተዘጋጀው ቅዱስ ጊዮርጊስ በተሰኘው ቤ/ክ  ውስጥ ሳምንታዊ ባእልን ለማክበር የተገኘው ክርስቲያ 12 ሰዎች ብቻ መሆናቸው ነው። በሳንታ ማሪያ ደግሞ 20 ብቻ። በአንፃሩ በአቅራቢያው የሚገኘው የብሩን ስትሬት ኢስቴት መስጂድ የገጠመው ችግር ከዚህ የተለየ ነው፣ ለሰጋጆች የሚበቃ ቦታ በማነሱ መጨናነቅ! መስጂዱ 100 ሰዎችን ብቻ የሚያስተናግድ ጠባብ ክፍል ያለው በመሆኑ ለጁሙዐ የሚታደመው ምእመን ጎዳና ላይ ሊፈስ ግድ ሲለው ይታያል። ይህ ሁኔታ በዚሁ ከቀጠለ ክርስትና በእንግሊዝ ወደ ታሪካዊ ቅርስነት እየተቀየ ሲሄድ ኢስላም ግን የሃገሪቱ የወደፊት ሃይማኖት ይሆናል። ይህን ግምት የሚያጠናክሩ ተጨባጭ እውነታዎች አሉ። ከነዚህም ውስጥ አንዱ ከሃገሪቱ ሙስሊም ማህበረሰብ ውስጥ ግማሽ (50%) አካባቢው ከ25 አመት እድሜ በታች መሆኑ ሲሆን ከክርስቲያኑ ህዝብ ደግሞ ሩቡ (25%) ከ65 አመት እድሜ በላይ ያሉ አዛውንቶች መሆናቸው ነው። ይህም ከ20 አመታት በኋላ ወደ ቤ/ክ ከሚሄዱ ክርስቲያኖች የሚልቁ ንቁ ሙስሊሞች ይኖራሉ ማለት ነው፤ የናሺናል ሴኪዩላር ሶሳይቲ ዳይሬክቴር የሆነው ከይዝ ፖርቺየስ እንደገለፀው። በሌላ በኩል የሃገሪቱ ክርስቲያን በየጊዜው ለክርስትናው ጀርባውን እየሰጠ በመሆኑ የተነሳ የቤ/ክርስቲያናቱ ቁጥር በፍጥነት እያሽቆለቀለ ነው። ከ2001 ጀምሮ ለንደን ውስጥ ብቻ 500 ቤ/ክርስቲያናት ወደግል መኖሪያነት ተቀይረዋል። በተመሳሳይ ጊዜ በሃገሪቱ የሚገኙ መስጂዶች ቁጥር ሲታይ ግን በከፍተኛ ፍጥነት እያሻቀበ ነው ያለው። ከ2012 እስከ 2014 ባሉት አመታት ራሳቸውን የአንግሊካን ክርስትና ተከታዮች እንደሆኑ ሲገለፁ የነበሩ እንግሊዛውያን ቁጥር ከ21% ወደ 17% በማሽቆልቀል በሶስት አመታት ውስጥ ብቻ ቤ/ክርስቲያኗ የ1.7 ሚሊዮን ተከታይ ኪሳራ ደርሶባታል። የሙስሊሙ ቁጥር ግን በአንድ ሚሊዮን አካባቢ እድገት አሳይቷል። ይሄ 5% ከማይሞላው ከሃገሪቱ የሙስሊሙ ቁጥር አንፃር ሲታይ እጅግ ከፍተኛ እድገት ነው። (ይስተዋል! በጁላይ 2015 በተካሄደው የህዝብ ቆጠራ መሰረት የእንግሊዝ ህዝብ ብዛት 64 ሚሊዮን ሲሆን የሙስሊሙ ቁጥር ከዚህ ውስጥ 4.4% ነው።) ሆኖም ግን ግምቶች እንደሚያስቀምጡት በ2020 የጀማዐ (ህብረት) ሶላት ላይ የሚገኙ ሙስሊሞች ቁጥር ቢያንስ ወደ 683ሺ ያሻቅባል ተብሎ ይጠበቃል። በአንፃሩ ሳምንታዊው በዓል ላይ የሚገኙት ክርስቲያኖች ቁጥር ወደ 679ሺ ይወርዳል ተብሎ ይገመታል። ወደ ቤ/ክ የሚመላለሰው ህዝብ ቁጥር ወደ መስጂድ ከሚመላለሰው ሙስሊም ህዝብ ጋር ሲነፃፀር በአንድ ትውልድ ዘመን ውስጥ ብቻ ሶስት እጥፍ ያነሰ ይሆናል። በ2015 በተደረገ ትንተና በሃገሪቱ የብዙ ሰዎች ስያሜ በመሆን ልቆ የተገኘው “ሙሐመድ” የሚለው ስም ነው። ታላላቅ የሃገሪቱ ከተሞች ከፍተኛ የሙስሊም ቁጥር አላቸው። ማንቸስተር 15.8%፣ በርሚንግሀም 21.8%፣ ብራድፎርድ 24.7%። በክርስቲያን ቤተሰብ ከሚወለደው ይልቅ በሙስሊም ቤተሰብ የሚወለደው ህፃን ቁጥርም የላቀ ነው። በብራድፎርድና በሌስተር ከከተማዎቹ ህፃናት ግማሾቹ ሙስሊሞች ናቸው። ከተወሰኑ አመታት በኋላ የከተማዎቹ ነዋሪዎችን የህዝብ ብዛት ስብጥር ይገምቱ እንግዲህ። በሌላ በኩል ለንደን ውስጥ ብቻ ኦፊሻሊ የሚታወቁ 100 የሸሪዐ ፍርድ ቤቶች አሉ። የሃገሪቱ ህግ አንዳንድ የሸሪዐ ህጎችን እንዲያካትት በሃገሪቱ ታዋቂ የሆኑ ግለሰቦች ሳይቀሩ እየጠየቁ ነው ያሉት። የብሪታኒያ ዩኒቨርሲቲዎችም ኢስላማዊ ህግ እያስተማሩ ነው። (የኛዎቹ ያሉትንም እየዘጉ እንደሆነ ልብ ይሏል።) በሳዑዲ ዐረቢያ የብሪታኒያ አምባሳደር የሆነው ሲሞን ኮሊስ ኢስላምን ተቀብሎ ወደ መካ በመሄድ ሐጅ አድርጓል። ጠላቶቹ የፈለገ ቢያሴሩ መጪው ዘመን የኢስላም ነው። በሃገራቸው ያለው አንፃራዊ ነፃነት ለኢስላም መስፋፋት ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ እንደሆነ የገባቸው ምእራባውያን በነፃ መድረኩ “ፍልሚያ” ኢስላም ልቆ እየወጣ እንደሆነ ቢረዱ ጊዜ በሙስሊሞች ላይ የነፃነት ምህዳሩን ማጥበብ፣ ሃይማኖቱን ጭራቅ አድርጎ የመሳል (islamophobia) ሰፋፊ ዘመቻዎችን መደገፍ፣ እንደ ዳዒሽ (isis) ያሉ ጠርዘኞችን በስውር መደገፍ፣ ኢስላማዊ ሃገራትን ማፈራረስና ሙስሊሞችን በገዛ ቀያቸው መጨፍጨፍ እንዲሁም ፀረ ኢስላም ፖሊሲ የሚያራምዱ አምባገነን ሃይላትን በፀረ ሽብር ዘመቻ ስም ያልተገደበ ድጋፍ ማድረግ አማራጭ ፖሊሲያቸው ሆኖ በገሃድ እየታየ ነው። “ልፋ ያለው በህልሙ ዳውላ ይሸከማል” እንዲሉ መስሏቸው እንጂ የኢስላም ግስጋሴን ምድራዊ ሃይል አይገታውም። ምክንያቱም ከላይ የተገባ መለኮታዊ ቃል አለና። { یُرِیدُونَ لِیُطۡفِـُٔوا۟ نُورَ ٱللَّهِ بِأَفۡوَ ٰ⁠هِهِمۡ وَٱللَّهُ مُتِمُّ نُورِهِۦ وَلَوۡ كَرِهَ ٱلۡكَـٰفِرُونَ } “የአላህን ብርሃን በአፎቻቸው ሊያጠፉ ይሻሉ። አላህም ከሃዲዎቹ ቢጠሉም እንኳ ብርሃኑን ገላጭ ነው።” [አሶፍ፡ 8] IbnuMunewor https://t.me/ibnukedir
Show all...
አግራሞቴን በብዕር 🔰 ሶብር ያስፈልጋል ከእኛ የሚጠበቀው በመልካም እሳቤ (ንያ) ጥረት ማድረግ ነው። ጥረታችንን እጥፍ ድርብ አድርጎ ወደ ስኬት መቀየሩ የአላህ ነው! ► ለመልካም ጥረታችን ምንዳውን የሚመነዳንም (አጅሩን የሚከፍለንም) አላህ ነው። ⭕️ ስለዚህ ነገሮች ምንም ያህል ቢከብዱን፣ ሰዎች ባይረዱን፣ ሰዎች ስለእኛ የማይሆን ነገር ቢያስቡም...... ሶብር ያስፈልገናል ማለት ነው! ► ጥረታችን፣ ልፋታችንን አላህ በእዝነቱ በብዙ እጥፍ አባዝቶ አጅሩን የሚሰጠን እሱ (አላህ) ነውና ተስፋ አንቆርጥም። ► የምንሰራው ነገር ለአላህ ብለን እስከሆነ ድረስ ተስፋም መቁረጥም አይገባንም። ❌ ተስፋ የሚቆርጡ ደካሞች ብቻ ናቸው❗️ ወድቆ የሚነሳ...... ወድቆ ከማያውቅ እጅግ በጣም ጠንካራ ነው❗️ ▲ ስለዚህ መውደቅን ፍራቻ « መሞከርን አንፍራ» !! ተስፋ አንቁረጥ❗️ ወንድማችሁ:- ረሻድ ኢብኑ ሙዘሚል Telegram: t.me/SharpSwords1 Tiktok: tiktok.com/@sharpswords1 YouTube: youtube.com/@SharpSwords1 Instagram: Instagram.com/sharp_swords1 Ummalif: ummalife.com/ReshadMuzemil
Show all...
View Of Al Baqi Cemetery During Rain At Madinah Al Munawwarah !
Show all...
ለጎደኛህና ለጎረቤትህ ጥሩ ወዳጅ ሁን! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿خيرُ الأصحابِ عندَ اللهِ خيرُكم لصاحبِه، وخيرُ الجيرانِ عندَ اللهِ خيرُكم لجارِه﴾ “አላህ ዘንድ መልካም ጎደኛ ማለት ለጎደኛው መልካም የሆነው ነው። አላህ ዘንድ መልካም ጎረቤት ማለት ለጎረቤቱ መልካም የሆነው ነው።” 📚 ሶሂህ አልጃሚ: 3270
Show all...