en
Feedback
ICS DIGITAL INVEA

ICS DIGITAL INVEA

Open in Telegram

✅ Online Service #ፓስፖርት ቀጠሮ ማስያዝ ለምትፈልጉ በሙሉ። ☞አዲስ ፖስፖርት አመልካቾች/New Passport ☞ ፖስፖርት ለማደስ/Expired Passport

Show more
1 932
Subscribers
No data24 hours
-67 days
-2730 days
Posts Archive
ለፓስፖርት እርማት መሟላት ያለባቸው ሰነዶች የፓስፖርትዎን እድሜ፣የትውልድ ቦታ፣ ፎቶግራፍ፣ፊደል ለማስተካከል መሟላት ያለባቸው - ኦርጅናል ፓስፖርት (ፓስፖርቱ የጠፋ ከሆነ የፖሊስ ማስረጃ) - የልደ
ለፓስፖርት እርማት መሟላት ያለባቸው ሰነዶች የፓስፖርትዎን እድሜ፣የትውልድ ቦታ፣ ፎቶግራፍ፣ፊደል ለማስተካከል መሟላት ያለባቸው - ኦርጅናል ፓስፖርት (ፓስፖርቱ የጠፋ ከሆነ የፖሊስ ማስረጃ) - የልደት ምስክር ወረቀት - አንድ ጉርድ ፎቶግራፍ የፓስፖርትዎን ሙሉ ስም ለመቀየር - የፍርድ ቤት ውሳኔ - ኦርጅናል ፓስፖርት (ፓስፖርቱ የጠፋ ከሆነ የፖሊስ ማስረጃ) - የታደሰ የቀበሌ መታወቂያ - አንድ ጉርድ ፎቶግራፍ ከላይ የተጠቀሱትን ሰነዶች አሟልተው በኦንላይን www.ethiopianpassportservices.gov.et በመመዝገብ 3ሰዓት ሳያልፍ በመረጡት ክፍያ አማረጭ ክፍያ በመፈፀም የቀጠሮ ወረቀት ፕሪንት አውት በማድረግ ፓስፖርትዎን በመቀበያ ቀን( delivery date) ያመለከቱበት ኢሚግሬሽን ቅርንጫፍ ከላይ የተጠቀሱትን ሰነዶች ይዞ በአካል ቀርቦ የሚስተካከልልዎት መሆኑን እንገልፃለን፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት —— Telegram: https://t.me/ethiopia_passportservice https://t.me/Icsofficialservice www.facebook.com/ethiservice

መስከረም 03 2016.pdf2.80 MB

ከመስከረም 3/2017 ዓ.ም ጀምሮ ፓስፖርት የምትወስዱ ደንበኞቻችን ከዚህ በታች ሙሉ ስም ዝርዝር የለቀቅን እና በ 7876 አጭር የፅሁፍ መልዕክት የላክን ሲሆን በስም መነሻ ፊደላችሁ ቀን ብቻ ከሰኞ
ከመስከረም 3/2017 ዓ.ም ጀምሮ ፓስፖርት የምትወስዱ ደንበኞቻችን ከዚህ በታች ሙሉ ስም ዝርዝር የለቀቅን እና በ 7876 አጭር የፅሁፍ መልዕክት የላክን ሲሆን በስም መነሻ ፊደላችሁ ቀን ብቻ ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 3:00-09:00 ሰዓት ቅዳሜ ከጠዋቱ 3:00-6:30 ሰዓት ጎተራ በሚገኘው ኢሚግሬሽን ቢሮ በመገኘት  ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት —— Telegram:- https://t.me/Icsofficialservice https://t.me/ethiopia_passportservice Facebook:- www.facebook.com/ethiservice

05 ጳጉሜ፣ 2016.pdf3.23 MB

ከመስከረም 2/2017 ዓ.ም ጀምሮ ፓስፖርት የምትወስዱ ደንበኞቻችን ከዚህ በታች ሙሉ ስም ዝርዝር የለቀቅን እና በ 7876 አጭር የፅሁፍ መልዕክት የላክን ሲሆን በስም መነሻ ፊደላችሁ ቀን ብቻ ከሰኞ
ከመስከረም 2/2017 ዓ.ም ጀምሮ ፓስፖርት የምትወስዱ ደንበኞቻችን ከዚህ በታች ሙሉ ስም ዝርዝር የለቀቅን እና በ 7876 አጭር የፅሁፍ መልዕክት የላክን ሲሆን በስም መነሻ ፊደላችሁ ቀን ብቻ ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 3:00-09:00 ሰዓት ቅዳሜ ከጠዋቱ 3:00-6:30 ሰዓት ጎተራ በሚገኘው ኢሚግሬሽን ቢሮ በመገኘት  ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት —— Telegram: https://t.me/Icsofficialservice https://t.me/ethiopia_passportservice Facebook: www.facebook.com/ethiservice

የመጨረሻ ጥሪ ለአዲስ አበባ አመልካቾች አዲስ ፓስፖርት አመልክታችሁ አሻራና ፎቶ ሰጥታችሁ በቀጠሮ ቀናችሁ ያልደረሰላችሁ ደንበኞቻችን እሁድ እሁድ መጣችሁ እንድትስተናገዱ በተደጋጋሚ ጥሪ ማስተላለፋችን
የመጨረሻ ጥሪ ለአዲስ አበባ አመልካቾች አዲስ ፓስፖርት አመልክታችሁ አሻራና ፎቶ ሰጥታችሁ በቀጠሮ ቀናችሁ ያልደረሰላችሁ ደንበኞቻችን እሁድ እሁድ መጣችሁ እንድትስተናገዱ በተደጋጋሚ ጥሪ ማስተላለፋችን ይታወሳል፧ ነገር ግን አገልግሎቱን ለማግኘት ብዙ ደንበኞች በስራ ቀናት በመምጣት ላይ ስላላችሁ ለመጨረሻ ጊዜ የፊታችን እሁድ ጳጉሜ 3/2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 - 8:00 ሰዓት የአመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት፣  የልደት የምስክር ወረቀትና መታወቂያችሁን በመያዝ ኢሚግሬሽን ዋና ቢሮ በአካል በመምጣት እንድትስተናገዱ በጥብቅ እናሳስባለን። —————— የክልሎችን ፕሮግራም ወደፊት የምናሳውቅ ይሆናል። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት —— Telegram: https://t.me/Icsofficialservicehttps://t.me/ethiopia_passportservice Facebook: www.facebook.com/ethiservice

ጅማ፣ ባህር ዳር እና ሀዋሳ ፓስፖርታችሁን የምትወስዱ ደንበኞቻችን ጽ/ቤቶቹ በሚያወጡት ኘሮግራም መሰረት በመገኘት ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያ
ጅማ፣ ባህር ዳር እና ሀዋሳ ፓስፖርታችሁን የምትወስዱ ደንበኞቻችን ጽ/ቤቶቹ በሚያወጡት ኘሮግራም መሰረት በመገኘት ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት —— #Telegram #Facebook #Tiktok https://t.me/Digitalinveaics https://t.me/Icsofficialservice https://t.me/ethiopia_passportservice https://www.facebook.com/ethiservice https://vm.tiktok.com/ZM622h9yg/

7ኛው ሲቪል ምዝገባና ቫይታል ስታቲስቲክስ ቀን አከባበርን አስመልክቶ የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት —— Telegram: https://t.me/Icsofficialservice
+1
7ኛው ሲቪል ምዝገባና ቫይታል ስታቲስቲክስ ቀን አከባበርን አስመልክቶ የተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት —— Telegram: https://t.me/Icsofficialservice https://t.me/ethiopia_passportservice Facebook: https://www.facebook.com/ethiservice

የተከበራችሁ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ተከታታዮችን የሲቪል ምዝገባ እና ቫይታል ስታቲስቲክስ ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ7ኛ ጊዜ “Strengthening the linkage of civil registration and vital statistics to legal identity systems through digitalization for enhanced inclusion” በሚል መሪ ቃል በሐዋሳ ከተማ ከነሐሴ 25-26/2016 ዓ.ም በድምቀት ይከበራል፡፡  የሲቪልና ምዝገባ እና ቫይታል ስታቲስቲክስ መረጃ አስመልክተን በተከታታይ እያቀረብን ሲሆን ዛሬ የሲቪል ምዝገባና ቫይታል ስታቲስቲክስ ግለሰብን ከመንግስት አስተዳደር ጋር እንዴት እንደሚያገናኝ እናያለን። የአንድ ሀገር መንግስት ህዝቡን የሚስተዳድርበት አስተዳራዊ ስርዓት በየደረጃው በመዘርጋት ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት ለመስጠት በተለያየ መንገዶች ከህዝቡ ጋር ይገናኛል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ መንግስት በሚሰጣው የተለያዩ አገልግሎት ከግለሰቦች በቀጥታ ሊገናኙ የሚችሉበት አንዱ መንገድ ህጋዊና ግለሰባዊ የሲቪል ምዝገባ እና ቫይታል ስታቲስቲክስ (ልደት፣ሞት፣ጋብቻ፣ ፍቺ፣ ጉዲፈቻ) መረጃዎች አማካኝነት ነው፡፡ በአንድ ሀገር አግባባዊ የሲቪል ምዝገባ እና ቫይታል ስታቲስቲክስ አሰራር አማካኝነት ሰዎች ከልደት ጀምሮ እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ በክብር መዝገብ ሰነድ ተመዝግበው በመንግስት ደረጃ እንዲታወቁ ይደረጋል፡፡ የአንድ አካባቢ ማህበረሰብ በመንግስትና በግለሰቦች እጅ በሚገኝ ህጋዊ የማንነት የሰነድ ማስረጃ አማካኝነት ያለ ሶስተኛ ወገን ምስክርነት በቀጥታ ከመንግስት የህግና አስተዳደር አገልግሎት መስጫ ተቋማት ጋር በመገናኘት አገልግሎት ያገኛል፡፡ በዚህ ረገድ በኢኮኖሚ በበለፀጉ ሀገሮች የሲቪል ምዝገባ እና ቫይታል ስታቲስቲክስ ስርዓት አማካኝነት መንግስት ዜጎቹን በግለሰብ ደረጃ ከልደት እስከ ዕለተ ሞታቸው ድረስ ዕለታዊ የአኗኗራቸውን ሁኔታ በመከታተል ለችግሮቻቸው አማራጭ የመፍትሄ ሃሳቦችን ያመነጫል፣ ይተገብራልም፡፡ ከሲቪል ምዝገባ አንዱ የሆነው የልደት ኩነትን ምዝገባ ስንመለከት የአንድ ሰው ማንነት ከቤተሰቡ ጀምሮ በመንግስት የሚለየው በስሙ ነው፡፡ ሰዎች በቤተሰባቸው የተሰጣቸው ስም በማናቸውም ጊዜ በማያጠራጥር መልኩ እንዲታወቅና ህጋዊ እንዲሆን በመንግስት ሰነድ ሊመዘገብ ይገባል፡፡ ይኸም የሚሆነው በልደት ምዝገባ ከመለያ ስም በተጨማሪ የልደት ትክክለኛ ቀን፣ ልደቱ የተከሰተበት ቦታ፣ ዜግነት እንዲሁም የወላጆችን ማንነት የሚያረጋግጡ መሰረታዊና ህጋዊ መረጃዎችን እንደተወለደ እንዲኖሩት ያስችላል፡፡ የልደት መመዝገብ ግለሰቦች በማህበረሰብ አባልነት ከየአካባቢው የመንግስት አካል ማህበራዊና አስተዳደራዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት የሚያስችላቸው ህጋዊ መረጃ ባለቤት የሚያደርግ ህጋዊ ሰነድ ነው፡፡ በሌላ በኩል ህፃናት እንደተወለዱ መንግስት ባዘጋጀው የልደት የክብር መዝገብ በክብር መዝገብ ሹም ሲመዘገቡ መንግስት የህፃናቱን መወለድ በክብር መዝገብ አማካኝነት ስለሚያውቅ ህፃናቱ እድሜአቸውን ተከትሎ የሚያስፈልጋቸውን የጤናና የትምህርት ፍላጎት አስቀድሞ ለማቀድ መነሻ የሆነውን መሰረታዊ መረጃ ያስገኝለታል፡፡ ይኸም አሰራር ማህበረሰቦችን አልፎም ግለሰቦችን ከመንግስት ዕቅዶችና አተገባበሮች ጋር በማገናኘት የማስፈጸም አቅምን ከማጎልበቱም በላይ የመንግስትና ህዝብ ትስስር በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሰረተ ስለሚያደርግ ህዝብ በመንግስት አስተዳደር የሚሰጡ አገልግሎቶች ላይ አመኔታ እንዲኖረው በማድረግ በኩል ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት —— Telegram: https://t.me/Icsofficialservice Facebook: https://www.facebook.com/ethiservice

photo content

ጅማ፣ ባህር ዳር፣ ጋምቤላ፣ ሰመራ፣ አዳማ እና ሀዋሳ ፓስፖርታችሁን የምትወስዱ ደንበኞቻችን ጽ/ቤቶቹ በሚያወጡት ኘሮግራም መሰረት በመገኘት ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ወደ ተቋ
ጅማ፣ ባህር ዳር፣ ጋምቤላ፣ ሰመራ፣ አዳማ እና ሀዋሳ ፓስፖርታችሁን የምትወስዱ ደንበኞቻችን ጽ/ቤቶቹ በሚያወጡት ኘሮግራም መሰረት በመገኘት ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት —— Telegram: https://t.me/Icsofficialservice https://t.me/ethiopia_passportservice https://www.facebook.com/ethiservice https://vm.tiktok.com/ZM622h9yg/

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትን የበለጠ ተደራሽ እና ምቹ ለማድረግ የፓስፖርት ማመልከቻ እና ሂደት ለአመልካቹ የመኖሪያ ቦታ ወይም የስራ ቦታ ቅርብ በሆኑ የኢሚግሬሽን እና የዜግነት ጽሕፈት ቤቶች
የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎትን የበለጠ ተደራሽ እና ምቹ ለማድረግ የፓስፖርት ማመልከቻ እና ሂደት ለአመልካቹ የመኖሪያ ቦታ ወይም የስራ ቦታ ቅርብ በሆኑ የኢሚግሬሽን እና የዜግነት ጽሕፈት ቤቶች ብቻ የተወሰነ ይሆናል። ለአመልካች የመኖሪያ ቦታ ወይም የስራ  ርቀው ላሉ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጽ/ቤቶች የሚቀርቡ ማመልከቻዎች እንደማይስተናገዱ ስናሳውቅ ከአክብሮት ጋር ነው። To make the services of the Immigration and Citizenship Service more accessible and convenient, passport application and processing will now be limited to the Immigration and Citizenship Offices closest to the applicant's residence or place of work. Please be advised that applications submitted to Immigration and Citizenship offices outside of an applicant's residence or designated area of work will not be processed. —— Telegram:https://t.me/Icsofficialservice Facebook: https://www.facebook.com/ethiservice

የተከበራችሁ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ተከታታዮችን የሲቪል ምዝገባ እና ቫይታል ስታቲስቲክስ ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ7ኛ ጊዜ “Strengthening the linkage of civil registration and vital statistics to legal identity systems through digitalization for enhanced inclusion” በሚል መሪ ቃል በሐዋሳ ከተማ ከነሐሴ 25-26/2016 ዓ.ም በድምቀት ይከበራል፡፡ የሲቪልና ምዝገባ እና ቫይታል ስታቲስቲክስ መረጃ አስመልክተን በተከታታይ እያቀረብን ሲሆን ዛሬ የወቅታዊና አስተማማኝ የሲቪል ምዝገባ እና ቫይታል ስታስቲክስ መረጃ በፍትህ አካላት ማስረጃ አቀራረብ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን እንዴት መቅረፍ እንደሚያስችል እናያለን። የዜጎችን ትክክለኛ መረጃ ከመያዝ አኳያ ከፍተኛ ትርጉም ካላቸው የመረጃ ምንጮች አንዱ የወሳኝ ኩነቶች መረጃ ነው፡፡ ይህም ምዝገባ ወጥ በሆነ የአሰራር ስርዓት በአገር ደረጃ ተግባራዊ ሲደረግ የሚገኙ መረጃዎች የህዝባችንን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል ቁልፍ የመረጃ ምንጭ ነው፡፡ በፍትህ አስተዳደሩ ስርዓት ቀልጣፋና ውጤታማ አሰራር እንዲኖር ለማድረግ ከምዝገባው የሚመነጩ የግለሰቦች መረጃዎች ለፍትህ ስርዓቱ የሚሰጠው ጠቀሜታ የጎላ ነው፡፡ በአገራችን የሲቪል ምዝገባና ቫይታል ስታቲስትክስ ምዝገባ ተግባራዊ ለማድረግ የሚያስችል የህግ ማዕቀፍ ከመውጣቱ በፊት በአግባቡ የተመዘገቡ ኩነቶች ባለመኖራቸው ፍርድ ቤቶችን ከሲቪል ምዝገባና ቫይታል ስታቲስትክስ ጋር ተያይዞ በሚነሱ ክርክሮች ላይ በቂና ታማኝ የሆነ የተመዘገበ መረጃ ስለማያገኙ የሚሠጡት ውሳኔ ፍትሐዊነት አጠራጣሪ የሚሆንበት ሁኔታ አለ፡፡ በዚህ ረገድ በፍርድ ቤቶች ልጅነትን፣ ወላጅነትን፣ እድሜን በማረጋገጥ፣ ስለጠፉ ሰዎች ለማረጋገጥ፣ ከመደፈር ጋር ተያያዥነት ያለውን ለማረጋገጥ፣ የወጣት አጥፊዎችን የእድሜ ክልል ለማረጋገጥ ወዘተ የልደት፣ የሞት፣ የጋብቻና የፍቺ ህጋዊ መረጃዎች አለመኖራቸው ትክክለኛ ፍትህ ከመስጠት አኳያ የሚታዩ ችግሮች ናቸው፡፡ ለአብነት በወጣትነት እድሜ ክልል ውስጥ የሚገኝ አንድን ግለሰብ በወንጀል ወይም በፍትሐብሔር ተጠያቂ ለማድረግ ወይም ላለማድረግ ግለሰቡ ወይም ግለሰቧ ለአካለ መጠን የደረሰ ወይም የደረሰች ስለመሆኑ ወይም መሆኗ ለማረጋገጥ በቂና አሳማኝ ማስረጃ ማግኘት አይቻልም ነበር፡፡ በዚህ ምክንያትም ፍርድ ቤቶችና ሌሎች የፍትህ አካላት የሲቪል ምዝገባና ቫይታል ስታቲስትክስ ዙሪያ የሚቀርቡትን አቤቱታዎችና ክርክሮች እንደ ልደት፣ ጋብቻ፣ ፍቺና ሞት ለማረጋገጥ አላስፈላጊ ጊዜና ገንዘብ አጥፍተው በሰው ምስክር ወይም ከሌሎች ተቋማት በሚቀርቡላቸው አስተማማኝ ባልሆኑ ማስረጃዎች ላይ በመመስረት ለማረጋገጥ ይገደዳሉ፡፡ ይህም ሆኖ ግን በዚህ መልኩ የሚገኙ ማስረጃዎች አሳማኝ ላይሆኑ ይችላሉ፡፡ ይህም አሰራር በፍትህ መዘግየትና ትክክለኛ ፍትህን ለመስጠት የማስረጃ አቀራረብና የውሳኔ አሰጣጥ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ ይኖረዋል፡፡ ስለሆነም የሲቪል ምዝገባና ቫይታል ስታቲስትክስ ምዝገባ አሰራር የሚገኙ ግለሰባዊና ማህበራዊ መረጃዎች በሌላ በማነኛውም የምዝገባ ሥርዓት ሊገኙ የማይችሉ ህጋዊ ሰነዶች ከመሆናቸውም በላይ ኩነቶቹ እንደተከሰቱ አንድ ጊዜ በአግባባዊ የአመዘጋገብ ሥርዓት ከተመዘገቡ ሌላ ተጨማሪ መረጃ መሰብስብ ሳያስፈልግ በፍትህ አካላት ማስረጃ አቀራረብና ውሳኔ አሰጣጥ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ ያስችላል፡፡ https://t.me/Icsofficialservice https://t.me/ethiopia_passportservice https://t.me/Ics_ethiopiaservice https://www.facebook.com/ethiservice

photo content

በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ 550/2024 መሰረት ለመደበኛ፣ ለአስቸኳይ፣ ለእድሳት፤ ለጠፋ እና እርማት ፓስፖርት አገልግሎቶች ከነሃሴ 1 ጀምሮ  2016 ዓ/ም ተግባራዊ የሚሆን የዋጋ ማሻሻ
+2
በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ 550/2024 መሰረት ለመደበኛ፣ ለአስቸኳይ፣ ለእድሳት፤ ለጠፋ እና እርማት ፓስፖርት አገልግሎቶች ከነሃሴ 1 ጀምሮ  2016 ዓ/ም ተግባራዊ የሚሆን የዋጋ ማሻሻያ ክፍያ ዝርዝር ። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ❇️❇️❇️@IcsService❇️❇️❇️ ብራንቾቻችን ከነዚህ ወጪ የምንናስፋፋ ይሆናል። <<<<<<<<<<👇>>>>>>>>>> ❇️Super Telegram Channel ❇️ https://t.me/Icsofficialservice ☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️              Addis Ababa t.me/ethiopia_passportservice            👉DIGITAL invea https://t.me/Digitalinveaics              👉Adama https://t.me/AdamaIcs                👉Hawassa https://t.me/Hawassaics              👉Mekelle https://t.me/Mekelleics              👉Jimma https://t.me/Jimmaics               👉Jijiga https://t.me/Jigjigaics              👉Bahirdar https://t.me/BahirdarIcs              👉Diredawa https://t.me/Diredawaics              👉Semera https://t.me/SamaraIcs           👉GambellaI https://t.me/Gambellaics              👉Assosa   https://t.me/Assosaics             👉Hossana        t.me/Hossanaics

የተከበራችሁ የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት የማህበራዊ ሚዲያዎቻችን ተከታታዮችን የሲቪል እና ቫይታል ስታቲስቲክስ ምዝገባ ቀን በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ7ኛ ጊዜ “Strengthening the linkage of civil registration and vital statistics to legal identity systems through digitalization for enhanced inclusion” በሚል መሪ ቃል በሐዋሳ ከተማ ከነሐሴ 25-26/2016 ዓ.ም በድምቀት ይከበራል፡፡ የሲቪልና ቫይታል ምዝገባ መረጃ አስመልክተን በተከታታይ እያቀረብን ሲሆን ዛሬ የወቅታዊና አስተማማኝ የሲቪል እና ቫይታል ስታስቲክስ ምዝገባ መረጃ ለዘላቂ ልማትና ድህነት ቅነሳ ያለውን አስተዋፅኦ እናያለን። በኢትዮጵያ የሲቪል እና ቫይታል ስታስቲክስ ምዝገባ ስርአት መገንባት በዋነኝነት የሚኖረው ጠቀሜታ አገሪቱ ከልማዳዊ አሰራር የተላቀቀ የማንነት መለያ የመረጃ ስርአት እንዲኖራት ያስችላል፡፡ ስም፣ ዜግነት፣ ዕድሜ፣ የነዋሪነት መታወቂያ ስርዓት፣ የፓስፖርት ዝግጅት ፣ የቤተሰብ መዝገብ ማደራጀት፣ የአገር ደህንነት መረጃዎች በተደራጀ መልኩ መያዝ ሲጀመር በየዘርፉ መልካም አስተዳደርን እንዲሁም የተሟላና የተቀላጠፈ አሰራር እንዲኖር የሚያበረክተው አስተዋፅኦ የላቀ ነው፡፡ በመሆኑም ዜጎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታዎች ፍትሃዊ በሆነ መልኩ እንዲያገኙ ያስችላል፡፡ አገሪቱ በምታደርጋቸው የልማት እንቅስቃሴዎች የተማረ፣ ብቁ እንዲሁም ጤናማ የሰው ሃይል ያስፈልጋታል፡፡ ለዚህም የህዝብ ጤና አገልግሎት ከልደት ጀምሮ የተያዘ የተሟላ የማንነት መረጃን ማደራጀት ይጠይቃል፡፡ የህፃናት የበሽታ መከላከልና የጤና እንክብካቤ አገልግሎት እንደሚሰጥ የታወቀ ነው፡፡ ለዚህም ሁሉንም የአገሪቱን ክልል እና የህብረተሰብ ክፍል ያካተተ የልደት ምዝገባ መኖር ህፃናትን ከመወለድ ጀምሮ ማንነታቸውን በማወቅ ዕድገታቸውን የተከተለ የክትባትና ሌሎች የጤና ክትትልና አገልግሎት የመስጠት ተግባራትን በአስተማማኝ መረጃ ላይ በመመስረት ለማከናወን ያስችላል፡፡ በተመሳሳይ ከወሊድ በኋላ እናትየው ከወለደችው ህፃን ጋር የተቀናጀ የጤና አገልግሎት በአግባቡ ተጠቃሚ ለመሆን ሁሉን አቀፍ የልደት ምዝገባ መኖር አገልግሎቱን ቀልጣፋና ተጠያቂነት የሰፈነበት እንዲሆን ያስችለዋል፡፡ ስለሆነም በጤናው ዙሪያ የሚሰሩ ስራዎችን ወቅታዊና አስተማማኝ መረጃዎች ሊገኝ የሚችለው ቋሚ፣ቀጣይ እና አስገዳጅ የልደት ምዝገባ ሥርዓት ሲዘረጋና የልደት ስታትስቲክስ በቀጣይነት ሲጠናቀር ነው፡፡ የተሟላ የልደት ምዝገባ ሥርዓት በሌለበት ከክልል መስተዳድሮች ላሉ የአስተዳደር ዕርከኖች ዓመታዊ የልደት ምጣኔ ስታቲስቲክስ ማዘጋጀትና ማቅረብ አይቻልም፡፡ በመሆኑም በዝቅተኛው የአስተዳደር ዕርከኖች በየሴክተሩ የሚዘጋጁ ዕቅዶችንና አፈፃፀማቸውን በአስተማማኝ የስነ-ህዝብ መረጃ ላይ በመመስረት ለመከታተልና ለመገምገም አይቻልም፡፡ ስለሆነም በወቅታዊና አስተማማኝ የስነ-ህዝብ ስታቲስቲክስ መረጃ ላይ በመመስረት የልማት ሥራዎቻቸውን ለመምራት፣ ለመከታተልና ለመገምገም በአግባባዊ አሰራር የተደራጀ የልደትና የሞት ምዝገባ ሥርዓት በመዘርጋት እና ወቅታዊ መረጃዎችን ማሰባሰብ እና ጥቅም ላይ እንዲውሉ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ በአጠቃላይ አገራችን ለጀመረችው የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ መሰረት የሆኑትን ሰብአዊ መብቶች በአግባባዊ መረጃ ስርዓት ለመደገፍና ለማስፈጸም እንዲሁም የዘለቄታ ልማትና የድህነት ቅነሳ ስትራቴጂ ተግባራዊ ለማድረግ በአገሪቱ እስከ ዝቅተኛው የአስተዳደር ዕርከን ወቅታዊ፣ አስተማማኝ እና በቋሚነት የስነ-ህዝብ መረጃዎችን ከማቅረብ አንጻር የሲቪል እና ቫይታል ስታቲስቲክስ ምዝገባ ስርዓት ጉልህ ሚና ይኖረዋል፡፡ —— Telegram: https://t.me/ethiopia_passportservice https://t.me/Icsofficialservice Facebook:https://www.facebook.com/ethiservice

photo content

በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ 550/2024 መሰረት ለመደበኛ፣ ለአስቸኳይ፣ ለእድሳት፤ ለጠፋ እና እርማት ፓስፖርት አገልግሎቶች ከነሃሴ 1 ጀምሮ 2016 ዓ/ም ተግባራዊ የሚሆን የዋጋ ማሻሻያ ክፍያ
+2
በሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ 550/2024 መሰረት ለመደበኛ፣ ለአስቸኳይ፣ ለእድሳት፤ ለጠፋ እና እርማት ፓስፖርት አገልግሎቶች ከነሃሴ 1 ጀምሮ 2016 ዓ/ም ተግባራዊ የሚሆን የዋጋ ማሻሻያ ክፍያ ዝርዝር ሙሉ ደንቡን ከድረ ገፃችን ማግኘት ይችላሉ። አማርኛ🇪🇹: http://ics.gov.et/download/328/?tmstv=1722940201 —የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት Sirrefama Gatii Tajaajilaa Passporti Guuyyaa Hagayaa Irraa kaasee 1/2016 Idilee fi Ariifachisaa Check out our Ordinary Passport Price List for New, Urgent, Renewal, Lost, and Correction services. Effective August 6, 2024, per Council of Ministers Regulation 550/2024. Download the full regulation from our website English 🇺🇸: http://ics.gov.et/download/324/?tmstv=1722940149 —Immigration and Citizenship Service

ሐምሌ 30.pdf3.63 MB

ከሐምሌ 30/2016 ዓ.ም ጀምሮ ፓስፖርት የምትወስዱ ደንበኞቻችን ከዚህ በታች ሙሉ ስም ዝርዝር የለቀቅን እና በ 7876 አጭር የፅሁፍ መልዕክት የላክን ሲሆን በስም መነሻ ፊደላችሁ ቀን ብቻ ከሰኞ
ከሐምሌ 30/2016 ዓ.ም ጀምሮ ፓስፖርት የምትወስዱ ደንበኞቻችን ከዚህ በታች ሙሉ ስም ዝርዝር የለቀቅን እና በ 7876 አጭር የፅሁፍ መልዕክት የላክን ሲሆን በስም መነሻ ፊደላችሁ ቀን ብቻ ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 3:00-09:00 ሰዓት ቅዳሜ ከጠዋቱ 3:00-6:30 ሰዓት ጎተራ በሚገኘው ኢሚግሬሽን ቢሮ በመገኘት  ፓስፖርታችሁን መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እየገለፅን ወደ ተቋማችን ስትመጡ ኦንላይን ያመለከታችሁበትን ፕሪንት አውት ይዛችሁ እንድትመጡ እናሳስባለን። የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት —— Telegram: https://t.me/Icsofficialservice Facebook: https://www.facebook.com/ethiservice