en
Feedback
ልዩ ዜና

ልዩ ዜና

Open in Telegram

ድል ለኢትዮጵያ ጥቆማ‼️ በዚህ ቻናል ወቅታዊ፣ታማኝ እና ፈጣን መረጃ ያገኛሉ፣በውሸት አካውንት እንዳትሸወዱ‼️‼️

Show more
4 007
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
photo content

ዲፕሎማሲያችን❓❓ ቻይና ከሶማሊያ ጎን እንደምትቆም አሳወቀች‼️ ቻይና የሶማሊያን ብሄራዊ አንድነት: ግዛታዊ ሉዋላዊነት መከበር ይገባዋል ስትል ከኢትዮጵያ መንግስት አካሄድ በተቃራኒው መሆኗን አስታውቃለች። ================ ለፈጣን ወቅታዊ መረጃዎች ቻናላችንን join በማድረግ ይከታተሉ👇👇

photo content

ከዚህ ቀደም በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ሲሰጡ ከነበሩ የትምህርት አይነቶች መካከል ሥነ ምግባርና የሥነ ዜጋ ትምህርት (Civics and Ethical Education) በዘንድሮው ዓመት 2016 ዓ/ም አይሰጥም‼️ በሚኒስቴሩ የሥርዓተ ትምህርት ማበልፀጊያ መሪ ሥራ አስፈፃሚ ቴዎድሮስ ሸዋርገጥ (ዶ/ር) እንዳሉት  በተያዘው በጀት ዓመት የ2ኛ ደረጃ ትምህርት በአዲሱ ሥርዓተ-ትምህርት መሠረት እየተተገበረ ነው፡፡ በዚህ መሠረትም በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶች ተለይተው የመማር ማስተማር ሒደቱ እየተካሄደ ይገኛል ነው ያሉት፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም በ2016 ዓ.ም በ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና የሚሰጡ የትምህርት ዓይነቶችን መወሰን ማስፈለጉን አስረድተዋል፡፡ ይህን ተከትሎም በ2016 ዓ.ም ለ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሁለቱም ዘርፎች ስድስት ስድስት የትምህርት ዓይነቶች እንዲሰጡ መወሰኑን ተናግረዋል። በዚህ መሰረትም የተፈጥሮ ሣይንስ ተማሪዎች እንግሊዝኛ ሒሳብ ፊዚክስ ኬሚስትሪ ባዮሎጂ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት እንዲወስዱ መወሰኑን ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ የማህበራዊ ሣይንስ ተማሪዎች እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ታሪክ፣ ጂኦግራፊ፣ ኢኮኖሚክስ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት የሚፈተኑ ይሆናል ነው ያሉት፡፡ የኢኮኖሚክስ ፈተና ለ2016 ዓ.ም ከ12ኛ ክፍል ብቻ የሚዘጋጅ መሆኑን ጠቁመው ÷ሌሎች የትምህርት ዓይነቶች ከ9 እስከ 11ኛ ክፍሎች በነባሩ ሥርዓተ ትምህርት እንዲሁም የ12ኛ ክፍል በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት እንደሚሆን ተናግረዋል፡፡ የሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች ትምህርት ቢሮዎችም የፈተና አሰጣጡን በተመለከተ ለተማሪዎች፣ ለወላጆች፣ ለመምህራን እና ለትምህርት ማህበረሰቡ ቅድመ ዝግጅት እንዲያደርጉ ከወዲሁ እንዲያሳውቁ አመላክተዋል፡፡

photo content
+1

አዲሱ የመሬት ይዞታ አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ 18 ዓመት ያልሞላቸውን ልጆች የመሬት ባለቤት የሚያደርግ መሆኑ ተነገረ ሀገሪቱ ለደረሰችበት የዕድገት ደረጃ የማይመጥን እንዲሁም የዘመነ መረጃ አያያዝ ስርዓትን በመከተል ረገድ ክፍት አለበት የተባለዉ እና በ1997 ዓ.ም. የወጣዉ የመሬት ይዞታ አስተዳደርና አጠቃቀም አዋጅ በአዲስ ሊተካ መሆኑ ተነግሯል። ነባሩን አዋጅ የሚተካዉ ይህ ረቂቅ አዋጅ ከመሬት ጋር በተያያዘ በየጊዜው ለሚነሱ ክሶች መፍትሔ እንደሚሰጥ ታምኖበታል። በአዲሱ ረቂቅ አዋጅ ላይ የወል "መሬትን የመጠቀምን፣ በጋራና በኩታ ገጠም የማረስንና የማከራየትን እንዲሁም ከባለሀብት ጋር በጋራ በማልማት የመጠቀም፣ መሬቱን በዕዳ ዋስትና የማስያዝ፣ 18 አመት ያልሞላቸው ልጆች በውርስ ወይም በስጦታ መሬት እንዲያገኙ የሚያደርግ፣ የመሬት ክርክሮችን በሽምግልና መፍታት ካልተቻለ በመደበኛ ፍርድ ቤት ውሳኔ እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑ" ተነግሯል ። አሁን ላይ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የግብርና ጉዳዮች  ቋሚ ኮሚቴ የገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ረቂቅ አዋጅን ማዳበር የሚያስችል ግብኣት ለመሰብሰብ በክልል ከተሞች ዉይይት በማድረግ ላይ ይገኛል። አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ለአርሶና አርብቶ አደሩ እንዲሁም አርሶ አደሩ መሬትን የማከራየት፣ የመሬት ሰነድ አስይዞ የመበደርን መብትን የሚሰጥ፣ የሴቶችንና ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ፣ ሩቅ ያለን መሬት በአቅራቢያ ካለ መሬት ጋር በመለወጥ አልምቶ የመጠቀምን መብት እንደሚሰጥም ነው ካፒታል የዘገበው።

photo content

በአሶሳ ከተማ ሪፈር የሚጻፍላቸው ሕሙማን መንገድ ዝግ በመሆኑ ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑ ተሰማ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማ ወደ አዲስ አበባም ሆነ ወደ አጎራባች አካባቢዎች የሚወስደው መንገድ በፀጥታ ምክንያት ዝግ በመሆኑ፣ ለከፍተኛ ሕክምና ሪፈር የሚጻፍላቸው ሕሙማን ሕክምና ባለማግኘታቸው ሕይወታቸው እያለፈ መሆኑን የአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል አስታወቀ፡፡ ከአሶሳ ከተማ ተነስቶ ወደ መተከልና ኦሮሚያ ክልል የሚወስደው መንገድ በፀጥታ ችግር ምክንያት በመዘጋቱ ሕሙማን የከፋ ችግር ውስጥ መውደቃቸውን፣ የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሶፊያ አወት ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ከአጎራባች ሱዳን ፈልሰው የመጡ ስደተኞችና ምዕራብ ኦሮሚያ አካባቢ የሠፈሩ ዜጎች ሙሉ ለሙሉ የሕክምና አገልግሎት የሚያገኙት አሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል በመሆኑ፣ ሆስፒታሉ አገልግሎት ለመስጠት ከአቅሙ በላይ እንደሆነበት አስረድተዋል፡፡ ሆስፒታሉም ከፍተኛ የሆነ የሕክምና ግብዓት እጥረት እንዳለበት የገለጹት ሥራ አስኪያጇ፣ ሆስፒታሉ ወደ ሌላ ቦታ ሄደው ሕክምና እንዲያገኙ ሪፈር የሚጽፍላቸው ሕሙማን አቅም ያላቸው ብቻ የአየር ትራንስፖርት ተጠቅመው የሕክምና አገልግሎት እያገኙ ነው ብለዋል፡፡ በክልሉ አብዛኛውን ነዋሪ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ ያለ ሲሆን፣ ወደ አዲስ አበባ ከተማም ሆነ ወደ ሌሎች አጎራባች አካባቢዎች በአየር ትራንስፖርት ሄደው ለመታከም የገንዘብ ችግር ስለሚገጥማቸው ሞታቸውን የሚጠባበቁበት ሁኔታ መፈጠሩን አብራርተዋል፡፡ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ቁጥር አንድ ከሚባሉት ሆስፒታሎች ውስጥ ሆስፒታሉ አንዱ መሆኑን ገልጸው፣ ሆስፒታሉም በአሁኑ ወቅት በቀን ከ150 በላይ ለሆኑ ሕሙማን አገልግሎት እየሰጠ ነው፡፡ ‹‹ለሆስፒታሉ የሚቀርበው መድኃኒትና ሆስፒታሉ የሚሰጠው አገልግሎት ጭራሽ የማይመጣጠን ነው፤›› ያሉት ወ/ሮ ሶፊያ፣ በክልሉ በተፈጠረው የፀጥታ ችግር ምክንያት መድኃኒት እየቀረበ ያለው በአየር ትራንስፖርት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ በአየር ትራንስፖርት መድኃኒት ቢመጣም ቶሎ ቶሎ የሚያልቅ መሆኑን፣ መድኃኒት ለመግዛትም ሆነ ለመድኃኒት ማጓጓዣ ሆስፒታሉ ከፍተኛ ወጪ እያወጣ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ ሆስፒታሉ የቀዶ ጥገና፣ የማዋለድ፣ የዓይን ሕክምናና ሌሎች አገልግሎቶችን የሚሰጥ መሆኑን፣ ከዚህ በፊትም በክልሉ የፀጥታ ችግር ባልነበረበት ወቅት ሕሙማንን በፍጥነት በአምቡላንስ በማመላለስ አገልግሎት ይሰጥ እንደነበር አስረድተዋል፡፡ ይሁን እንጂ በፀጥታ ችግር ምክንያት አምቡላንሶች እንደ ልብ ተንቀሳቅሰው አገልግሎት እንደማይሰጡ፣ ከዚህ ቀደም አንድ አምቡላንስ በታጣቂ ኃይሎች መቃጠሉንና ውስጥ የነበሩ ሕሙማንና ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል፡፡

photo content

አይ ኤምኤፍ ለኬንያ አዲስ የ 941 ሚሊዮን ዶላር ብድር አፀደቀ አለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም  የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት የገንዘብ አቅምን ለማጠናከር ለኬንያ ከ941 ሚሊየን ዶላር በላይ አዲስ ብድር ሰጥቷል። አይ ኤም ኤፍ ረቡዕ እለት ባወጣው መግለጫ ላይ የስራ አስፈፃሚው ቦርድ 941.2 ሚሊዮን ዶላር ብድር ማፅደቁን እና ወዲያውኑ 624.5 ሚሊዮን ዶላር መክፈሉን አስታውቋል። በተለያዩ የብድር ተቋማት የሚከፈለው አጠቃላይ ክፍያ 2.6 ቢሊዮን ዶላር ገደማ እንደሚደርስም አክሏል። ኬንያ ሰፊ የዕዳ ጫና፣ የኑሮ ውድነት እና የገንዘብ ምንዛሪ ጨምሮ በርካታ ኢኮኖሚያዊ ተግዳሮቶችን እየታገለች እንደምትገኝ ተሰምቷል። መቀመጫውን በዋሽንግተን ያደረገው ኤጀንሲው የኬንያ ኢኮኖሚ እድገት በ2023 ከነበረው 5.1 በመቶ ዘንድሮ ወደ 5 በመቶ አካባቢ እንደሚገመት ትንበያዉን አስቀምጧል።

ከቀናት በፊት ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በየነ መንግሥታት ድርጅት (ኢጋድ) ጋር ግኙነት እንዳቋረጠ የገለፀው በጄነራል አብዱል ፈታህ አልቡርሃን የሚመራው የሱዳን መንግሥት ዛሬ ከኢጋድ አባልነት መውጣቱን አሳውቋል። የሱዳንን ብሔራዊ ጦር የሚመራው የሱዳን መንግሥት ኢጋድ በኡጋንዳ ኢንቴቤ አድርጎት በነበረው አስቸኳይ ስብሰባ የተፋላሚውን የፈጥኖ ደራሽ ኃይል አዛዥ በስብሰባው እንዲሳተፉ መጋበዙ ‘የሃገሪቱን ሉላዊነት ጥሷል’ በማለት ከኢጋድ ጋር ያለውን ግንኙነት አቋርጦ ነበር። ዛሬ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ባወጣው መግለጫ ከኢጋድ አባልነት ሀገሪቱ መውጣቷን ይፋ አድርጓል።

አትሌት ታደሰ ለሚ ከግድያ ሙከራ ተርፏል #Ethiopia | አትሌት ታደሰ ለሚ እሁድ ታህሳስ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ለጉዳይ ከወጣበት ስፍራ ወደ መኖሪያ ቤቱ ሲመለስ ከቀኑ 11:30 በሱሉልታ ከተማ
+3
አትሌት ታደሰ ለሚ ከግድያ ሙከራ ተርፏል #Ethiopia | አትሌት ታደሰ ለሚ እሁድ ታህሳስ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ለጉዳይ ከወጣበት ስፍራ ወደ መኖሪያ ቤቱ ሲመለስ ከቀኑ 11:30 በሱሉልታ ከተማ በተለምዶ አስር ኪሎ ተብሎ በሚጠራ አካባቢ የግድያ ሙከራ እንደተደረገበት ተገለፀ። አትሌቱ ሲያሽከርክር የነበረውን መኪና መንገድ ዘግተው፣ መኪናው ከመቱበት በኋላ የግድያ ሙከራ እንዳደረጉበት ተገልጿል። የግድያ ሙከራው በሚደረግበት ወቅት እንደ አጋጣሚ በአካባቢው የትራፊክ ፖሊሶዎች ደርሰው ሊታርፉት እንደቻሉ ተጠቁማል። የግድያ ሙከራ ሲያደርጉ የነበሩት አካላት የያዙትን መኪና ተራፊኮቹ የተመለኩት ቢሆንም ሊደረስባቸው ባለመቻሉ ለግዜው ማምለጣቸው ተነግርዋል። እንድ አትሌቱ አስታየት ከሆነ የግድያ ሙከራው ለአራተኛ ግዜ እንደተሞከረበት ጠቅሶ፣ በጫካ ልምምድ በሚያደርግበት ስፍራ በመምጣት የግድያ ሙከራውን ቢያደርጉም፣ አብረውት ልምምድ በሚሰሩ ጓደኞዎቹ አማካኝነት መትረፉን አስረድተዋል ። አትሌቱ ኢትዮጵያን በተለያዩ ሻምፒዮናዎች በ800 እና 1500 ሜትር መወከሉ ይታወሳል።

በአማራ ክልል አጣዬ፣ውጫሌ፣ውርጌሳ እና ኮምቦልቻ የኢንተርኔት አገልግሎት ተለቋል። ወልዲያ 2G እና 3G እየሰራ ነው። አዩዘሀበሻ

#ሶጌ ከትናንት በስቲያ አርብ ታህሳስ 19/2016 ዓ.ም በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ ካማሺ ዞን ቦሎ ጅጋንፎይ/ምዥጋ ወረዳ ሶጌ ከተማ ጠዋት ታጣቂዎች ወደ ከተማው በመዝለቅ ከፍተኛ ጥቃትና መድመት ማድረሳቸውን የወረዳው አስተዳደር ገልጿል። በጥቃቱ የ3 ሰዎች ህይወት አልፏል። በወረዳው የሚገኙ 2 ባንኮች (የአዋሽ ባንክ እና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ) መዘረፋቸውንም ገልጿል። ከዚህ በተጨማሪ የተለያዩ መጠን ያላቸው 8 ተሽከርካሪዎች መቃጠላቸውን አመልክቷል። በወረዳው የነበሩ ጸጥታ አስከባሪዎች ለግዳጅ ወደ ሌላ ስፋራ መንቀሳቀሳቸውን ተከትሎ ታጣቂዎቹ በቀላቀሉ ወደ ወረዳው በመግባት ጥቃት ማድረሳቸው ነው የተነገረው። በዕለቱ ለ3 ሰዓታት ያህል ከተማውን ተቆጣጥረው እንደነበርና በሶጌ ከተማ ውስጥ የሚገኙ አንድ ፖሊስ ጣቢያ መቃጠሉን፣ ሁለት ባንኮችም መዘረፋውንና ሌሎችም በርካታ የመስሪያ ቤት ንብረቶች መዘረፋቸውን ወረዳው አመልክቷል። በዛሬው እለት በከተማው መረጋጋት መስፈኑን ተከትሎ ከአካባቢው ሸሽተው የነበሩ ነዋሪዎች ሲመለሱ መዋሉ ተመላክቷል። ቃላቸውን የሰጡ የወረዳው ነዋሪዎች በዕለቱ ከፍተኛ የተኩስ ድምጽ ስለነበር አብዛኛው የከተማዋ ነዋሪ አካባቢውን ለቀው ሸሽተው እንደነበር ገልጸዋል፡፡ በወረዳው አንድ ፖሊስ ጣቢያ መቃጠሉንና የቁም እንስሳትን ጨምሮ የንብረት ዝርፍያ መፈጸሙን ነዋሪዎቹ አመልክተዋል፡፡ 5 ተሸከርካሪዎች በአንድ ስፋራ መቃጠሉን የገለጹ ሲሆን መጠናቸው ያልታወቀ ሌሎች የወረዳው ተሽከርካሪዎች በታጣቂዎች መወሰዱን አብራርተዋል፡፡ ጥቃቱን በመሸሽ ላይ የነበሩ 4 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን እንደሚያውቁም ጠቁመዋል፡፡ አርብ ዕለት በሶጌ ከተማ የደረሰውን ጥቃት በወረዳው አቅራቢያ ይንቀሳቀሳሉ ያሏቸው የሼኔ ታጣቂዎች መፈጸማቸውን የወረዳው አስተዳደር ገልጿል። በካማሺ ዞን ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ከክልሉ መንግስት ጋር የሰላም ስምምነት ላይ ከደረሱ ወዲህ በአካባቢው ሰላም መስፈኑን የክልሉ መንግስት ከዚህ ቀደም መግለፁ ይታወሳል። #ዶቼቨለ

ሰበር ዜና! ኢትዮጵያ የወደብ ባለቤት ሆነች **** ኢትዮጵያ የቀይ ባሕር በር ለማግኘት እና ለማልማት የሚያስችላትን ስምምነት ከሶማሊ ላንድ ጋር ፈፅማለች። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) እና የሶማሊ ላንድ ፕሬዚዳንት ሙሴ ባሂ ሁሉን አካታች የሆነውን የጋራ መግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል። በዚሁ መሠረት ለብዙ ዘመናት ወደብ አልባ ሆና የቆየችው ሀገራችን ከሶማሊ ላንድ ጋር ባደረገችው ስምምነት በሊዝ የወደብ ባለቤት መሆን ችላለች።