cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking ÂŤAccept allÂť, you agree to the use of cookies.

avatar

RemnantsOfGod|🌍| RoG👑📖

“በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።” — ዮሐንስ 15፥7

Show more
Advertising posts
264
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-430 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
= = = = = = =🕊🕊🕊= = = = = = = 🕊 እጅግ ውድ ሆኖ በገንዘብ የማይገዛ፤ በኮተታ ኮተት ብዛት የማይገኝ፤ ብዙዎች ለመቁጠር የሚያዳግት ገንዘብ ተከበው💵💰💸💴💰💸💵 ፤ሊገዙት ግን ያልቻሉት እና ፈፅሞም የማይችሉት፤በአማርኛ ፊደል ሶስት ሆኖ በቃል አንድ የሆነ፤ በውስጡ ግን በጣም ብ...ዙ ...ነገሮችን የያዘ በምድር ላይ ካሉ ወሳኝ እና ትልቅ ነገሮች አንዱ ብቻ ሳይሆን ዋነኛውም ጭምር ነው... ። 🕊 🕊 🕊 እጅግ ውድ ሆኖ 🤔 በየቀኑ በየዜናው መጀመሪያና እና መጨረሻ በሀገራችን ብቸኛው በነፃ የሚሰጡን ፤ ከየሰዉ አፍ የሚሰማ ተራ የሚመስል: ግን በምድር ለታደሉት ብቻ ፤በሰማይ ደግሞ ዋና መፍለቂያ እና መገኛው የሆነ: እሱ ባለበት. . . ድህነት፤ ረሀብ፤ስደት ፤ጦርነት ማይኖርበት :: አንድ መስሎ በውስጡ ግን ...ሀሴት፤ደስታ፤ የማይቋረጥ እረፍት... የያዘው እውቁና ትልቁ ነገር ሰላም እና ሰላም ብቻ ነው 🤔። * * * * * * * * * * * "ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም።ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።" _ዮሐንስ 14፥27 . . . ✍ 1/9/2016 ዓ.ም 🕊 🤗🙏
190Loading...
02
እግዚአብሔር የነገርን ምስጢር እና አደራረግ የሚገልጥ አምላክ ነው፡፡ ዳንኤል 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁹ የዚያን ጊዜም ምሥጢሩ በሌሊት ራእይ ለዳንኤል ተገለጠለት፤ ዳንኤልም የሰማይን አምላክ አመሰገነ። ²⁰ ዳንኤልም ተናገረ እንዲህም አለ፦ ጥበብና ኃይል ለእርሱ ነውና የእግዚአብሔር ስም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይባረክ፤ ²¹ ጊዜያትንና ዘመናትን ይለውጣል፤ ነገሥታትን ያፈልሳል፥ ነገሥታትንም ያስነሣል፤ ጥበብን ለጠቢባን እውቀትንም ለአስተዋዮች ይሰጣል። ²² የጠለቀውንና የተሠወረውን ይገልጣል፤ በጨለማ ያለውን ያውቃል፥ ብርሃንም ከእርሱ ጋር ነው። ²³ ጥበብንና ኃይልን የሰጠኸኝ፥ እኛም የለመንንህን ነገር አሁን ያስታወቅኸኝ፥ አንተ የአባቶቼ አምላክ ሆይ፥ የንጉሡን ነገር አስታውቀኸኛልና እገዛልሃለሁ አመሰግንህማለሁ። … ²⁸ ነገር ግን ምሥጢር የሚገልጥ አምላክ በሰማይ ውስጥ አለ፥ እርሱም በኋለኛው ዘመን የሚሆነውን ለንጉሡ ለናቡከደነፆር አስታውቆታል። በአልጋህ ላይ የሆነው ሕልምና የራስህ ራእይ ይህ ነው። … ³⁰ ነገር ግን ይህ ምሥጢር ለእኔ መገለጡ ፍቺው ለንጉሡ ይታወቅ ዘንድ፥ አንተም የልብህን አሳብ ታውቅ ዘንድ ነው እንጂ በዚህ ዓለም ካሉ ሰዎች ይልቅ በጥበብ ስለ በለጥሁ አይደለም።
260Loading...
03
https://youtu.be/WeNWdlspvbk?si=jWsEY3T_X7s5LsTN
221Loading...
04
Media files
170Loading...
05
የምታምነውን እወቅ | የእግዚአብሔር ባህርያት | ፓስተር አስፋው በቀለ |www.operationezra.com
320Loading...
06
ኢሳይያስ 51 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እናንተ ጽድቅን የምትከተሉ እግዚአብሔርንም የምትሹ፥ ስሙኝ፤ ከእርሱ የተቈረጣችሁበትን ድንጋይ ከእርሱም የተቈፈራችሁበትን ጕድጓድ ተመልከቱ። ² ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም፥ ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሳራ ተመልከቱ፤ አንድ ብቻውን በሆነ ጊዜ ጠራሁት፥ ባረክሁትም አበዛሁትም። ³ እግዚአብሔርም ጽዮንን ያጽናናል፤ በእርስዋም ባድማ የሆነውን ሁሉ ያጽናናል፥ ምድረ በዳዋንም እንደ ዔደን በረሀዋንም እንደ እግዚአብሔር ገነት ያደርጋል፤ ደስታና ተድላ ምስጋናና የዝማሬ ድምፅ ይገኝበታል። ⁴ ወገኔ ሆይ፥ አድምጠኝ፤ ሕዝቤ ሆይ፥ ስማኝ፤ ሕግ ከእኔ ይወጣልና ፍርዴም ለአሕዛብ ብርሃን ይሆናልና። ⁵ ጽድቄ ፈጥኖ ቀርቦአል፥ ማዳኔም ወጥቶአል፥ ክንዴም በአሕዛብ ላይ ይፈርዳል፤ ደሴቶች እኔን በመተማመን ይጠባበቃሉ፥ በክንዴም ይታመናሉ። ⁶ ዓይናችሁን ወደ ሰማይ አንሡ፥ ወደ ታችም ወደ ምድር ተመልከቱ፤ ሰማያት እንደ ጢስ በንነው ይጠፋሉ፥ ምድርም እንደ ልብስ ታረጃለች፥ የሚኖሩባትም እንዲሁ ይሞታሉ፤ ማዳኔ ግን ለዘላለም ይሆናል፥ ጽድቄም አይፈርስም። ⁷ ጽድቅን የምታውቁ ሕጌም በልባችሁ ያለ ሕዝብ ሆይ፥ ስሙኝ፤ የሰውን ተግዳሮት አትፍሩ፥ በስድባቸውም አትደንግጡ። ⁸ እንደ ልብስም ብል ይበላቸዋል፥ እንደ በግ ጠጕርም ትል ይበላቸዋል፤ ጽድቄ ግን ለዘላለም ማዳኔም ለትውልድ ሁሉ ይሆናል። ⁹ የእግዚአብሔር ክንድ ሆይ፥ ተነሥ፥ ተነሥ፥ ኃይልንም ልበስ በቀድሞው ወራትና በጥንቱ ዘመን በነበረው ትውልድ እንደ ሆነው ተነሥ። ረዓብን የቈራረጥህ ዘንዶውንም የወጋህ አንተ አይደለህምን? ¹⁰ ባሕሩንና የታላቁን ጥልቅ ውኃ ያደረቅኸው፥ የዳኑትም ይሻገሩ ዘንድ ጠሊቁን ባሕር መንገድ ያደረግህ አንተ አይደለህምን? ¹¹ እግዚአብሔርም የተቤዣቸው ይመለሳሉ ወደ ጽዮንም ይመጣሉ፤ የዘላለምም ደስታ በራሳቸው ላይ ይሆናል፤ ደስታንና ተድላን ያገኛሉ፥ ኀዘንና ልቅሶም ይሸሻል። ¹² የማጽናናችሁ እኔ ነኝ፥ እኔ ነኝ፤ የሚሞተውን ሰው እንደ ሣርም የሚጠወልገውን የሰው ልጅ ትፈራ ዘንድ አንተ ማን ነህ? ¹³ ሰማያትንም የዘረጋው ምድርንም የመሠረተውን ፈጣሪህን እግዚአብሔርን ረስተሃል፤ ያጠፋ ዘንድ ባዘጋጀ ጊዜ ከአስጨናቂው ቍጣ የተነሣ ሁልጊዜ ቀኑን ሁሉ ፈርተሃል፤ የአስጨናቂው ቍጣ የት አለ? ¹⁴ ምርኮኛ ፈጥኖ ይፈታል፤ አይሞትም ወደ ጕድጓድም አይወርድም፥ እንጀራም አይጐድልበትም። ¹⁵ ሞገዱም እንዲተምም ባሕርን የማናውጥ አምላክህ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፥ ስሜም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው። ¹⁶ ሰማያትን እዘረጋ ዘንድ ምድርንም እመሠርት ዘንድ፥ ጽዮንንም፦ አንቺ ሕዝቤ ነሽ እል ዘንድ ቃሌን በአፍህ አድርጌአለሁ፥ በእጄም ጥላ ጋርጄሃለሁ። ¹⁷ ከእግዚአብሔር እጅ የቍጣውን ጽዋ የጠጣሽ ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ንቂ፥ ንቂ፥ ቁሚ፤ የሚያንገደግድን ዋንጫ ጠጥተሻል ጨልጠሽውማል። ¹⁸ ከወለደቻቸው ልጆች ሁሉ የሚመራት የለም፥ ካሳደገቻቸውም ልጆች ሁሉ እጅዋን የሚይዝ የለም። ¹⁹ እነዚህ ሁለት ነገሮች ሆነውብሻል፥ ማንስ ያስተዛዝንሻል? መፈታትና ጥፋት ራብና ሰይፍ ናቸው፤ እንዴትስ አድርጌ አጽናናሻለሁ? ²⁰ ልጆችሽ ዝለዋል፤ በወጥመድ እንደተያዘ ሚዳቋ በአደባባይ ሁሉ ራስ ላይ ተኝተዋል፤ በእግዚአብሔር ቍጣና በአምላክሽ ተግሣጽ ተሞልተዋል። ²¹ ስለዚህም ያለ ወይን ጠጅ የሰከርሽ አንቺ ችግረኛ፥ ይህን ስሚ፤ ²² ስለ ወገኑ የሚምዋገት አምላክሽ ጌታሽ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ የሚያንገደግድን ጽዋ የቍጣዬንም ዋንጫ ከእጅሽ ወስጃለሁ፤ ደግመሽም ከእንግዲህ ወዲህ አትጠጪውም። ²³ ነፍስሽንም፦ እንሻገር ዘንድ ዝቅ በዪ በሚሉአት በአስጨናቂዎችሽ እጅ አኖረዋለሁ፤ ጀርባሽንም ለሚሻገሩት እንደ መሬትና እንደ መንገድ አደረግሽላቸው።
370Loading...
07
በሀዋሳ አዲስ ከተማ ሙሉ ወንጌል የወጣቶች የድራማና የስነፅሁፍ ህብረት የተሰናዱ ሁለት ዝግጅቶች #ብኤርለሃይሮኢ ቀን: ነገ ማክሰኞ ሚያዚያ 29 ቦታ:በሀዋሳ አዲስ ከተማ ሙሉ ወንጌል ሰዓት: 11:00 #ሎዶቅያዊት ቀን: ግንቦት 02 ቦታ:በሀዋሳ ሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ሰዓት: 11:00
280Loading...
08
“ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።” — 1ኛ ጴጥሮስ 2፥24 አሜን🙏
480Loading...
09
Hawaz Tegegn        መዳፉ የፋሲካ መዝሙ🎸 😭😭 ያ እኔን በፍቅር ያቀፈበት እጆቹ በችንካር ተመቱ እኔ ያስጠጉኝ ጉኖቹ ውስጥ ጦር ገባባቸው😭😭 በዚህ ሰዓት የውዴ የተተለተለው ስጋውና የፈሰሰው ደሙ ከእንግዲህ ጭለማ " በቃ " ሞት " በቃ "ባርነት " በቃ "  ሲሉኝ ሰማኃቸው፤ ውዴም በታላቅ ድምፅ ተፈፀመ  ብሎ ጮኽ። “ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።”   — ዮሐንስ 19፥30 የፈሰሰው  ደሙ  ከሩቅ  እየጠራኝ አስነባኝ  መከራው   ያምላኬ እንዳላዝን    አዝኖ  እንዳልደማ   ደምቶ  እስከሞት  ወዶኛል  ጌታዬ በጥፊ  የመቱት  ምራቅ  ቢተፉበት መች  ሰለቸው  ይሆ  የኔ  አባት😭 ከዚህም  በላይ  አልፎ  ቤዛ  ሆኖልኛል ጌታዬ  እስከሞት  ወዶኛል🙌 ከዘባነ  ኪሩብ  መስቀል  ያስመረጠው ሌላ  ምንም   አይደል  ፍቅር  ነው ተከሳሹ   ድኜ   ዳኛው   ተከሰሰ ሊያከብረኝ  ውድቀቴን   ለበሰ ሁሉም  ሲዝቱበት   ይሰቀል   እንደሚሸለት  በግ  ዝም  አለ ሸክሜን  ተሸክሞ  ቢያቀረቅርልኝ ወንበዴው   ፀድቄ  ቀና አልኩኝ “ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ #ለመታረድ #እንደሚነዳ #ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት #ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።”   — ኢሳይያስ 53፥7 መች  ሰለቸው  ይሆ  የኔ  አባት😭 ከዚህም  በላይ  አልፎ  ቤዛ  ሆኖልኛል ጌታዬ  እስከሞት  ወዶኛል🙌 ከዘባነ  ኪሩብ  መስቀል  ያስመረ ያ የሮማ   ጅራፍ   ጀርባህን   ያረሰው ፅድቄን   የፃፍክበት  ብዕር  ነው ትሁት  አካልህን   ደጋግሞ  ጠቀሰው ደምህ  እንደ ቀለም  ሊሆነው ተዘርግተህላት  #ነፍሴ  አነበበችህ🥺 በሰንበር  ተከፍለው  ገፆችህ አማረብኝ  ጎንህ  ውሃ  ደም  ሲያነባ  ጠውልገህ  የቆላው  አበባ ተባረኩበት❤
622Loading...
10
እዩ ተመልከቱት ፤ የክርስቶስን መስቀል ዛሬም ሲፈውስ ፤ የነፍስን ቁስል። © ቢቶ
380Loading...
11
የዛሬ ሳምንት በሀዋሳ ሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን
450Loading...
12
እንደምን ጨካኝ ነው በልጁ ይሉኻል፣ ኃጢአትን ሰቅለው ወንበዴዎች መኻል! . ደካማ ነው አሉ ልጁን ካላዳነ፣ ሕዝብን ባንድ አድኖ ደም እየከደነ! . ይህ ተርታ ሕዝብ ኹሉ ተባብሮ ባንድ ቃል፣ "ራስህን አድን" ብሎ ይሣለቃል፣ ነገ በሱ ሊድን መኾኑን መች ያውቃል? #ሰሙነ_ሕማማት © Abere Ayalew
381Loading...
13
<<ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?>> <<ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን? እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ። እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል። እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም። መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም። ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ።>> ዩሐ.13፥12-17 ~~~~ [ትህትና ሊያስተምረኝ ወዶ እግር አጠበ ባሪያውን ወርዶ እራሱን አዋርዶ] ~~~ በአቧራማዋ እስራኤል በነጠላ ጫማ (Sandals) መንቀሳቀስ የተለመደ ነበር። የጋራ ምግብ ከመቅረቡ በፊት ደግሞ ሰው እግሩን ታጥቦ ነው የሚቀመጠው፣ እጅ መታጠብ በኛ ዘንድ እንደተለመደው። ምክንያቱ ደግሞ ጠረጴዛው ዝቅ ያለ (low table) ስለሆነ ነው። ኢየሱስ ተነስቶ እግራቸውን ሲያጥብ የመጨረሻው ተራ ሎሌ ባሪያ የሚያደርገውን እየከወነ ነበር። ደቀመዛሙርቱም ራሱን 'በማዋረዱ' ሳይገረሙ አይቀሩም። የነፍሳችን ጌታና መሲህ፣ የሕያው እግዚአብሔር ልጅ፣ የአለምን ኅጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ... ሲሉት የከረሙት ሰዎች እግሩን ማጠብ ሲጠበቅባቸው እሱ ቀድሞ እግራቸውን ለማጠብ ማበሻ ማንሳቱ ባያስደንቃቸው ነው የሚገርመው። ምንም እንኳን እንደ ምድራዊ ንጉስና ነፃ አውጪ መጠበቃቸው የሚያደርጋቸውን እያንዳንዱን ድርጊቶቹን በአግባቡ ለመገንዘብ ቢከብዳቸውም፤ እንደ ስቅዩ-ሎሌ (suffering Servant) መምጣቱን አርፍደው ነው የተገነዘቡት (ኢሳ. 53)። ~~~~~~~ [ደቀመዛሙርቱ እግራቸው ቆሸሸ አደፈ ጎደፈ ፍጹም ተበላሸ ሁሉን የፈጠረ ሰውን የወደደ ጭቃውን ሊያስወግድ ወደ ታች ወረደ] ~~~~~~ ምጡቅ የሆነ፣ ሁሉን የሚገዛና ሁሉ በሁሉ የሆነ አምላክ እግር ሊያጥብ ዝቅ አለ፣ ከአቧራማ እግሮች ስር ተገኘ። "ፍጹም የቆሸሸን" ሰው ለማንፃት ፍጹም ንፁህ የሆነው ወልድ ራሱን ባዶ በማድረግ ወደ ታች ወረደ (ፊል. 2፥6-11)። ቃል መገለጡና በውርደት መንቀሳቀሱ አስደናቂ ነበር። የእግዚአብሔር ልጅ የህማም ሰው በመሆን፣ ቤት አልበኛ በመሆን፣ የድኻ ወዳጅ በመሆን፣ የኅጢአተኛ ወዳጅ በመሆን የተሰበረውን አለም ራሱን በመስቀል ለመስበር ተገኘለት። እንዴት ያለ የትህትናና የፍቅር ጥግ አሳየን! የእግራቸውን ቁሻሻቸውን ሲያፀዳ፣ አደፋቸውን ሲያጠራ ፈለጉን እንድንከተል ይመስላል "ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?" ብሎ የጠየቀን። አለሙ በኅጢአቱ ሲዳሽቅ ራሱን ለመላ አለሙ የቆረሰው ጌታ፣ ከአለሙ ድካምና ደዌ ራሱን ሳይሸሽግ የተገመሰለት አምላክ በድርጊቱ የምንቆርሰው እውነትን ችሮናል። ~~~ [እሱ ያላጠበው ከእርሱ ጋር አይኖርም አይቆርስም ከአምላክ ጋር አንድነት የለውም ጴጥሮስ ይህን አይቶ ሰውነቴን ደሞ እጠበኝ ጌታ ሆይ አለውም ተማጽኖ] ~~~~~ ኢየሱስ ስለራሱ ከነበረው ግንዛቤ አንዱ የሚያደርገውን የሚያደርግበት ምክንያትን ጠንቅቆ ማወቁ ነው።በኢየሱስ ያደረገው ስለራሱ በማቴ. 20፥28 እንዳለው "ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም።" ራሱን ዝቅ አድርጎ ሌሎችን ሊያገለግል ነው የመጣው። ከግዞት በኋላ እስራኤል ያጣችውን ፖለቲካዊ ነፃነትን ለእስራኤል ለመቸር ሳይሆን በኅጢአት ግሳንግስ የታፈነውን አለም ከህማሙ ለመፈወስ ነው የመጣው። እግዚአብሔር ለእስራኤል ብሎም ለአሕዛብ የሰጠውን ተስፋ በእርሱ የሚፈጸምበት እግዚአብሔር "ምርጤ፣ ባሪያዬ" ያለው መሆኑ በአግልግሎቱ ቁልጭ ብሎ ይታይ ነበር። ለዚህ ነው የገዛ የራሱን ዐለም ከውልደቱ ጀምሮ በትህትና፣ በዝቅታ፣ በመዋረድ፣ በመከራና ፍዳን በመቀበል ያናገረው። ብቸኛው ቋንቋ መስቀል የሆነው። ከማገልገሉም ባሻገር ሕይወቱ እንደሚነግረን በትህትና መሞላቱን ነው። ከአመጣጡ እስከ አሟሟቱ ድረስ ድንቅ በሆነ ትህትና የተሞላ ነው። ~~~~ [በሚደነቅ ብርሃን የሚኖር ፈጣሪ አልፋና ኦሜጋ የፍጥታት ሰሪ ማበሻ ጨርቅ ወስዶ እግር ሊያጥብ ወረደ ዝቅ አ'ረገ ራሱን ለሰው ተዋረደ] ~~~~ የኢየሱስ ዝቅ ብሎ እግር ማጠቡ ዘማሪ ደረጄ ከበደ እንዳለው "ትህትናን ሊያስተምረኝ ወዶ" ነው። ያደረገልን ራሳችንን በትህትና ዝቅ አድርገን የባልንጀራችንን እግር እንድናጥብ ነው። ጉድፉን እንድናጠራ፣ ከክፉና እኩይ እንድንከላከለው እንዲሁም ራሳችን ለባልንጀራችን አሳልፈን እንድንሰጥ ነው። "በክርስቶስ ኢየሱስ የነበረው ያ አስተሳሰብ" በእኛ እንዲኖር ነው። እግር ጉድፍ ሲያነሳ እንድንጠርገው በዚያም ትህትናችን እንዲታይ ተጠርተናል። ~~~~~~~ [የሁሉ ማሰሪያ አላማ ያለው ነው ጌታ ይህን አድርጎል እኔስ እንደምን ነው? የወንድሜን እግር እስካጥብ ዝቅ ካልኩ እውነትም 'የሱስን በእርግጥ ተከተልኩ] ~~~~~ ኢየሱስ የደቀመዛሙርቱን እግር አጥቦ ሲጨርስ "እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና" ብሏቸዋል። በሚደንቅ ብርሃን የሚኖር ምጡቅ አምላክ እግር ለማጠብ ማበሻ ጨርቅ ወስዶ የታናናሾችን ስራ ከሰራ እኛማ እንዴት ፈለጉን አንከተል?! እንደ ክርስቶስ ተከታይ እሱን በህይወቱ ልንመስል ይገባልና፣ ትሁት መሆን አለብን። የክርስቲያን መለኪያው ክርስቶስን መምሰል ነው። ዝቅ ማለት፣ ራሱን ማወረድ፣ ራሳችንን የሚጠቅመውን ብቻ ሳይሆን ሌሎች የሚጠቅመውንም ማድረግን ከጌታ ልንማር ይገባናል።የዝቅታን መንፈስ ይስጠን! ~~~~~~~ [ባሪያ ከሚያኖረው አይበልጥም አላቸው መልክተኛም አይበልጥ ይልቁን ከላከው እንግዲህ ጌታችሁ እኔ ይህን ስፈጽም አድርጉት ለሁሉም ዛሬ ሁኑ እናንተም] ~~~~~~ ባሪያ ከጌታው እንደማይበልጥና እኩልም እንዳይደለ ሁሉ ጌታ የፈፀመው ድርጊት እንደ ክርስቶስ ባሪያዎች ልንከተለው የተገባ ነው። እግር ማጠብ ግዴታ እግር ማጠብ አይደለም። ክብርን መተው፣ ራስን ዝቅ ማድረግ፣ ራስን ማዋረድ፣ ራስን ለሌሎች መቁረስ፣ ትህትና ነው። ጌታ ያደረገውን እርስ በእርስ እያንዳንዳችን እናደርገው ዘንድ የተገባ ነው። የክርስቲያን መለያው፣ የአማኝ መታወቂያው የክርስቶስን ፈለግ መከተሉ እስከሆነ ድረስ አንዳችን ለሌሎቻችን ራሳችንን ዝቅ በማድረግ ማገልገል ይገባናል። Every good thing in the Christian life grows in the soil of humility. Without humility, every virtue and every grace withers. That's why Calvin said humility is first, second, and third in the Christian faith. John Piper እዚህ ጋር አንድ ዝማሬን እንዘምራለን፣ አብረን በፀሎት እንቃትታለን :- [ከከበረው እንቁ ሰው ከሚሻማበት እኔስ ትህትናን ባገኝ በዚ'ች ዕለት ጥማቴም ፀሎቴም ዝቅ ዝቅ ማለት] ~~~~~ <<ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን?>> ዩሐ. 13፥12 መልካም ፀሎተ ሐሙስ! መልካም ቀን! © አማኑኤል አሰግድ
330Loading...
14
Media files
480Loading...
15
ኢሳይያስ 53 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ⁴ በርግጥ እርሱ ደዌያችንን ወሰደ፤ ሕመማችንንም ተሸከመ፤ እኛ ግን በእግዚአብሔር እንደ ተመታ፣ እንደ ተቀሠፈ፣ እንደ ተሠቃየም ቈጠርነው። ⁵ ነገር ግን እርሱ ስለ መተላለፋችን ተወጋ፤ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ በእርሱ ላይ የወደቀው ቅጣት ለእኛ ሰላም አመጣልን፤ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን። ⁶ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ እያንዳንዳችንም በየመንገዳችን ነጐድን፤ እግዚአብሔርም፣ የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ ጫነው። ⁷ ተጨነቀ፤ ተሠቃየም፤ ነገር ግን አፉን አልከፈተም፤ እንደ ጠቦትም ለዕርድ ተነዳ፤ በሸላቾች ፊት ዝም እንደሚል በግ፣ አፉን አልከፈተም። ⁸ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኀጢአት ተመቶ፣ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ፣ ከትውልዱ ማን አስተዋለ? ⁹ በአፉ ተንኰል ሳይገኝበት፣ ምንም ወንጀል ሳይሠራ፣ አሟሟቱ ከክፉዎች፣ መቃብሩም ከባለጠጎች ጋር ሆነ።
600Loading...
16
The hope of glory|የክብር ተስፋ ቅዱሳን ክርስቶስ በውስጣቸው ሲኖር የዘለዓለም ሕይወት ተስፋቸውን እንዲያስቡ መተማመንን ይፈጥርባቸዋል፡፡ በሰማይ በአብ ቀኝ ያለው ጌታችን ክርስቶስ ኢየሱስ በተመሳሳይ ሁኔታ በእኛም ውስጥ በሙላቱ እንዳለ ማረጋገጫችን ነው፡፡ ይህም የክብር ተስፋ የሆነው ክርስቶስ በውስጣችን አለ፡፡ ያ ሞትን ድል አድርጎ የተነሣው በአብ ቀኝ የተቀመጠው ዳግመኛ ተመልሦ የሚመጣው ለዘለዓለም ከእርሱ ጋር የሚያኖረን የክብር ተስፋችን ኢየሱስ ስፍራ ቀይሮ ሰማይ ብቻ አይደለም ከእኛ ጋር በእኛ ውስጥ ነው፡፡ ይህ የቅዱሳንን ልብ ያጽናናል፡፡ ይህ የአማኞችን ልብ ያሳርፋል፡፡ የክብር ተስፋችን ክርስቶስ ኢየሱስ ከእኛ ጋር በውስጣችን አለ፡፡ ቆላስይስ 1 (አዲሱ መ.ት) " ...እርሱም የክብር ተስፋ የሆነው በእናንተ ውስጥ ያለው ክርስቶስ ነው።"
481Loading...
17
የምታምነውን እወቅ | ዶክትሪን ምንድነው | አስፋው በቀለ (ፓ/ር)| www.operationezra.com
680Loading...
18
የምታምነውን እወቅ | ስነመንፈስ ቅዱስ | ክፍል አንድ| ፓስተር አስፋው በቀለ
690Loading...
19
Media files
1021Loading...
20
Media files
10Loading...
21
=== ✍ ✍ ✍=== ... በድካም ስሜን ሆኜ ያልሰራኅቸውን (ማድረግ የነበረብኝ ነገሮች ) እና በሰራኃቸው ስህተቶች ስብሰለሰል: እንቅልፍ ከማይወስደኝ በዬ የስንፍና አነባበብ :ጋደም እንዳልኩ ከመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል አሁን እንኳን መልህክቱን እንጂ ክፍሉን የማላስታውሰው ፩ ምዕራፍ አንብቤ ልተኛ ለስለስ ያለ መዝሙር ከፍቼ መስማት ስጀምር....: አንድ የሚያሳርፍ ሀሳብ ቀሰቀሰኝ እና ፃፊ ፃፊ✍✍ አለኝ.. ። ከተገረምኩበት እና በህይወቴ ካገኘሁት ቁም ነገር አንዱ ነበር... 🤔ሰው በምድር ላይ ሲኖር፡ሀሳቡ ሞልቶለት ያለመው፤ የተመኘው፤ የፈለገው ነገር ሁሉ ቅፅጰት በማይጠይቅ ሁኔታ ቢሆንለት እንኳን :ሞላልኝ አይልም:: ወይም ምኞቱ አያልቅም: ባገኘው ነገር ቁጥር ልክ ወይም እጥፍ ፍላጎቱ እና ምኞቱ ይጨምራል እንጂ አይቀንስም። ግን ደሞ ከዚህ ሁሉ ነገር ጀርባ አንድ ያላስተዋለለው ነገር አለ ። ዛሬ ብርቁ የሆነበት ነገር ሁሉ...: ልክ እንደ ብስኩት እና ቸኮሌት ሽፋን በሚያጓጓ ነገር የተሳለ ሊበሉት ቢፈልጉ እንደማያገኙት እና አርቴፊሻል እንደሆነ የተቀመጠ ፎቶ፤ ቀፎ አይነት ነገር እንደሆነ 🤔። ምክንያቱም የምድር ህይወት ማለት እኮ: ባይገልፀውም ከውቅያኖስ ላይ በስኳር ማንኪያ እንደሚነሳ ውሀ ናት። በጣም የሚያናድደው እና የሚያሳዝነው ደሞ:ይሄን ባለማስተዋልና አርቆ ባለማሰብ :<<ለምን ፈተና አላለፍኩም ፤ ዲቪዬ ተቃጠለ፤ ለምን ሰው ተወኝ፤ ለምን ተበደልኩ ፤ ተገፋው፤ከሰው በታች ሆንኩ፤ ኑሮ መረረኝ>>፡ በሚል ሰበብ...ሰፋሪው ሳይሰፍርላቸው የራሳቸውን ህይወት ከውቅያኖስ ሊቀዱ የገቡ ...ትናንሽ ማንኪያዎች አውጪ ላያገኙ ሰምጠው መቅረታቸው ነው። 🤔አስባቹታል፤ ለየትኛው ፈተና፤?ለየትኛው ሰላም ያለው አሜሪካ፤?ለየትኛው ከንቱ ላልሆነ ሰው፤?ለየትኛው በዳይ እና በደል፤?ለየትኛው መገፋት፤?ከየትኛውስ ሰው በታች፤? ኸረ ለየትኛውስ እድሜና ኑሮ ...🤔?...። ከመግፋት እኮ መገፋት ፤ከመጣል ደሞ መውደቅ፤ሰውን ከማሳዘን ማዘን...ይሻላል እኮ.. ብፅህና ስለሆነ። ግን ሁ ሉ ም ያልፋል ፤ይቀራል ። ከላይ የተጠቀሱት ነገሮች በሙሉ . . . የ ከ ን ቱ ከ ን ቱ እኮ ናቸው 🤔እናማ... አለፈ እና ገና ለገና ብሎ መብሰልሰሉም ወግ ሆኖ ነው እንጂ: ከዚ በኃላ ከ ን ቱ እና የከንቱ ከ ን ቱ ብቻ ናቸው።🙏 ✍ሀና11/8/2016 ዓ.ም
1000Loading...
22
Media files
570Loading...
23
የምታምነው እወቅ | ስነመላዕክት | አስፋው በቀለ (ፓ/ር)
951Loading...
24
https://youtu.be/Po3xR1KylMk?si=fn-DaJSNeJUzLXGA
630Loading...
= = = = = = =🕊🕊🕊= = = = = = = 🕊 እጅግ ውድ ሆኖ በገንዘብ የማይገዛ፤ በኮተታ ኮተት ብዛት የማይገኝ፤ ብዙዎች ለመቁጠር የሚያዳግት ገንዘብ ተከበው💵💰💸💴💰💸💵 ፤ሊገዙት ግን ያልቻሉት እና ፈፅሞም የማይችሉት፤በአማርኛ ፊደል ሶስት ሆኖ በቃል አንድ የሆነ፤ በውስጡ ግን በጣም ብ...ዙ ...ነገሮችን የያዘ በምድር ላይ ካሉ ወሳኝ እና ትልቅ ነገሮች አንዱ ብቻ ሳይሆን ዋነኛውም ጭምር ነው... ። 🕊 🕊 🕊 እጅግ ውድ ሆኖ 🤔 በየቀኑ በየዜናው መጀመሪያና እና መጨረሻ በሀገራችን ብቸኛው በነፃ የሚሰጡን ፤ ከየሰዉ አፍ የሚሰማ ተራ የሚመስል: ግን በምድር ለታደሉት ብቻ ፤በሰማይ ደግሞ ዋና መፍለቂያ እና መገኛው የሆነ: እሱ ባለበት. . . ድህነት፤ ረሀብ፤ስደት ፤ጦርነት ማይኖርበት :: አንድ መስሎ በውስጡ ግን ...ሀሴት፤ደስታ፤ የማይቋረጥ እረፍት... የያዘው እውቁና ትልቁ ነገር ሰላም እና ሰላም ብቻ ነው 🤔። * * * * * * * * * * * "ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም።ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።" _ዮሐንስ 14፥27 . . . ✍ 1/9/2016 ዓ.ም 🕊 🤗🙏
Show all...
❤ 1
እግዚአብሔር የነገርን ምስጢር እና አደራረግ የሚገልጥ አምላክ ነው፡፡ ዳንኤል 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁹ የዚያን ጊዜም ምሥጢሩ በሌሊት ራእይ ለዳንኤል ተገለጠለት፤ ዳንኤልም የሰማይን አምላክ አመሰገነ። ²⁰ ዳንኤልም ተናገረ እንዲህም አለ፦ ጥበብና ኃይል ለእርሱ ነውና የእግዚአብሔር ስም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይባረክ፤ ²¹ ጊዜያትንና ዘመናትን ይለውጣል፤ ነገሥታትን ያፈልሳል፥ ነገሥታትንም ያስነሣል፤ ጥበብን ለጠቢባን እውቀትንም ለአስተዋዮች ይሰጣል። ²² የጠለቀውንና የተሠወረውን ይገልጣል፤ በጨለማ ያለውን ያውቃል፥ ብርሃንም ከእርሱ ጋር ነው። ²³ ጥበብንና ኃይልን የሰጠኸኝ፥ እኛም የለመንንህን ነገር አሁን ያስታወቅኸኝ፥ አንተ የአባቶቼ አምላክ ሆይ፥ የንጉሡን ነገር አስታውቀኸኛልና እገዛልሃለሁ አመሰግንህማለሁ። … ²⁸ ነገር ግን ምሥጢር የሚገልጥ አምላክ በሰማይ ውስጥ አለ፥ እርሱም በኋለኛው ዘመን የሚሆነውን ለንጉሡ ለናቡከደነፆር አስታውቆታል። በአልጋህ ላይ የሆነው ሕልምና የራስህ ራእይ ይህ ነው። … ³⁰ ነገር ግን ይህ ምሥጢር ለእኔ መገለጡ ፍቺው ለንጉሡ ይታወቅ ዘንድ፥ አንተም የልብህን አሳብ ታውቅ ዘንድ ነው እንጂ በዚህ ዓለም ካሉ ሰዎች ይልቅ በጥበብ ስለ በለጥሁ አይደለም።
Show all...
የምታምነውን እወቅ | የእግዚአብሔር ባህርያት | ፓስተር አስፋው በቀለ |www.operationezra.com
Show all...
ኢሳይያስ 51 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እናንተ ጽድቅን የምትከተሉ እግዚአብሔርንም የምትሹ፥ ስሙኝ፤ ከእርሱ የተቈረጣችሁበትን ድንጋይ ከእርሱም የተቈፈራችሁበትን ጕድጓድ ተመልከቱ። ² ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም፥ ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሳራ ተመልከቱ፤ አንድ ብቻውን በሆነ ጊዜ ጠራሁት፥ ባረክሁትም አበዛሁትም። ³ እግዚአብሔርም ጽዮንን ያጽናናል፤ በእርስዋም ባድማ የሆነውን ሁሉ ያጽናናል፥ ምድረ በዳዋንም እንደ ዔደን በረሀዋንም እንደ እግዚአብሔር ገነት ያደርጋል፤ ደስታና ተድላ ምስጋናና የዝማሬ ድምፅ ይገኝበታል። ⁴ ወገኔ ሆይ፥ አድምጠኝ፤ ሕዝቤ ሆይ፥ ስማኝ፤ ሕግ ከእኔ ይወጣልና ፍርዴም ለአሕዛብ ብርሃን ይሆናልና። ⁵ ጽድቄ ፈጥኖ ቀርቦአል፥ ማዳኔም ወጥቶአል፥ ክንዴም በአሕዛብ ላይ ይፈርዳል፤ ደሴቶች እኔን በመተማመን ይጠባበቃሉ፥ በክንዴም ይታመናሉ። ⁶ ዓይናችሁን ወደ ሰማይ አንሡ፥ ወደ ታችም ወደ ምድር ተመልከቱ፤ ሰማያት እንደ ጢስ በንነው ይጠፋሉ፥ ምድርም እንደ ልብስ ታረጃለች፥ የሚኖሩባትም እንዲሁ ይሞታሉ፤ ማዳኔ ግን ለዘላለም ይሆናል፥ ጽድቄም አይፈርስም። ⁷ ጽድቅን የምታውቁ ሕጌም በልባችሁ ያለ ሕዝብ ሆይ፥ ስሙኝ፤ የሰውን ተግዳሮት አትፍሩ፥ በስድባቸውም አትደንግጡ። ⁸ እንደ ልብስም ብል ይበላቸዋል፥ እንደ በግ ጠጕርም ትል ይበላቸዋል፤ ጽድቄ ግን ለዘላለም ማዳኔም ለትውልድ ሁሉ ይሆናል። ⁹ የእግዚአብሔር ክንድ ሆይ፥ ተነሥ፥ ተነሥ፥ ኃይልንም ልበስ በቀድሞው ወራትና በጥንቱ ዘመን በነበረው ትውልድ እንደ ሆነው ተነሥ። ረዓብን የቈራረጥህ ዘንዶውንም የወጋህ አንተ አይደለህምን? ¹⁰ ባሕሩንና የታላቁን ጥልቅ ውኃ ያደረቅኸው፥ የዳኑትም ይሻገሩ ዘንድ ጠሊቁን ባሕር መንገድ ያደረግህ አንተ አይደለህምን? ¹¹ እግዚአብሔርም የተቤዣቸው ይመለሳሉ ወደ ጽዮንም ይመጣሉ፤ የዘላለምም ደስታ በራሳቸው ላይ ይሆናል፤ ደስታንና ተድላን ያገኛሉ፥ ኀዘንና ልቅሶም ይሸሻል። ¹² የማጽናናችሁ እኔ ነኝ፥ እኔ ነኝ፤ የሚሞተውን ሰው እንደ ሣርም የሚጠወልገውን የሰው ልጅ ትፈራ ዘንድ አንተ ማን ነህ? ¹³ ሰማያትንም የዘረጋው ምድርንም የመሠረተውን ፈጣሪህን እግዚአብሔርን ረስተሃል፤ ያጠፋ ዘንድ ባዘጋጀ ጊዜ ከአስጨናቂው ቍጣ የተነሣ ሁልጊዜ ቀኑን ሁሉ ፈርተሃል፤ የአስጨናቂው ቍጣ የት አለ? ¹⁴ ምርኮኛ ፈጥኖ ይፈታል፤ አይሞትም ወደ ጕድጓድም አይወርድም፥ እንጀራም አይጐድልበትም። ¹⁵ ሞገዱም እንዲተምም ባሕርን የማናውጥ አምላክህ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፥ ስሜም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው። ¹⁶ ሰማያትን እዘረጋ ዘንድ ምድርንም እመሠርት ዘንድ፥ ጽዮንንም፦ አንቺ ሕዝቤ ነሽ እል ዘንድ ቃሌን በአፍህ አድርጌአለሁ፥ በእጄም ጥላ ጋርጄሃለሁ። ¹⁷ ከእግዚአብሔር እጅ የቍጣውን ጽዋ የጠጣሽ ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ንቂ፥ ንቂ፥ ቁሚ፤ የሚያንገደግድን ዋንጫ ጠጥተሻል ጨልጠሽውማል። ¹⁸ ከወለደቻቸው ልጆች ሁሉ የሚመራት የለም፥ ካሳደገቻቸውም ልጆች ሁሉ እጅዋን የሚይዝ የለም። ¹⁹ እነዚህ ሁለት ነገሮች ሆነውብሻል፥ ማንስ ያስተዛዝንሻል? መፈታትና ጥፋት ራብና ሰይፍ ናቸው፤ እንዴትስ አድርጌ አጽናናሻለሁ? ²⁰ ልጆችሽ ዝለዋል፤ በወጥመድ እንደተያዘ ሚዳቋ በአደባባይ ሁሉ ራስ ላይ ተኝተዋል፤ በእግዚአብሔር ቍጣና በአምላክሽ ተግሣጽ ተሞልተዋል። ²¹ ስለዚህም ያለ ወይን ጠጅ የሰከርሽ አንቺ ችግረኛ፥ ይህን ስሚ፤ ²² ስለ ወገኑ የሚምዋገት አምላክሽ ጌታሽ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ የሚያንገደግድን ጽዋ የቍጣዬንም ዋንጫ ከእጅሽ ወስጃለሁ፤ ደግመሽም ከእንግዲህ ወዲህ አትጠጪውም። ²³ ነፍስሽንም፦ እንሻገር ዘንድ ዝቅ በዪ በሚሉአት በአስጨናቂዎችሽ እጅ አኖረዋለሁ፤ ጀርባሽንም ለሚሻገሩት እንደ መሬትና እንደ መንገድ አደረግሽላቸው።
Show all...
👏 1
በሀዋሳ አዲስ ከተማ ሙሉ ወንጌል የወጣቶች የድራማና የስነፅሁፍ ህብረት የተሰናዱ ሁለት ዝግጅቶች #ብኤርለሃይሮኢ ቀን: ነገ ማክሰኞ ሚያዚያ 29 ቦታ:በሀዋሳ አዲስ ከተማ ሙሉ ወንጌል ሰዓት: 11:00 #ሎዶቅያዊት ቀን: ግንቦት 02 ቦታ:በሀዋሳ ሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ሰዓት: 11:00
Show all...
“ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።” — 1ኛ ጴጥሮስ 2፥24 አሜን🙏
Show all...
🔥 1
Hawaz Tegegn        መዳፉ የፋሲካ መዝሙ🎸 😭😭 ያ እኔን በፍቅር ያቀፈበት እጆቹ በችንካር ተመቱ እኔ ያስጠጉኝ ጉኖቹ ውስጥ ጦር ገባባቸው😭😭 በዚህ ሰዓት የውዴ የተተለተለው ስጋውና የፈሰሰው ደሙ ከእንግዲህ ጭለማ " በቃ " ሞት " በቃ "ባርነት " በቃ "  ሲሉኝ ሰማኃቸው፤ ውዴም በታላቅ ድምፅ ተፈፀመ  ብሎ ጮኽ። “ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።”   — ዮሐንስ 19፥30 የፈሰሰው  ደሙ  ከሩቅ  እየጠራኝ አስነባኝ  መከራው   ያምላኬ እንዳላዝን    አዝኖ  እንዳልደማ   ደምቶ  እስከሞት  ወዶኛል  ጌታዬ በጥፊ  የመቱት  ምራቅ  ቢተፉበት መች  ሰለቸው  ይሆ  የኔ  አባት😭 ከዚህም  በላይ  አልፎ  ቤዛ  ሆኖልኛል ጌታዬ  እስከሞት  ወዶኛል🙌 ከዘባነ  ኪሩብ  መስቀል  ያስመረጠው ሌላ  ምንም   አይደል  ፍቅር  ነው ተከሳሹ   ድኜ   ዳኛው   ተከሰሰ ሊያከብረኝ  ውድቀቴን   ለበሰ ሁሉም  ሲዝቱበት   ይሰቀል   እንደሚሸለት  በግ  ዝም  አለ ሸክሜን  ተሸክሞ  ቢያቀረቅርልኝ ወንበዴው   ፀድቄ  ቀና አልኩኝ “ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ #ለመታረድ #እንደሚነዳ #ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት #ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።”   — ኢሳይያስ 53፥7 መች  ሰለቸው  ይሆ  የኔ  አባት😭 ከዚህም  በላይ  አልፎ  ቤዛ  ሆኖልኛል ጌታዬ  እስከሞት  ወዶኛል🙌 ከዘባነ  ኪሩብ  መስቀል  ያስመረ ያ የሮማ   ጅራፍ   ጀርባህን   ያረሰው ፅድቄን   የፃፍክበት  ብዕር  ነው ትሁት  አካልህን   ደጋግሞ  ጠቀሰው ደምህ  እንደ ቀለም  ሊሆነው ተዘርግተህላት  #ነፍሴ  አነበበችህ🥺 በሰንበር  ተከፍለው  ገፆችህ አማረብኝ  ጎንህ  ውሃ  ደም  ሲያነባ  ጠውልገህ  የቆላው  አበባ ተባረኩበት❤
Show all...
❤ 1
Photo unavailableShow in Telegram
እዩ ተመልከቱት ፤ የክርስቶስን መስቀል ዛሬም ሲፈውስ ፤ የነፍስን ቁስል። © ቢቶ
Show all...