en
Feedback
መቂ ቅድመ ግቢ ጉባዔ

መቂ ቅድመ ግቢ ጉባዔ

Open in Telegram
241
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
"በሥላሴ ገመድ ፍጹም ታስረናል። ከልባችን በማይነቀል በቅንዋተ ፍቅሩ ተቸንክረናል፣ እሱ ወዶናል አይጠላንም። እኛም አንተወውም።" /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ/
"በሥላሴ ገመድ ፍጹም ታስረናል። ከልባችን በማይነቀል በቅንዋተ ፍቅሩ ተቸንክረናል፣ እሱ ወዶናል አይጠላንም። እኛም አንተወውም።" /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ/

፳፱.አቡነ ዘበሰማያት (አቤል ተስፋዬ).mp34.84 MB

የበዓታ ለማርያምን ክብረ በዓል በጎንደር በዓታ። እንኳን አደረሳችሁ ክቡራን ክርስቲያኖች። ፀቃውዕ ይውኅዝ እምከናፍሪኪ ሐሊብ ወመዓር እምታሕተ ልሳንኪ። ወይቤላ ንዒ ንሑር ኀበ ደብረ ከርቤ ደብረ ጥበ
የበዓታ ለማርያምን ክብረ በዓል በጎንደር በዓታ። እንኳን አደረሳችሁ ክቡራን ክርስቲያኖች። ፀቃውዕ ይውኅዝ እምከናፍሪኪ ሐሊብ ወመዓር እምታሕተ ልሳንኪ። ወይቤላ ንዒ ንሑር ኀበ ደብረ ከርቤ ደብረ ጥበብ። በድጋሚ እንኳን አደረሳችሁ።

ታህሣሥ3 በዚች ዕለት የመድኀኒታች የኢየሱስ ክርስቶስ እናት ድንግል ማርያም በተወለደችበት በ3 ዓመቷ ለቤተመቅደስ ስጦታ ሁና መሰጠቷን እናስባለን። ሐና እና ኢያቄም፥ ዘካርያስ የሚባል ካህን በሊቀ ካህንነት ያገለግል በነበረበት ወቅት ለቤተ እግዚአብሔር ሰጥተዋታል። ውድ የቤተክርስቲያን ቤተሰቦች የበአታ ለማርያም ታቦት በደብረ ምሕረት በቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ስለሚገኝ በዓለ ንግሷ ተክብሮ ይውላል። የምንችል ሰዎች አንግሠን ጠዋት ተማሪ የሆንን ደግሞ ተሳልመን ጸሎት አድርሰን ቀናችንን በበረከት እንድንጀምር የአምላካችን የልዑል እግዚአብሔር ፍቃድ ይሁንልን።🙏 ©Kidmegibigubae

ታኅሣሥ ፫ ቀን በአታ ለእግዝትነ ማርያም ውስተ ቤተ መቅደስ፥ ወፋኑኤል። ዘነግህ ምስባክ፦ እበውእ ቤተከ ምስለ መባየ፥ ወእሁብ ብፅዓትየ ዘነበብኩ በአፉየ፥ ዘእቤ በከናፍርየ አመ ምንዳቤየ። መዝ65፥13 ወንጌል፦ ማቴ 1፥1-17 በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ ቅዱሳት መጻሕፍት። ዕብ 9፥1-11። 2ዮሐ 1፥ 5-8 የሐዋርያት ሰራ፥ 1፥12-15። ምስባክ፦ ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ እዝነኪ ርዕሲ ሕዝበኪ ወቤተ አቡኪ እስመፈተወ ንጉሥ ሥነኪ። መዝ44፥10 ወንጌል፦ ሉቃ 1፥39-57 ቅዳሴ፦ ዘእግዝትነ። ©kidmegibigubae

የዛሬ የነፍስ ምግባችን ሮሜ 7 እኔ ግን ለኀጢአት የተሸጥሁ ሥጋዊ ነኝ።የማደርገውን አላውቅና፣የምወደውንም ያንኑ የምጠላውን ብቻ እሠራለሁ እንጂ ።የማልወደውን የምሠራ ከሆንሁ ግን ያ የኦሪት ሕግ መሠራት ለበጎ እንደ ሆነ ምስክሩ እኔ ነኝ።እንግዲያስ በእኔ ላይ ያደረች ኀጢአት ናት እንጂ ፥ያን የማደርገው እኔ አይደለሁም።በእኔ ማለት በሥጋዬ መልካም ነገር እንደማይኖር አውቃለሁ፣መልካም ሥራ ለ መሥራት መሻቱስ በእኔ ዘንድ አለ፤በጎ ምግባር መሥራት ግን የለኝም።ያን የምወደውንም በጎ ነገር የማደርግ አይደለም፣ነገር ግን ያን የምጠላውን ክፉውን አደርጋለሁ።የማልወደውንስ የምሠራ ከሆነ ከሆነ የምሠራው እኔ አይደለሁም፣በእኔ ላይ ያደረች ኀጢአቴ ናት እንጂ።ሮሜ 7 14-20 ክፉውን እንድናሸንፍ ይርዳን❤️

ለቅድመ ጊቢ መዝሙር ጥናታችን ያግዘን ዘንድ ታሰቦ የተዘጋጀ ነው አውርደን ማጥናት ደግሞ የእኛ ትንሹ ሀላፊነት ነው

mezmur.docx0.22 KB

የዛሬ የነፍስ ምግባችን 1ዮሐ3 "...በዚህም የእግዚአብሔር ልጆችና የሰይጣን ልጆች ይታወቃሉ፤ጽድቅንም የማይሠራ ሁሉ ከእግዚአብሔር የተወለደ አይደለም፤ወንድሙንም የሚጠላ እንዲሁ ነው" 1ዮሐ3:10            ልጆቹ ሆነን እንኖር ዘንድ እርሱ ይርዳን❤️

+ቤተ ክርስቲያን+ ወርቅ በእሳት በተፈተነ ቁጥር ጥራቱ እየጨመረ ይሄዳል። እንዲያውም በትርጓሜያችን ወርቅን ሰባት ጊዜ በከውር (በወርቅ ማቅለጫ) ሲያቀልጡት ከወርቅ የበለጠ ዕንቍ ይሆናል ይላል። ሰውም እንዲሁ ነው በመከራ በተፈተነ ቁጥር እንደ ወርቅ እየጠራ ይሄዳል። ሰማዕታት መከራውን አልፈው ቅድስናቸውንና ንጽሕናቸውን ገለጡ። ከመ ወርቅ በእሳት ፈተኖሙ የተባሉ ሰማዕታት ናቸው። እሳቱ የበለጠ ቢነድ ወርቁን የበለጠ ያጠራዋል። እሳት የሚያስፈራው ገለባን እንጂ ወርቅን አይደለም። ቤተክርስቲያን ንጽሕት ናት። የንጽሕናዋ ምንጭ ደግሞ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። ከውስጥም ከውጭም የሚፈትኗት ብዙዎች ቢሆኑም ይህ ፈተናና መከራ ንጽሕናዋን የበለጠ ይገልጣል እንጂ በፈተናው አትጠፋም። የቤተክርስቲያን ራሷ ክርስቶስ ነው። በእርሱ ሁልጊዜ ደስ ይለናል። ቤተክርስቲያን ለክፉዎች ሰይፍ ናት። እርሷን ተመርኩዘው በስሟ ቢነግዱ የሚጎዱት ራሳቸው ናቸው እንጂ ቤተክርስቲያን አይደለችም። በሽተኞች መድኃኒታቸውን ቢያቃጥሉ በሽተኞች ራሳቸው ይሞታሉ እንጂ መድኃኒቱ አይጎዳም። ፈተናዎች እስከ ዕለተ ምጽአት መልካቸውን እየቀያየሩ ቢመጡ እኛ የበለጠ እየጠነከርን መሄድ አለብን እንጂ ተስፋ መቁረጥ አይገባም። "ዝናብም ወረደ፥ጐርፍም መጣ፥ነፋስም ነፈሰ፥ያንም ቤት ገፋው በአለት ላይም ስለ ተመሠረተ አልወደቀም" ማቴ. ፯፣፳፭። ራሳችንን ዐለት በተባለ በክርስቶስ አስተምህሮ ላይ መመሥረት አለብን።

ነቢያት ጌታ "ይወርዳል ይወለዳል" ብለው የተናገሩት ትንቢት እንዲፈጸም ተመኝተው ጾሙ ጸለዩ:: እኛ ስለምን እንጾማለን? ክርስቶስ ተወልዶ ፣ ተጠምቆ ፣ አስተምሮ ፣ ተሰቅሎ ፣ ሞቶ ፣ ተነሥቶ ፣ ዐርጎ ፣ በአባቱ ቀኝ አይደለምን? አሁን ለምን እንጾማለን? ብለን እናስባለን:: ጌታ በእኔና አንተ ልብ ውስጥ እውነት ተወልዶአልን? እውነት የእኛ ልብ እንደ ቤተልሔም ግርግም ለክርስቶስ ማደሪያ ሆኖአል? ማደሪያ አሳጥተን ከእናቱ ጋር አልመለስነውም? የጥምቀቱ ትሕትና በእኛ ልብ መቼ ደረሰ? የስቅለቱ ሕማም መች በእኛ ሕሊና ተጻፈ? የትንሣኤው ተስፋ የዕርገቱ ልዕልና በእኛ ልቡና መቼ ዐረፈ? ስለዚህ ነቢያት "ውረድ ተወለድ" ብለው የጾሙትን ጾም እንጾማለን:: ጌታ ሆይ በእኔ ሕይወትም ውስጥ ውረድ ተወለድ የእኔን ሰውነት ማደሪያህ አድርገው:: ሕዋሳቶቼ ከኃጢአት አርፈው እንደ ቤተልሔም ግርግም ማደሪያህ ይሁኑ:: የቤተልሔም እንስሳት ትንፋሽ ገበሩልህ ፣ የቢታንያ ድንጋዮች ዘማሪ ቢጠፋ ሊዘምሩ ዝግጁ ነበሩ ፣ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለክብርህ ተቀደደ ፣ ጨረቃ ላንተ ደም ለበሰች ፣ ፀሐይ ስላንተ ጨለመች ፣ ከዋክብት ለስምህ ረገፉ ፣ ዓለቶች ለፍቅርህ ተሰነጠቁ:: ከቤተልሔም እንስሳት ፣ ከቢታንያ ድንጋዮች ፣ ከቤተ መቅደስ መጋረጃ እኔ እንዴት አንሼ ልገኝ? የቢታንያ ድንጋይ ያወቀህን ያህል ሳላውቅህ ፣ የቤተ መቅደስ መጋረጃ የተረዳህን ያህል ሳልረዳህ እንዴት ልኑር? ዓለት ላንተ ሲሰነጠቅ የኔ ልብ ለምን ከዓለት ደነደነ? ጨረቃ ደም ስታለቅስ እኔ መከራህ ለምን አልተሰማኝም? ሙታን በሞትህ ሲነሡ እኔ ምነው ከኃጢአት ሞት መነሣት ተሳነኝ? ለዚህ ነው በእኔ ሕይወት ገና አልተወለድክም የምለው:: ስለዚህ ጌታ ሆይ የነቢያትህን ጾም ጸሎት ሰምተህ የወረድህ የተወለድህ ጌታ ሆይ በእኔም ሕይወት ውረድ ተወለድና እኔም ከመላእክት ጋር አብሬ ልዘምር ፣ ከሰብአ ሰገል ጋር ሥጦታህን ልቁጠር ፣ ከእረኞች ጋራ ልደነቅ:: ልደትህ ሳይገባኝ ምጽዓትህ እንዳይደርስብኝ እርዳኝ:: ጾመ ነቢያት ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ

02 Track 2.mp35.07 MB

እንኳን ለበዓለ ቅዱስ መርቆሬዎስ አደረሳችሁ "ሰማዕታት የዚችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ። ስለመንግሥተ ሰማያትም መራራ ሞትን ታገሡ" ቅዱስ ኤፍሬም የሰማዕታት ዓለማቸውና ደስታቸው ክርስቶስ ነው። ከ
+1
እንኳን ለበዓለ ቅዱስ መርቆሬዎስ አደረሳችሁ "ሰማዕታት የዚችን ዓለም ጣዕም በእውነት ናቁ። ስለመንግሥተ ሰማያትም መራራ ሞትን ታገሡ" ቅዱስ ኤፍሬም የሰማዕታት ዓለማቸውና ደስታቸው ክርስቶስ ነው። ከእርሱ የሚለያቸው ነገር ሲመጣ ማንንም ሳይፈሩ፣ ማንንም ሳያፍሩ በፍቅር ይገሥጻሉ። ካልተመለሰ ያወግዛሉ። ለሃይማኖታቸው አስተምህሮ እስከሞት ድረስ ይታመናሉ። እንደሀገሩ ይኖሩ እንደ ወንዙ ይሻገሩ ብለው ከክፋት ጋር ተስማምተው አልኖሩም። ሹመታቸው፣ ሽልማታቸው፣ ንብረታቸው ክርስቶስን ከማምለክና ለክርስቶስ ከመገዛት አልከለከላቸውም። ክርስቶስ ለሰማዕታት አብነት ለመሆን በመስቀል ተሰቀለ። ሰማዕታት ከእግዚአብሔር ውጭ የሚፈሩት ኃይል የለም። የሰማዕቱ በረከት ይደርብን።

ሶበ ተዘከርነኀ.mp39.33 MB

የዛሬ የነፍስ ምግባችን ዕብ.11:32 "እንግዲህ ምን እላለሁ ? ስለ ጌዴዎን፥ስለ ባርቅ፥ስለ ሶምሶን፥ስለ ዮፍታሔ ፥ስለ ዳዊት፥ስለ ሳሙኤልና ስለ ሌሎች ነቢያት እነግራችሁ ዘንድ ጊዜዬ አጭር ነውና።እነርሱ በእምነት ተጋደሉ ፤ነገሥታትን ድል ነሡ ፤ጽድቅን አደረጉ፤ተስፋቸውን አገኙ፤የአናብስትን አፍ ዘጉ።የእሳት ኀይልን አጠፉ፤ከሰይፍ ስለት አመለጡ፤ከድካማቸው በረቱ፤በጦርነት ኀይለኞች ሆኑ ፤የባዕድ ጭፍሮችንም አባረሩ"ዕብ 11:32-34               "ነገር ግን በወደደን በእርሱ ከአሸናፊዎች ሁሉ እንበልጣለን" ሮሜ.8:37 💙💙

ሕይወተ ነፍስ ሰጥቼ በሕይወት እንዲኖሩ አደርጋቸዋለሁ ጽድቃንን በርሷ የሚታመኑበት ቅዱሳን መንፈስ ቅዱስ ተቀብለው ደስ ይላቸዋል፡፡ 🌹ሰላምን (ኢየሱስ ክርስቶስን )ሀገር በተባለው ማኅፀን ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የጸነሰች ድንግል ማርያም ናት "ሕፃን ተወዶልናል ወንድ ልጅም ተሰጥተኖል አለቅነትም በጫንቃው ላይ ይሆናል ስሙም ድንቅ መካር ኃያል አምላክ የዘላለም አባት የሰላም አለቃ ተብሎ ይጠራል (ኢሳ9:6) እርሱ ሰላማችን ነውና ( ኤፌ 2:14 )ተብሎ እንደተጻፈ። 🌹የእግዚአብሔር ከተማ የሰላም ሀገር የተባለች ጽዮን እንደሆነች በዝማሬው ነግሮናል "ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገር እግዚአብሔር አንቺ የእግዚአብሔር ሀገር ሆይ በአንቺ የተደረገው ግሩም ነው" (መዝ 86:3) 🌹"አንሰ ተሠየምኩ ንጉሠ በላዕሌሆሙ በጽዮን በደብረ መቅደሱ" እኔ ግን ( እኔስ ) በመመስገኛው ተራራ ንጉሥ ሆኜ ተሾምኩባቸው (መዝ 2:6) የጽዮን ተራራ የተባለችው ድንግል ማርያም ናት።ምክንያቱም ደብረ ጽዮን ( የጽዮን ተራራ) አምባ መጠጊያ እንደነበረች ሁሉ ድንግል ማርያምም አምባ መጠጊያ ናት በቁሙም ቃሉ ጽዮን ማለት አምባ መጠጊያ ማለት ነው። 🌹እመቤታችንም ለኃጢአንና ለጻድቃን ለክርስቲያን ሁሉ በእናትነቷ በአማላጅነቷ በተሰጣት የምሕረት ቃል ኪዳን አምባ መጠጊያቸው ናትና በዚህ ምክንያት እመቤታችን ፀወነሥጋ ፀወነ ነፍስ ፀወነ ጽድቃን ወኃጢአን ትባላለች። 🌹ደብረ መቅደስ አላት ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን መድኃኔዓለም ክርስቶስ ማኅፀኗን ዓለም አድርጎ ተመስግኖበታልና በነገረ ማርያም "ድንግል አድነነት ርዕስ መንገለ ከርሣ" የሚል ቃል አለ። መላዕክቱ በማኅፀን ያለውን ፈጣሪያቸውን ሲያመሰግኑት ለመስማት አንገቷን ወደ ማኅፀኗ ዘንበል በማድረግ ቅዳሴያቸውን ታደምጥ ነበርና ነው።(ዮሐ 1-42) 🌹በድንግል ማርያም ማኅፀን በእውነተኟይቱ ደብር ቤተ መቅደስ በጽዮን በተዋሕዶ የከበረው የነገሠው የእግዚአብሔር የባሕሪ ልጅ መሲህ( ክርስቶስ) የነፍሳችን የሥጋችን ንጉሥ የጌቶች ጌታ የነገሥታት ንጉሥ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።( ራዕ 19:11-16) ሉቃ 1:30) 🌹ድንግል ማርያምን ለእናትነት ለዙፋንነት ለማደሪያነት የመረጠ እግዚአብሔር ነው "ልዑል ማደሪያውን ቀደሰ" (መዝ 45-4) "የወደደውን የጽዮን ተራራ መረጠ እግዚአብሔር ድንግል ማርያምን መረጠ ማደሪያውን ለየ: ቀደሰ በመዝሙረ ዳዊት 77:68 ላይ "የይሁዳን ሕዝብ መረጠ የወደደውን የጽዮንን ተራራ" ተብሎ እንደተጻፈ ከይሁዳ ነገድ የሆነችውን ድንግል ማርያምን መርጦ አደረባት ቅድስት ንጽሕት ናትና። 🌹"እግዚአብሔር በቅድስናው ዙፋን ይቀመጣል" (መዝ 46:8) ስለተባለ ማኅፀኗን ዓለም: ዙፋን አድርጎ ነገሰባት (መዝ 131:13) ታዲያ እግዚአብሔር የመረጣት ማን ይቃወማል (ሮሜ 8-34) እንኳን እግዚአብሔር ያከበረውን እግዚአብሔር የሾመው ቀርቶ ሰው የመረጠውና የሾመው እንኳን ይከበራል። 🌹ድንግል ማርያም የሕያዋን ሁሉ ደስታ ናት "የምድር ሁሉ ደስታ የጽዮን ተራራ ነው" (መዝ 47:2) ተብሎ ተጽፏልና። ለጊዜው የምድር ሁሉ ሲል የአዳም ልጆች የሥጋ ለባሾች ሁሉ ደስታ ቤተመቅደስ ነው ሲል ነው።በተፈጠርንበት ምድር ይለናል። ከአፈር ተፈጥረናልና ፍጻሜው ግን የሕያዋን ሁሉ የምድር ሁሉ የሥጋ ለባሾች ሁሉ ደስታ በእመቤታችን በድንግል ማርያም ነው ለምን ቢሉ" "በእንተ ሔዋን ተዓፅው ኖኅተ ገነት ወበእንተ ማርያም ድንግል ተረኅወ ለነ ዳግመ" ( ውዳሴ ማርያም ዘኃሙስ: ቅዱስ ኤፍሬም) በሔዋን ያጣነውን ገነት :ያጣነውን ደስታ በእመቤታችን በድንግል ማርያምማ የደስታችን መፍሰሻ የጽዮን ተራራ እናታችን ሆና ተሰትታናለች። (ዮሐ19-26) 🌹በመሆኑም ትንቢት የተነገረላት ሱባኤ የተቆጠረላት ከአምላካችን የተሰጠችን ጸጋችን በረከታችን አክሊላችን ሞገሳችን ናት።መወጣጫ መሰላላችን መሸጋገሪያችን ድልድያችን እመቤታችን ናት። 🌹ልዑለ ቃል ኢሳይያስ ስለ ጽዮን ዝም አልልም ያለው የማይታየው የማይዳሰሰው የማይጨበጠው ወይም በቦታና በዘመን የማይወሰነው አምላክ ከድንግል ማርያም በነሳው ሥጋ ስለታዬ ስለተዳሰሰ ከእኛ ጋር ስለሆነ መርገማችን ስለሻረልን እንባችን ስላበሰለን እንቆቅልሻችን ስለፈታልን ወጥመዳች ስለበጣጠሰልን ከሞት ወደ ሕይወት ስላሸጋገረን ጽዮን የድኅነታችን ምክንያት ናትና ስለ ጽዮን ዝም አልልም አለ። 🌹እኛም የዘመነ ሐዲስ ክርስቲያኖች ስለ ጽዮን ዝም አንልም ቀደምት አበው በምሳሌዓቸው ነቢያት በትንቢታቸው ሐዋርያት በስብከታቸው ሊቃውንቱም 👉አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው 👉ቅዱስ ኤፍሬም በውዳሴው 👉አባ ጊዮርጊስ በሰዓታቱ 👉አባ ጽጌ ድንግል በማኅሌቱ 👉ቅዱስ ያሬድም በዜማው ስለ እመቤታችን ዝም አላሉም። 🌹ይልቁንም ጽዮንን ክበቡአት በዙሪያዋም ተመላለሱ (መዝ47-12) ነው ያሉት : አቁራሪተ መዓት ነሽና አማልጂን አስምሪን ይቅርታን አስጪን የእናት ልመና ፊት አያስመልስ አንገት አያስቀልስምና ከልጅሽ ከወዳጅሽ ምሕረትን አሰጪን እያልን ልንከባት ይገባል። 🌹ነቢዩ ኢሳይያስ ስለ ጽዮን ዝም አልልም ማለቱ በምሥጋና በውዳሴ በዝማሬ በቅዳሴ ማለቱ ነው።በመጽሐፍ ቅዱስ "ጻድቃን ሆይ በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ ለቅኖች ምስጋና ይገባል"ተብሎ ተጽፏልና።ለቅኖች ምስጋና የሚገባ ከሆነ እመቤታችን ደግሞ ከቅኖች በላይ ከጻድቃን በላ ናትና ምስጋና ይገባታል።መላእክት እንኳን እመቤታችን አመስግነዋል "..ጌታ ከአንቺ ጋር ነው አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ" (ሉቃ 1-41) 👉ድንግል ማርያም ራሷ "እነሆ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል" (ሉቃ 1-48)። 🌹ለዚህም ነው እኟም የምናመሰግናት የምንዘምርላት የምናከብራት ከፍ ከፍም የምናደርጋት "ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን ይላል በውስጧም ሰው ተወለደ (መዝ 86:5)" እንዲል ቅዱስ ዳዊት የአዳም ዘር ሁሉ እናታችን እመቤታችን እያለ ያመሰግናታል፡፡ #ወስብሐት_ለእግዚአብሔር!!! ✍️ኃ/ሚካኤል {ጐሥዓ} በጸሎታችሁ አስቡኝ። ©️ፍኖተ ሕይወት ዘኢትዮጵያ [በኃ/ሚካኤል {ጐሥዓ}።   ❤#መልካም_በዓል_ያድርግልን!

ፍኖተ ሕይወት ዘኢትዮጵያ [በኃ/ሚካኤል {ጐሥዓ} ❤#ስለ_ጽዮን_ዝም_አልልም" (ኢሳ 62:1) ✍️በከመ ፀሐፈ ኃ/ሚካኤል {ጐሥዓ}። ✍️ኃ/ሚካኤል {ጐሥዓ} እንደ ፃፈው። 🌹ይህንን የተናገረው ልዑለ ቃል ኢሳይያስ እግዚአብሔር የራቀውን አቅርቦለት የረቀቀውን አጉልቶለት ትንቢት በሚናገርበት ዘመን ሲሆን #ጽዮን የሚለው ስም እንደአገባቡ ይፈታል ልብስ በየፈርጁ እንዲለበስ የቅዱሳት መጽሐፍት ቃልም በስልት በስልቱ ይተረጉማል።መጽሓፍ ቅዱስ በትርጉሜ ስልት ሲበለት መልክ መልክ አለው አንዱ ቃል እንደያገባቡ የተለያየ ትርጓሜ ይሰጣል በመሆኑም ከላይ በርዕሳችን የተጠቀሰው የነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት ብንመለከት ቃሉ ኅብርነት ያለው ሆኖ ይገኛል። 🌹#ጽዮን የሚለው ቃል ኢየሩሳሌም ቤተክርስቲያን መንግሥተ ሰማያት ወይም ድንግል ማርያም ቤተመቅደስ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።ኢየሩሳሌም ቤተእስራኤል (ቤተ ያዕቆብ) ቤተ መቅደስ ተብሎ የሚፈታበት ጊዜ አለ።በሌላ ሥፍራ ደግሞ የቃሉ አገባብ ኢየሩሳሌም ድንግል ማርያም ወይም መስቀል ክርስቶስ ተብሎ ሊተረጎም ይችላል።እንግዲህ አርዕስትን ተመልክቶ ስለምን እንደተነገረ በማስተዋል ካላዩት ካልመረመሩት በዘፈቀደ እንተርጉም ቢሉት ምስጢሩ ሊገኝ አይችልም። ትርጓሜውም የተሳሳተ ይሆናል ከምሥጢር ዳህፅ(መሰናክል) ለመጠብቅ መጻሕፍት መመርመር መምህራንን ማነጋገር በጸሎት በትኅትና እግዚአብሔርን ግለጽልን በማለት ይህን ቃል የተለያየ ትርጉም እንዳለው ለማሳየት በምሳሌ እንመልከት፦ ፩ኛ፦ወደ ጽዮን ተራራና ወደ ሕይው እግዚአብሔር ከተማ ደርሳችኋል ( ዕብ 12፡22) 🌹ከዚህ ላይ #የጽዮን_ተራራ ያላት ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን (መንግሥተ ሰማያትን) ነው መንግሥተ ሰማያትም የእግዚአብሔር ክብር ስለማያበራለት መብራቷም በጉ ስለሆነ ፀሐይ ጨረቃ የሚያስፈልጋት ከተማ በመሬት ላይ የለችም ኢየሩሳሌም ወይም የዳዊት ከተማ የተባለችው ደብረ ጽዮን (የጽዮን ተራራ) አይደለችም ሰማያዊት ኢየሩሳሌም መንግሥተ ሰማያት መሆኗን ያስተውላል።በመሆኑም የጽዮን ኢየሩሳሌም መንግሥተ ሰማያት ደብረ ጽዮን ወይም ኢየሩሳሌም ሰጥተን ብንተረጉም በምስጢር እንስታለን በትርጉም እንገድፋለን። ፪ኛ፦ጽዮን የሚለው ቤተመቅደስን ነው። 🌹የቃል ኪዳኑ ታቦት በመቅደስ ይኖራልና በጽዮን ታቦተ ጽዮን መቅደሱም የጽዮን መቅደስ ተብሏል"የእግዚአብሔር ታቦት የገባበት ሥፍራ ሁሉ ቅዱስ ነው"(1መጽ ነገ፦8፡11) እንዲሁም አቤቱ ለአንተ በጽዮን ምሥጋና ይገባል እንዲል ዳዊት በመዝሙሩ በጽዮን በተራራው በጽዮን በቤተ መቅደስ ምሥጋና ይቀርባል ዝማሬ ይዘመራል ቅዳሴ ይቀደሳል ሰዓታትና ማኅሌት ይቆማል ቃለ እግዚአብሔር ይነገራል።ስብሐት እግዚአብሔር ይፈሳል በቤተመቅደስ ያዘኑ ይጽናናሉ ያለቀሱ እንባቸው ይታበሳል የተጨነቁ ይረጋጋሉ።በቤተ መቅደስ እግዚአብሔር:- 👉ስላደረገልን ነገር ሁሉ ምስጋና እናቀርብበታለን።"ስለማይነገር ስጦታው እግዚአብሔር ይመስገን" (2ቆሮ9፡15) "አድርገህልናልና አመሰግንሀለሁ" (መዝ 51፡9) 👉ለጥያቄዎቻችን መልስ እናገኝ ዘንድ ኃጢአታችን ይሰረይ ዘንድ ታሪካችን ይቀየርልን ዘንድ ወጥመዳችን ይበጣጠስልን ዘንድ ቀንበራችን ይሰበርልን እንቆቅልሻችንም ይፈታ ዘንድ ከእግዚአብሔር ዘንድ የምንነጋገርበት ሥፍራ የጽዮን ተራራ ቤተመቅደሱ ስለሆነ ልዑለ ቃል ኢሳይያስ ስለ ጽዮን ዝም አልልም ስለ ኢየሩሳሌም ( የሰላም ሀገር) ቤተ መቅደስም ጸጥ አልልም አለ። ፫ኛ፦ጽዮን የሚለው ቃል የሚያመለክተው ክርስቶስ ስለተሰቀለበት ዕፀ መስቀል ነው። 🌹በመመስገኛው ተራራ በጽዮን እነግሳለሁ ይላልና (መዝ 2፡6) መስቀሉን መንግሥት አድርጎ በመስቀል ተቅሰሎ ሳለ የመንግሥት ሥራ ሠርቷል። ጌትነቱን አምላክነቱን አዳኝነቱን ገልጾበታል የመንገሥት ሥራ በመስቀል ስለተሠራበት መስቀል ኃይልነ መስቀል ጽንዕነ መስቀል ቤዛነ ይባላል። መስቀሉንና የተተከለበትን ሥፋራ ደብረ ቀራንዮ ደብረ መቅደሱ የመመስገኛው ተራራ ይላቸው ከዚህ አስቀድሞ ጌታችን ለቤዛ ዓለም ሳይሰቀል በፊት በቀራንዮ ተራራ መላእክት በቀትር እየመጡ ያመሰግኑ ይቀድሱ ነበር ጌታ በተሰቀለ ጊዜ እንደልማዳቸው ሊያመሰግኑ ቢመጡ ተሰቅሎ ቢያዩት ደንግጠው በመስቀሉ ዙሪያ እነደ ሻሽ ተነጥፈው እንደ ቅጠል ረግፈው "ለከ ኃይል" ኃያል መባል ይገባሀል ኃይል ለአንተ ይሁን "ለከ ጽንእ" ጽኑ ብርቱ መባል ይገባሀል ጽንዓት ብርታት ለአንተ ይሁን እያሉ አመስግነውታል። 🌹በሌላው ዳዊት"አምባይቱን ጽዮንን ያዘ እርሷም የዳዊት ከተማ ናት (2ሳሙ 5:7)"እንዲሁም ዳዊትም ሄዶ የእግዚአብሔርን ታቦት ከአቢዳራ ቤት ወደ ዳዊት ከተማ አመጣው ተብሎ እንደተጻፈ የጽዮን ተራራ (አምባ) የተባለችው ሰማያዊት ኢየሩሳሌም አይደለችም በቁሙ ዳዊት የነገሠበት መናገሻ ከተማው ናት እንጂ (2ሳሙ6:12) በመሆኑም ነቢዩ ኢሳይያስም ቅጥርዋ ፈርሶ ውስጧ ተመዝብሮ ሕዝቧ ተማርኮ ወደ ፋርስ ባቢሎን ምድር ወርደው ሀገሪቱ ባድማ ሆና ነበርና ከእንግዲህ ወደህ የተተወ አትባይም ምድርሽም ከእንግዲህ ወዲህ ውድማ አትበል (ኢሳ 62:4) ሀገሪቷ ስትመዘበር ቅጥርዋ ሲፈርስ ብዙዎች ከሰይፍ የተረፉት በረሃብ ሲቀጡ በመንፈስ ተመልክቶ ስለ ጽዮን ዝም አልልም ስለ ኢየሩሳሌምም ጸጥ አልልም አለቅሳለሁ እጮሃለሁ በማለት ተናገረ። ፬ኛ፦የቃል ኪዳኑን ታቦት ጽዮን ይለዋል (2ኛ፦ሳሙ፦6:12) 🌹በእግዚአብሔር ጣት የተጻፉ አስርቱ ትእዛዛት ያሉበት ሕዝቡንም ይባርክበት የነበረው የቃል ኪዳን ታቦት ኢያሱ ባህረ ዮርዳኖስን ለሁለት የከፈለበት ታቦት በኋላም የአቢዳራን ቤት የባረከችው ዳጎንን የሰባበረችው ታቦት ዳዊትም ከአቢዳራ ቤት ወደ ዳዊት ከተማ ወደ ጽዮን ስላመጣት ታቦቲቱም በጽዮን (በጽዮን ተራራ) ስላረፈች በቦታው ታቦተ ጽዮን ( የጽዮን ታቦት) ተብላለች (ዘጸ 3፥18 ፣ኢያ 3:14-17) 7 ፭ኛ፦"አቤቱ ስለፍርድህ ጽዮን ሰምታ ደስ አላት"(መዝ 96:8) 🌹በዚህ የመጽሕፍ ቅዱስ ክፍል ጽዮን ያላት በቁሙ የዳዊትን ከተማ ወይንም ኢየሩሳሌምን ከፍ ብሎም የእግዚአብሔርን ከተማ ኢየሩሳሌም ሰማያዊትን ነው ተብሎ ቢተረጎም ስህተት ነው።ለምን ቢባል ቦታው ግእዕዛን የለውምና እንደ ሰው የደስታ ወይም የኃዘን ስሜት ተራራ ከተማ ሰማይ እንደማይሰማቸው የታወቀ ነውና።በመሆኑም ትክክለኛው ትርጉም ሲፈለግ የእግዚአብሔርን ፍርድ ሰምታ ደስ ያላት ጽዮን ማናት ቢሉ በቀጥታ ስለቤተ ያዕቆብ ስለ ትሩፋን የተነገረ መሆኑን ማስተዋል ይቻላል፡፡ ፮ኛ፦ጽዮን  የተባለችው ድንግል ማርያም ናት 🌹"እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ።አሮጊቶችዋን እጅግ እባርካለሁ፥ድሆችዋንም እንጀራ አጠግባለሁ።ካህናቶችዋንም ደኅንነትን አለብሳቸዋለሁ፥ ቅዱሳኖችዋም እጅግ ደስ ይላቸዋል።" 🌹በዚህ የመጽሕፍ ቅዱስ ክፍል ጽዮን ያላት ድንግል ማርያም ናት (መዝሙር 132፥13-16) ምዕመናኖቿን በቃል ኪዳኑ በእናትነቷ በምልጃዋ የሚያምኑትን ፈጽሜ አከብራቸዋለሁ ድሆቿ ነዳያንን ነፍስን አክለ ሥጋ አክለ ነፍስ ብእለ ሥጋ ብዕለ ጸጋን ሰጥቼ ደስ አሰናቸዋለሁ የሥጋ የነፍስ እህልን የሥጋ ብልፅግናና የነፍስ ሀብተጸጋን ሰጥቼ ደስ አሰኛቸዋለሁ ማለት ነው አንድም ሥጋውን ደሙን ልጅነትን( ከሥላሴ በጥምቀት መውለድን )ሰጥቼ ደስ አሰኛቸዋለሁ ካህናቶቹንም አገልጋዮቿን ሕይወተ ሥጋ

#ቢፈልግባትም_መልካሙ_ገብሬ #አልተገኘባትም_ከበለሷ_ፍሬ ለስልሶላት ነበር ሀይማኖት መሬቱ ተቀጥሮላት ነበር አጥር ሥርዓቱ ተለቆሞላት ነበር ድንጋይ ፈተናዋ ፍሬ ግን ታጣባት መበጨረሻዋ ፍሬ የሌለባት ቅጠል ስለሆነች ተካዋን በምግባር ስላላስደሰተች መልካሙ ገበሬ ሊቆርጣት ተነሳ ሌሎች እንዳይጠፉ በእርሷ የተነሳ ለንስሃ የሚሆን እድሜ እንዲሰጣት ጠባቂ መልአኳ ተማጸነላት ምክር እና ተግሳጽ ይጨመርላት ታፈራ ከሆነ ለአመት እንያት ልመናውን ሰመቶ ጌታውም ፈቀደ ጥቂት እድሜን ሊሰጥ ሊታገስ ወደደ ዳግመኛ ሲመጣ ፍሬ ካላፈራች ተቆርጣ ወደ እቶን እሳት ትጣላለች

የዛሬው የነፍስ ምግባችን ፊል.2 "...እንደ እግዚአብሔር ልጆች ንጹሓንና የዋሃን ትሆኑ ዘንድ፥በማያምኑና በጠማሞች ልጆች መካከል ነውር ሳይኖርባችሁ በዓለም  እንደ ብርሃን ትታያላችሁ ፤የሕይወትን ቃል እያስተማራችሁ፥ክርስቶስ በሚመጣበት ቀን እኔ እንድመካ ፤የሮጥሁ በከንቱ አይደለምና።ስለ ሃይማኖታችሁም የአምልኮ መሥዋዕት እሠዋለሁ።እነሆም እኔ በእናንተ ደስ ይለኛል፤እናንተም በእኔ ደስ ይበላችሁ።ከእኔም ጋር ሐሤት አድርጉ" ፊል.2:15-18       ፍሬ እንድናፈራ አምላክ ይርዳን❤️

የዛሬ የነፍስ ምግባችን የሐዋ 2ና ሮሜ 8 "ቃሉንም ተቀብለው ተጠመቁ፣በዚህችም ዕለት ሦስት ሺህ ያህል ሰዎች ተጨመሩ።በሐዋርያት ትምህርትና በአንድነት ማዕድን በመባረክ፥በጸሎትም ጸንተው ይኖሩ ነበር።ሰው ሁሉ ፈራቸው።፤በሐዋርያትም እጅ ብዙ ተአምራትና ድንቅ ሥራ ይደረግ ነበር።ያመኑትም ሁሉ በአንድነት ይኖሩ ነበር፤ገንዘባቸውም ሁሉ በአንድነት ነበር።መሬታቸውንና ጥሪቲቸውንም እየሸጡ ለእያንዳንዱ እንደሚያሻው ይሰጡ ነበር።ሁልጊዜም አንድ ልብ ሆነው በቤተ መቅደስ ያገለግሉ ነበር፤በቤትም ኅብስትን ይቆርሱ ነበር፣በደስታና በልብ ቅንነትም ምግባቸውን ይመገቡ ነበር፣እግዚአብሔርንም ያመሰግኑ ነበር፣በሕዝቡም ሁሉ ዘንድ መወደድ ነበራቸው፣እግዚአብሔርም የሚድኑትን ዕለት ዕለት በእነርሱ ላይ ይጨምር ነበር" የሐዋ 2:41-47 "ወንድሞቻችን ፥ሆይ አሁንም በሥጋ ሳለን በሥጋ ፈቃድ እንኖር ዘንድ አይገባም።እንደ ሥጋ ፈቃድ ብትኖሩ ትሞታላችሁ፣ነገር ግን በመንፈሳዊ ሥራ የሥጋችሁን ፈቃድ ብትገድሉ ለዘለዓለም በሕይወት ትኖራላችሁ።"ሮሜ 8:12-13      ልቦናችን ወደ እግዚአብሔር የሚያንጋጥጥበት ንባብ ይሁንልን❤️❤️❤️