241
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
August '24
August '24
+1
in 0 channels
July '24
+6
in 0 channels
Get PRO
June '24
+9
in 0 channels
Get PRO
May '24
+2
in 0 channels
Get PRO
April '24
+1
in 0 channels
Get PRO
March '24
+10
in 0 channels
Get PRO
February '24
+249
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 06 August | 0 | |||
| 05 August | 0 | |||
| 04 August | +1 | |||
| 03 August | 0 | |||
| 02 August | 0 | |||
| 01 August | 0 |
Channel Posts
ክፍል ፭
ኢየሱስ ክርስቶስ የት ተወለደ?
የሕይወት እንጀራ ክርስቶስ በእንጀራ ቤት ተወለደ (ሉቃ. ፪፣፬-፲፭)። ቤተልሔም ማለት የእንጀራ ቤት ማለት ነው። የክርስቶስ መወለድ ድንገት እንደ እንግዳ ደራሽ፣ እንደ ውሃ ፈሳሽ አይደለም። በቅዱሳን ነቢያት የሰውን ሥጋ ተዋሕዶ እንደሚወለድ ትንቢት ሲነገር ነበርና (ኢሳ. ፯፣፲፬)። ከጽድቅ ለተራበው ዓለም መንፈሳዊ ምግብ ይሆን ዘንድ የሕይወት እንጀራ ክርስቶስ በእንጀራ ቤት ተወለደ።
ቤተልሔም በእስራኤል ሀገር ያለች የዳዊት ከተማ የነበረች ቦታ ናት። ነቢያቱ፣ ነገሥታቱ ተወልደውባታል። የነቢያት ሀገር ናት። ከነቢያቱ፣ ከነገሥታቱ ግን የሕይወት እንጀራ ሆኖ የተራበውን ዓለም ማጥገብ የቻለ አልነበረም። ወልደ እግዚአብሔር ግን ከድንግል ማርያም ተወልዶ ዘለዓለማዊ ሕይወትን የሚሰጥ የሕይወት እንጀራ ሆነ። ምእመናን ንሥሓ ገብተው፣ ሥጋውን በልተው፣ ደሙን ጠጥተው በእርሱ ሕያዋን ሆነው ይኖራሉ። እርሱም በእነርሱ ይኖራል።
© በትረማርያም አበባው
የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው።
| 2 | ክፍል ፬
ቃለ እግዚአብሔር
ወልድ ዋሕድ በተዋሕዶ ከበረ ዋነኛ ትምህርታችን ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ በሃይማኖተ አበው እንደተናገረው ሥጋ መክበሩ ቃል ስለተዋሐደው ነው እንጂ መንፈስ ቅዱስ ክብር ሆኖት አይደለም።
ኢየሱስ ክርስቶስ ቃለ እግዚአብሔር ነው። ይህም ማለት ቃለ አብ፣ ቃለ መንፈስ ቅዱስ ነው ማለታችን ነው። በአንድ ህልውና በአንድ ባሕርይ ለሚኖሩ ሦስቱ አካላት ቃላቸው እርሱ ነው። ይህ ቃል ከሰው፣ ከእንስሳት፣ ከመላእክት ቃል (ድምፅ) የተለየ ነው። እነዚህ ቃላት (ድምፆች) ዝርዋን ናቸው እንጂ አካላውያን አይደሉም። ቃለ እግዚአብሔር አአትሪኮን፣ አተርጋዎን፣ ቦርፎሪኮን ከሚባሉት ቃላት የተለየ ቃል ነው።
ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር የሰሙት ድምፅ እንኳ ዝርው ነው። አካላዊ ቃል የሚባለው ከሦስቱ አካላት አንዱ አካል ነው። ከንባብ (ንግግር) የተለየ አካላዊ ቃል ነው። ይህ ቃል ሥጋ ሆነ። ይህም ማለት ረቂቁ አካለ ቃል ግዙፉን አካለ ሥጋ በተዋሕዶ ገንዘቡ አደረገው ማለታችን ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ምድር እየተመላለሰ ሲያስተምር ለሕዝቡ ጆሮ ይሰማ የነበረው ድምፅ ዝርው ስለሆነ አካላዊ አይደለም። ራሱ ክርስቶስ ግን አካላዊ ቃል ነው። እርሱ የተናገረው ንግግር ግን ከእርሱ ከአካላዊ ቃል የተገኘ ንግግር (ንባብ) ነው እንጂ ራሱ ንግግሩ አካላዊ አልነበረም።
© መ/ር በትረማርያም አበባው
የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው። | 261 |
| 3 | ክፍል ፫
አማኑኤል
አማኑኤል ማለት እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆነ (እግዚአብሔር ምስሌነ) ማለት ነው። እግዚአብሔር በአካል ከፍጥረቱ ተለይቶ አያውቅም። እርሱ በአካል የሌለበት ቦታ የለምና። በረድኤትም በብሉይ ኪዳን ከቅዱሳን አበው፣ ከቅዱሳን ነቢያትና፣ ከቅዱሳን ነገሥታት ጋር ነበር። ይህኛው "ምስሌነ" ግን አነጋገሩ ከረድኤት የተለየ "ምስሌነ" ነው። በረድኤት ከእኛ ጋር መኖርን ብቻ የሚገልጽ አይደለም። የእኛን ሥጋ ተዋሕዶ ከእኛ ጋር መኖሩንም የሚገልጽ አነጋገር ነው። አማኑኤል የሚለው ስም ስመ ሥጋዌውን የሚገልጽ ስም ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ እኛን ለማዳን እንደእኛ ሰው ሆኖ ክሦ፣ ቤዛ ሆኖ አድኖናል።
እንግዲህ ምንንም፣ ማንንም አንፈራም። የሚያስፈራን ፍጡር የለም። ምክንያቱም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው። በእምቢታችን ጸንተን፣ በራሳችን ፈቃድ ከእግዚአብሔር ጋር መኖር አንፈልግም ብለን ከሰይጣን ጋር ካልተባበርን በስተቀር እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ስለሆነ በእርሱ ሁሉን አሸንፈን እንኖራለን።
እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ሆኖ ነጻነትን መለሰልን፣ ፍጹም መንፈሳዊ ደስታን ሰጠን። እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ከሆነ ሁሉ አለን። ኵሉ ብነ እንዘ አልብነ ኵሉ እንዳለ።
© በትረማርያም አበባው
የፌስቡክ ገጼ:- Betremariam Abebaw
https://www.facebook.com/profile.php?id=100075547015721 ነው።
የዩቲይብ ቻናሌ:- ንሕነ ዘክርስቶስ
https://youtube.com/@edenawizechristos?si=6V4y-73OM3LTzhAf ነው። | 228 |
| 4 | No text... | 251 |
| 5 | ክፍል ፩
_ኢየሱስ_
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሚጠራባቸው ስሞች አንዱ ኢየሱስ ነው። ኢየሱስ ማለት መድኃኒት ማለት ነው። ዓለም በአዳም በደል ምክንያት ታሞ ይኖር ነበር። ዓለምን መፈወስ የቻለ ሰው ደግሞ እስከ ክርስቶስ ልደት ድረስ አልተገኘም ነበር። ስለዚህ ዓለምን ለማዳን ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ፣ ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ተዋሐደ። ዓለምን የማዳን ሥራውም ከማኅፀን በተዋሕዶ ጀመረ። በዓለም ላይ ብዙ መድኃኒቶች ቢኖሩም መድኃኒትነታቸው የጸጋ ማዳን ነው። በባሕርይው አዳኝ የሆነ እግዚአብሔር ነው። እርሱ እግዚአብሔር ሥጋን ተዋሕዶ አድኖናልና ኢየሱስ ተብሏል። ሰውን ያዳነው፣ ወደቀደመ ቦታውም የመለሰው ኢየሱስ ነው። ሌሎች ፍጡራን ቢያድኑ ግን ማዳንን ከክርስቶስ በጸጋ ተቀብለው ነው። ኢየሱስ የሚለው ስም በአማርኛ መድኃኒት፣ መድኃኒ ዓለመ፣ መድኃኔ ዓለም ተብሎ ሊገለጽ ይችላል።
የኢየሱስ ስሙ፣ አካሉ፣ ሁለንተናው አዳኝ ነው። ስለሆነም በየጊዜው በየሰዓቱ ከሰይጣን ተንኮል ያድነን ዘንድ ስሙን እንጠራለን። ስለሆነም እንደ ደራሲው ኢየሱስ ኢየሱስ ኢየሱስ ሠረፀ እምቤተ ሌዊ፣ ኮሬባዊ መለኮታዊ፣ ቃል ሰማያዊ እምድንግል ተወልደ እንለዋለን።
© በትረማርያም አበባው | 252 |
| 6 | ክፍል ፪
ክርስቶስ
ክርስቶስ በዕብራይስጥ ማስያስ፣ በዐረብ መሢሕ፣ በግሪክ ክርስቶስ፣ በግእዝ ቅቡዕ ማለት ነው። ቅቡዕ ማለትም የተቀባ ማለት ነው። ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው የሆነ አምላክ፣ አምላክ የሆነ ሰው ነው። ወልደ እግዚአብሔር ከድንግል ማርያም የነሣውን ሥጋ ሲዋሐድ በአምላክነት አከበረው። ሥጋም ቃልን ስለተዋሐደ ከብረ። ስለዚህም ቅቡዕ ተባለ። ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው መባሉ በሰውነቱ እንደሆነ ሁሉ ቅቡዕ መባሉም በሰውነቱ ነው። በአምላክነቱ ክብርን (ቅብዕን) የሚሻ አይደለምና። ክርስቶስ ለተዋሐደው ሥጋ ክብር የሆነውም ራሱ ቃል ነው። እንጂ የቅባት እምነት አራማጆች እንደሚሉት መንፈስቅዱስ ቅብዕ (ክብር) አልሆነውም። በሥላሴ ዘንድ ቅብዕ፣ ተቀባዒ፣ ቅቡዕ የሚል አካላዊ ግብር የለምና። በማክበር፣ በክብር አንድ ስለሆኑ አብ አከበረው፣ ወልድ አከበረው፣ መንፈስ ቅዱስ አከበረው ቢል አንድ ነው። ለሥጋ ክብር የሆነው በተለየ አካሉ ቃል ነው። ምክንያቱም ሥጋ ቃልን ሆነ እንጂ ልብን ወይም እስትንፋስን አልሆነምና ነው። ሥጋ ከበረ መባሉ እንኳ ቃልን ሆነ ማለት ነውና።
ክፍል ፫ ይቀጥላል።
© በትረማርያም አበባው | 247 |
| 7 | https://telegra.ph/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5-%E1%89%82%E1%88%AD%E1%89%86%E1%88%B5-%E1%8A%A5%E1%8A%93-%E1%89%85%E1%8B%B5%E1%88%B5%E1%89%B5-%E1%8A%A2%E1%8B%A8%E1%88%89%E1%8C%A3-01-24 | 267 |
| 8 | ክርስቶስ ማን ነው?
√ ቅድመ ዓለም የነበረ የአብ ልጅ ነው።
√ ከድንግል ማርያም የተወለደ ፍጹም ሰው ነው።
√ ፍጹም አምላክ ነው
√ ፍጥረታትን ሁሉ የፈጠረ ነው።
√ የአብና የመንፈስ ቅዱስ ቃላቸው ነው።
√ አዳምን ለማዳን ሥጋን የተዋሐደ ነው።
√ ቤዛችን፣ መድኃኒታችን፣ ጌታችን ነው።
√ ክርስቶስ እግዚአብሔር ነው።
√ ክርስቶስ ንጉሠ ነገሥት፣ አምላክ ነው
√ ከሁለት አካል አንድ አካል፣ ከሁለት ባሕርይ አንድ ባሕርይ የሆነ ነው። ሰው የሆነ አምላክ፣ አምላክ የሆነ ሰው ነው። አምላክም ሰውም ነው።
በቅዱሳት መጻሕፍት ራሱ ስለራሱ የነገረን ይህንና የመሳሰለውን ነው። ሁልጊዜም እኛን ለማዳን ስለኛ ቤዛ ሆኖ በመስቀል የተሰቀለልንን ጌታ እናስበዋለን። መመኪያችን፣ ደስታችን፣ ሕይወታችን እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው።
© በትረማርያም አበባው | 253 |
| 9 | ቤተክርስቲያን የተመሠረተችው በክርስቶስ ላይ ነው። ስለሆነም አካሉ ናት። የቤተክርስቲያን አገልግሎት ሁሉ ማዕከሉ ክርስቶስ ኢየሱስ ነው። ብዙ ጊዜ የቤተክርስቲያንን ትምህርት ጠንቅቀው ሳያውቁ ትተዋት የሄዱ ሰዎች ማንነቷን ሳያውቁ ሲሳደቡ ይስተዋላል። በማንነቷ ሳይሆን እነርሱ ናት ባሏት ማንነት ይሰድቧታል። ነገር ግን ይህ አይገርምም። አካሏ ክርስቶስ ምንም ጥፋት ሳይኖርበት በአደባባይ ተሰድቧል። በአደባባይ ተሰቅሏልና።
ስለዚህ የሌላ እምነት ሰዎች ቤተክርስቲያን ስለኢየሱስ የምታስተምረው ምን እንደሆነ መጀመሪያ ጠይቁ እወቁ። የቤተክርስቲያን አካል፣ የቤተክርስቲያን ሕይወት በመስቀል ተሰቅሎ ያዳነን ኢየሱስ ነው።
"እኛስ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን" ቅዱስ ጳውሎስ | 246 |
| 10 | የቃናውን ወይን የቃና ሰርገኞች ጠጥተው ጨርሰውታል። ከትውልድ ወደ ትውልድ ሳይተላለፍ በታሪክ ብቻ እንማረዋለን። የቀራንዮውን ወይን ግን እስከ ዕለተ ምጽአት ምእመናን ንሥሓ እየገቡ ይጠጡታል። እርሱም ንጽሐ ሥጋን ንጽሐ ነፍስን ያጎናጽፋቸዋል። ለምእመና ልዩ ቀን (ዕለት ኅሪት) ንሥሓ ገብተው ከዘለዓለማዊው ወይን የሚጠጡበት ቀን ናት።
#ዕለት #ኅሪት #ዕለተ #መድኃኒት
እስራኤላውያን ከግብፅ የወጡባት ቀን ዕለት ኅሪት ትባላለች። ባሕረ ኤርትራን የተሻጉረባት ቀን ደግሞ ዕለተ መድኃኒት ትባላለች። ጌታ የተፀነሰባት ዕለት ዕለት ኅሪት ትባላለች። የተወለደባት ቀን ደግሞ ዕለተ መድኃኒት ትባላለች። አንድም የተወለደባት ቀን ዕለት ኅሪት ትባላለች። የተሰቀለባት ቀን ዕለተ መድኃኒት ትባላለች። አንድም የተሰቀለባት ቀን ዕለት ኅሪት ትባላለች። ከሙታን የተነሣባት ቀን ዕለተ መድኃኒት ተብላበች። ሰው ንሥሓ የሚገባባት ቀን ዕለት ኅሪት ትባላለች። ሥጋውን ደሙን የሚቀበልባት ቀን ደግሞ ዕለተ መድኃኒት ትባላለች። ዕለት ኅሪት፣ ዕለተ መድኃኒት በንባብ እንጂ በምሥጢር አንድ ናቸው።
ጌታ ጥር ፲፩ በውሃ ተጠመቀ። በዕለተ ዐርብ ከጎኑ በፈሰሰው ንጹሕ ውሃ (ማየ ገቦ) ደግሞ እኛ እንድንጠመቅ አደረገን። ጌታ በቃና ዘገሊላ ውሃውን ወደ ወይን ለውጦ ሠርገኞችን አስደሰታቸው። ወይን ያስተፌሥሕ ልበ ሰብእ ማለትኮ ይህ ነው። ወይን ደመ ክርስቶስ ምእመናንን ያስደስታል። በዕለተ ዓርብ ደሙን አፍስሶ አነጻን። ወይን ክርስቶስ እስከ ዕለተ ምጽአት ለሚነሡ ምእመናን መድኃኒት የሚሆን መጠጥን ሰጠን።
ስለ ቃና ወይን ስንናገር ንሥሓ ገብተን ዋናውን ወይን ደመ ክርስቶስን መቀበል ይገባናል። | 243 |
| 11 | በእምነታቸዉ_ዳኑ_አዲስ_የ_ቅዱስ_ገብርኤል_ዝማሬ_ዲ_ን_አቤል_ተስፋዬ360p.mp3 | 240 |
| 12 | *ሰኞ - ጥር 13 2016 ዓ.ም*
*ዘፍጥረት 1-5*
በዛሬው እለት ኦሪት ዘፍጥረት ምዕራፍ 1 እስከ 5 ድረስ እናነባለን። በእነዚህ ምዕራፎች ውስጥ እግዚአብሔር በስድስት ቀናት ውስጥ ፍጥረታትን እንዴት እንደፈጠረ፥ በስድስተኛው ቀን አዳምና ሔዋንን ፈጥሮ በሰባተኛው ቀን እንዳረፈ እናነባለን። በገነት ውስጥ አዳም እና ሔዋን እግዚአብሔርን እንዳልታዘዙ፥ በዚህም ምክንያት ከገነት እንደተባረሩም ተጽፎ ይገኛል። በተጨማሪም በልጆቻቸው በአቤል እና በቃየን መካከል ችግር ተፈጥሮ፥ ቃየን ወንድሙ አቤልን እንደገደለው የምናነበውም በእነዚህ ምዕራፎች ውስጥ ነው። በምዕራፍ አምስት ላይ ከአዳም እስከ ኖኅ ድረስ ያለውን የዘር ግንድ የምናገኝ ሲሆን፥ ይህም ቀጣይ ለምናነባቸው ታሪኮች ያዘጋጀናል።
*የክለሳ ጥያቄዎች*
1) እግዚአብሔር በመጀመሪያው ቀን ምን ፈጠረ?
2) እግዚአብሔር የሰው ልጅን የፈጠረው በስንተኛው ቀን ነው?
3) በዘፍጥረት 2 መሠረት፥ አዳም የተፈጠረው እንዴት ነው?
4) እግዚአብሔር በገነት ውስጥ ለአዳም እና ሔዋን የሰጠው ኃላፊነት ምን ነበር?
5) አዳም እና ሔዋን እግዚአብሔርን ባለመታዘዝ የበሉት ምን ነበር?
6) የአዳም እና ሔዋን አለመታዘዝ ምን ውጤት አስከተለ?
7) በዘፍጥረት 4 ላይ የተጠቀሱት የአዳም እና የሔዋን ልጆች እነማን ናቸው?
8) በአቤልና ቃየን መካከል የነበረው ግጭት በምን ተነሳ? ፍጻሜውስ ምን ሆነ?
9) በዘፍጥረት 5 ያለው የዘር ግንድ ዓላማው ምንድር ነው?
10) በዘፍጥረት 5 መጨረሻ ላይ የተጠቀሰው ሰው ማን ነው?
ለውይይት እና ክትትል እንዲመች ከዚህ በኃላ ንባቡን ለመቀጠል የሚከተለውን join አድርጉ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/+3kpzSPDfiVMzYzQ0 https://t.me/BetMetsahfte | 113 |
| 13 | + የትውውቅ መርሐ ግብር + (ቻሌንጅ/ሞክረኛ)
ከውሃ የወጣ ዓሳ፥ ከአፈር የተነቀለ ተክል፥ ከአየር የተለየ ሰው ሙት መሆኑ እርግጥ ነው። ለክርስቲያን ደግሞ ሞቱ ከእግዚአብሔር መለየት ነው። አንድ ክርስቲያን ከእግዚአብሔር ቃል ጋር ያለው ግንኙነት ከተቋረጠ፥ በጸሎትም አምላኩን ማነጋገሩን ከተወ የሞቱ ዋዜማ ላይ መሆኑን እንረዳለን። የቫይታሚን እጥረት የሰውነት መቀንጨርን እንደሚያስከትል ሁሉ፥ ከእግዚአብሔር ቃል ስንለይ መንፈሳዊ ሕይወታችን ይቀነጭራል። ይህ እንዳይሆን መጸለይ፥ የእግዚአብሔርም ቃል በውስጣችን እንዲያድር ቅዱስ መጽሐፉን በርትተን በጸሎት መንፈስ ማንበብ ይኖርብናል።
ብዙ ጊዜ “ሰው ከእግዚአብሔር ቃል አልገናኝ አለ! ሰው የአምላኩን ቃል አያውቅም!” ወዘተ እየተባለ አስተያየት ሲሰጥ ይስተዋላል። በእርግጥ እውነት ሊሆን ይችላል። ሆኖም ግን ችግሩን እያገዘፉ ከመኖር፥ መፍትሔው ላይ ማተኮሩ ብልህነት ነው። ጨለማውን እያማረሩ መኖር ይቻላል፤ ወይም ደግሞ እንደ አቅማችን ሻማ መለኮስ። ምርጫው እንግዲህ የእኛው ነው።
ይህንን ታሳቢ በማድረግ አንድ ቻሌንጅ/ሞክረኛ አዘጋጅቻለሁ። ይህም ቻሌንጅ መጽሐፍ ቅዱስን ከኦሪት ዘፍጥረት አንስቶ እስከ ዮሐንስ ራእይ ድረስ በስድስት ወር ውስጥ አንብቦ ማጠናቀቅ ነው። በአጭሩ ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር የሚደረግ የትውውቅ መርሐ ግብር ብሎ ማሰብ ይቻላል። መጽሐፍ ቅዱስ ሁሌም አዲስ እንደመሆኑ፥ ሁሌም ትውውቅ ይፈልጋል። “አውቄዋለሁ። ጨርሼዋለሁ።” የሚል ቃል ለመጽሐፍ ቅዱስ አይሠራም። ቤተ-ክርስቲያንንም ለመረዳት ትልቁ ቁልፍ መጽሐፍ ቅዱስ መሆኑ እሙን ነው። እግዚአብሔር ቢፈቅድ እና ብንኖር፥ በዓመት ሁለት ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስን ከጫፍ እስከ ጫፍ ማንበብ እንችላለን ማለት ነው። ንባቡን ሳያውቁ ምስጢሩን መጠየቅ የማይሆን ነውና፥ አስቀድመን ንባቡን ማወቅ ይገባል። ጥልቅ የሆነው የእውቀት ጉዞም የሚነሳው ማንበብ ከመጀመር ነው።
ክርስትና የኅብረት ጉዞ እንደመሆኑ መጠን፥ ይኽም ጉዞ የኅብረት ቢሆን ጥቅሙ ብዙ ነው። እግዚአብሔር ቢፈቅድ ይህ ጉዞ በነገው እለት ጥር 13 2016 ይጀምርና ሐምሌ 16 2016 ይጠናቀቃል። ይኽንን ጉዞ አብራችሁ ከእኔ ጋር ለመጓዝ ፈቃደኛ የሆናችሁ ሁሉ፥ በኮሜንት ላይ አሳውቁኝ። የፌስቡክ ቻት ግሩፕ ከፍተን አብረን ጉዞውን እንጀምራለን።
ኑ፥ ከእግዚአብሔር ቃል ጋር አብረን እንጓዝ!
🖋 Fresenbet G.Y Adhanom | 271 |
| 14 | ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን በጥር ፲፪ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቃና ዘገሊላ በተደረገ ሠርግ ቤት ያደረገውን ተአምር በማሰብ በዓልን ታደርጋለች፡፡ ጌታችን ከጥምቀቱ በኋላ በዶኪማስ ሠርግ ቤተ ከእናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም እንዲሁም ከደቀ መዛሙርቱ ጋር ታጋብዞ በነበረበት ጊዜ ለእንግዶች ወይን ጠጅ አለቀባቸው፡፡
በዚህም ጊዜ “እናቱ ጌታችን ኢየሱስን የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም” አለችው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም “ አንቺ ሴት ሆይ ካንቺ ጋር ምን አለኝ? ጊዜዬ ገና አልደረሰም” አላት፡፡ እናቱም ለአሳላፊዎቹ “የሚላችሁን ሁሉ አድርጉ” አለቻቸው፡፡ በዚህም እንደ አይሁድ ልማድ የሚያነጹባቸው ስድስት የድንጋይ ጋኖች ነበሩ፡፡ ከእነርሱም እያንዳንዱ ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዙ ነበር፡፡ ጌታችን ኢየሱስም “ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው” አላቸው፤ እስከ አፋቸውም እስከ ላይ ሞሉአቸው፡፡ አሁንም ቀዱና ወስደውም ሰጡት፡፡ አሳዳሪውም ያን የወይን ጠጅ የሆነውን ውኃ ቀምሶ አደነቀ፤ ከወዴት እንደመጣም አላወቀም፤ የቀዱት አሳላፊዎች ግን የወይን ጠጅ የሆነውን ያን ውኃ ያውቁ ነበር፡፡ ውኃውን የሞሉ እነርሱ ነበሩና፡፡ አሳዳሪውም ሙሽራውን ጠርቶ “ሰው ሁሉ መልካሙን የወይን ጠጅ አስቀድሞ ያጠጣል፤ ከጠገቡ በኋላም ተርታውንም ያመጣል፤ አንተ ግን መልካሙን የወይን ጠጅ እስከአሁን አቆየህ” አለው፡፡ ጌታችን ኢየሱስም በቃና ዘገሊላ ያደረገው የተአምራት መጀመሪያ ይህ ነው፤ ክብሩንም ገለጠ፤ ደቀ መዛሙርትም አመኑበት፡፡ (ዮሐ.፪፥፩-፲፩) | 270 |
| 15 | የጥንቷን ቤተ ክርስቲያን ካላወቅሃት፣ አማናዊው ክርስትና፣ ኦርቶዶክሳዊ ማንነት ከሌለህ እንዲህ አንዲት ጠብታ ጸበል ግንባሬ ላይ እስክታርፍ መጋፋቴ አይገ'ለጽልህም።
አንዲት ጠብታ መለኮታዊ ጸጋ ያረፈባት ጸበል ለነፍሴ እንዴት ያለ ፍስሐ፣ እንዴት ያለ ጸጋ እንደምታጎናጽፍልኝ ምስክሩ እኔው ነኝ።
#ኦርቶዶክሳዊነት! | 278 |
| 16 | ጌታ ለምን ተጠመቀ?
፩) ማያትን ይቀድስ ዘንድ
፪) ለተጠማቅያን አብነት ለመሆን
፫) ትንቢቱን ለመፈጸም
#ጌታ #የት #ተጠመቀ
፩) ዮርዳኖስ በተባለ ወንዝ
#ኢየሱስ #በማን #ተጠመቀ
፩) በዮሐንስ መጥምቅ
#ክርስቶስ #በምን #ተጠመቀ
፩) በውሃ
#በዮርዳኖስ #ለምን #ተጠመቀ
፩) የአዳምንና የሔዋንን የዕዳ ደብዳቤ ለመሻር
#መድኃኔዓለም #መቼ #ተጠመቀ
በ30 ዓመቱ፣ ጥር 11 ቀን በዕለተ ማክሰኞ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ተጠመቀ።
#አማኑኤል #ሲጠመቅ #ምን #ሆነ
ዮሐንስ መጥምቅ ውሃ በእፍኙ አድርጎ በጌታ ራስ ሲያደርግ ውሃዎች በጌታ ራስ ላይ ሳሉ ይፈሉ ነበር። ማያት ፈልሁ ዲበ ርእሱ እንዲል። በተጨማሪም መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በራሱ ላይ አረፈ። አብም የምወደው ልጄ ይህ ነው ብሎ በደመና ላይ ድምፁን አሰማ።
#ምእመናን #ልጅነትን #ለማግኘት #በምን #ይጠመቃሉ
፩) ከክርስቶስ ጎን ከፈሰሰው ማየ ገቦ
#ሰዎች #ሲጠመቁ #ምን #ይሆናሉ?
፩ የእግዚአብሔር የጸጋ ልጆች ይሆናሉ።
፪) ከጥምቀት በፊት የሠሩት ኃጢአት ይሠረይላቸዋል።
ካህኑ ውሃውን አቅርቦ ጸሎትን ሲጸልይበት ውሃው ከክርስቶስ ጎን የፈሰሰውን ማየ ገቦ ይሆናል። ማየ ገቦ ደግሞ መለኮት የተዋሐደው ውሃ ነው። ስለዚህ በዚያ ተጠምቀን የእግዚአብሔር ልጆች እንሆናለን። ሕፃናት ወንዶች በ40 ቀን፣ ሴቶች በ80 ቀን ይጠመቃሉ። ንኡሰ ክርስቲያን ደግሞ ሦስት ዓመት የሃይማኖትን ትምህርት ተምረው በማንኛውም የእድሜ ጊዜ ሳሉ ይጠመቃሉ።
ምሥጢረ ጥምቀት ከአምስቱ አዕማደ ምሥጢር ስለሆነ ማንኛውም ክርስቲያን ሊያውቀው ይገባል።
©Kidmegibigubae | 279 |
| 17 | መንጽሔ አበሳ ወሀበነ ማየ።
ኃጢአትን የሚያስተሠርይ ንጹሕ ውሃን (ማየ ገቦን) ሰጠን። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይገባል።
እንኳን አደረሳችሁ። | 286 |
| 18 | ከተራ ምንድን ነው?
ከተራ 'ከበበ' ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡
በጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰቡ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላሉ፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥሉ ይውላሉ፡፡ የምንጮች ውኃ እንዲጠራቀም ይከተራሉ (ይገድባሉ) ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ በመገደብ ለመጠመቂያ (ለጥር 11) ዝግጁ የሚያደርጉበት ዕለት ነው፡፡
በተጨማሪ በአቅራቢያ የሚገኙት ቤተክርስቲያናት ተሰብስበው ከዚሁ ከተቆፈረው ገንዳ ወይም ከተገደበው ጅረት አጠገብ ባለው ዳስ ወይም ድንኳን ታቦቶቻቸውን ያሳድራሉ ሊቃውንቱም በዚያው እግዚአብሔርን በማህሌት ሲያመሰግኑ ያድራሉ።
በበዓለ ጥምቀት የታቦታቱ ወደ ወንዝ መውረድ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ ለመጠመቅ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ የመሄዱ ምሳሌ ነው፡፡ ታቦቱ የጌታችን፣ ምሳሌ ሲሆኑ ካህናቱ የመጥምቁ ዮሐንስ ምሳሌ ናቸው፡፡ መዘምራኑና ሕዝቡ ደግሞ ዮሐንስ ያጠመቃቸው ሕዝቦች ምሳሌዎች ናቸው፡፡
መልካም የከተራ በዓል | 425 |
| 19 | ውድ የቤተ ክርስቲያን ቤተሰቦች እንደምን አመሻቹ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን
ነገ ማለትም 10/05/2016 በበዓለ ከተራ የቃል ኪዳኑን ታቦት አጅበን "ሆረ ኢየሱስ እምገሊላ ሐበ ዮሐንስ " እያልን በደስታ እና በዝማሬ የቃልኪዳኑን ታቦት ወደ ጥምቀተ ባህሩ እንደምንወስድ ይታወቃል ስለዚህ ሁላችንም የቅድመ ግቢ ተማሪዎች ብንችል በደብረ አሚን ቅዱስ ጊዮርጊስ ተገኝተን የማንችል ልጆች ደግሞ ከሚቀርቡን አብያተ ክርስቲያናት በመገኘት የቃልኪዳኑን ታቦት እንድናጅብ እና የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆን ይላል
ቅድመ ግቢ ጉባኤ | 306 |
| 20 | ፲.ሥላሴ (አቤል ተስፋዬ).mp3 | 336 |
