en
Feedback
መቂ ቅድመ ግቢ ጉባዔ

መቂ ቅድመ ግቢ ጉባዔ

Open in Telegram
241
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለመመለስ አፍረው ነው እንጂ እውነቱን ያውቋታል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አስተምህሮዋ እንከን የሌለበት ንጹሕ እውነት እንደሆነ ያውቁታል። አንዳንዶች ለሥጋ አድልተው እውነትን ገፍተው ቢሄዱም ኅሊናቸው ሲያሳድዳቸው ይኖራል። ይሁዳ ለገንዘብ ብሎ ከኅሊናው ተጣልቶ ከእውነተኛው ኢየሱስ ርቆ ነበር። በዚያው ክፋቱ እንደጸና ሞቷል። ኢየሱስ የዓለም መድኃኒት ነው። እኛን ለማዳን ስለእኛ ተወልዶ በመስቀል ተሰቅሎ ያዳነን ቤዛችን ነው። ተሰቅለ በእንቲኣነ የሚለው በመጽሐፈ ሊቃውንት ሲታተት እንደ ጻድቃን እሴት ሽቶ፣ እንደ ኃጥኣን ስቶ አይደለምና በእንቲኣነ (ስለእኛ) አለ እንላለን። ስለእኛ የሰውነትን ሥራ ሠርቷል። በመስቀል ተሰቅሎም ከአባቱ ጋር አስታርቆናል። ይህንን ቤተክርስቲያን ከሐዋርያት ጀምሮ እስካሁን የምታስተምረው ትምህርት ቢሆንም ከሓድያን ግን እነርሱ በቅርብ የደረሱበትና ቤተክርስቲያን የማታውቀው ያስመስሉታል። ራሳቸው በፈጠሩት ውሸት ሌላውን ለመውቀስ ይጥራሉ። ቅድስት ቤተክርስቲያን ጻድቃንን የጸጋ ክብር ታከብራለች። አንዳንዶች ጻድቃንን ማክበር ክርስቶስን እንዳለማክበር ቆጥረው ቤተክርስቲያንን ሲሰድቧት ይስተዋላል። እንኳንስ በእግዚአብሔር ሕግ ተመርተው እግዚአብሔር የሚወዳቸው ጻድቃንን መውደድና ማክበር ማንኛውንም ሰው እንድንወድኮ ከአሥሩ ሕግ በአንዱ ታዝዘናል። ራሱ ክርስቶስ እንኳ ጻድቃንን "እናንተ የአባቴ ቡሩካን" ብሎ እንደሚጠራቸው በወንጌል ተገልጿል። "ቡሩካን" እንዳላቸው አስተውል። የክርስቶስን እናት ድንግል ማርያምን ለምን ትወዷታላችሁ ብለው ይቀናሉ። ክርስቶስ ሕግን ፈጽሟል። ከሕግ አንዱ ደግሞ እናትን ማክበር ነው። ስለዚህ ክርስቶስ እናቱን አክብሯታል። ታዲያ እርሱ ያከበራትን ብናከብራት ችግሩ ምን ላይ ነው። አምላክ ናት ብለንኮ አይደለም ያከበርናት። አምላክን በሥጋ የወለደች ናት ብለን ነው የምናከብራት። ክብሩም የጸጋ ክብር ነው። ታቦትን የምናከብረው የከበረው የክርስቶስ ሥጋና ደም ስለሚፈተትበት ነው። የኢየሱስ ስም ስለተጻፈበት ነው። የምናከብረው አክብሮትም አምላክ ነው ብለን አይደለም። የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ስሙ ስለተጻፈበት ነው። ክርስቶስን ሁልጊዜ እንድናስብ የሚያደርጉንን ብናከብራቸው እንኳ ክብሩ የጸጋ አክብሮት እንጂ አምላክ ስለሆኑ አይደለም። የቤተክርስቲያን ሥርዓቷ፣ አስተምህሮዋ ንጹሕ ነው። ትምህርቷ የተመሠረተው በኢየሱስ አስተምህሮ ነው። የአንዳንድ አማኞችን ስሕተት አጉልቶ በማሳየት ቤተክርስቲያንን ለመንቀፍ መጣር እውነትን ላለማግኘት የሚደረግ ጥረት ነው። በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ አማኞች ከምእመን እስከ ፓትርያርክ በግላቸው ሥጋዊ ፍላጎት አይሎባቸው ሊሳሳቱ አልፎም ሊክዱ ይችላሉ። ያ ግን የራሳቸው ችግር እንጂ የቤተክርስቲያን አይደለም። በቤተክርስቲያን አስተምህሮ መሄድ አቅቷቸው ቢወድቁ ችግሩ የራሳቸው ነው። በትእቢት ተወጥረው ከእውነተኛው አስተምህሮ አፈንግጠው የሄዱ ሰዎች ከጩኽትና ከእልህ እንዲሁም ከትእቢት ወጥተው በንጹሕ ኅሊና አስተምህሮዋን አይተው ወደ እውነት ቢመለሱ መልካም ነው። ©Kidmegibigubae

+• የተሻለው መንገድ •+ አንድ ነገር በሕይወታችን ሲፈጠር በብዙ አይነት መንገድ ምላሽ ልንሰጥ እንችላለን:: ለክርስቲያን ግን አንድ ከሁሉ የተሻለች መንገድ አለች:: ጸሎት ምርጫ የሌለው የክርስቲያን መንገዱ ነው:: ጭንቀት ቢመጣብህ ጸልይ:: ሐዘን ቢደርስብህ ጸልይ:: ደስታ ብታገኝ ጸልይ:: ብትታመም ጸልይ:: ብትድንም ጸልይ:: ሰዎች ቢበድሉህ ጸልይ:: ሰዎችን እየበደልክ ራስህን ስታገኘውም ጸልይ:: ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።" (1 ተሰ 5:17) የሚለውን እያስታወስክ በሁሉም ሁኔታ ውስጥ ጸልይ:: ዜና አበው ላይ "ክንፍ የሌለው ወፍ፥ ትጥቅ የሌለው ወታደርና፥ የማይጸልይ ሃይማኖተኛ አንድ ናቸው::" የሚል ቃል አለ:: እንግዲህ እወቅበት! ክንፍ እንደሌለው ወፍ እና ትጥቅ እንደሌለው ወታደር እንዳትሆን ሁሌም ጸልይ! 🖋 Fresenbet G.Y Adhanom

ውድ የቤተክርስቲያን ቤተሰቦች ሰላመ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን እያልን !! እንደ እግዚአብሔር መልካም ፈቃድ የጌታችንን ልደት እንደ መላዕክቱ እና እንደ እረኞቹ በዝማሬ እና በደመቀ መልኩ አክብረናል ለህይወታችን ለነፍስ ለስጋችን የሚሆን ስንቅ ሰንቀናል በረከትም አግኝተናል እና ይህን ሁሉ ላስፈፀመን ለቅዱስ እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁን በመቀጠልም ለመርሀ ግብሩ መሳካት ብዙ አስተዋፅኦ ያደረጋቹ እህት ወንድሞቻችን እግዚአብሔር አምላክ ፀጋውን አብዝቶላቹ ከዚህ በላይ እግዚአብሔር የምታገለግሉበትን እድሜና ጤና ያድልልን .... ለማርያም ጌታችን ማርያምስ በጐውን እድል መረጠች እንዳለው ሁሉ በጐውን እድል መርጣቹ በመርሀ ግብሩ ተገኝታቹ የተማራቹ ሁላቹም እግዚአብሔር አምላክ በጐውን እድል ያድልልን እንላለን ቅድመ ግቢ ጉባዔ !!!

እንኳን ለ2016 ዓ.ም. ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል አደረሳችሁ ! ድንግል ሆይ ! ሰው አምላክ መሆን አይችልም ። ሰው አምላክ ለመሆን ፈለገ ፣ ነገር ግን ሞትን አመጣ ። አምላክ ግን ሰው መሆን ይችላል ። አምላክ ሰው ሆኖ ሰውን አምላክ አደረገው ። ሰው በዕፀ በለስ አምላክ ለመሆን ፈለገ ። በዕፅ ያልተገኘን አምላክነት በዕፅ ፈለገው ። አዳም በዕፀ በለስ አምላክነትን ሲፈልግ ፣ አምላክ አምላክነትን ያገኘው በቅጠል ነው ብሎ ማመኑ ነው ። በዚህም እግዚአብሔርን ተዳፈረ ። በቅጠል ያልተገኘ አምላክነትን በቅጠል መፈለግ ትርፉ ውርደት ነው ። ቅጠል ሐሰተኛ ትልቅነትን ያመጣል ። ዛሬም አደንዛዥ ዕፁ ያልሆኑትን እንደሆኑ እንዲሰማቸው ያደርጋል ። ድንግል ሆይ አምላክነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነ ፣ በኃይል የሚነጥቀው የሌለ ፣ በፈቃዱ ለሰው አምላክነትን የሰጠ እርሱ ቡሩክ ነው ። ቃል ሥጋ ሆነ ። አምላክ ሰው ሆነ ። አምላክ ሰው ነው አይባልም ። በሁነት/በመሆን ግን አምላክ ሰው ሆነ ። አምላክ ሰው በመሆኑም ሰው አምላክ ሆነ ። ድንግል ሆይ ይህን ባየሽ ጊዜ የሰው ሩጫ በልብስ እሳትን ለመጫር ፣ በዋሻ ፀሐይን ለማሰር መሞከር አይደለም ወይ  አምላክ የእርሱ ያልሆነውን ሰውነት ገንዘብ ባደረገ ጊዜ ፣ ሰውም ከተዋሕዶ የተነሣ የእርሱ ያልሆነውን አምላክነት ገንዘብ አደረገ ። የምድር ገዥው አዳም ፣ በበደሉ እርሱንም አጣ ። በተዋሕዶ ግን በሰማይና በምድር ሥልጣን አገኘ ። የከበረው ጥቁር ወይም ነጭ የሰው ዘር ሳይሆን መለኮት የተዋሐደው ባሕርየ ሰብእ ነውና ሰው የአምላክ ዘመድ ሆነ ። ዛሬ በመቃብር ሥጋችንን ብናየው ፣ በሥላሴ ዙፋንም እያየነው ነው ። “ትንሽ ሥጋ ከመርፌ ትወጋ” እንዲሉ መለኮትም ሥጋን ለዘላለም በመቃብር አይተወዉም ። ሙሴ ከቤተ መንግሥት ተሰድዶ ልዑል መባልን አስቀምጦ በኮሬብ ተገኘ ። የልዑል አብ ልጅም ክብሩን ትቶ መጣ ። ክብሩን አላጣም ። ክብሩን ሸፍኖ በሥጋ ትሕትና ተገለጠ ። ልዑል በዚህ ምድር ተሰደደ ፣ ሙሴ በወገኑ ቅንዓት ክርስቶስም በሰው ልጆች ቅንዓት ይህን አደረገ ። ሙሴ በደብረ ኮሬን ለቀናለት ሕዝብ የነጻነት ዜና ሰማ ፣ ክርስቶስም በደብረ ቀራንዮ ለቀናለት የሰው ልጅ ድኅነት አመጣ ። እርሱ በዚህ ልክ ዝቅ ካላለ እኛ ከፍ ማለት አንችልም ። የሰው ብልሽት አያል ነውና የሠራው እጅ ካልሆነ ማንም አያበጀውም ። ሰው ዘመደ አምላክ በመሆን ዳነ ። ድንግል ሆይ ለዚህም ድልድይ እንድትሆኚ የተመረጥሽ አንቺ ነሽ ! ምስጋና በመቅደስ ፣ ምስጋና በሰማይ ይሰማ ነበር ። አሁን ግን በማኅፀንሽ የምስጋና አደባባይ ተሠራ ። ሰማይን ለማየት ቀድሞ ቀና ማለት ይገባ ነበር ፣ አሁን ግን ዝቅ ብለሽ የመላእክትን ምስጋና ሰማሽ ። ሊቀ ካህኑ በዓመት አንድ ጊዜ የሚገባባት ኅቱም መቅደስ አንቺ ነሽ ። ሊቀ ካህናት ክርስቶስ በገባበት ማኅፀንም ፍጡር ሊቀመጥ አይችልም ። የወልድ እናቱ ፣ ወላዲተ አምላክ ተብለሽ የምትጠሪ ፣ ሁሉን አጥተሸ ሁሉን ያገኘሽ ፣ በነፍስሽ ሰይፍ አልፎ እሞሙ ለሰማዕታት የተባልሽ አንቺ ነሽ ። ድንግል ሆይ ልጅሽን በወለድሽ ጊዜ የተሰማሽ ደስታ በእኛም በምንወድሽ ይደርብን ! አሜን ! ይቀጥላል .......

ውድ የቤተ ክርስቲያን ቤተሰቦች ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን እያልን ነገ ማለትም ታኅሳስ 29 ቀን ቅድመ ግቢያችን የክርስቶስን ልደት በድምቀት ያከብራል። በመሆኑም እረኞች በልደቱ ክርስቶስን ለማመስገን ከመላዕክቱ ጋር ሆነው ለምስጋና እንደተባበሩ ሁሉ እኛም ነገ መርሀ ግብሩ ላይ በመገኘት የበረከቱ ተካፋይ እንድንሆን እያልን በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን። ማሳስቢያ፦ መርሀ ግብሩ የሚጀመረው 8፡00 ስለሆነ ሁላችንም ቀደም ብለን በመገኘት ለመርሀ ግብሩ በጊዜ መፈፀም አስተዋፅኦአችንን እንድናደርግ ስንል እናሳስባለን። ቦታ ፦ ደ/አ/ቅ/ጊ/ሰ/ት/ቤት(ቅድመ ግቢ መማርያ) አደራሽ ሰዓት፦ 8:00 ቅድመ ግቢ ጉባዔ አይቀርም !!!

የገና ጨዋታ ሰብአ ሰገል በኮከብ እየተመሩ ወደ ቤተልሔም ሲሔዱ “የተወለደው የአይሁድ ንጉስ ወዴት አለ” በማለት ቢጠይቁ ይህንን አስደንጋጭ ጥያቄ የሰማው ንጉሥ ሔሮድስ “እኔ ንጉሥ ሆኜ ሳለሁ ሌላ ን
የገና ጨዋታ ሰብአ ሰገል በኮከብ እየተመሩ ወደ ቤተልሔም ሲሔዱ “የተወለደው የአይሁድ ንጉስ ወዴት አለ” በማለት ቢጠይቁ ይህንን አስደንጋጭ ጥያቄ የሰማው ንጉሥ ሔሮድስ “እኔ ንጉሥ ሆኜ ሳለሁ ሌላ ንጉሥ እንዴት ይወለዳል” በማለት የተወለደውን ንጉሥ ለመግደል አገልጋዮቹን ከሰብአ ሰገል ጋር ሄደው ቦታውን አይተው እንዲመለሱ ላካቸው፡፡ የሔሮድስ አገልጋዮች ከተቀላቀሉ በኋላ እየመራ ያመጣቸው ኮከብ ጌታ የተወለደበትን ቦታ መምራቱን አቆመ፡፡ ሰብአ ሰገል ተጨንቀው “የኮከቡ እርዳታ ለምን ተለየን” ብለው ሲመረምሩ ከነሱ ዓላማ ውጭ ሌላ ሀሳብና ተንኮል ይዘው የተገኙ ሰዎችን አገኙ፡፡ “በእናንተ ምክንያት የእግዚአብሔርን እርዳታ አጣን”፡፡ ብለው ሦስቱም ነገሥታት(ሰብአ ሰገል) ከአንዱ ወደ አንዱ እየተቀባበሉ በብትር እየመቱ አስወገዷቸው፡፡ ኮከቡም እየመራ ጌታ በተወለደበት ቦታ ቤተልሔም አደረሳቸው ከእረኞችና ከመላእክት ጋራ አመሰገኑት፡፡ እረኞች ጌታ በተወለደ ጊዜ ጨለማ ተሸንፎ አካባቢያቸው በብርሃን ተመልቶ መንፈስ ቅዱስ በገለጸላቸው ምስጢር ከመላእክት ጋራ “ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ሥምረቱ ለሰብእ” እያሉ ሲያመስግኑና ሲደሰቱ አድረዋል፡፡ በዓሉ እረኞች ክብር ያገኙበት ምስጢር የተገለጠላቸው ስለሆነ በስነ ቃል “በገና ጨዋታ አይቆጡም ጌታ” እየተባለም በጨዋታ እንደሚከበር እንደሆነ አበው ይናገራሉ፡፡ ይህ ትውፊት የገና ጨዋታ እየተባለ ወጣቶች አዛውንቶች በጨዋታ ያከብሩታል፡፡ ራሱ የተቆለመመውና ሩሯን የሚያጎነው በትር የጌታችን ምሳሌ ሲሆን ሩሩ ደግሞ የሳጥናኤል ምሳሌ ነው:: ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን ዝቅ አድረጎ የሰውን ሥጋ በመልበስ ወደዚህ ምድር እንደመጣና በሩር የተመሰለውን ሰይጣንን እንደቀጠቀጠው የሚያሳይ ምሥጢር ያለው ጨዋታ ነው:: #ልደት #ተወለደ_ናሁ #መልካም በዓል

New_video🛑ልደተ_ክርስቶስ_ዘማሪ_አቤል_ተስፋዬ_አቤል_በገና_🛑360p.mp34.35 MB

++ በዚያ .. በዚህ ++ '' በዚያ በአባቱ ቀኝ አለ፤ በዚህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ አለ በዚያ ብቻውን የማይታይ ኃይል ነው፤ በዚህም የማይዳሰስ ኃይል ከሥጋው ጋር የሚዳሰስ ሆነ በዚያ ተሸካሚዎቹ
++ በዚያ .. በዚህ ++ '' በዚያ በአባቱ ቀኝ አለ፤ በዚህም በእናቱ ማኅፀን ውስጥ አለ በዚያ ብቻውን የማይታይ ኃይል ነው፤ በዚህም የማይዳሰስ ኃይል ከሥጋው ጋር የሚዳሰስ ሆነ በዚያ ተሸካሚዎቹ እሳት የተሳለባቸው አራቱ እንስሳት ናቸው፤ በዚህም ተሸካሚዎቹ ሰው በመሆን መንገድ አራቱ ጠባዕያት ናቸው በዚያ አባት ያለእናት በዚህም እናት ያለምድራዊ አባት አለው በዚያ ገብርኤል በፍርሃት ይቆማል፤ በዚህም ገብርኤል በሐሴት የምሥራች ይናገራል በዚያ በጽርሐ አርያም የሚደነቅ ከማይታይ አብ የመወለድ ምስጋና በዚህም በቤተልሔም የሚደነቅ ከድንግል የመወለድ ምስጋና አለው በዚያ ከሰማያውያን ካህናት በወርቅ ማዕጠንት የዕጣኑን መዓዛ ይቀበላል፤ በዚህም ወርቅና ከርቤን ሽቱንም ከሰብአ ሰገል ይቀበላል በዚያ ኪሩቤልና ሱራፌል ከግርማው የተነሳ ይንቀጠቀጣሉ፤ በዚህም ማርያም አቀፈችው ሰሎሜም አገለገለችው በዚያ የመብረቆች ብልጭልጭታ በፊቱ ይገለጣሉ፣ የእሳትም ወላፈን ከአዳራሹ ይወጣል፤ በዚህም አህያና ላህም በትንፋሻቸው አሟሟቁት በዚያ የእሳት ዙፋን አለ፤ በዚህም የደንጊያ በረት አለው በዚያ የዕብነበረድ የሰማይ ንጣፍ፤ በዚህም የላሞች ማደሪያ በረት ማረፊያው ሆነ'' (መጽሐፈ ምሥጢር፣ ዘልደት ምንባብ - በአባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ) እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሰን! ©Kidmegubigubae

#የጽናጽል ትርጉምና ምሳሌነቱ
+5
#የጽናጽል ትርጉምና ምሳሌነቱ

To_Mother_Mary____English_Orthodox_Tewahedo_Hymn(360p).mp36.29 MB

I_Found_Tranquility____English_Orthodox_Tewahedo_Hymn(360p).mp35.77 MB

Melody_of_Yared____English_Orthodox_Tewahedo_Hymn(360p).mp36.98 MB

_The_Virgin_gave_birth_to_her_creator_English_Ethiopian_Orthodox.mp37.49 MB

የጨዋ ትምህርት በኢትዮጵያ ውስጥ ከሌሎችም በዓላት ደመቅ ብሎ ከሚከበረው በዓል የቅዱስ ገብርኤል በዓል አንዱ ነው። ነገር ግን በሕዝቡ ዘንድ አንድ ምንጭ የሌለው ነገር ግን በልማድ የገባ የጨዋ ትምህ
የጨዋ ትምህርት በኢትዮጵያ ውስጥ ከሌሎችም በዓላት ደመቅ ብሎ ከሚከበረው በዓል የቅዱስ ገብርኤል በዓል አንዱ ነው። ነገር ግን በሕዝቡ ዘንድ አንድ ምንጭ የሌለው ነገር ግን በልማድ የገባ የጨዋ ትምህርት አለ። እርሱም “ቅዱስ ገብርኤል ቁጡ ነው” የሚል ነው። በምን አወቅኽ? ማን ተናገረ? ቢባል መልስ የለም። ድርሳኑም መልኩም ስንክሳሩም አይናገርም።  ጌታ በተሰቀለ ጊዜ ገብርኤል ተቆጥቶ ተናዶ ሰይፋን ቢወረውር መጋረጃውን ቀደደው የሚልም ይሰማል። ይኽ በጣም ስኽተት ነው። መቆጣት መናደድ ስሜት ነው። መላእክት እንዲኽ ያለ ስሜት የላቸውም።  ለጥቅምት መድኃኔ ዓለም የማሕሌት ቀለም “አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእ ሚካኤል አርመመ ወገብርኤል ተደመ” የሚል አለ። ጌታ በተሰቀለ ጊዜ ሚካኤል ዝም አለ ገብርኤልም ተደነቀ ነው የሚለው እንጅ ተቆጣ አይልም። መሰቀሉ በመላእክት ዘንድ ድንቅ ነበር። ሰማይና ምድርን ፈጣሪ ኾኖ በፍጡር እጅ መሰቀሉ ያስደምማቸው ነበር።  ገብርኤል የቁጣ መልአክ አይደለም። ርኅሩኅ፣ መበስር ነው። የሚያጸና የሚያጽናና መልአክ ነው። እንጅ ገብርኤልን የምናከብረው ስለሚቆጣ ብለን አይደለም።  መ/ር ንዋይ ካሳሁን

በተያያዘ የጌታን ልደት ምክንያት በማድረግ እረኞች በቤተልሔም ከመላዕክቱ ጋር እንዳመሰገኑ (እንደ ዘመሩ) ሁሉ እኛም እግዚአብሔርን በመዝሙር የምናመሰግንበት፣ ነዳያንን በመጋበዝ በነርሱ ምርቃት በረከት የምናገኝበት እንዲሁም የተለያዩ ልደትን የሚያወሱ የኪነ ጥበብ ዝግጅቶች የሚቀርቡበት ልዩ ዝግጅት በበዓሉ ማግስት በ 29 ስለተዘጋጀ ... ከነገ ጀምሮ በቅድመ ግቢ ጉባዔ በመገኘት መዝሙር በማጥናት የበረከቱ ተካፋይ እንሁን !!! ቦታ ፦ ደብረ አሚን ቅዱስ ጊዮርጊስ አዳራሽ ሰዓት ፦ ከቀኑ 9፡ዐዐ ጀምሮ

<< ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱ ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና >> ሉቃስ 2፥11 ውድ የቤተ ክርስቲያን ቤተሰቦች እንደሚታወቀው በቤተ ክርስቲያናችን ከሚከበሩ ዐበይት በዓላት መካከል የጌታችን የልደት በዓል (ገና) አንዱ ነው። እንደ ቤተክርስቲያናችን ትውፊት በዘመነ ዮሐንስ የልደት በዓል የሚከበረው በወርሀ ታኅሳስ በቀን28 ነው። ቅዱስ ሉቃስ እንደሚነግረን ከሆነ መድኃኒት እርሱ ክርስቶስ ተወልዶልናል ለእኛ ለበሽተኞች መድኃኒት ፣ ፈውስ ሊሆነን መቷል ወይም ተወልዷል ይለናል ስለዚህ በዚህ ቀን ከክርስቶስ ጋር በመሆን በቤቱ በመቅደሱ በመገኘት ልናከብረው ይገባል። እንዲሁም እግዚአብሔር አምላክ ለክብሩ ቢያበቃን እንደ ቅድመ ግቢ ጉባዔ ተማሪነታችን የተማርነውን በፍሬ የምናይበት ጭምር ነው ።በተጠራንበት ልደት ተገኝተን በቅዱስ ሥጋው በክቡር ደሙ የምንከብርበት ዕለትም ጭምር ነው ። ስለዚህ ሁላችንም ልደት ተጠርተናል እና ለልደት ደግሞ ስጦታ ይዘጋጃል እና እኛም ለእሱ (ለባለ ልደቱ) የምናቀርበውን ስጦታ ማዘጋጀት አለብን። እሱም የሚሆነው በንስሀ የነፃ ንፁህ ሰውነት ይዞ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን መገኘት ብቻ ነው ። በተለያዩ ምክንያቶች ደግሞ ለቅዱስ ቁርባኑ መብቃት ያልቻልን እህት እና ወንድሞች ዕለቱን በቤቱ በመገኘት በማኅሌት፣ በኪዳን እንዲሁም በቅዳሴ በመሳተፍ እንድናሳልፍ ስል በእግዚአብሔር ስም እናሳስባቹሃለን ። በልደቱ ቤት ለመገኘት እግዚአብሔር አምላክ ይርዳን አሜን !!!!

ወበእንተዝ ኀሠሥኩ አእሚርየ ኪያከ። ኦ ገብርኤል ናዝዘኒ ወአስምአኒ ቃለከ። እንኳን ለቅዱስ ገብርኤልዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ። ©Kidmegibigubae
ወበእንተዝ ኀሠሥኩ አእሚርየ ኪያከ። ኦ ገብርኤል ናዝዘኒ ወአስምአኒ ቃለከ። እንኳን ለቅዱስ ገብርኤልዓመታዊ ክብረ በዓል አደረሳችሁ። ©Kidmegibigubae

ለሥጋም ለነፍስም የማይጠቅም መልካም ሐሳብ የለም። እንዲሁ በሥጋም በነፍስም ጉዳትን የማያመጣ ክፉ ሐሳብም የለም። ሐሳብ ሲቀደስ ንግግርና ተግባርም ይቀደሳሉ። ሐሳብ ሲረክስ ደግሞ ንግግርና ተግባርም
ለሥጋም ለነፍስም የማይጠቅም መልካም ሐሳብ የለም። እንዲሁ በሥጋም በነፍስም ጉዳትን የማያመጣ ክፉ ሐሳብም የለም። ሐሳብ ሲቀደስ ንግግርና ተግባርም ይቀደሳሉ። ሐሳብ ሲረክስ ደግሞ ንግግርና ተግባርም ይረክሳሉ። ሰው ልዑል ኅሊና ሲኖረው በእግዚአብሔር ደስ ይለዋል። ትምክህቱም፣ ደስታውም እግዚአብሔር ይሆናል። በሥጋዊ ጥቅም የማይታለል፣ ሥጋዊ መከራን የማይሰቀቅ፣ ለእውነት ያደላ ንጹሕና ልዑል ኅሊና ሊኖረን ይገባል። ©kidmegibigubaemeki

_ኦርቶዶክሳዊ የጾታ ትት 4.m4a77.88 MB