cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ስነፅሁፍ በወንጌል - Gospel Literature

◉ውድ የዚህ ቻናል ቤተሰቦች በዚህ ቻናል ላይ ፦ ➫ #አጭር_እና_ረጅም_ልብወለዶች ➫ #መንፈሳዊ_ተውኔት ➫ #መንፈሳዊ_ትረካዎች ➫ #መንፈሳዊ_ፅሁፎች ➫ #መንፈሳዊ_መነባነቦች ➫ #መንፈሳዊ_ድርሰቶች_ያገኛሉ። ለአስተያየት ጥያቄ 👉 @wunu_pa አጋር ቻናል 👉 @zema_sink 👉 @wunuye_picture Since Thursday 11-9-2014-

Show more
Advertising posts
10 334
Subscribers
+3424 hours
+1287 days
+67130 days
Posting time distributions

Data loading in progress...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
Publication analysis
PostsViews
Shares
Views dynamics
01
.        🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘           #!#ክፍል 31 .......መከረኛ እንባዬ እየረገፈ ተቀመጠችና ውሀ ጠጣች እኔ በገዛ ቤቷ ፋታ አልሰጥ አልኳት ለመረጋጋት እየሞከረች እኔም ጩኸት ያጀበው ጥያቄዬን ሳላቆም አማን መጣ ሲያየን ተደናገጠ እፁብ ምን ትሰሪያለሽ አለኝ ናዲን ከዚህች ሰይጣን ውጪ ማንም ምንም ሊያደርገው አይችልም ከሰማችህ አንተ ጠይቃት አልኩት ። አንቺ ተረጋጊ ብሎ ወንበር ሰጠኝ ስለማከብረው ተቀመጥኩ ይኸውልሽ ማህሌት እኛ ትልልቅ ሰዎች ነን እንደዚህ አይነት ጨዋታ አያምርብንም እግዚአብሔርን መፍራት እንደሆነ አቁመሻል ግን ቢያንስ በዚህ ሰአት እድሜያቸው የገፋ ቤተሰቦቹ ክፉኛ ተጨንቀዋል እባክሽ እልህሽን ለጊዜው ተወት አድርጊውና ወንድሜ የት ነው ያለው አላት ። እንዴ ነገሩ እውነት ነው እንዴ ይሄቺ እብድ ስትበጠብጠኝ አእምሮዋ ተነክቶ መስሎኝ ነበር የታገስኳት የምሯን የው ናኦድን ውለጂ ምትለኝ አለችው አታስመስይ ማህሌት እስከዛሬ ጌታን ብዬ ስትጫወቺብኝ ዝም ብዬሻለሁ አሁን ገና በማይቀለደው ቀለድሽ አልኳት ተዐምር እየተንሾካሸከች ኸረ እፁ በናትሽ ዛሬስ ለጌታ ስትይ እንደ በፊቱ እሷን ተያትና ለጌታ ትተን ከእኛ ሚጠበቀውን እናድርግ አለችኝ አንቺ ልጅ ዝም በይ በእርሷ ቦታ ወደ አንቺ እንዳልዞር አልኳት ። አማን ቀጠለ እባክሽ ማህሌት በጨዋ ደንብ እናውራ ብዬ ነው ናኦድ የት ነው አላት ቆይ ለምንድነው የምትለምናት ህግ አፍንጫዋን ይዞ ያስለፈልፋት የለ አልኩት አንቺ አበዛሽው እንደ አንቺ ስላልሆንኩ ነው ቤቴ መተሽ ስትጨፍሪ ዝም ያልኩሽ አይ ካልሽ አሁን ያልሽው ለአንቺ ይሆናል በጥበቃ እየተጠፈጠፍሽ ትወጪያለሽ አሁን ቤቱን ለቀሽ ውጪ አለችኝ ። ብዙ ነገር ልናገራት አልኩና ራሴን ለመግዛት ሞከርኩ አማንም እፁ በቃ ነይ በዚህ መንገድ አይሆንም ብሎ አስወጣኝ እና ለፖሊስ እናመልክት አልኩት 24ሰአት ስላለፈው ቤተሰቡም ለፖሊስ አመልክቷል ሆስፒታል እያለሽ ከፖሊስ ጣቢያ ሲጠሩኝ የው ትቼሽ የሄድኩት ከሰዎች ጋር ግጭት አለው ብለው ሲጠይቁኝ ስለ ብሩክም ስለ ማህሌትም ያለውን ነገር ነግሬያቸዋለው አንቺ አትጨናነቂ መጥሪያ ሲደርሳት እዛው ትናዘዛለች አለኝ ። አማን ምኑን ልረጋጋ እሺ ምን እንዳደረጉት ምን አውቃለሁ  እኔ እኮ ነኝ ጦስ የሆንኩበት ምነው በእሱ ቦታ እኔን ባደረገኝ ብዬ አለቀስኩ ኸረ አንቺ ልጅ ምን እየሆንሽ ነው እኛ ሳናስብ ቀርተን ነው እኛ ሳንጨነቅ ቀርተን ነው ግን ማልቀስ ምንም መፍትሄ አይሆንም ጤና ስትሆኚ ነው ነገሮችን ምን ማድረግ እንዳለብሽ እንኳን መወሰን የምትችይው እኔ አይከፋኝም አብሮ አደግ ወንድሜ የት ምን ላይ እንዳለ ሳላውቅ ቆሜ ስሄድ ምንም የተፈጠረ አልመስልማ  ውስጤ ቢከስልም እሱን ማግኘት የምችለው ጠንክሬ ነገሮችን በጥንቃቄ ማድረግ ስችል ነው በሚል ነው አሁን እቤት ልሸኛቹ ይህቺን ትንሽ ልጅም ያለ እድሜዋ አታስጨንቂያት ለእናትሽም አስቢላቸው እንጂ ብሎ ተቆጣኝ እሺ አሙ እኔስ ምን ላድርግ አቅም ቢከዳኝ የማደርገው ባጣ እኮ ነው እንባ የሚቀድመኝ እሺ እንዳልከኝ ለመጠንከር እሞክራለሁ አልኩት ውስጤ እንደማይችለው እያወኩ እቤት ደረስን እሱ ወደ ናዲ ቤተሰቦች ተመለሰ ።  ወደ ጓዳ ገባሁና ጌታ ሆይ እኔ አቅም የለኝም ባለበት አንተ ጠብቀው አንዳች ክፉ ዜና መስማት አልፈልግም ብዬ ጌታ እግር ስር አለቀስኩ ። አማን ደወለልኝ..... .............ይቀጥላል......... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
10Loading...
02
እውነተኛ የክርስቲያኖች ቻናል እነዝህ ብቻ ናቸው እናንተም ተቀላቀሉ
800Loading...
03
ሰላም ቅዱሳን በTELEGRAM ቻናል ተወዳጅ የሆኑትን በደረጃ አስቀምጠናል እናንተም JOIN በማለት በተሰብ ይሆኑ 🙏 ለማስታወቅያ ስራ👉@skat_kal
2980Loading...
04
.        🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘           #ክፍል30 ......መሞከር ጀመርኩ  በጭራሽ ስልኩ አይሰራም እንዳፈጠጥኩ ነጋልኝ ስልኩ አሁንም ዝግ ነው ወዲያው አማን ደወለልኝ አሙ ስልኩ ለሊቱን ሙሉ ዝግ ነው አሁንም እንደዚያው አልኩት ሰላምታም ሳልሰጠው አትጨናነቂ እፁ ምንም አይሆንም እኔ እቤት እሄድና ደውልልሻለሁ አለኝ የእርሱን ስልክ እየጠበኩ እዛው እንቅልፍ ወሰደኝ ። የተኛሁበት ክፍል በር ተከፈተ ተዐምር አትረብሺኝ ለሊቱን አልተኛሁም አልኩኝ በደከመ ድምፅ ምላሽ አልሰጠችኝም የእግሯ ኮቴ ቀረበኝ አጠገቤ ስትቆም ምን ፈልገሽ ነው ብዬ ብርድ ልብሱን ከፊቴ ላይ ሳነሳው ማሂ ነበረች በየሱስም አንቺ ምን ትሰሪያለሽ አልኩኝ አፍሽን ዝጊ ብላ አፈጠጠች የያዘችውን ትልቅ ሹል ቢለዋ እያሳየችኝ ። ማሂ ምን እያደረግሽ ነው እኔ እኮ ጓደኛሽ ነኝ አልኳት ከት ብላ ስቃ ጓደኛ እኮ አንቺ የኔ ጓደኛ የማይሆነውን ህይወቴን እንዳመሰቃቀልሽው ለዘላለሙ ናኦድን ወደማታዪበት አሰናብትሻለሁ ብላ ቢለዋውን ወደ ላይ አነሳችው ና ወደ ሆዴ ቁልቁል ሰደደችው ማሂ ብዬ ጮኹኩ ምንድነው በኢየሱስ ስም ተዐምርና ማሚ ነበሩ ምን አይተሽ ነው ። በርግጌ ስነሳ ምንም ነገር የለም ምን አይተሽ ነው አሉኝ ሰውነቴ በላብ ተጠምቋል እንጃ ማሚ ቅዠት አይሉት ህልም ብቻ መጥፎ ነገር ነው ያየሁት ናዲ ትናንት ከሸኘኝ ጀምሮ ስልኩ አይሰራም አማንም ደውላለሁ ብሎ ዝም አለ ብዬ በፍጥነት ፒጃማዬንም ሳልቀይር ክፍት ጫማ እንዳደረኩ ወደ እነ ናዲ ቤት  ሄድኩ የጊቢው በር  እስኪከፈት ነብሴ ተጨነቀች በሀይል ነበር የምደበድበው ታናሽ እህቱ በፍጥነት መጥታ ከፈተችልኝ እርሷም ከውጪ በጉጉት ምትጠብቀው ነገር አለ መሠል እኔ መሆኔን ስታይ ኤጭ ብላ ወደ ኋላ ተመለሰች ተከትለዋት ሙሉ ቤተሰቡና አማንም በረንዳውን ሞልተውት ነበር ። ናዲስ አልኩኝ ሁሉም አፍጠውብኛል ዝም አሉ ንገሩኝ እንጂ ናዲስ አልኩኝ አሁንም ዝም አማን ናዲስ ብዬ ጮኹኩኝ እናትየው አንቺን እንጠይቅሽ እንጂ ትናንት አንቺን ሊያገኝ ወጣ ከተባለበት መቼ ተመለሶ አሉኝ እንባ ባደከመው ድምፅ አማን ናዲ እዚህ የለም አልኩኝ አቅሜ ሲከዳኝ ይታወቀኛል እንባዎቼ እየረገፉ አዎን በለኝ ወይም ናዲን አሳየኝ አልኩት እፁ ተረጋጊ ነይ እስቲ ወደዚህ አረፍ በይ አለኝ ሰማይ ምድሩ ዞረብኝ እያኋቸው ሰዎቹ ብዥዥዥ ይሉብኝ ጀመር ። ከዚያ ራሴን ያገኘሁት የፈረደበት ሆስፒታል ነበር አጠገቤ ተዐምር ነበረች ግሉኮሱን ልነቅለው ስል ነርሶቹን ጠራቻቸው መሠለኝ ትንሽ ነው ይሄ ብቻ ይለቅ ብለው ከለከሉኝ ሆስፒታሉን በአንድ እግር አቆምኩት  ለእኔ አይታወቀኝም የናዲ ነገር ብቻ ነው የሚያሳስበኝ ለ4ሆነው ከአቅማቸው በላይ ስሆን መርፌ አምጥተው ወጉኝ በድጋሚ ስነቃ ጎረቤቶቻችን ነበሩ ግሉኮሱ ተነቅሎ ነበረ በፍጥነት ብድግ አልኩ ትንሽ እንደማዞር ሲያደርገኝ  አልጋው ላይ ቁጭ አልኩና ራሴን አረጋግቼ ተነስቼ ወጣሁ እፁ ተረጋጊ የት ነው የምትሄጂው አሁንም ትወድቂያለሽ እያለች ተዐምር ትከተለኛለች  እርምጃዬ ከአልጋ የተነሳ ሰው አልመስልም እልህ ና ንዴቴ ህመሜን አስረሱኝ ተዐምር አልቆም ስላት ከፊት ለፊቴ በሩጫ አልፋኝ ቆመች ዞር በይልኝ ብዬ ገፈተርኳት አሁንም ትከተለኝ ጀመር ጎረቤቶቻችን ለማሚ ደወሉላት መሠለኝ ደወለች ስልኬ ተዐምር ጋር ነበር ይኸው ማሚ ሰማችልሽ መሠለኝ እፁብ ቁሚ እያለከለከች ትለምነኛለች የሆስፒታሉ ርዝመት ከሀገር ሀገር ስደት ጉዞ መሠለኝ እንደወጣን ታክሲ ውስጥ ገባሁና ብር እንደያዘ ሰው ወደነ ማሂ ሱፐርማርኬት  እንዲነዳው ነገርኩትና ሄድን ተዐምር ብር ይዛ ነበር እንደወረድኩ ወደ ሱፐር ማርኬቱ በቀጥታ ገባሁ ተቀምጣ ስልኳ ላይ አፍጣ ነበር ብቻ በሁለት እጄ እንቅ አደረኳት ናዲን የት አደረስሽው አንቺ ክፉ የእስከዛሬው አንሶሽ ትንፋሽ አትሯት እንዴት ትተንፈስ የሱፐር ማርኬቱ ሰራተኞች እንደምንም አስለቀቁኝ ጥበቃ ኸረ የህግ ያለ እያለ አንዱ ሲንጣጣ ተው ብላ በእጇ ምልክት አሳየችው  እያሳለች መናገር ፈልጋለች ግን ደም ስሯ ተገታትሯል ከሞት አፋፍ ሳትመለስ አልቀረችም ። ተዐምር አንቺ እፁ አብደሻል እንዴ ሌላው ቢቀር ክርስትናሽን ረሳሽው አለችኝ ገላመጥኳት ና አንቺ ሰይጣን ናዲ የት ነው ያለው አልኩኝ መከረኛ እንባዬ እየረገፈ....... ............ይቀጥላል ........... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
7260Loading...
05
ሰላም ቅዱሳን በTELEGRAM ቻናል ተወዳጅ የሆኑትን በደረጃ አስቀምጠናል እናንተም JOIN በማለት በተሰብ ይሆኑ 🙏 ለማስታወቅያ ስራ👉@skat_kal
3840Loading...
06
የዛሬው አጠር ስላለ 2 ክፍል ፖስቻለው enjoy it😊
9810Loading...
07
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘          #ክፍል_29 ........ድንግጥ ብሎ ቀረ ። ወዲያው ለማስቀየስ ማለት አለኝ ናዲ ብቻህን ለመጨነቅ እየሞከርክ ነው እኔ እድሌ ጠማማ ነው ባክህ ስንት ነገር አለፈ በቃ እፎይ ብዬ ሳላበቃ ሌላ ጣጣ ትናንት እህትህና እናትህ ሲጨቃጨቁ ሰምቼአቸዋለሁ አልኩትና በረጅሙ ተነፈስኩ በጣም ደነገጠ ፊቱ ልውጥውጥ አለ ምን እንደሚለኝ እንኳን ያጣ መሠለኝ ከእነርሱ ሀሳብ በላይ የእኔ መስማት አስጨነቀው ። አንዴ አፉን ይይዛል አንዴ ጭንቅላቱን ይይዛል ጭንቅንቅ ሲል  አሳዘነኝ ናዲ የኔ መስማት ከሆነ ያስጨነቀህ እሱ አያሳስብህ ። ከቤተሰቦችህ ጋር በእኔ ምክኒያት ባትጋጭ ደስ ይለኝ ነበር ግን ምን ማድረግ ይቻላል የኔ መዘዝ ሁሌም ላንተ እንደተረፈ ነው አልኩት ። ብስጭት ብሎ በሚያስፈራ አስተያየት አየኝ እኔና አንቺ መሀል የኔ ያንቺ ሚባል ነገር አለ እንደሱ እንዴት ታስቢያለሽ ደግሞ  እግዚአብሔርን አምነዋለሁ ቤተክርስቲያን እንኳን ምታውቀውን አይደለም ቤተ ክርስቲያን ራሱ ጌታ የሚያውቀውን የኔ ቤተሰቦች ቢሆኑ ብሩክ ቢሆን ማሂ ብትሆን ልፉ ሲላቸው ነው እድሌ ምናምን እያልሽ ይብሱን አታበሳጪኝ እግዚአብሔር ለእኔና ለአንቺ ስንት ነገር አላደረገልንም እንኳን ይህቺን ልጁን ሰጥቶን የለ ምን አስጨነቀሽ ለእርሱ እንተውለታለን በራሱ መንገድ ያሰማምረዋል አለኝ ተፅናናው ደግሞ አባቢ ራሱ እንዴት የተባረከች አስተዋይ ልጅ ነች ሲልሽ ነበር በጣም ነበር ደስ ያለኝ ማሚ መጥታ ደስታዬን አቀዘቀዘችው እንጂ ሁሉንም  ለምን እንዳደረገ ራሱ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ዝም ማለት ነው እሺ እፁዬ አለኝ ። አብረን እያለን ቴክስት ደረሰው መሠለኝ ይህቺ ልጅ ወሬ ከየት ነው ምታመጣው ጌታ ሆይ አለ የእኔም ስልክ የአዲስ የመልዕክት ድምፅ አሰማኝ ። ሳየው ብሩክ ነበር ስሚ አማች ይሆኑኛል ያልሻቸው ሰዎች አይኗን ላፈር አሉ ተባለ እና ምን ይሻልሻል መቼም ናኦድሽ በአንድ እናቱ እንደማይደራደር የታወቀ ነው ስሰማ እኔን ይመርጣል ብለሽ እንዳትሳሳቺ ይላል ። ይሄ ሰይጣን ብዬ ስልኩን ጠረጴዛው  ላይ ስወረውረው ምንድነው አለኝና ስልኩን አንስቶ አነበበው እኔም የእርሱን ስቀበለው ማሂ ነበረች ቤተሰቦችህ ያቺን መዘዘኛ ለቤቱ ክብር አትመጥንም አሉአ ገና ምን አይተህ የእኔ ግፍ 😂😂  ይላል እነዚህ አጋንኝቶች ምን አድርጉ ነው የሚሉን አሁንስ አበዙት ቆይ ባልሰራላቸው እንስሶች አልኩኝ ሳግና ንዴት እየተናነቀኝ እንዴ እፁ ስሜታዊ እየሆንሽ ነው የኔ እናት እንዴት ብትናደጂ ነው ከአንደበትሽ ክፉ ወጥቶ የማያውቅ መፅሀፍ ለሰነፍ እንደ ስንፍናው አትመልስለት ነው የሚለው እነርሱም የዘሩትን በሚያጭዱበት ጊዜ እኛም የዘራነውን መልካም እናጭዳለን እናቴ አትናደጂ በቃ ንቀሽ ተያቸው ስናወራ ስናወራ ሰአቱ ነጎደ እረ መሸ እኮ ተነሺ ብሎ እስከ እቤት አድርሶኝ ተመለሰ ። ከነማሚ ጋር ተጨዋውተን የተዐምርን ቡና ጠጥቼ ወደ ጓዳ ገባሁና አምላኬን አውርቼው ነገሬን አደራ ሰጥቼው መፅሀፍ ቅዱሴን አነሳሁ አንብቤ ስጨርስ ናዲ ሌላ ቀን በግዜ ነው የሚደውልልኝ ስደውልለት ስልኩ አይሰራም ለፀሎት ዘግቶት ነው የሚሆነው ብዬ ከአንድ ሰአት በኋላ ደወልኩለት አይሰራም ጌታ ሆይ ፍርሃት ፍርሃት አለኝ ለአማን ደወልኩና ከተኛበት ተነስቶ በደከመ ድምፅ አወራኝ አትጨናነቂ እኔ እደውልለታለሁ አለኝ ጠበኩ 30ደቂቃ አልደወለም አገኘኸው ብዬ ቴክስት አደረኩለት እፁ ይቅርታ ያልደወልኩት አስጨንቅሻለው ብዬ ነው ጠዋት እንሞክርለታለን ያው እሱ ረጅም ሰአት አይደል የሚፀልየው የተለመደ ነው ተኚና ጠዋት እንደውላለን አለኝ ። እኔ በየት በኩል እንቅልፍ ይውሰደኝ ደጋግሜ መሞከር ጀመርኩ...... ..........ይቀጥላል ........ @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
9140Loading...
08
.     🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘          #ክፍል_28 .... ሸኙኝ ማሚና ተዐምር ከሱቅ አልገቡም ነበር መሄጃ የለኝ ጌታዬ ላይ ተነፋረኩኛ ጌታ ሆይ በእኔ ምክኒያት ይሄ ቤተሰብ ሰላም ማጣት የለበትም ናዲን ከተናገሩት በጣም ይጣላቸዋል እርግጠኛ ነኝ ከቤተሰቡ እንዲቂያቂያም አልፈልግም ያውም በእኔ ምክንያት ። መንፈስ ቅዱስ ከፋኝ አልኩት የተሰማኝን እየለፈለፍኩ ልክ ስሞታ እንደሚናገር ህፃን እርሱም ደግሞ አፅናናኝ ጭንቀቱን ረሳሁና ራሱን አየሁት ከቆይታ በኋላ ለናዲ ደወልኩለት አያነሳም በቃ ለጌታ ሰጥቼ ተኛሁ ከረጅም ደቂቃዎች በኋላ ደወለልኝ ። እፁዬ ይቅርታ የሆነ ጉዳይ ይዤ ነበር አለኝ በቃ ሲጨቀጭቁት ነበረ ብዬ ገባኝ ድምፁ ተረብሾ እንደሆነ ያሳብቃል ምን እንደሆነ መጠየቅ ሁሉ አስጠላኝ ገብቶኝ ለምን እንዳልገባው ሆናለሁ ብዙም አላወራንም ስልኩ ተዘጋ ። ማሚ  እንደመጣች ፊቴን ነው የምታየው ግንባሬን ነው የምትስመው ምንድነው ፊትሽ ምን ተፈጠረ አለችኝ እንደገና ተነፋረኩባታ ብዙ መከረችኝ አትፍሪ ጌታ ከእናንተ ጋር ከሆነ አይደለም ቤተሰቡ ሙሉ የአለም ህዝብ ቢያድምባቹ ምንም አይፈጠርም ለበጎ ነው የኔ ቆንጆ ልጅ አለችኝ ። በጠዋቱ ተነስቼ እቤት መስራት ያለብኝን ሁሉ ሰራሁና ናዲን አገኘሁት በጣም ተረብሾ ተጨናንቋል ምን እንደሆነ ብጠይቀው አልጋገር አለ ነው በድብብቆሽ  ነው ቸምንቀጥለው ስለው ትንሽ ከቤት ተጋጭቼ ነው አለኝ በምን አልኩት ሊያለቅስ ደረሰ አንቺ አታውቂውም የቤተሰብ ጉዳይ ነው አለኝ እየከፋው በእኔ ምክንያት ነዋ አልኩት ድንግጥ ብሎ ቀረ...... ...........ይቀጥላል ........ @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
8100Loading...
09
.        🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘           #ክፍል_27 እሁድ እቤታቸው ተጋብዣለሁ  ቀናቶች አልሄድ ብለውኝ ስጓጓ ከርሜ አይደርስ የለ ቀኑ ደረሰና ያስደስታቸዋል ብዬ ያሰብኩትን አለባበስ ለብሼ ሄድኩኝ ናዲና አማን ነበር ይዘውኝ የሄዱት እቤታቸው ተውቧል እነርሱ አምረውና ደምቀው ነበር የጠበቁን የምግቡ ና የቡናው መዐዛ ቤቱን ድግስ ቤት ድግስ ቤት አሰኝቶታል እነዚህ ሰዎች በዚሁ ሊያስቀሩኝ አስበው ነው እንዴ ናዲ አልኩት ፈገግ አለና እኔም አልገባኝም እስቲ እንጠይቃቸዋለን አለኝ ሁሉንም በየተራ ሰላም አልኩ ሁለት እህትና ሶስት ወንድም አሉት አንዷ ታላቁ ስትሆን አንዷ ታናሹ ነች አንዱ ታላቁ ሲሆን ሁለቱ ታናናሾቹ ናቸው ። አባትየው ፈገግታቸው በቂ ነው እንደ በረዶ የነጣው ፀጉራቸው ና ፂማቸው ልዩ ውበትን ችሮአቸዋል አባትህ ደስ ሲሉ እኮ ውበታቸው ከፊት ይልቅ ጨምሯል እውይ ፀጉራቸው ገፅታቸው ሲያምር አልኩት እኔም በእርሱ እኮ ነው የወጣሁት አለኝ ጉረኛ የሳቸውን ያክል እንኳን አታምርም አልኩት አማን ቀስ ብሎ እናንተ ምን ትንሾካሾካላችሁ በጋራ ከቤተሰቡ ጋር አታወሩም እንዴ አለን ፋዘርን ካየኋቸው ቆየሁ ለዛ እኮ ነው አልኩት ። ለዛ ያለው ጨዋታ እየተጨዋወትን ቆየን ናዲማ የማላውቀው ናዲ ጨዋ ሆኖ አረፈው በጣም ነው የሚያከብራቸው ከጌታ ቀጥሎ  ለቤተሰቡ ባለው ክብር አይደራደርም ። ሴቶቹ  እየተንጎዳጎዱ ያስተናግዱናል  ። እናትየው በየመሀሉ እየተነሱ ይመለሳሉ ምን ጎደለ ብሉ ጠጡ ይሉናል ። መፀዳጃ ቤት መሄድ ፈለኩ ና አንዷን እህቱን ስጠይቅ ወደ ውስጥ እለፊ አለችኝ ። በግምት እየሄድኩ ጆሮዬ ውስጥ ሚሰቀጥጥ ወሬ ዘለቀ እርምጃዬን ገታ አድርጌ ቆምኩ አሁን የኔ ልጅ ሴት አጥቶ ነው እናቱ ነበሩ እማዬ ዝም በይ በጥልቀት ስለማታውቂያት ሴት እንዴት እንዲ ታወሪያለሽ ። አፍሽን ዝጊ ገና በ12ኛ ክፍል አልነበር እንዴ ልታገባ የነበረው የአሜሪካ ዳይስፖራ አስጠልቶት የተዋትን የኔ ልጅ በምን እዳው ነው? ገና ያለ እድሜዋ አይደል እንዴ መቅበጥ የጀመረችው እኔ  ስንት ነገር ቸርች ውስጥስ እንደተወራ አታውቂም እኔ በህይወት እያለው ልጄ እሷን አያገባም እንዴት እስከዛሬ አትነግሩኝም ወይኔ ዘውዲቱ እናትና ልጅ ይጨቃጨቃሉ እዛው አዙሮ ሊጥለኝ መከረኛ እንባዬ እርግፍ እርግፍ አለ  ከኋላዬ የእግር ኮቴ ሲሰማኝ ቶሎ እንባዬን ጠራረኩና ወደ ኋላ ተመለስኩ እፁዬ ግቢ አለችኝ ታናሹ ሊዲያ ነበረች ተመልሼ ተቀመጥኩ ። የሚያወሩትን ሁሉ አልሰማም ድንዝዝ ብዬ እነዚያን ቃላቶች በድግግሞሽ ያቃጭሉብኝ ጀመር አይደል እንዴ የኔ ልጅ አሉ አባቱ ህህህ ብዬ ከሄድኩበት የሀሳብ ማዕበል ተመለስኩ ልክ አይደለሁ ወይ አሉኝ ኸረ ልክ ኖት አልኩኝ ምን እንዳሉም ሳልሰማ እናትየው ተመልሰው መጥተው ተቀመጡ ሳያቸው አልቅሽ አልቅሽ አለኝ ሰው እንዴት በቀድሞ ማንነቱ ይለካል  ለነገሩ ጥሩ ስራ መልካም ነገር በህይወቴ ሆኖ ቢያልፍ ማንም አያስታውሰውም ነበር ሳልፈልገው በህይወቴ ለተፈጠረ ያውም እኔን ጎድቶ እኔን ሰብሮ ላለፈ ጉዳይ በየጊዜው መልኩን እየቀያየረ ያሰቃቸኛል ። ምን ሆነሻል ልክ አይደለሽም አለኝ ናዲ ደህና ነኝ አልኩ ሊወርድ ጥቂት የቀረውን ዕንባ ዋጥ ለማድረግ ከውስጤ ጋር ትንቅንቅ ገጥሜ ኸረ እፁብ አትዋረጂ ዋጪው ዋጪው ራሴን አበረታው ዘንድ ሞከርኩ  እንዴ አመመሽ እንዴ አለኝ ኸረ በጭራሽ ዝም ብዬ ነው አልኩት ። ወጥተሽ ጥፊ ጥፊ አሰኘኝ መከረኛዋ እናቴ እቅፍ ውስጥ መሆን አጓጓኝ ከመች መች ደረሰ ብዬ የጠበኩትን ቀን በምን ቀን እዚ ቤት መጣሁ ለማለት አበቃኝ እየመሸም ስለነበር አባትየው ከመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል አካፈሉን ። የፈራኸው አይወርስህም በሚል ርዕስ አሁን ይሄ መልዕክት ለእናትየው ነው ለእኔ ነው ግራ ግብት ብሎኝ አሜን አንኳ እንዴት ልበል ተሳሰርኩ እናትየው አሜን አይወርሰኝም ቤቴ አይገባም እያሉ ይቀበሉ ነበር ግራ ግብት እንዳለን ፀልየውልን ናዲና አማን ሸኙኝ....... ........ይቀጥላል .......... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 0030Loading...
10
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘            #ክፍል_26 .....እኮ እንዴት አልኩት በጣም በረጅሙ ተነፈሰና ጓደኞችሽ ደወሉልኝና በጣም መታመምሽን ነገሩኝ  የእውነት በራሴ በጣም ነበር የተናደድኩት እውነት ቢሆን ኖሮ እንኳን በቃ ስላልቻልኩ ልደውልልሽ ነበር ልክ ልደውል አልደውል ስታነሳ ምን ብዬ ልጀምር ይቅርታ አድርጌልሻለው ልበላት ወይስ እስክትደውል ጠብቄ ኮስተር ብዬ ላውራት እያልኩ ከራሴ ስሟገት አቤል ደወለልኝ በቃ ደስ አለኝ እንደሌላ ቀኑ በሰው ስልክ ደውላ ነው ብዬ አነሳሁት ሲነግረኝ እየቀለደም መስሎኝ ነበር ጭራሽ ራሷን ስታ አልነቃ ብላለች ሲለኝ ምሆነውን አጣሁ።   ደስ እያለኝ በፈገግታ ተመስጬ ስሰማው  ንግግሩን አቆመና ኸረ አትመሰጪ በቃ አላወራም አለኝ እሰይ ተጋደልናታ ብዬ ስኮሳተር ስቀልድ ነው ከዚያ የእግዚአብሔር ነገር ዝም ብዬ ብቻ ተነስቼ ልመጣ ስል አማን ደወለልኝ የት ን ደብሮኛል አለኝ ነገርኩት ደስ አለው በጣም እኔ ተናደድኩ ታማለች እያልኩህ ምን ሆነሀል ብዬ ስጣላው አይ ደስ ያለኝ ሰላም ሊወርድ በመሆኑ ነው ስጠብቀው ነበር አለኝ እኚህ ሰዎች አውቀው ነው እንዴ አልኩና ከሆነም ይሁን ብዬ ስነሳ በቃ አብረን እንሂዳ አለኝ መጣን የእውነት ባላይሽ ይሻለኝ ነበር በቃ ራሴን ይቅር አልለውም ነበር አለኝ ። ወሬ አታብዛ ወደዛ የፊልም አክተር አክተር አትጫወት አልኩት ጉዱ መች አለቀና አለኝ የምኑ ስለው አቤል ለአንቺ ሲል የማሂን የሶሻል ሚዲያዎች ሰርች አድርጎ ማውራት ከጀመሩ ሰነባብተዋል ለእኔ እንዳለኝ የድሮ ማንነቴን ተጠቅሜ ሙሉ እምነቷን ስትጥልብኝ ምንም አትደብቀኝም ብሎ የተፃፃፉትን አሳየኝ የእኔና የአንቺ አብሮ መሆን ሰላም እንደሚነሳት ከብሩክ ጋርም አብረው እንደሚያሴሩ ነገረችው ። ራሴን ጠላሁት ከአንቺ ይልቅ እነሱን አመንኳቸው ለስቃይና በሽታ ዳረኩሽ ክፉ ነኝ አይደል  እውነት ቢሆን እንኳን የስንት ቀን መልካምነትሽን በአንድ ጊዜ ስህተት ቀየርኩት እንዴት እንዳስቻለኝ ራሱ ይገርመኛል ጨካኝ ነኛ ?አለኝ ሳላስበው ለካ እየተነፋረኩ ነው  ቁስሌን አስታወሰኝ  ግን አሁን በዚያ ከመከፋት ይልቅ በጊዜው በሆነው መልካም ነገር ማመስገን ይሻላል ብዬ እምባዬን ጠራረኩኝ እፁ ይቅርታ የምልበት አቅም ራሱ የለኝም ምን እንደምልሽ ራሱ ሲል እንግዲ አታሽቃብጥ በቃ ያለፈው አልፏል በራሴው ታሪክ እንደ አሰለቃሽ ፊልም ልታስለቅሰኝ ነው እንዴ ብዬ ፈገግ አልኩ ። ከዚህች ከማሂ ጋር ግን ብዙ ማወራው ጉዳይ አለኝ በቁጭት ነው የሚያወራው እንግዲ አታናደኝ በቃ ንቆ መተው ነው አይሻልም ሰላም ለምን እናጣለን አማን በሩን ከፍቶ ገባ እናንተ ልጅቷ ማረፍ ሲኖርባት አፍጣቹ የሆድ የሆዳችሁን ታወራላችሁ ብሎ ተቀመጠ በል ሂድ አረፍ በል እኔ እጠብቃታለሁ አለው በስልኬ ሰአት ሳይ 10ሰአት  አዎ ሂድ አልኩት ግደሉኝ ከዚህ አልሄድም አለ ከደረቀ ስለማይሰማ ተውነው  ስለ እግዚአብሔር መልካምነት በሚገርም አገላለፅ ይሰብከን ጀመር አማንም በተራው ሲያወራ እንዳፈጠጥን ነጋ  እነ ሊዩም መጡ  ህክምናዬን ጨርሼ እንድወጣ ተፈቀደልኝ ። ጌታን አያመሠገንን ወጣን አቤሎና ሊየን አመሠገንኳቸው የራስ ሰው አይመሠገንም አለች ሂዩ ። እነ ናዲም ያን ቀን ሆቴል አርፈው ስራ ስለሚስተጓጎልባቸው ተመለሱ ። ቀኖች እየገፉ አመቶች እየተተካኩ ልመረቅ ደረስኩ በየእረፍቱ እነ ማሚ ጋር እየተመላለስኩ የብሩክ ዛቻና ጭቅጭቅ ሳይቆም የማሂም ሴራ ሳይቆም እግዚአብሔር እየረዳን ብዙ ቀናቶች አለፉ ሊዩና አቤሎም የሶስታችንም ጓደኝነት እንደተጠበቀ ሆነ እግዚአብሔር ከረዳቸው መጪ አመት የመጋባት እቅድ አላቸው ፊተኞች ኋለኞች ይሆናሉ እያሉ ያስቁኛል ቆይ በምን ልትኖሩ እያልኩ ሳናድዳቸው ከቤተሰቦቼ ጋር እሰራለሁ እሷ ምን በወጣት ደግሞ ተመርቀንስ ስራ የለ ማለት የሁሌ ንግግሩ  ነው አቤሎ ለቤተሰቡ በቸኛና የሀብታም ልጅ ነው ። የማይደርስ የለ እግዚአብሔርም ጤናችንን ጠብቆ ሰላማችንን ጠብቆ በድካማችን አግዞን ተመረቅን ማሚና ናዲ ተዐምር አማን መጥተው አስመረቁኝ የአቤሎና የሊዩ ቤተሰቦችንም በደንብ ተዋውቀናል ቤተሰቦቻችንም እርስ በእርስ ተዋውቀው አዳማ ላይ ደስ የሚል ግዜ አሳለፍን ከሊዩና አቤሎ ተለይቶ መኖርን ደግሞ ልጀምር ነው አሰንደእነርሱ መልካም ጓደኛ በዘመኔ ገጥሞኝ አያውቅም ። እንደዋወላለን ረጅም ሰአት አወራቸዋለው በቃ ቢከፋኝም ተላቅሰን ከተለያየን ቀን ጀምሮ እየኖርኩት ነው ያለ እነርሱ ። እንግዲ ተመርቆ ወዲያው ስራ የለ ከማሚ ጋር ንግዱን አጧጥፈው ጀመር ጀግናዋ እናቴ ከትንሹ ተነስታ ትልቅ ወደ ትልቅ ሱቅ አሳድጋዋለች ። በጅምላ ብቻ እቃዎችን ታስረክባለች ። ብሩክ ተብዬው አሁን ድር ይደውላል አላነሳም እርሱም ተስፋ አይቆርጥም ማሂ ስታየኝ እንኳን መንገድ ትቀይራለች ። የናዲ እህትና ወንድሞች ስለእኛ ቢያውቁም እናትና አባቱን እንድተዋወቅ እሁድ እቤታቸው ተጋብዣለሁ ........ ..........ይቀጥላል........... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 1750Loading...
11
.          🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘           #ክፍል_25 ......ከዚያ በኋላ የሆነውን አላስታውስም ራሴን ያገኘሁት ከሌላ ቀኑ በተለየ አልጋ ላይ ነበር ነጭ ኮርኒስና የመብራቱ ብርሀን በብዥታ ታየኝ ። እንዴ ነቃች መሠለኝ የአቤል ድምፅ ነበር እጄን የግሉኮስ ካኖላው ህመም ተሰማኝ  ከደቂቃ በኋላ አይኔ በጥራት አሳየኝ አንገቴን አዙሬ ሳይ ህልምም መሠለኝ አሁንም አልነቃሁም ብዬ አሰብኩ ናዲ ወንበር ላይ ተቀምጧል እንዳየሁት ከተቀመጠበት ብድግ አለ እየቃዠው አይደለማ ብዬ ለመነሳት ስሞክር ሰውነቴ አልታዘዝ አለኝ አቃሰትኩ ። አትነሺ ያምሻል አለኝ  የእውነት የራሱ ድምፅ ነው ጌታ ሆይ ምን ይሳንሀል አልኩ በውስጤ አይኖቼ ሱስ ይመስል የለመዱት አይቅርብኝ ይመስል እንባዬን ይዘረግፉት ጀመር ለምን ታለቅሺያለሽ አሁን እኮ መጥቻለሁ አለኝ እንባዬን እየጠረገ ሊዩና አቤል ግርግዳ ተደግፈው ቆመዋል ሳያቸው ፈገግ አሉልኝ ሳያቸው ደስ አለኝ ጤንነት ተሰማኝ ከእኔ ጋር በምን እዳቸው ነው የሚንከራተቱት የእኔ ምርጥ ጓደኞች አልኩ በሆዴ እፁ እድለኛ ነሽ ሳይደግስ አይጣላም አይደል የሚባለው ጓደኞችሽ በጣም መልካም ናቸው አለኝ ። ከዚያም በላይ ናቸው አልኩት ዶክተሩ መጣ ከኋላውም አንድ ሰው ጁስ ይዞ ገባ ማየው ደግሞ እያልኩ ናዲ ከተቀመጠበት ተነሳ እፁብ እንዴት ነሽ አለኝ ደህና ነኝ አልኩት  በደንብ ረፍት ካደረግሽና ከዚህ በኋላ ምግብ በአግባቡ ከተመገብሽ ይበልጥ ደህና ትሆኚያለሽ ይህንን ጨርሺና ግሉኮሱም ይበቃሻል ብዙ አታስወሯት ረፍት ታድርግ ብሏቸው ወጣ እፁብ እንዴት ነሽ ፀጉረ ልውጡ ደህና ነኝ አልኩት ፊቴ ላይ ማነው የሚለው ጥያቄዬ ተነበበለት መሠለኝ ኦው አማን ነኝ ስላየሁሽ ደስ ብሎኛል አለኝ  ድምፅህ አልጠፋኝም ነበር በስልክም ቢሆን ግን እንዴት መጣችሁ አልኩት እሱ ምን ይሰራልሻል ዋና መምጣታችን አይደል አለኝ ናዲ ።አንተ ዝም በል አንተን ያናገረህ የለም አልኩት አቤል ኸረ እፁ ልፋታችንንማ ገደል አትከቺውም ካላሁት ብለሽ በሞትና በህይወት መካከል አልሆንሽም አለ ሁሉም ሳቁ ያኔ ነበራ አሁን ከፈለገ ተመልሶ መሄድ ይችላል አይሞቀኝ አይበርደኝ አልኩት ። እንደማላደርገው አውቀሽ ነዋ አለኝ አንተ እንድታወራ አልተፈቀደልህም አልኩት ። እሺ ብሎ ዝም አለ አንጀቴ ተንሰፈሰፈ ገፅታው ሲያሳዝን ከልቤ መስሎት ድንግጥ ነው ያለው  ልክ እንዳልናፈኩት ሳስመስል ለራሴም ገረመኝ ሲያወሩ ሲስቁ ሰአቱ ነጎደ  ። አይ እግዚአብሔር ትገርመኛለህ እኮ ባልጠበቁህ መንገድ ትመጣለህ አሁን ምን ቢሉት ነው የመጣው ታማለች ብለውት ነው የመጣው ወይስ እውነቱን አውቆ ለነገሩ እራሳቸው ይነግሩኝ የለ ሆነም ቀረም ግን ስለሆነውም ስላልሆነውም ስምህ ይባረክ አልኩኝ ። እፁ ምነው የት ሄድሽ አለችኝ ሊዩ ኸረ የት እሄዳለሁ  እናቴ ደውላ አታውቅም አልኳቸው ደውላ ነበር በፌሎ ምሽግ ገብታለች አልኩኝ ጌታ ይቅር ይበለኝና ስትወጣ እኛ ራሳችን አንደውላለን ብዬአቸው ነበር ደውይላቸው አለችኝ ስንት ቀን ሆነኝ አልኳት 4ቀን የስኳርና ግሉኮስ መጠንሽ በጣም ወርዶ ነበር እና በዚህ እድሜ ለአቅመ ትልቁ ጨጓራ ደርሰሻል እንኳን ደስ ያለሽ አለኝ አቤል ቀውስ ብዬ ሳኩ ለማሚ ደወልኩላት በቃ ስፍስፍ አለች የሆነ ነገርማ ታውቋታል እኔ እኮ ቢጨንቀኝ ልመጣ ነበር ፀሎት ሲሉ አልዋጥ ብሎኝ ኡፍፍፍፍፍፍ ጌታ ይባረክ ሰይጣን ስንቱን አሳሰበኝ መሠለሽ አለችኝ አይዞሽ እናቴ ደህና ነኝ አትጨናነቂ ብዬ አረጋጋኋት ደስ አላት ሌላም ሌላም ነገር ስትነግረኝ ቆይተን ስልኩ ተዘጋ ። የናዲ ስልክ ደጋግሞ ይጠራል አያነሳም  ለምን አታነሳውም አልኩት አላስፈላጊ ስልክ ነው አለኝ ወዲያው የጓደኛው ስልክ ጠራ ኸረ ጀለስ ወደ እኔ ዞረች አለው አላየሁትም በላት እንደ አመሏ በውሸትና ክፋቷ ልትሞላኝ ነው አለ በስጭትጭት እያለ ማሂ ናት አልኩኝ ካቀረቀረበት ቀና አለ ። ለምን አታነሳላትም አልኩት ድጋሚ ህይወቴን ትበጥብጠው አለኝ ወደህና ፈቅደህላት መስሎኝ የበጠበጠችህ አልኩት ። ኸረ እፁ እንደሱ አይደለም አለኝ እየተስለመለመ እውይ ሊያስለቅሰኝ ነው እንዴ እፁብ አታደርጊውም አትጃጃዪ አልኩኝ ለራሴ ኮስተር ብየረ አልፈታ አልኩት እፁዬ እንደዚህ ስትሆኚ ታስፈሪያለሽ ከጥፋቴ አንፃር ባይገባኝም እስቲ እን ደበፊቱ ሁኚልኝ አለኝ ዝም አልኩት አቤሎና ሊዩ እየመሸም ስለሆነ በጠዋት እንመጣለን ብለው ወደ ጊቢ ሄዱ ነገ ጠዋት እኛም ልንወጣ እንችላለን ግን እስቲ ኑ አላቸው እስከ ምሽቱ 5ሰአት ምናምን አማን ሲለፈለፍ እንቅልፍ ወሰደኝ የሆነ  ሰአት ላይ ሰነቃ አማኑ የለም ናዲ አንዷ ወንበር ላይ ጥቅልልል ብሎአል አሳዘነኝ እንደምንም ባለኝ በሌለኝ ሀይል ተነሳሁና ብርድ ልብሱን አለበስኩት እኔ አንሶላውን እና ፎጣ ነበረ እሱን ለብሼ ገና ደቂቃ ሳይሆን ነቃ አይኑን እያሻሸ ለምን ተነሳሽ አለኝ ብርዱስ አልኩት የምን ብርድ የለም እኮ አለኝ አማንስ አልኩት መኪና ውስጥ አረፍ በል ብዬው ገብቷል ይመጣል አለኝ ። ብርድ ልብሱን መልሶልኝ ፎጣውን ደርቦ ተቀመጠ ቆይ እንዴት መጣህ አልኩት ፈገግ አለና እግዚአብሔር ነዋ በራሱ መንገድ አርጎ አለኝ እኮ እንዴት አልኩት....... ..........ይቀጥላል ........... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 3130Loading...
12
.          🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘         #ክፍል_24 ከአንዱ ጥግ ተቀመጥኩ በትንሹ ለመረጋጋት ሞከርኩ ለሊያ ደወልኩላት በፍጥነት ከአቤል ጋር እየከነፉ መጡ ስለተደናገጡ ላረጋጋቸው ብዬ ደህና ነኝ አልኳቸው ጁስ ገዝተው አመጡልኝ ትንሽ ነብስ ዘራሁ በጣም ተቆጡኝ አንቺ ስትኖሪ ነው እኮ ከናዲጋርም አብራቹ መሆን የምትችሉት ደህና ስትሆኚ ነው እውነቱንም ልታስረጂው ምትችይው በዚህች ጥቂት ግዜ እንደዚህ ከስተሽ  ማዘር ብታይሽ ምን እንደሚፈጠር አስቢ ቢያንስ ለእርሷ ስትይ ደህና መሆን አለብሽ አሉኝ ።እንደሱ ሳላስብ ቀርቼ እኮ አደለም ግን ብዬ እምባ ያረገዙ አይኖቼ እንደ ዝናብ አነቡ ምናገረው እንኳን አጣሁ ሁለቱም ተደናግጠው ተያዪና ማሂ እፁዬ በቃ ተረጋጊ የባሰ አስከፋንሽ እንዴ ነገ መልካም ይሆናል በዛሬው ሀዘን ነገ እንስቅበት ይሆናል እግዚአብሔር መልካም ነው አደል አለችኝ በአዎንታ አንገቴን ነቀነኩላት ። አቤል ቀጠለ እፁ እኔ ዋጋ ከፍዬ አስታርቃቹአለው እንደዚህ አትሁኚ ትንሽ ብቻ ግዜ ስጪኝ አለኝ ። አይይይ ልፋ ሲልህ ነው አልኩ በሆዴ ለነገሩ እኔን ለማፅናናት ስለሆነ ልፋቱን ከንቱ ላደርግበት አልፈለኩም አመሠግናለሁ አልኩትና ፈገግ አልኩ በጭንቅ ውስጥ እንኳ ብሆን ሰዎች ላይ ፊትን መከስከስ አይሆንልኝም ሁለቱም ደስ አላቸው ደጋግፈው ከተቀመጥኩበት አነሱኝ እሱን ቻው ብለነው ከሊዩ ጋር ወደ ዶርም ሄድን አረፍ አልኩበት ስለ መፅሐፍ ቅዱስ ሀሳቦች ማታ ስታነብ የተገረመችበትን እየነገረችኝ  እኔም ከዚህ በፊት  የተረዳሁትን እየተወያየን ቆየን ስልክ ተደወለልኝ በተደወለ ቁጥር ናዲ ነው እያልኩ ተንገብግቤ ሳየው እርሱ አይሆንም ጭራሽ አዲስ ቁጥር ነው አንስቼ ሄለው አልኩ ሄለው እፁብ አለኝ እኔ ፦አቤት እሱ፦እንዴት ነሽ? እኔ፦ደህና ነኝ እግዚአብሔር ይመስገን ። እሱ፦ህና መሆንሽ መልካም ነው ። ይቅርታ ማን ልበል ? እኔን እንኳን አታውቂኝም አማን እባላለሁ የናኦድ ጓደኛ ነኝ አለኝ ። በቅፅበት ከተኛሁበት ቁጭ አልኩ ናዲ ምን ሆነ ?.ኸረ  ምንም አልሆነም ተረጋጊ እኔ ለስራ ክፍለ ሀገር ነበርኩ ስለ እኔ ይንገርሽ አይንገርሽ አላውቅም ሁሌ ስለአንቺ ያወራኝ ነበር ። ያኔ አብራቹ ሳትሆኑ በፊት ካለው ቅርርባቹ ጀምሮ አሁን አሁን ስለ አንቺ አያወራኝም ምክኒያቱን ስጠይቀው ሊነግረኝ ፈቃደኛ አልነበረም የስራ ኮንትራቴን ጨርሼ ተመልሼያለሁ ። እና እርሱም በጣም ተጎድቷል ባስማማቹ ደስ ይለኝ ነበር አለኝ ። እንኳን ተጠይቄ ለማን ልተንፍስ ስለው የነበረ ጉዳይ አደል እንዴ አልኩና አንድ በአንድ ተረኩለት ። በጣም አዝኖ ማሂ ላይ የሚያየው ነገር መጀመሪያም እንዳላማረውና አሁንም ከዘገየን ማሂ አእምሮውን አቁስላ ልታለያያቹ ነው ምትፈልገው ሲመስለኝ  ያ እንዲሆን የማልፈቅድበት ምክኒያት ትዝ ይለኛል ናኦድ በጣም የምትጠይው ሰአት ምርር ብሎት ፀልይልኝ አለኝ ስንት ሰአት በሙሉ የፀሎት ሰአቴን አቃጥዬብሻለው ብሎ ሳቀ የፀሎቴ መልስ ናት ብዬውም ነበር  በጣም ጥሩ ሰው ነህ ጌታ ይባርክህ አልኩት አሜን የቻልኩትን ለማድረግ እሞክራለሁ አትጨናነቂ አለኝ አመስግኜው ስልኩ ተዘጋ ለሊያ ስነግራት በጣም ደስ አላት አንቺ ምን አይነት ናት ጓደኛሽ አለችኝ ተይ አትፍረጂባት እኔና አንቺም በእርሷ ቦታ ብንሆን እግዚአብሔር ካልረዳን እንደዚሁ ነው ምንሆነው ክፉ አልነበረችም እኮ እሷ ባትቆጣኝ ከናዲ ጋር ራሱ አልቀራረብም ነበር እንዳልጎዳው ስትቆጣኝ ልታስማማን ስትጥር ነበር የዛሬን አያድርገውና ሁሉንም ግዜ ይፈታዋል አልኳት ።ኀ ከናዲ ጋር ስትታረቁ ይቅር ትያታለሽ አለችኝ እኔስ በምህረት አይደል የቆምኩት ለምን አልላትም አሁን እንኳን የተቀየምኳትን ትቼዋለሁ አልኳት ሆሆሆሆሆ ይሄ የጤና አይደለም ግድ የለሽም እፁ በይ አሁን ጁስ ገዝቼልሽ ልምጣ ብላ ወጣች ። እንዲህ እንዲህ እያሉ ቀናት ነጎዱ ። እኔም የለየላት የጨጓራ ታማሚ ሆኜ ራሴን አገኘሁት ዛሬም ክሊኒክ ነው ነገም መውደቅ ነው የክሊኒኩን ግሉኮስ አጋመስኩት ብል ማጋነን አይሆንብኝም አሁንማ ለመዱት ዶክተሮቹ ይቆጡኝ ጀመረ ከዚህ በኋላ ራስሽን ከሳትሽ አደጋ ውስጥ ነሽ ምግብ በአግባቡ ተመገቢ መድኀኒት በስርአት ውሰጂ ምትጨናነቂውን አቁሚ አሉን እስማማና አልተገብረውም ። ጠዋት ከእንቅልፌ ነቃሁና መነሳት አቃተኝ ቤቱ ይዞራል ስልኬን እንደምንም አነሳሁት 12:10 ይላል ሰአቱ አቤል መልዕክት አስቀምጦልኛል እፁ ትንሽ ነገር ነው የቀረው በቅርቡ ከናዲ ጋር አስታርቃቹአለሁ ይላል አይ አቤል እኔን ለማፅናናት እንቅልፍ ማጣትም ጀመርክ አልኩ ሙሉ ሰውነቴ በላብ ተጠምቋል ሊዩ አጠገቤ ስለተኛች ደምፅ ማውጣት ሸክም ሆኖብኝ በእጄ ጠራኋት ከዚያ በኋላ የሆነውን አላስታውስም ........... .............ይቀጥላል ........... @Gospel_literature @Gospel_literature .✍written by Aksan Adane
1 5570Loading...
13
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘          #ክፍል23 ስከፍታቸው ምነው ህልም በሆነ ይሄ ብሩክ አሁንም ተጫወተብኝ እግሬ ስር ሲወድቅ ሲጠመጠምብኝ አብረን ተቀምጠን ሁሉንም በፎቶ ላከልኝ እንኳን አጋጣሚ ሆን ተብሎ በዕቅድ ለፕሮግራም የተነሳነው ፎቶ ነው የሚመስለው እንዳየሁት ሰውነቴ በሙሉ ጋለ እንዴ አይደረግም የንዴት ሳቅ አይሉት ማልቀስ ሁኔታዬን በምን ልግለፀው ሊያም ጥጋቡም መጡ ጓደኛዬ ጉድ ሆንኩልሽ አልኳት ሁኔታዬ አስደንግጧት ምነው እፁ አለችኝ እዛው እንባዬ እርግፍ እርግፍ አለ ምነው ምን ተፈጠረ አለችኝ ሊዩ እኔ ለፈተና ብቻ ነው እንዴ የተፈጠርኩት ቆይ እኔ መጥፎ ሰው ነኝ ለምንድነው ደስተኛ ሆኜ መቆየት የማልችለው ግራ ገብቷት ስልኬን ተቀብላኝ አየችው ። የማወራውን እንኳን በቅጡ ሳላውቀው ብሶቴን በእንባ ጅረት በጆሮአቸው አንቆረቆርኩት ልታረጋጋኝ ጥብቅ አድርጋ አቅፋኛለች ምንድነው ደህና አይደለሽም  አለኝ አሳዝኜው ይሆን አልገባኝም ደህና ነኝ ብዬ እየተጣደፍኩ ወደ ዶርም ሄድኩ ለናዲ ደወልኩለት ስልኬን አያነሳም ብዙ መልዕክቶች ፃፍኩለት አይመልስም ማልቀስ አልፈለኩም ግን እንባዬ ይወርዳል ። ሊዩ መጣች ምትለኝ እንኳ ጠፍቷት በዝምታ አቀረቀረች ። ሊዩ ስልኬን አያነሳም ዋሽቼው ነው የሚመስለው ምንም እንዳትደብቂኝ ብሎኝ ነበር እኮ ምነው ያኔውኑ በነገርኩት አልኳት በእኔ እንደውልለት  አለች አያነሳም  አልኳት አቤል ምረዳቹ ነገር ካለ ደውሉልኝ ብሏል አለችኝ አቤል ደግሞ ማነው አልኳት ማለቴ ጥጋቡ ስሙን ነግሮኝ ነው አለችኝ ። እኔን ሊረዳኝ የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው ትናንትም ያለፍኩት በእርሱ አይደል አሁንም ለእርሱ ልተውለት እንጂ ምንም ማድረግ አልችልም አልኳት ። እፁ መልሰሽ እኔኑ ታፅናኝኝ አይ አንቺ የታመንሽበት አምላክ ይርዳሽ አለችኝ ። በጣም ክፍት አለኝ በተለይ ናዲ የዋሸሁት  መስሎት ራሱን ይጎዳል ደጋግሜ ብፅፍለትም ምንም ምላሽ የለም ደግነቱ አሳይመንቱን በግዜ ጨረስኩ እንጂ እንዴት ላንብብ የእውነት እንዲ ይጨክናል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር ስልኬን አያነሳ በሌሎች ስልኮች ብደውል አያነሳ ጭራሽ ዘጋው ሳምንት ሆነ ሊዩ አትረበሺ ሰይሰጣን በዚህ አሳቦ ትምርትሽ ላይ እንድትደክሚ ነው እጅማ አንሰጥም እያለች ታበረታኛለች እንደበፊቱ በሞራል ባይሆንም አነባለሁ ማሚ ስትደውል ሁሌም ሰላም ነው ነው የምላት ልነግራት እልና ማስጨነቅ እንጂ ምን አመጣለሁ ብዬ እተወዋለሁ  ። ከካፌ ስወጣ ጥጋቡና ጓደኞቹ  ተገትረው ነበር አንደኛው አይቶን እንደለመዱት ሁሉም ሲዞሩ ኤጭ አሁንም ሊጃጃል እንዳይሆን አለችኝ ባክሽ ተይው ነይ አትያቸው አልኳት ገና ትንሽ እንደተራመድን ተነጥሎ እየመጣ ነው መጣልሽ አለችኝ ኡፍፍፍፍፍ ምንድነው ደግሞ እያልኩ በሆዴ ስሚ ማስረዳት ከደበረሽ በግልፅ አታወሪም አለኝ እርምጃዬን አላቆምኩም ከኋላ ከኋላ እየተከተለ ነው አንቺን እኮ ነው አሁንም አልተውሽም ማለት ነው ምትወጣጠሪውን ነገር አለኝ መልስ አልሰጠሁትም  እርምጃውን አፈጠነው ና ከፊት ለፊቴ ቆመ መልሺልኝ እንጂ አለኝ አይኑን እያጉረጠረጠ በደከመ ትንፋሽ በተቅለሰለሰ ድምፅ እባክህን አሁን ላይ ከአንተ ጋር ሽንጤን ገትሬ ቃለ ምልልስ የማደርግበት አቅም የለኝም ለምን አትተወኝም ሁሉም ነገር አድክሞኛል እባክህ ቢያንስ እህት ካለህ እዘንልኝ አትከታተለኝ አልኩት እያየሁት ፊቱ ተቀየረ  አሳዘንኩት መሠለኝ ዘወር ብሎ አሳለፈኝ  መንገዴን ቀጠልኩ ሳላስበው ብዙ ተራምጄያለው ለካ ሊያ አጠገቤ የለችም የት ሄዳ ነው የሚሆነው እያልኩ ልደውልላት ስልኬን ከኪሴ ሳወጣ ማሂ ደወለችልኝ ደግሞ ምን አገኘች ከናዲ ጋር በመጣላታችን ደስታዋን ልትገልጥልኝ ነው እንዴ ምን አስባ ነው እያልኩ ስገረም ስልኩ ተዘጋ መልሼ ልደውል አልደውልም ሲጀመር በምን ሞራል ልታወራኝ ነበር የደወለችው ትንሽ እንኳን አታፍርም  በቆምኩበት ብቻዬን ስለፈልፍ ሊያ መጣች አንቺ የት ሄደሽ ነው አልኳት ጥጋቡ ነዋ አሳዘነችኝ ምናምን አላለኝም መሠለሽ ጓደኛዬ ጌታ እየተጠቀመብሽ ነው ሴቱ ሁሉ የሚፈራው ጥጋቡ ለሰው ማዘን ከጀመረ ተመስገን ነው ሌላ መን ይባላል ብላ ሳቀች  ደግሞ ቢያንስ ወደ ጌታ ልናቀርበው ከቻልን ይህንን አጋጣሚ መጠቀም አለብን እፁ እንደሚከብድ አውቃለሁ ግን መቀየር አለበት አደል አለችኝ ሊዪ ሳላስብ ቀርቼ አይደለም ገና ከተጣላን ግዜ አንስቶ እንዴት እንደምመሠክርለት ሳስብ ነበር ነገሮች እየከረሩ መጡ እንጂ አሁን ትንሽ ነገሮች መረጋጋት አለባቸው እኔም በሙሉ ቀልቤ አይደለሁም አልኳት አይዞሽ ጓደኛዬ ይህም ያልፋል አለችኝ ። ከጥጋቡ ጋር በትንሹም ቢሆን ተቀራርበናል ሰዎች ሁሉ ይገረሙ ጀመር ጓደኞቹ በቃ ተጃጃለ ብለው ተናደውበት አብረውን አያሳልፉም በፊት ባህሪውን የሚያውቁ ደግሞ እፁብና ሊያ ለየላቸው ከዱርዬ ጋር መዋል ጀመሩ የሚል ከቅርብ ሰዎቻችን ሀሜትና ትችት እያስተናገድን ነው ። ጭራሽ ከልጅነቱ ቸርች ውስጥ አድጎ እንደነበረ እና እንደዚህ ለመሆን ያበቃው ምክኒያት እንዳለ ነገረን ከሱስ መውጣት እንደሚፈልግ ግን እንዳቃተውም ነገረን አብሮን ቸርች ይሄድ ጀመር በመሀል ተደብቆን ይጠፋል ። ስለ ናዲ ስለነገርኩት ደግሞ በጣም ያዝንልኛል ሁለቱም ከጎኔ ሆነው እያፅናኑኝ ነው ። ከናዲ ጋር መራራቁ ክፉኛ እየጎዳኝ ከሰውነት ተራ እየወጣሁ ነው ይጨንቀኛል ይነስረኛል ንባብ አይገባኝም ሁሉንም ትቼ ልመለስ እልና ያቺ ምስኪን እናቴና እህቴ ፊቴ ድቅን ይሉብኛል ጨክኜ ለመጋፈጥ እጥራለሁ ዛሬ ሰኞ ነው ከክላስ ወጥቼ ወደ ዶርም እየሄድኩ ከዞረኝ ከባድ ራስ ምታት ነበረው ራሴን ለመቆጣጠር ብሞክር ሰማይ ምድሩ ይዞራል ከእዱ ጥግ ተቀመጥኩ ........ ...........ይቀጥላል.......... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 4180Loading...
14
ካህን በገዛ ቁስልህ አተረፍከኝ ከፍለህ አቋደስከኝ.... Graphics By ➪ @wunu_pa @wunuye_picture @wunuye_picture
1 3020Loading...
15
.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘           #ክፍል 22 ......በንዴት ንግግር ኸረ በጭራሽ አለች እሷም  ግራ ተጋብታ እፁ አንቺን ለማግኘት ከዚህ የተሻለ መንገድ አልነበረም ብሎ ተቀመጠ ለምን አትተወኝም ብዬ ጮኹኩበት ምንድነው እፁ አለችኝ ሊያ ብሩክ ተብዬው ነው አልኳት የታለ እቃው ብላ አፈጠጠችበት ስልኬንስ ከየት አመጣህ አለችው ሁለታችንም መልስ እየጠበቅን አቆበቆብን እሱ ዝም ብሎ አቀረቀረ ተናዳለች በጣም እፁ እኔ ምንም የማውቀው ነገር የለም ጌታን ነው  የምልሽ አለችኝ ተነሺ እንሂድ አልኳት እኩል ብድግ አልን ገና ሁለቴም ሳልራመድ እፁ እባክሽ ብሎ እግሬ ስር ተንበረከከ ሰዉ ሁሉ ትኩረቱን ወደ እኛ አደረገ ሰውዬ ያምሀል እንዴ አታዋርደኝ ኸረ ባክህ ተነስ አልኩ በንዴት ፊቴ ሲሞቅ ይታወቀኛል አልነሳም እፁ ይቅርታ ካላደረግሽልኝ ።ሊያም ተሸማቃ በሁለት እጆቿ አፏን ይዛለች  ከረ ጌታን ፍራ ባክህን አልሰማ ሲለኝ ተነስ እሺ እኔ አልተቀየምኩህም አልኩት  አመሠግናለሁ ብሎ ተጠመጠመብኝ ሲያፈጥ የነበረው ሰው በጭብጨባ ሆቴሉን አደመቁት ምነው መሬት ተከፍታ በዋጠችኝ በሰርጌ ቀን ሲቀር እንኳን እንዲ አልተሸማቀኩም ሰዉ ትኩረቱን እስኪያነሳልኝ አንገቴን ደፍቼ  ተቀመጥኩ ሊያም ስቅጥጥ ብሏት ተጠግታኝ ተቀመጠች እፁዬ አይዞሽ ተረጋጊና እንውጣ አለችኝ አልቅሽ አልቅሽ አለኝ እፁቤ አንቺ ላይ ጨክኜ አልነበረም  ያን ሁሉ በደል የፈፀምኩብሽ የገጠመኝ ሁሉ.. አላስጨረስኩትም እጄን ዘረጋሁ ዝም በልልኝ መሆኑ ገባውና ዝም አለ ላየው ሁሉ ቅፍፍ እያለኝ ነበር እንደምንም ራሴን አረጋግቼ ። ትሰማኛለህ ያንተን የፈጠራ ታሪክ የምሰማበት ግዜ የለኝም በቃ አንዴ ሆኗል በዚህ አላማርርም ምንም ካንተ መስማት አልፈልግም ለዘመናት ጥያቄ ሆኖብኝ ነበር መልስ ባሻኝ ሰአት የት ነበርክ አሁን ለራሴ ያንቺ ስላልሆነ የጌታ ፈቃድ ስላልሆነ ብዬ መልሼለታለው በምህረት ስለቆምኩ ይቅርታህን እቀበላለሁ ዳግመኛ ግን ላይህ አልፈልግም ብዬው ብድግ አልኩ  ሊያም ተከተለችኝ ። ሊያ ጨንቋት እፁዬ ተጠቀመብኝ አደል የእውነት ቀድሜ ሴራ መሆኑን ብገምት እንሂድ ብዬ አላስጨንቅሽም ነበር እኔ እራመዳለሁ እሷ ትለፈልፋለች አንቺ ምን አጠፋሽ በቃ መሆን ነበረበት ሆነ አልኳት እኔ እኮ ትገርሚኛለሽ ነገሮችን ቀለል ማድረግ ታውቂበታለሽ አለችኝ አክብጄ ምንም ስላልጠቀሙኝ ነዋ ከሰውነት ተራ አወጡኝ ከአምላኬም ከሰውም ፀበኛ አደረጉኝ ስለዚህ አሁን በተቃራኒው ቀለል እያደረኩ መኖርን መርጫለው አልኳት መንገድ ላይ  በኮንትራት ወደ ጊቢ ተመለስን ። ከሰአት በኋላ ልብስ ስናጥብ አሳለፍን አሳይመንት መስራት ስለነበረብኝ ወደ ላይብረሪ ገባን ናዲ ደጋግሞ ይደውላል እንዳያቋርጠኝ ለመጨረስም እየተቃረብኩ ስለነበር አላነሳሁለትም ደጋግሞ ደወለ አላነሳሁም ቢቸግረው በሊያ ስልክ ደወለ ኸረ እፁ ችግር ገጥሞት ቢሆንስ አለችኝ እየተከራከርን ሳልወጣ ተዘጋ መልሶ በሌላ ስልክ ተደወለልኝ ራሱ ነው የሚሆነው ብዬ ስልኩን ይዤ ወጣሁ  ከአንዱ ጥግ ሄጄ  አነሳሁት አሀ ከእኔ ጋር ነው ችግሩ አለኝ የምን ችግር አልኩ ደጋግሜ ደውዬ ነበረ ሳታነሺ ቀርተሽ ስልኩ ሌላ ሲሆን ማንሳትሽ ገርሞኝ ነው አለኝ ። አንተ ደግሞ ነገር አትብላ ሰላምታ አይቀድምም አንተው መሆንህን አውቄ ነው ስልኩን ያነሳሁት ላይብረሪ ነበርኩ ላራሴ ኑሮ መሮኛል አታባብስብኝ አልኩት  ብስጭትጭት ማለቴ ገርሞታል ምነው ምን ገጠመሽ አለኝ ባክህ ይሄ ነዋ አልኩና ድንግጥ አልኩ ሳስተውል ከነገርኩት ይበሳጫል ብዬ ዋጥ አደረኩት ማነው እርሱ አለኝ አታውቀውም  አንዱ አናዶኝ ነው አልኩት ማነው ምን አደረገሽ አለኝ ዝም ብሎ ነው ባክህ የጉርምስና ጥጋብ ያልበረደለት ለምን እንደመጣ እንኳን አይገባኝም እዚህ ያሉት ሁሉ ታታሪና ጎበዝ ተማሪዎች ናቸው እርሱ ጉራና ጉልበቱን ተማምኖ ነው መሠለኝ እዚህ ያለው ብዬ ላወራ ያልነበረውን ስለ ጥጋቡ ዘባረኩለት ለራሴ ራሱ ገረመኝ ይሄን ያህል አናዶኛል እንዴ ብዬ እና ምን አድርጎ አናደደሽ አለኝ አይ ተወው በቃ ሲጀመር ቀለል አርገው ላወራ ያልነበረውን ነው ያወራሁት ። እና ደግሞ ደህና ከሆንክ መጨረስ ያለብኝ አሳይመንት አለ  እሱን ስጨርስ ልደውልልህ ብዬው ስልኩን ዘጋሁት የሆነ ነገር ክብድ አለኝ ከኋላዬ ዞር ስል እንደ ሃውልት ተገትሯል ልቤ ትርክክ አለ  በኢየሱስ ስም አንተ ምን ትሰራለህ አልኩት ምነው ምን አስደነገጠሽ አለኝ ማን እኔ ነኝ ምደነግጠው አልኩት ምን አልባት ስጋዬን እየበላሽ ስለደረስኩብሽ ይሆናላ የተደናገጥሽው አለኝ እኔ እፁብ አንተን መናገር ፈርቼ ነው ስጋህን ምበላው በጣም ነው ምታሳዝነኝ ሲጀመር ስላንተ ስለማውራቴ ምን ማረጋገጫ አለህ ለምንድነው ቆይ ምትከታተለኝ አልኩት ይሄ ከአቅምሽ በላይ የሆነ ትዕቢትሽ እስኪበርድልሽ አልተውሽም አለኝ ደግሞ ሚገርመኝ ሌሎቹ ከእሩቅ እንኳን ሲያዩኝ መንገድ ይቀይራሉ የኘንቺ ትዕቢት ግን ፈገግ አልኩ ሌሎቹ ራሳቸውን ስለሚንቁ ይሆናላ የሚንቀጠቀጡልህ እኔ ከእግዚአብሔር በቀር የምፈራው ነገር የለም መንቀጥቀጥ ካለብኝም ለጌታዬ ነው እርሱንም ንጉስ ስለሆነ የፍቅር እንጂ ያጠፋኛል ይገለኛል የሚል የፍርሀት መንቀጥቀጥ አይደለም ምክኒያቱም እርሱ ፍቅር ነው ከእርሱ ጋር ሆኜጰደግሞ ምን ለሰው አንቀጠቀጠኝ አልኩት ዝም ብሎ ያየኛል እእእእ ነቃ በል አንጂ የምን መደመም ነው በቃ ሂድ እኔ ወደ ንባቤ ልመለስ ነው ከፈለክ ደግሞ አብረኸኝ ማንበብ ትችላለህ ብዬው ገባሁ ። ሊያ ምንድነው ምን ሆኖ ነው አለችኝ እየተንሾካሾከች ዝም ብሎ ነው ምንም አልሆነም ይልቅ አምልጦኝ ስለ ብሩክ ልነግረው ነበር አስቀይሼ ስለ ጥጋቡ ስነግረው ይሄ ኮቴ ቢስ ከኋላዬ ተገትሮ ሰማኝ አልኳት ህህህህ ብላ ጮኸች ሳታስበው ድምጿ ጮክ ብሏል ደንገጬ ፀጥ አልኩ  ሁሉም ዞር ዞር ብሎ አየንአንቺ የምሻል እንዴ አልኳት እና ምንም አላለሽም አለችኝ ምን አስደነገጠሽ  በኋላ እናወራለን አሁን አርፈሽ አንብቢ አልኳት ። ብዙም አልቆየም መፅሀፍ ይዞ ከፊትለፊታችን ተቀመጠ ሁለታችንም ተያየን እሷ ስለምትፈራው አቀረቀረች እንድታስረጂኝ ነው የመጣሁት አለኝ ልጁ ጤና የለውም እንዴ ከየት ያመጣው ትህትና ነው አልኩና በሆዴ የቱ ነው የከበደህ አልኩት አሳየኝ እኔ እየተንሾካሾኩ ማስረዳትአልችልም ይህቺን ሁለት መስመር የምትሆን እስክጨርስ አንብበው ወጥተን አስረዳሀለው አልኩት ሊያ ገርሟት አንዴ እሱን አንዴ እኔን ታየናለች ስለኬ ላይ ቴክስ ደረሰኝ ናዲ ነበር ቴሌግራም ላይ ያስቀመጥኩት እይው ይላል ። ምን ይሁን ብዬ እዛው ከፈትኩ ፎቶዎች ነበሩ ኤጭ ይቀልዳል እንዴብዬ ሳልከፍታቸው አሳይመንቱን ጨረስንና ተነሱ አልኩኝ ሊያ ፈርታው ልትሞት ነው ቀድሜያቸው ወጣሁ እሷ ተከተለችኝ ፎቶዎቹን ስከፍታቸው ምነው ህልም በሆነ .......... .............ይቀጥላል............ @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 6200Loading...
16
እኔን ለማደን ነው የደም ላብ ..... Graphics By ➪ @wunu_pa @wunuye_picture @wunuye_picture
1 5240Loading...
17
.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘           #ክፍል_21 ደስ አለኝም ከፋኝም በእርሱ መደሰት ደስ ቢለኝም እንደዛሬው አይነት ደስ የሚል ቀን አሳልፎ እንደማያውቅ ሲነግረኝ ከፋኝ ማንበብ ስለነበረብኝ ቻው ተባባልንና ለማሚ ደውዬላት አወራንና በግዜ እራት በልቼ ወደ ላይብረሪ ስሄድ ከዛ ጥጋብ አናቱ ላይ ከወጣ ልጅ ጋር ተጋጨን  እያየህ አትሄድም አልኩት ባላይስ ምን ልታመጪ አለኝ የወደቀውን ደብተሬን እያነሳሁ ቢያንስ ይቅርታ መጠየቅ ልመድ አልኩት ና ሄድኩ እስከ 6ሰአት እረፍት እያደረኩ አነበብኩና ወደ ዶርም ስመለስ አንዲት ቀጭን ቆንጆ እህት ብላ ጠራችኝ እርምጃዬን ገታ አድርጌ አቤት አልኳት ለምንድነው ብቻሽን ነው ምትገቢው ምትወጪው አለችኝ በጥርጣሬ እያየኋት አይ ባህሪዬ ነው አልኳት ። ጓደኛ መሆን እንችላለን አለችኝ ሆ ደግሞ ምን አይነት ዘመን መጣ እያልኩ በሆዴ አሁን እንደ ፍቅር ጥያቄ ላስብበት ልበላት ወይስ ምንድነው እያልኩ ከራሴ ስሟገት ምነው ይደብርሻል አለችኝ እውነት ለመናገር እንኳን ከማላውቀው ሰው ጋር ከማውቀውም ጋር ቀስ በቀስ ካልሆነ መቀራረብ አይሆንልኝም አልኳት ችግር የለውም አላስጨንቅሽም ሊያ እባላለሁ አለችኝ እፁብ አልኳት እያወራን ወደ ዶርም ደረስን አሷም ወደ ብሎኳ እኔም ወደ ራሴ ብሎክ ገባን ደክሞኛል ቢሆንም ፀልዬ ነው መተኛት ያለብኝ ብዬ ፀለይኩ ዶርም ውስጥ አህዛቦችም አንድ ክርስቲያንም አለች ግን ማናቸውንም አልቀርብም ክርስቲያኗም እስከዚህም ናት ስፀልይ ደስ አይላቸውም ስልክ እያወሩ ይጮሀሉ ወይ ዘፈን ይከፍታሉ ወይ ይስቃሉ ለእኔ ግድ አይሰጠኝም ለመተኛት ብሞክር እንቅልፍ እንቢ አለኝ ግን በጣም ደክሞኛል ስልኬን አንስቼ ቴሌግራሜን ከፈትኩት ናዲ ብዙ ፎቶዎች ልኮልኛል ከፍቼ አየኋቸው በጣም ያምራሉ ማሂ ባትቀይርብኝና ግራ ባታጋባኝ አልቀናም ነበር የምር ክፍት አለኝ እምባ እየተናነቀኝ እንደምንም ተኛሁ ቀናት እየሄዱ ከሊያ ጋረም በጥቂቱ እየተቀራረብን ነው አብረን ካፌ ላይብረሪ ቸርችም መሄድ ጀምረናል። ክላስ መምህሩ የለም ነበር ዶርም አረፍ ብዬ ሊያ እያለከለከች መጣች ምንድነው አልኩኝ ጋደም ካልኩበት በቅፅበት ቁጭ አልኩኝ እፁ እፁ ምንድነው አልኳት በሰላም ከክላስ ወጥቼ ስመጣ ያ የተጣላሽ ልጅ ስልክሽን በግድ ተቀበለኝ አልሰጥም ብዬው ነበረ እጄን በግድ ጠምዝዞ ነው የተቀበለኝ ትንፋሽ ሳትወስድ በአንዴ ተነተነችው እና ምን አስደነገጠሽ አልኳት መረጋጋቴ ገርሟት አንቺ ይሄ አጋንንት እኮ ነው ደህና ሰው መስሎሽ ጥጋቡን እኮ ነው ሰምተሽኛላ አለችኝ ባክሽ ተይው ትንሽ  ተረጋጊ ና ወደ ንባባችን አልኳት ። ስሙን ስለማናውቅ ጥጋቡ ነው ምንለው ይደውላል መልዕክት ይፅፋል እኔ ምንም መልስ አልሰጠውም ። የመጣሁ ሰሞን ናዲም ያለማቋረጥ ይደውልልኝ ነበረ አሁን እኔ ነኝ ምደውለው አንተ ግን አይደብርህም እየተቀየርክ ነው አልኩት እኔ እኮ እንዳልረብሽሽ ብዬ ነው ንባብ ላይ ምናምን ትሆኚያለሽ እያልኩ ይቅርታ እናቴ አይለመደኝም አለኝ ይሁንልህ እንዳትደግመው ብዬ አለፍኩት። ዛሬ ደግሞ በማለዳው ፀሀዪ አትውጡ አትውጡ ያሰኛል ቀኑ ቅዳሜ ነውና ሊያ በማታውቀው ስልክ ተደውሎላት ከቤት ዕቃ ተልኳል ተቀበይ ተባልኩ ብላኝ እየወጣን ጥጋቡና ጓደኞቹ ዘውትር ከሚጉለቱበት ቦታቸው ሰፍረዋል አንደኛው ብቻ ነበረ እየየን የነበረው ሁሉም ወደ  እኛ ዞሩ ወይኔ እፁ ተዋረድን በሌላ መንገድ እንሂድ እያየኋት ውሃ ሆነች እፁ በናትሽ እኚ ሰይጣኖች ሊጋተቱን እንዳይሆን ብላ ቆመች አንሂድ እንጂ ያምሻል እንዴ እኔ በራሴ ባልተማመንም እግዚአብሔር ከእኔ ጋር እያለ እንኳን እነዚህን ሰይጣንን አልፈራም ነይ በይ በናትሽ አልኳት አካሄድ ሁሉ ጠፍቶባት ክንዴን ጥብቅ አድርጋ ስትደነባበር አጠገባቸው ተጋረብን ጥጋቡ ከተቀመጠበት ተነሳ ያው እንደፈራሁት አለች ሁኔታዋ ያስቃል ፊት ለፊታችን መጥቶ ተገተረ አንቺ ጥጋብሽ መች ነው ሚበርድልሽ አለኝ እጆቼን አጣምሬ ዝም ብዬ አየሁት ደግሞ ርዝመቱ ቆይ ስለ እኔ  አልነገሩሽም ንቀትሽ እንዴት ነው አለኝ ቆይ ማነሽ አንቺ ደምስሩ እየተገታተረ  በፍቅር እንጂ በጉልበት አላምንም አልኩት መረጋጋቴ ይገርመዋል አቤሎ ችግር አለ አለው ከተጎለቱት መሀከል አንዱ እቺ ትንሽዬ ጊንጥ በራሷ ላይ ችግር ልትሆን መሠለኝ ለጊዜው ምንም የለም አለው ከመንገዴ ዞር ትልልኝ አልኩት ባልልስ አለኝ ጊንጥ ህይወትን ልታሳጣ ሁሉ ትችላለቻ ሌላ ምን ይፈጠራል አልኩት የንቀቱን ከት ብሎ ሳቀ እየገለፈጠ ገፈተርኩትና አልፌ መንገዴን ቀጠልኩ ቁሚ ብዬሻለው አለኝ ዝም ብዬው ተራመድኩ እፁ እንቁም ጉድ ያመጣብናል በናትሽ በሰላም እንኑር አለችኝ አትንቦቆቦቂ ወደዛ ዝም ብለሽ ተራመጂ አልኳትና በመሉ በራስ መተማመን ወጣን የተባልነው ሆቴል ደርሰን ተቀመጥን ከደቂቃዎች በኋላ ስልኩ ተደወለላት አንስታ አዎ መጥቻለው እዛው ነኝ ብላ ዘጋችው ምን ሊሆን ይችላል እነ ማሚ ሳይነግሩኝ እንዴት ዕቃ ይልካሉ ደውለውም ተቀበይ አላሉኝ አለችኝ ምን ከቤት አልተደወለልሽም አለኳት አዎን ቆይ ልደውልላት ብላ ስልኳን እንዳነሳች ተደወለላት አንስታ አዎ አየውህ ብላ እጇን ከፍ አደረገች  የፊቷ ገፅታ ከጀርባዬ ሰው እየመጣ እንደሆነ አሳበቀልኝ  ከተቀመጠችበት ብድግ ብላ አንተ ነህ አለች ቀና ብዬ ሳየው ድንጋጤ ወረረኝ ትተዋወቃላችሁ አልኩኝ ግራ በመጋባትና በንዴት ንግግር ............ . ..............ይቀጥል............. @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 7180Loading...
18
.        🤔ጥያቄዬ🤔 Present by Hopeful_Tube 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘          #ክፍል_20 ......እንዴት ልመን ከቆመ ታክሲ ስር ተደበኩ አጎንብሼ በቀስታ ማየት ጀመርኩ ጌታ ሆይ እሱ አይደለም በለኝ አብረው ምን እየሰሩ ነው ደጋግሜ አየሁት ራሱ ብሩክ ነበር የት ተዋውቀው ነው ምንስ እያደረጉ ነው መላሽ በሌለው ጥያቄ ብዛት ተጨነኩ ብቻ ለደቂቃዎች እዚያው ቆዩና መኪናውን አስነስቶት ሄዱ ቀጥ ብዬ ወደ ቤት ተመለስኩ በሀሳብ ደንዝዤ ቀረሁ ። ማሂ ለዚ ነበር የተቀየረችብኝ ለብሩክ ብላ ብቻዬን ለፈልፋለው ይሄ ሰውዬ ምን እየሰራ ነው ለምንስ መጣ በጥያቄ ብዛት እንቅልፍ አጥቼ ስላደርኩ ሲነጋ እንቅልፍ ወሰደኝ ስነቃ 5ሰዓት ሆኗል ናዲ በተደጋጋሚ ደውሎ ከመጨነቁ የተነሳ ብዙ ቴክስቶች አስቀምጦልኛል ደግሞ ከነገ ወዲያ ወደ ጊቢ እሄዳለሁ መልሼ ደወልኩለት ንግግሩ ሲያሳዝን ምን አድርጌሽ ነው አስጨነቅሽኝ እኮ አለኝ ስለ ማሂ ሳልነግረው ማታ ስላልተኛው ነው ብዬ ይቅርታ ጠየኩት እነ ማሚም ደብሯቸዋል መጀመሪያ ስሄድ እንኳን እንደዚ አልከፋቸውም ነበር ። ሁሉንም ነገር ለጌታ ሰጥቼ ተውኩት  ናዲን አግኝቼው ሌሎችጨአብረውኝ ወደ ጊቢ ሚመለሱ ጓደኞቼንም አግኝቻቸው ወደ ቤት ተመለስኩ ሱቅ ዘግተው እቤት ቡና እያፈሉ ነበር ገባሁና በዝምታ ተዋጥኩ ምነው የኔ ልጅ አለችኝ ምንም እማ አልኳት የኔ ልጅ ልትሄጂ ስለሆነ ከፍቶሽ ነው ጠንካራ አልነበርሽ አለችኝ ማሚን ምደብቃት ነገር ስለሌለ አይ እማ አሁን አሁን እየደከመኝ ነው ደግሞ ለሱ ብቻ አይደለም አልኳት እና ከናኦድ ጋር ሰላም አይደላችሁም አለችኝ ኸረ ሰላም ነን አልኳት ተዐምር ጣልቃ ገባችና እና ለዛች ለማሂ ባልሆነ አይገርምሽም ትበዢባታለሽ እንደ አንቺ አይነት ጓደኛ ደግሞ አግኝታ ነው ቀረሽባት የኔ እህት ከማንም ብትበልጥ እንጂ አታንስም ካልሆነ እኔ እናገራታለሁ አለች በቁጣ መንፈስ ደምስሯ ተገታትሮ ኸረ ተረጋጊ አንቺ አይጥ አቅም እንዳለው ሰው የምን ያዙኝ ልቀቁኝ ነው አንደሱ አይደለም ብዬ  በረጅሙ ተነፈስኩ ። እና ምንድነው ኸረ ባክሽ አታስጨንቂን አለችኝ እናቴ ማሂና ብሩክን አንድ አብረው አየኋቸው አልኳት ምን ብሩክ ብሩክ አለችኝ ዝም አልኩ ማሚ ደግሞ አሜሪካ ነው የተባለው ነዋ አለቻት ተዐምር ምን ይሄ ነብሰ በላ ምን ሊሰራ መጣ አለች ከመጣ እንደቆየና የሚፅፍልኝን ቴክስቶች ና ያለኝን ነገርኳት በይ በይ አሁን በላይሽ ላይ እየተመሳጠሩ ነው የሚሆነው ሳይውል ሳያድር ለናኦድ ንገሪው አለችኝ እማ እንደሱ አይሆንም ናዲ ብነግረው እንኳን አያምነኝም በእሷ ላይ ሙሉ እምነት አለው አልኳት እና አንቺ ነሽ የማትታመኚው ካልሆነም እኔ ራሴው ነግረዋለሁ አለችኝ ኸረ እናቴ ምን ሆነሻል አዎን አሁንም ህይወትሽን ከሚያመሰቃቅሉት ክብሬ ማዕረጌ አማች ምናምን ሳልል እኔው ራሴ ጠርቼ እነግረዋለው አለችኝ እልህ እና ቁጣ እየተናነቃት  በቃ አንቺ አትጨናነቂ እራሴ እነግረዋለሁ አልኳት ። ሁሉንም ትቼ ከጌታ ጋር አሳለፍኩ ጭንቀቴንም ሀዘኔንም በእርሱ ረሳለሁ ከፀሎቴ በኋላ ለናዲ ደወልኩለት አያነሳም ደጋግሜ ደወልኩ በቃ ፀሎት ላይ ይሆናል ብዬ ተኛሁ  ። በጠዋት ተነስቼ  ስልኬን ሳይጰበተራው እርሱም ደውሎልኝ ነበር እንደገመትኩትም ፀሎት ላይ ነበርኩ አለኝ በኋላ እንገናኝ ተባብለን ስልኩ ተዘጋ ነገ ስለምወጣ እቃዎቼን አስተካከልኩ   እቤቱንም በደንብ አስተካክዬ  ሱቅም አዲስ ዕቃዎች ሲገቡ በሚገባ አስተካክዬ በስራ አሳለፍኩ ና ከሰአት በኋላ የተለመደው ካፌ ናዲን አገኘሁት የሌለ ደብሮኛል እሱም እንደ ከፋው ፊቱ ያስታውቅበታል ከማውራት ይልቅ በዝምታ በየራሳችን ሀሳብ ተውጠን ለረጅም ደቂቃዎች ተፋጠን ተቀመጥን እፁ ግን ሳትሄጂ ከነ ማሚ ጋር ባስተዋውቃችሁ ደስ ይለኝ ነበር ግን ዘገየሁ በስራ ተጠምጄ ደግሞ ቀኑ እንዴት ይፈጥናል  አለኝ እሱ ምን ያሳስባል እመለስ የለ አልኩት ። ብዙ መከረኝ አፅናናኝ የጌታን ቃል ዘራብኝ ደግሞ ከራሱ እንደማያወራ ያስታውቃል በቃ በንግግሩ እንኳን መንፈስ ቅዱስ የሚጠቀምበት ሰው እና ምንም እንዳልደብቀው አስጠነቀቀኝ  ስለ ማሂ ልነግረው እልና ከእኔ በፊት የነበራቸውን መልካም ግንኙነት ከማበላሽ በውስጤ ለመያዝ ወሰንኩኝ እየመሸም ስለነበር በጊዜ መሄድ ስለነበረብኝ ቻው ልለው ተገደድኩ እርሱ ፊት ላለማልቀስ በጣም ጥረት አድርጌ ነበር ግን አልቻልኩም ፍርሃቴ ና ሀዘኔ ከጥንካሬዬ ሚዛን ደፍቶ ውስጤን ፈንቅሎ በእንባ ወጣ እሱም በጣም አዝኗል ግን እኔን ለማጠንከር ኮስተር ብሎ ተቆጣኝ የእኔና የእርሱ መጨረሻ ይሄ እንዳልሆነ ደግሞም በእግዚአብሔር እጅ እንደሆነ ነግሮ በታክሲ እስከ እቤት አደረሰኝ ና በቃ ቻው ብዬው ገባሁ ገና ስገባ ከሰላምታ በፊት እኩል ነገርሽው አሉኝ አዎ ልልም ፈለኩ አልነገርኩትም ልልም ፈለኩ በቃ ዝም ብዬ ወደ ጓዳ ገባሁ እንዲሁ ስነፋረቅ መሽቶልኝ እነ ማሚንም እያስደበርኳቸው ስለሆነ ራሴን ተቆጣጥሬ  አብሬያቸው እራት በላሁ ኮስተር ብዬ እነሱን ለማስረሳት እንዳልከፋኝ ማስመሰልን መረጥኩ ። ልክ በፊት ስሄድ እንደመከረችኝ አሁንም መከረችኝ  ፀለየችልኝ መረቀችኝ በቃ መመለሴ ግድ ሆነና በማለዳው ከልጆች ጋር ወደ ጊቢ ተመለስኩ  ። ለሳምንት ያክል ምግብ  አልበላ አለኝ የመጀመሪያ ግዜ እንኳን እንዲ አልሆንኩም ዝም ብሎ ይከፋኛል ግን ጌታን ሳወራው እፅናናለሁ በስልክ  አገኛቸዋለሁ ደግሞ የናዲ ልደት ነው ቢያንስ አጠገቡ ብኖር ደስ ይለኝ ነበር ። ጠዋትም እንኳን ተወለድክ ብዬው ነበር ከክላስ ስወጣ ደውሎልኝ ማሂ ሰርፕራይዝ እንዳደረገችው ና በጣም ደስ የሚል ቀን እንዳሳለፈ ነገረኝ  ነገረኝ ደስ አለኝም ከፋኝም.......... ............ይቀጥላል ........... @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 7840Loading...
19
.       🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘            #ክፍል_19 ......አኔ የምልህ ቅድም  ብሩክ ደውሎልኝ ነበረ ብዬ  ነገርኩት ምነው በቀረብኝ ስልኩን ካልሰጠሽኝ እኔ አወራዋለው ብሎ ጭቅጭቅ እንደምንም አረሳስቼው ስልኩ ተዘጋ ወደ ፀሎቴ ተመለስኩኝ ማሂ ከስራ ስትመለስ ጎራ ትላለች ብጠብቃት ብጠብቃት አልመጣችም ደወልኩላት ከስራ አምሽቼ ነው የወጣሁት ብላ ይቅርታ ጠየቀችኝ በቃ ነገ እንገናኝ አልኳት ። ዛሬም ከቤት ሳልወጣ አሳላፍኩ ማሂን ዛሬም ብጠብቃት አልመጣችም ስደውልላት ከክላስ አርፍጄ ስለወጣሁ ቤት መሄድ ነበረብኝ አለችኝ ቅዳሜ እና እሁድ ዊኬንድ ትማራለች ። ደግሞ ከናዲ ጋር ቸርች ደብዳቤ አስገብተናል ማሂ ምክኒያት እየደረደረች ሳላገኛት ሳምንት አለፈኝ ። ናዲን አግኝቼው በወሬ መሀል ምሳ አብረው እንደበሉ ሲነግረኝ እንዴ እኔ ካገኘኋት ሳምንት አለፈ እኮ አልኩት እንዴ ቸርችስ አለኝ ሳላናግራት ቶሎ ትወጣለች አልኩት እንዴ ምን ሆና ነው ከስራ ስገባ እኮ ሁሌ አብረን ነው ምንገባው አለኝ በጣም ደነገጥኩ ምን አስቀይሜአት ቢሆን ነው ስልኬን አታነሳም ቴክስትም ምን አልባት ከስንት አንዴ ነው ምትመልስልኝ ውስጤ ሰላም አጣ ምን ተናግሬያለሁ ብዬ ለመጨረሻ ግዜ የተገናኘንበትን ቀን ለማስታወስ ሞከርኩ እሱ ስልክ መደወል ጀመረ በሀሳብ ስንት ቀናትን ተጓዝኩ ግን ምንም ትዝ የሚለኝ ነገር የለም ። እንዴ እፁ እእ ምን አልከኝ ብዬ ከሄድኩበት ተመለስኩ እንዴ ምን እያሰብሽ ነው አለኝ ምን አስባለው ማሂ ገርማኝ ነው እንጂ አልኩት እየመጣች ነው አለኝ ነው ጥሩ ነዋ እንደውም ጠይቃታለው አልኩኝ ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ስትመጣ አየኋት ተያየን እርምጃዋን ገታ አደረገች እንዴ ስል ናዲም ከእኔ አይኖች ጋር ወደ እርሷ ዞረ ስትራመድ የነበረችው እያዘገመች መጣችና ተቀመጠች ሰላምም አንባልም እንዴ ዛሬ ደግሞ አላት ስለደከመኝ ነው እንዴት ናችሁ አለች እኔ ከፊቷ ጀምሮ መቀያየሯ ገርሞኝ ዝምታን መረጥኩ ። ለደቂቃዎች ብቻቸውን ያወራሉ እፁ ምንድነው ዝም አልሽ አለኝ ኸረ ምንም አልኩ እምባ እየተናነቀኝ እሷ ምንም እንዳልተፈጠረ ኸረ በጭራሽ እንደማንተዋወቅ ነው የምትሆነው ። የሁለታችንንም ፊት በየተራ እያየ ምንድነው የሆናችሁት የማላውቀው ችግር አለ አለን እሷን ጠይቃት አልኩት ማሂ ምንድነው አላት እኔ ከስራ ስገባ ስለሚመሽ ቶሎ ስለምገባ እና አሳይመንት ምናምን ስለበዛብኝ ግዜ የለኝም ደግሞ ሁሉ እንዳለ አይቀጥልም እኮ አለች ንግግሯ እንኳን ለእኔ ለናዲ አልዋጥ እንዳለው ፊቱ ያስታውቃል ። ከሆነ መልካም አላት አሁን ራሱ መሄድ አለብኝ አባቢ ስራ ቦታ መጥቶ ካጣኝ ይናደዳል ብላ ተነስታ ሄደች ሳላውቀው እንባዬ ዝርግፍ አለ ። ናዲ ተደናግጦ እንዴ ምን ሆነሻል አለኝ አውቃለው ክፉ እንደሆንኩ መልካም ባህሪ እንደሌለኝ ግን ድክመቴን ብትነግረኝ ምን አለበት በባዶ ሜዳ እንዲ ከምትቀየርብኝ አልኩት ። አንቺ እንደሱ አይደለሽም መልካም የዋህ ነሽ እንጂ የራሷ ምክኒያት ይኖራት ይሆናል ደግሞ ሰውን ማስገደደድ አትችዪም የራሷ ህይወት ይኖራታል እግዚአብሔር መልካም ነው አይደለም ሌላው ወላጅ እንኳን የሆነ ሰአት ይቀየራል ማሂ ደግሞ ጥሩ ሴት ናት ሳታውቂ አሳዝነሻት ይሆናል እኔ በእርጋታ እጠይቃታለሁ አለኝ በማልቀሴ እንደተረበሸ ሁኔታው ንግግሩ ያስታውቃል ዋጥ አድርጌው ራሴን አረጋግቼ ወደ እቤት ተመለስኩ ከናዲ ጋር ከተለያየን ጀምሮ ማልቀስ ማቆም አልቻልኩም እንደዚ እንደምወዳት አላውቅም ነበር ። እየተነፋረኩ ተዐምር አይታኝ ለማሚ ነገረቻት ለሁለት ሲጨቀጭቁኝ ልነግራቸው አልነበረም ነገርኳቸው ተዐምር በለው ከማሂ ጋ ተጣልታ እንዲ ከሆነች ከናኦድ ጋር ሲሆን ማሚ ከቤት ልንባረር ሁሉ እንችላለን አለች ንግግሯ ፈገግ አደረገኝ ሚሚ ተቆጣቻት ብዙ መከረችኝ ስለ በፊት ጓደኞቿ ብዙ ብዙ አውርታኝ በይ እረፊ ካልሆነም እኔ አወራታለሁ ብላኝ በህብረት ወደ ፀሎት ገባን እግዚአብሔር መልካም ግዜ ሰጠን ያኔ ልጅ እያለሁ ተዐምርም ህፃን ሆና ነበር እንዲ ምንፀልየው ። የብሩክ መደወልና ካላነሳሽ እቤት መጣለሁ የሚለው ዛቻ እንደቀጠለ ነው ። የማሂን ጉዳይ ምንም ሳይቀየር ከረምኩ ጊቢ የምመለስበት ቀንም ደርሷል ከነማሚ ጋር ከናዲጋም ጥሩ ግዜ እያሳለፍኩ ነው ደግሞ ያለ እነሱ ኑሮ ልጀምር ነው ከአሁኑ ያሳስበኝ ጀመር ። ክፍት ብሎኝ ቸርች ለመሄድ ተነሳሁ በቀስታ እያዘገምኩ  እየሄድኩ ከእሩቁ ማሂን አየኋት አስፓልቱን ተሻግሬ ላናግራት ግራ ቀኝ ማየት ስጀምር ከሰው ጋር ናት መሠለኝ መኪና ውስጥ ገባች ልቤ ለሁለት ተከፈለ ያየሁትን እንዴት ልመን ....... .........ይቀጥላል....... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 8510Loading...
20
.       🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘            #ክፍል_18 ........ወደ ተለመደው ካፌ ሄድኩ ሁለቱም ተቀምጠዋል እየተፍለቀለኩ ሰላም አልኳቸው እና ተቀመጥኩ ማሂ የሁለታችንንም ፊት አፈራርቃ እያየች ምንድነው ምትደሳሰቱት ሁለታችሁም ፊታችሁ ፈክቷል አለችን ይብሱን ሳቄ መጣ ና ሳኩ ምንድነው የሆነ ነገርማ አለ ዛሬም ሰርፕራይዝ አለኝ እንዴ አለች ዝም ብላ እያየችኝ አንቺ አታፍጪ እሱ ይንገርሽ አልኳት እንዴ ምኑን በል ንገረኝ ብላ አይኖቿ መልስን እየጠበቁ ቀልቧን ወደ እርሱ አደረገች እሺ ማሂቲ  የእኔ ምርጥ ጓደኛ የኔ ልባም የኔ መልካም ሴት ምን መሠለሽ አላት በል በል ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ልታወራ እንዳይሆን ወደ ገደለው አለችው ከት ብዬ ሳኩ ያኔ እኔ ነበር እንደዛ የምላት ያውራ ምን አለበት ስለ ጌታ ያልተወራ ስለማን ሊወራ አልኳት አታሽቃብጪ ወደዛ እኔ ነበርኩ ያኔ ከዘፍጥረት-ራዕይ አወራ ያልኩት ወሬ ትታችሁ አትናገሩም አለች አንቺ ነሻ ያቋረጥሽኝ ያኔ ክታፅናኚኝ ተስፋ ስትሰጪኝ ስታበረታችኝ የነበረው እና እግዚአብሔር ቃል የገባልኝ ጉዳይ ሊፈፀም ነው አላት ማለት አለችው ። እፁዬ የአመታት ጥያቄዬን ተቀበለቸኝ እያልኩሽ ነው አላት ምን .. ተነሳች ተቀመጠች ...እንዴት ማለት መቼ አለች ቀልዴን መስሎሽ ነዋ ካላመንሽኝ እሷን ጠይቂያት አላት አይ ጥሩ ነው እንኳን ደስ አለህ ማለት እንኳን ደስ አላችሁ አለችን ማሂ ደስ አላላትም እንዴ አልኩኝ በውስጤ አይ የምጎዳው መስሏት አዝናለት ነው የሚሆነው እንደተለወጥኩ በተግባር አሳያታለሁ እሷ ባትመክረኝ እንደዚህ አልቀርበውም ነበር ማሂዬ አሁን ተቀይሬያለው ናዲን ትጎዳዋለች ብለሽ እንዳታስቢ ለውጤን ደግሞ በተግባር ነው የማሳይሽ አልኳት ሁለታችንንም አቀፈችን ትንሽ ተጨዋውተን እሱ ስራ መግባት ስለነበረበት ትቶን ሄደ አኛም ብዙ አልቆየንም የተፈጠረውን ተረኩላት ደስታዋን ገልፃኝ መክራኝ ተለያየን ። እቤት ሄድኩኝ ና እነ ማሚ ሱቅ ስለነበሩ እቤቱን በሙሉ አፅድቼ የሚገርም ምግብ ሰርቼ ቡና እያፈላሁ በበቀደሙ ስል ተደወለ አላነሳሁም ተደጋግሞ ተደወለ አላነሳሁም በቴክስት እፁብ ስልኬን አንሺ ካልሆነ እቤት ድረስ እመጣለሁ ይላል ንቄ ተውኩት ደግሞ በየ አጋጣሚው ደግሞ ከጌታ ጋር ማሳለፍን እየለማመድኩ ነው መፅሀፍ ቅዱስ አነባለሁ እፀልያለው ድሮ ሲቸግረኝና ሲጨንቀኝ ነበረ ምፀልየው ለካ ከእርሱ ጋር ማሳለፍ የነብስ ምግብ ነው ዝም ብሎ ደስ ይለኛል በመስቀል ላይ የተሰራልኝን ስራ ትኩረት ሰጥቼ ባሰላሰልኩት ቁጥር የደስታና የፍቅር እንባ ይሞላኛል ደግሞ ለጌታ ያልተነባ ለማን ሊነባ  ደስ የሚል ቀን አሳለፍኩ ናዲ ደውሎልኝ ረጅም ሰአት አወራሁት እፁ ለቤተክርስቲያን ማሳወቅ አለብን አለኝ ምኑን አልኩት የአሁን እጮኛዬ የወደ ፊት የትዳር አጋሬ መሆንሽን ነዋ አለኝ አንተ ልጅ ምን አስቸኮለህ አሁን አልኩት እንጠናና ልትይኝ ባልሆነ ስንት ግዜ አጠናሁሽ አደል እንዴ ለክፉም ለደጉም ቤተ ክርስቲያን ማወቅ አለባት የድብብቆሽ ታሪክ ለአገልግሎታችንም ለ ምንም ጥሩ አይሆንም አለኝ እሺ ካልክ ቆይ አብራችሁ ከሆናችሁ ስንት ግዜ ሆናችሁ ቢሉህስ አልኩት ምን እውነት እውነቷን ያደረግሽኝን ሁሉ አንድ በአንድ ነው ምተርክላቸው አለኝ ሳኩና ይሁንልህ እሺ እኔ የምልህ ቅድም...... ......ይቀጥላል ...... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 9720Loading...
21
.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘          #ክፍል_17 .......አላስጨረስኩትም ኸረ በጭራሽ ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ሲያየኝ ማለት እንደዚ ከቀለደብኝ ሰው ጋር የኔ ልብ ምን ይሰራል ። እነዚያ ግዜያት ታውሰውኝ ነው እንጂ ምንም አስቤ አይደለም የደበረኝ ሰዓቱ እኮ ሄዷል ለምን ወደ ቸርች አንሄድም አልኩት ምን እንደሚያርበተብተኝ ባይገባኝም ማወራውም ማስበውም ግራ የሆነ ነገር ነው ። እሺ ጥያቄዬስ ይኸው ለረጅም ግዜያት መልስሽን እየጠበኩ እፁብ አላሳዝንሽም አለኝ ወይኔ እንባ ተናነቀኝ ምንም ምናገርበት አቅም አጣሁ ፍርሃት ደስታ ስጋት አንደበቴን ቆላለፉት ለረጅም ደቂቃ ዝም አልኩና ራሴን ማዳመጥ ፈለኩ ውስጤ አንቺ ምን አይነት ሰው ነሽ ፀልየሽ አለቃቅሰሽ አሁንም የፀሎትሽን መልስ ልትገፊው ነው ምንም አትግደርደሪ  ይለኛል አንዴ ደግሞ ኸረ ሴት ልጅ እኮ ነሽ ወዲያው ስትነግሪው ይንቅሻል አንዴ ደግሞ ይሄ ሁሉ ጊዜ ጠበቀሽ ቢያንስ ጌታን ፍሪ ልክ ሰው እንደሚናገረኝ ከራሴ ሀሳብ ጋር ክርክር ገባሁ በመጨረሻም የመጨረሻ ቆርጦ ሀሳቡን የቀየረ ቀን እሮሮ ከማበዛ እነግረዋለው በሚለው ወሰንኩ ና በረጅሙ ተነፈስኩ እፁብ የዚህን ያክል የሚያስጨንቅሽ አልመሰለኝም ነበር ተይው በቃ ወደ ቸርች እንሂድ አትጨናነቂ አለኝ አንጀት በሚበላ ድምፅ ለመሄድ ከተቀመጠበት ሲነሳ ናኦድ አልኩት ግራ በመጋባት አይነት አስተያየት አየኝ ተቀመጥ አልኩት ትንፋሼን እየሰበሰብኩ ያነሳውን ስልክ መልሶ አስቀመጠና ተቀመጠ እውነት እነዚያ ግዜያት  ቀጥተውኛል እንደ አንተ አይነት ጌታን የሚፈራ፣ መልካም ፣ትሁት ፣ቅን ከዚህም በላይ የሆነ ሰው ማግኘት ዕድል ብቻ አይደለም እግዚአብሔር ለወደደው የሚሰጠው ስጦታ እንጂ የሴትነት ወጉ ይዞኝ እንጂ ጊቢ ባሳለፍኩአቸው ወራቶች ከዚያም በፊት ሁሉ ድጋሚ ጥያቄውን እንድታነሳልኝ ስሻውም ስፀልይበትም ነበር አሁን የፀሎቴ መልስ ነህ ማለት ነው አልኩት እያየሁት የፊቱ ፈገግታና ወገግታ ጨመረ እፁ እየቀለድሽ አይደለማ አለኝ ሁኔታው ፈገግ ያሰኛል ኸረ አንተ ልጅ ራስህን ግዛ እየሳኩ ። ከተቀመጠበት ተነስቶ አቀፈኝ የተቀመጥንበት ካፌ የሰዉ ብዛት አንተ ትኩረት እየሳብክ ነው ብዬ አረጋጋውት ደስታ ፊት ቢኖረው በእርሱ ይገለፅ ነበር ከአንቺ ጋ ገና ብዙ ማወራው ነገር አለ በይ ተነሽ ጌታዬን ላመስግንበት ወደ ቸርቻችን አለኝ ሲገረም ሲለፈልፍ ሲቀባጥር በሁኔታዎቹ ፈገግ እያልኩ ቸርች ደረስን እግዚአብሔር ድንቅ ና መልካም ጊዜ ሰጥቶን በቃሉ መክሮን በዝማሬ አረስርሶን እንደለመድነው ማሂ እና ሌሎች የቸርቻችን ልጆች ተሰባስበን ወደ ቤት ገባን ። ደስ ስላለኝ የሆነ ማወራለት ሰው ፈለኩ ደግሞ ከእናቴ ምደብቃት ነገር ስለሌለ ከጅምሩ አንስቼ እስከ ፍፃሜው ተረኩላት እና በጣም ተደሰተች የኔ ልጅ አሁን ገና መልካም ሰው ገጠመሽ አልዋሽሽም በቁም ነገር ልጄ ከዚህ ሰው ውጪ ሌላ ሰው ላይ እንዳትወድቅ ብዬ ጌታን ለምኜው ነበር ፀሎቴን ለሰማ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁንለት ብላ እልል አለች ። ተዐምርም ማሚ ድሮም እኔ ጠርጥሬ ነበር እኮ አለቻት አንቺ ልጅ ኸረ እባክሽ ቀስ ብለሽ እደጊ ማሚ አቺን ልጅ አንድ በያት እንጂ አልኳት ተይ የኔ ልጅ እሷ ለአንቺ ብላ እንጂ የኔ ልጅ ስርዐት አልባ ሆና አይደለም አለችኝ ና ተሳሳቁ ተጋገዛቹ ማለት ነው አልኳቸው አዎና ለአንቺ ናኦድ አለልሽ እኛ እርስ በእርስ ብንተጋገዝ አይሻለንም አለችኝ ፈገግ አልኩና ። ወደ ጓዳ ገብቼ ፀልዬ መፅሀፍ ቅዱስ አንብቤ ስነሳ ናኦድ ደወለልኝ ረጅም ሰአት ተወራሁት እና ተኛሁ ። የፍሬሽ ነገር ልክ ለዐመታት አይቼው እንደማላውቅ ሲነጋ እስካገኘው ጓጓሁ ለማሂ እንነግራታለን ብሎኝ ስራ ከመግባቱ በፊት ማሂን ልናገኛት ወደ ተለመደው ካፌ ሄድኩ... .......ይቀጥላል ...... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 8170Loading...
22
.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘          #ክፍል_16 .......ደንዝዤ ቀረሁ የዚያን ቀን ያዘንኩት ሀዘን የተሸማቀኩት ስሜት  የተዋረድኩት ውርደት ታወሰኝ ደግሞ ምን ሊሆን መጣ በሀሳቤ የኋላ ታሪኬን በሙሉ ቃኘሁት እንባዬ እየወረደ ነው ተዐምርም ናኦድም ተደናግጠው ከተቀመጡበት ተነስተው ተጠጉኝ ምነው እፁ ማነው የደወለው ? ምን ሆነሽ ነውበየተራ በጥያቄ ያጣድፉኝ ጀመር በተለይ ማሚ ይህንን መስማት እንደሌለባት አውቃለሁ ተዐምር ሰማች ማለት ደግሞ እናቴ ጋር መድረሱ አይቀሬ ነው የሆዴን በሆዴ እንደያዝኩ በዝምታ ተዋጥኩ የዚህኔ ለጥያቄው መልስ አልሰጥ ባይነቴ ያሰለቸው ናኦድ ስልኬን ተቀብሎኝ መደወል ጀመረ ። ሄሎ በዚህ ስልክ ተደውሎ ነበር አለ ቀጥሎም አዎ የእርሷ ነው ስልኩ ግን አንተ ማነህ አለው የብሩክን ምላሽ ባልሰማም የሆነ ነገር ግን ብሎታል ስልኩን ዘጋው ና እርሱም እንደ እኔው ቁጭ አለ እእእእእ ምንድነው አለች ተዐምር በተራው ወደ እርሱ እያፈጠጠች ዝም አላት እናንተ ሰዎች ደዋዩ አንደበት የሚቆልፍ ነው እንዴ ምን እየተካሄደ ነው ብላ ስትሄድ ተዐምር አልኳት እእእ ብላ ዞረች ዝም ብዬ አየኋት ምንድነው የሆንሽው እፁብ ነው እማዬን ልጥራት አለች እንዳትነግሪያት አልኳት ለምን አለችኝ በቃ አይመለከትሽም ምንም ነገር ብትነግሪያን የእውነት እንጣላለን አንቺ ህፃን አይደለሽም አልኳት ። አሁን ልጅ ነሽ ምናምን ስትይ አልነበር እንዴ የምን መገለባበጥ ነው ሲጀመር ምኑን ነው ምነግራት ስልክ ተደውሎላት ልሳኗ ተዘጋ ከዚያ ናኦድም በዚያ ስልክ ደውሎ ተለጎመ ይህን ነው ምነግራት ሆሆሆሆ እያለች ወጣች ሁኔታዋ ፈገግ አደረገኝ  ናኦድ አቀርቅሮ ምን እንደሚያስብ ባላውቅም በዝምታ ተውጠናል ። አንድም ሳናወራ በየመሀሉ ገዢ ሲመጣ እያስተናገድኩ ለሰአት ተቀመጥን ። ዝምታውን ለመስበር መሠለኝ እኔ የምለው ለምን ደነገጥሽ አለኝ በረጅሙ ተነፈስኩ ለምን አልደነግጥም እነዚያን ግዜያቶች ማስታወስ አልፈልግም ነበር ደግሞ ምክኒያቴን ላስረዳሽ ላግኝሽ ምናምን ይላል እንዴ ደፍረቱ አንተ ግን ለምን ደነገጥክ አልኩት ምላሽ አልሰጠኝም ዝም አለና ግን በቂ ምክኒያት ካለው ተቀብለሽው አብረሽው ትሆኛለሽ አለኝ እየቀለድክ ነው አልኩት በዚህ ይቀለዳል አለኝ ኸረ ጭራሽ እንዳታስበው አልኩት ማሚና ተዐምር መጡ እናንተ አስሬያቹ ጠፋው አይደል ይቅርታ ናኦድ ልጄ በሉ ተዐምር ቡና ታፍላላችሁ እቤት  ግቡ አለችን ኸረ ማሚ ያው አይደል እንዴ ውጪ ማኪያቶ እንጠጣለን በዚያውም ወደ ቸርች ስለምናልፍ አልኳት እሺ ይሁን ታዲያ በግዜ ተመለሺ የኔ ልጅ አለችኝ ወጣን ። እኔም በራሴ ሀሳብ እርሱም በራሱ ሀሳብ ተውጠን ፊት ለፊቱ ያለውን የማኪያቶ ብርጭቆ ያለማቋረጥ ያማስለዋል ኸረ አንተ ልጅ ልትቀደው ነው እንዴ ብዬ ፈገግ አልኩ  ቆይ ምን እየሆንክ ነው እኔ ራሱ እንደ አንተ አልተጨነኩም ነው ሌላ ምክኒያት አለህ ከእኔ ጉዳይ ውጪ አልኩት ምን ይኖረኛል አለኝ እና ተረጋጋ በቃ እኔን ለማስረሳት እንደ መሞከር ይባስ ታስጨንቀኛለህ እንዴ አልኩት ዕፁ ሰለቸኛ አለኝ ምኑ አልኩት ባንቺ ምክኒያት የሚፈራረቁብኝ ህመሞች እነዚያን የምትጠይኝን ግዜያቶች በስንት መከራ አልፈው አሁን ደግሞ ያውም ልታገቢው የነበረ እጮኛሽ ሲመጣ ደነገጥኩም ደስ አለኝም ግራ ገባኝም የሆነ በአንድ ግዜ የተደበላለቀ ስሜት ተሰማኝ  እንዴ ሀሳብህን የቀየርክ መስሎኝ አልኩት ። ለምን እቀይራለው እግዚአብሔር እንደማይዋሽ እኮ አይደለም እኔ ልጁ አጋንንት እንኳን ያውቃሉ ጊዜው ይርዘምም ፈተናው ይብዛም ያለኝ ነገር እንደሚፈፀም አንዳች ታክል አልጠራጠርም ምን አልባት አሁንም ልብሽ እዛ ይሆናል አላስጨረስኩትም ኸረ በጭራሽ አልኩ........ ...........ይቀጥላል........... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 9410Loading...
23
.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘            #ክፍል_15 .....እንቅልፍ ከየት ይምጣ ስገላበጥ አድሬ በጠዋት ከማሚ ጋር ቁርስ ሰርተን አብረን በላን ቤተሰቦቼ አንዳች ሳይሆኑ የጠበቀልኝን ጌታ እያመሠገንኩ እንደዛ የጓጓሁለትንም ቀጠሮ አስረስተውኝ ከማታ የቀጠለ ወሬ እየተወራ ናኦድ ደወለልኝ ወይኔ ማሚ ምን አይነት ሰው ነኝ ብዬ ስደናገጥ ምነው አሉኝ ሁለቱም በቶሎ ልብስ ቀያይሬ ወጣሁ ። የተቀጣጠርንበት ካፌ ስደርስ ተቀምጧል አሁንም በሰአት ጉዳይ አይደራደርም ማለት ነው እያልኩ በውስጤ አጠገቡ ደረስኩ ። ሰላምታ ተለዋወጥን አረፍ አልኩ የሆነ ነገር ውሰጂ አለኝ ኸረ ከቤት አይደል የምመጣው ብዬ እምቢ አልኩ የግድ ሲለኝ ወተት አዘዝኩ አቤት ጉዳዩን ለመስማት ካለኝ ጉጉት የተነሳ የሚያወራቸው ወሬዎችና ጥያቄዎቹ ትርጉም አልባ ሆኑብኝ ከረጅም ደቂቃዎች ወሬ  በኋላ እና እፁብዬ ወደ ዋናው ጉዳዬ ስመጣ እእእ በነገርሽ ላይ ማሂ በጣም ትለያለች ትህትናዋ መንፈሳዊነቷ ብስለቷ ምን ልበላት በአጠቃላይ ልባም ሴት ብትባል አይበዛባትም ሙሉ አካሌ ሲዝለፈለፍ ይታወቀኛል ተመሳስጦ ማውራት አልጀመረም እንዴ ናኦድ ምን ሆነሀል ስለ ጓደኛዬ ባህሪ እንደ አዲስ ልትነግረኝ  ነው አልኩት ኦው ይቅርታ እና ምን ልልሽ ነው ሰርፕራይዝ ላደርጋት አሰብኩና አንቺ ታስፈልጊኛለሽ አለኝ የሆነ ነገር እንደ መታው ሰው አናቴ የተከፈለ እስኪመስለኝ ደነገጥኩ ጌታ ሆይ ውሰደኝ አልኩ በእኔ ቤት በውስጤ ነው ግን ሳላውቅ አውጥቼዋለሁ ለካ እንዴ ወዴት ብሎ ፈገግ አለ መልሼ በሆዴ ወደ ራሱ ነዋ ምን ቀረኝ አልኩ ቀለበት ሊያስርላት ሆኖ ብቻ ጨርቄን ሊያስጥለኝ ባልሆነ እያልኩ ክፍት አለኝ ቆይ እንዴት ሳትነግሩኝ ግን አልኩት ። እንዴ እስከ አሁን እንዴት አታውቂም አለኝ ካልነገረችኝ በምን አውቅልሃለሁ አልኩት ዕንባ እየተናነቀኝ እናንተን ብሎ ጓደኛሞች ያውም ሁለታችሁም ሴቶች ሆናችሁ አለኝ ማሂ ግን እንዴት ደበቀችኝ ብዬ ገረመኝ ለነገሩ ቀና ቀናውን ባስብስ ትምህርት ላይ ሆኜ እንደዚህ አይነት ወሬ ምን ያደርግላታል ብላ ይሆናላ አልኩት እንዴ እንደዚህ አይነት ወሬ ስትዪ ማለት በዚህ በጥቂት ግዜ ፍቅር ጀመርን ማለት ከብዷት ይሆናላ  አልኩት ። ምን ብሎ ሳቀ ምን አለብህ ሳቅ የኔን የውስጥ ለቅሶ ባየህልኝ አልኩ በሆዴ ማውራት እስኪያቅተው ይስቃል አንተ ልጅ ጤነኛ አይደለህም እንዴ ምንድነው የሚያስቅህ ዞር ዞር እያልኩ ከኋላ ከጎን የተቀመጡ ሰዎችን  እየቃኘሁ አንቺን ልጠይቅሽ እንጂ የምን ፍቅር ነው ምታወሪው አለኝ ሳቁን እንደ ቀጠለ እና ሰርፕራይዝ ልባም ሴት ምናምን ያልከኝ እራስህ አይደለህ እንዴ ይብሱን ይስቅ ጀመር አንቺ ልጅ ይሄ የዋህነትሽ እኮ ነው የሚገርመኝ ገና ተናግሬ ሳልጨርስ ከእህቴ ጋር አፋቅረሽኝ አረፍሽው ምንም አልልም ጌታ ይቅር ይበልሽ እፎይ አልኩ በአንዴ ፊቴ ወደ ደስታ ሲቀየር እየታወቀኝ ባክሽ ዛሬ ልደቷ ነው እሱን ነበር አታውቂም ያልኩሽ አለኝ ወይኔ እኔ ምን አይነተሰ ሰው ነኝ ጌታን ረስቼዋለሁ አልኩት እና አሁን ደውይላት አለኝ ። ደውዬ አወራኋት እና እቤት የሚገርም ዝግጅት አድርገን ማሚ አሞኛል ብላ እንድትጠራት አደረግን በጣም ነበር ደስ ያላት የገዛንላትን ስጦታ ሰጥተናት ደስ የሚል ግዜ አሳለፍን አባቷ ደውሎላት እሷ ሄደች ማሚን እረፊ ብለናት ልጀንም ስራ አስፈትቼ ሱቅ ቁጭ አልን ። ቅድም የቀባጠርኩት ትዝ እያለው ይስቃል ከዚያ ለተዐምር ነገራት እና ሳቁብኝ  ሂድ እዛ ጥርሳቹ ይርገፍ የእውነት ግን ከፍቶኝ ነበር አልኩት እና ደነገጥኩ እንዴ ለምን አለኝ ምለው ጠፍቶኝ እንትን ስላልነገራቹኝ ነዋ አልኩት ተዐምር ኸረ እፁ አትዋሺ ቀንተሽ ነው አለችኝ ሂጂ አንቺ ልጅ አይደለሽ እንዴ አይጥ አልኳት እያጉረመረመች ዝም አለች ተያት ታውራበት የአሁን ልጆች እኮ ሲፈጠሩም በስለው ነው አለኝ እሺ አባባ ያኔ በኛ ግዜ እያልክስ ምትነግረኝ ነገር የለም አልኩት እንዴ ንቀሽኛል ቆይ ከተመረኩ እንኳን ቆየው እኮ ምን ቀረኝ አለኝ  እቺ ምላሰኛ ልጅ ምንም ሚስት ነው የቀረህ  እኔ ነኝ ያልኩህ ናኦድ ቶሎ በልና አግባ ግዜ እኮ ቆሞ አይጠብቅም አለችው ደንግጬ ኸረ ባክሽ ባክሽ ተዐምር ጓደኛሽ አደረግሽው እንዴ ብዬ አፈጠጥኩባተ የእቺ ጓደኛ ማለት የኔ ጓደኛ ማለት አይደል እንዴ ነው አግባ ስላልኩትም ቀንተሽ ነው አለችኝ ። ወይኔ ጨጓራዬን ገለበጠችው ብነክሳት ሁሉ ደስ ይለኝ ነበር ። ወዲያው የባለፈው ስልክ ተደወለልኝ አንስቼ ሄሎ አልኩኝ ሄሎ እፁብ ደህና ነሽ ደህና ነኝ አልኩ ፊቴ ጭምድድ አንዳለ ታናግሪኛለሽ ብሩክ ነኝ አለኝ  ልቤ ተሰነጠቀ ዝም አልኩ አንቺን ለማግኘት ኢትዮጵያዊ መጥቻለው እባክሽ አንዴ ላግኝሽ እና የገጠመኝን ላስረዳሽ አለኝ ስልኩን ዘግቼው ደንዝዤ ቀረው......... ............ይቀጥላል ........ @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 8010Loading...
24
.       🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘         #ክፍል_14 ..............ወደ ጊቢ የምመለስበት ቀን ደረሰ በጣም እየከፋኝ ነው እዚህ እነሱን  ለምጄ  በተለይ የናኦድ ጥቅም አሁን አሁን እየገባኝ ነው እየከበደኝም ቢሆን ወደ ግቢ ሄድኩ እነ ማሚ  እየናፈቁኝ ነው በጣም ማሂና ናኦድም ይደውሉልኛል እናቴ እንዴት አድርጋ እንዳስተማረችኝ ስለማውቅ ወጥሬ አነባለሁ እፀልያለሁ ፌሎ ህብረት አደርጋለሁ በቃ እግዚአብሔርም ሊቀርፀኝ ስለፈለገ በብዙ ሁኔታዎች እያለፍኩ ነው ። ዛሬ ፈተና ላይ ነን አንቺ እፁብ እፁብ አንቺን እኮ ነው ከፊት ለፊቴ አተኩሮ እያየኝ ያለው መምህር ፊቱ በቁጣ ቀልቷል የያዘውን ቀይ ብዕር እያገላበጠ አፍጦብኛል ከኋላ ጥሪው እየጨመረ ነው ጭራሽ ይጎትቱኝ ጀመረ አስተማሪው እንዳፈጠጠብኝ ነው  ራሴን ማዳን ስለነበረብኝ ቶሎ ቶሎ ሰርቼ ወጣሁ ። እየጠሩኝ የነበሩት እነማን እንደሆኑ እንኳን አላወኩም ። ሀገር ሰላም ብዬ እየጠሬጠርኩ ስለ ሰራኋቸው ጥያቄዎች እያሰብኩ ከኋላዬ መዶሻ የመታኝ ይመስል ትከሻዬ ላይ እጅ አረፈ ተደናግጬ ዞር አልኩ አንቺ ማን ስለሆንሽ ነው መልስ የከለከልሽኝ ብሎ አፈጠጠብኝ ። እኛ ክላስ መሆኑን እንኳን አስተውዬው የማላውቀው ፊት ይቅርታ እንተዋወቃለን አልኩት ። እውነትም አታውቂኝም ማለት ነው በደንብ እንተዋወቃለን ብሎ እጄን ጨመቀኝ ሰውዬ ያምሀል እንዴ አልኩት ሰማሽኝ አሁን ላጣሁት ፈተና እና ለዚህ ትቢትሽ ዋጋ ትከፍያለሽ ብሎኝ ሄደ ። ከቁም ነገርም አልቆጠርኩትም ዝም ብዬ መንገዴን ተጓዝኩ ሻይ ጠጥቼ ትንሽ አረፍኩና ወደ ላይብረሪ ተመለስኩ አንብቤ ስጨርስ እነ ተዐምር ስለ ናፈቁኝ ዶርም ተመልሼ ደወልኩላቸው በየተራ ሲያወሩኝ ሲያስቁኝ ሲያዝናኑኝ ቆይተን ተሰነባበትን ሱቁን በታታሪነት እየሰሩ ነው አንድም ነገር ሳይጎልብኝ እያስተማሩኝ ነው እኔም ማድረግ ያለብኝን ሁሉ በአግባቡ እከውናለው ማጥናት ባለብኝ ሰአት አላርፍም ማረፍ ባለብኝ ሰአት አላጠናም መፀለይ ባለብኝ ሰአት ሌላ ነገር አልከውንም እግዚአብሔር ብቻውን እየረዳኝ ነው የበቀደሙ ልጅ በየመንገዱ እየተከተለ ነገር ይፈልገኛል አሁንማ ከጓደኞቹ ጋር ተሰብስበው መንገድ ይከለክሉኛል አንዳንዴ እናደድና አንዳንዴም ከቁም ነገር አልቆጥራቸውም  የእነሱንም ዛቻና ፌዝ የትምህርቱንም ክበደት እንደምንም ጌታ አሳልፎኝ ከወራት በኋላ ወደ ቤት ተመለስኩ ከውጪ ሀገር  እንደሚመጣ ሰው በሚገርም አቀባበል ሰብሰብ ብለው ነበር የጠበቁኝ ማሂም ናኦድም ቤት ነበሩ በጣም ደስ አለኝ ያሳለፍኩትን ስነግራቸው ስንጨዋወት ቆይተን እነ ማሂ ወደ ቤት ሊሄዱ ልንሸኛቸው ስንወጣ ማሚና ማሂ ተመስጠው ሲያወሩ ናኦድ በሹክሹክታ ተሰናብተውን ሄዱ ነገ በጠዋት እንደሚፈልገኝ ነገረኝ ማሚና ተዐምር ሶለናፈቁኝ ረጅም ሰአት ስናወራ ስንስቅ አመሸን ።  እነሱ ሲተኙ ምን ሊነግረኝ ይሁን በሚል ጉጉት እንቅልፍ ከየት ይምጣ..... .........ይቀጥላል ......... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
1 9770Loading...
25
.        🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘 ✍ፀሀፊት አክሳን አዳነ           #ክፍል_13 ..........በማሚ ስልክ ደወልኩለት ሁለቴ እንደጠራ ሄሎ ማዘር አለኝ ማሚ አይደለሁም እፁብ ነኝ አልኩት ወዲያው ስልኩን ይዘጋዋል ብዬ ነበር የጠበኩት እሱ ግን ዝምታን መረጠ ። ይኸውልህ ናኦድ ስልኬን አላነሳ ስላልከኝ ነው በማሚ የደወልኩት ብዬ ሳልቸርስ ችግር ገጥሞሽ ነው እሺ ምን ልርዳሽ አለኝ ። ጌታ ሆይ በጣም ደነገጥኩ በተዘዋዋሪ ለችግርሽ ነው ምትፈልጊኝ መሆኑ ገባኝና አዎን ትልቅ ችግር ገጠመኝ እና ላገኝህ ፈልጌ ነበር አልኩት ። በረጅሙ ተነፈሰና እሺ አለኝ የእውነት ይብሱን በራሴ እንዳፍር አደረገኝ ጭራሽ መልሼ ለችግሬ ፈለኩህ እያልኩት ምን አይነት ልብ ነው ያለው አልኩኝ በሆዴ እና ነገ ሱቅ ትመጣለህ አልኩት ጭራሽ ለጉዳዩ ፈልጎኝ ሚመጣ አስመሰልኩት  እሺ አለኝ እሺ በጣም አመሠግናለሁ አልኩት ና ስልኩ ተዘጋ ። በቃ ሰላሜን ነሳኝ አንዴ ያደረኩትን እያስታወስኩ አለቅሳለሁ አንዴ ደግሞ ስላለው ልብ እየተገረምኩ ጌታን አመሠግናለሁ አንዴ ድርጊቶቹ እየታወሱኝ እስቃለሁ ስጮህበት እንኳን በመልካም ትህትና ነበር ምላሽ የሚሰጠኝ እንዲሁ ሳወጣ ሳወርድ ሊነጋ አቀላልቷል ። ተኛሁ ነገር ግን እንደ ከዚህ በቀደሙ አርፍጄ አልነበረም የተነሳሁት ቀጠሮ አክባሪ ስለሆነ በጊዜ ይመጣል በሚል በግዜ ወጥቼ ሄድኩ 2ሰአት ሲል ሱቁን አፅድቼ ከፋፍቼ የፈረደበትን ሬድዮ ከፍቼ ተቀመጥኩ ግን የጠበኩት አልነበረም የሆነው ናኦድ ሳይመጣ 6ሰአት ሆነ ቁርስ እንዳልበላው እንኳን ትዝ ያለኝ የህዝቡን የምሳ ሰአት ትርምስ አይቼ ነበር ሰራተኛው ተማሪው ነጋዴው የታክሲ መጨናነቁን አላፊ አግዳሚውን በአይኔ እየቃኘሁ እበሩ ላይ ተቀምጬያለሁ ። በጣም እየራበኝ ሲመጣ ገባሁና ለማሚ ደወልኩላት እናቴ ምሳ ከደረሰ ላኪልኝ ቁርስ እንኳን አልበላሁም አልኳት ውይ ውይ አፈር ልብላልሽ የኔ ልጅ አሁን እልካለው እኔ እናትሽ ይራበኝ አለችኝ ኸረ ምን በወጣሽ በቃ እንዳትቆይ ብዬ ስልኩን ስዘጋው ናኦድ ገብቶ ቆሟል እንዴ ኮቴም የለህ እንዴ ብዬ ሰላም አልኩት ምንም እንዳልተፈጠረ ነው ፊቱ ጌታ ሆይ ብቻ በውስጡ አቂሞብኝ እንዳይሆን እያልኩ እንዲቀመጥ ጋበዝኩት እኔም ወንበር ይዤ ተቀመጥኩ ። የእውነት ልትረዳኝ ፈቃደኛ ስለሆንክ አመሠግናለሁ አልኩት ግራ ገብቶት አየኝ ከእኔ የትህትናን ቃል እንደማይጠብቅ ተረዳሁ። እና የፈለኩህ አላስጨረሰኝም ከዚያ በፊት ግን ቁርስ አልበላሁም ስትዪ የሰማሁ መሠለኝ ቴክ አድርጌ ምግብ ላምጣ ብሎ ተነሳ ኸረ በጌታ አይሆንም አልኩት ካልሄድኩ ብሎ ሲከራከረኝ ማሚ ትልካለች ብዬ በመከራ እሺ አለኝ ። ቆይ ለምንድነው እንደዚህ ምትሆነው አልኩት  አልገባኝም እንዴት ሆንኩ ሁል ጊዜ እያስከፋውህ እንደዛ አሳዝኜህ ቢያንስ መጥፎ ፊት አታሳየኝም ? ለምን መጥፎ ፊት አሳይሻለው ያን ያህል ደግሞ አላስቀየምሽኝም ባይሆን የማትፈልጊያቸውን ነገሮች ስላደረኩ ይሆናል እንደዛ ያደረግሽው አይደለም በጥፋቴ ያለ ጥፋቴም ብታስቀይሚኝ ከክርስቶስ የተካፈልኩት ፍቅር ከነገሩ አንቺ እንደምትበልጪ ነው አለኝ በላዬ ላይ ፍም ልትከምር ስቃዬን ልታበዛው አልኩት ኸረ ጌታ እኮ እንደ እኛ አይደለም ከሀጢያት በቀር እንደ እኛ ተፈትኖ የለ ይረዳናል ይራራል ያንን ለማድረግሽ ምክንያት አታጪም አለኝ የእውነት በጣም ከፋኝ በሰው ፊት በፍፁም የማላለቅሰው እዛው ቀወጥኩት ናኦድ ወድጄ አይደለም እንደዛ ክፉ የሆንኩት አልኩት አውቃለሁ የገጠመሽን በሙሉ ለዛም ነበር ልቀርብሽ የሞከርኩት አለኝ እሺ ይቀርታ አድርግልኝ አልኩት ይቅርታ ባላደርግልሽማ አጠገብሽ አልገኝም ነበር አለኝ በጣም አመሠግናለሁ ብዬው ተዐምር ያመጣችውን ምሳ ለሶስት በልተን ተጨዋውተን ተለያየን ። አዕምሮዬ ሰላም አገኘ በጣም ነበር ደስ ያለኝ ። ከበፊቱ በላይ ቸርች መሄድ ጀመርኩ ይሄንን ስራም አቁሜ የማሚን ሱቅ ከፈትን ጌታ እየረዳን ጥሩ እየሰራን ነው ቀጣይ አመት ላይ ዊዝድሮ ሞልቼ ያቆምኩትን ትምህርት ልጀምር ነው የበፊቷን እፁብ ለመሆን በጣም እየጣርኩ ነው ጌታም እየረዳኝ ነው ። ማሂና ናኦድምም እየመጡ ይጠይቁናል ጥሩ ጓደኛሞች ሆነናል ። ነገሩ ተገልብጦ በተራዬ ስለ ናኦድ መፀለይ ጀመርኩ እውነትም እግዚያብሔርን የሚፈራ አለች ማሂ ናኦድ የወደፊት ባሌ እንዲሆን ተመኘው  ግን ምን ያደርጋል በተራው እሱ ሀሳቡን ሳይቀይር አልቀረም ያኔ ስላቀረበልኝ ጥያቄ እንዲያነሳ መንገድ ስከፍት አስቀይሶ ሌላ ነገር ያወራል ለነገሩ ይበለኝ ለሱ እንደ እኔ አይነት ሴት አትገባውም እንደ ራሱ መልካምና ልባም ሴት ናት ምትገባው እያልኩ ራሴን እወቅሳለሁ እነዚያን ጊዜያት ናፈኩአቸው ያኔ ምን ነበረበት በዚያ ህይወት ውስጥ ባልሆን ግን ደግሞ በአንድ ነገር አምናለው በእኔ ህይወት የእግዚአብሔር ፈቃድ ብቻ መፈፀም እንዳለበት የወደድከውን አድርግ ብዬ ለጌታ ተውኩለት ቀናቶች ገፍተው ወደ ጊቢ የምመለስበት ቀን ደረሰ........ ............ይቀጥላል.......... @Gospel_literature @Gospel_literature
1 9910Loading...
26
.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልበ-ወለድ📘          #ክፍል_12 .......እያለች ታሞግሰው ጀመር አስተያየቴ ገባት መሠለኝ ምነው እፁ ፊትሽን ጥለሽዋል እኮ አለችኝ የዚህን ያክል አልኩና ንዴቴን ገትቼ ራሴን መቆጣጠር ጀመርኩ ። ታውቂያለሽ በፊት ሁል ጊዜ ጠዋት ጠዋት ለኳየራችን ልጆች በሙሉ የመፅሀፍ ቅዱስ ጥቅስ ይልክልናል አንድ ቀን ሳይሰላች ማለት ነው አስቢው ለዚያ ሁሉ ሰው እና ይህን ሁለት ሶስት ቀን ሳይደርሰኝ ቀረ እኔ ጋ ብቻ መስሎኝ ሌሎቹን ስጠይቃቸው ኸረ እኛ ጋርም አልላከም አሉኝ ደውዬ ስጠይቀው ትንሽ ደብሮኝ ነው አለኝ እሱ ሰዎች የፈለገ ያክል ቢከፋቸው ዋጋ ከፍሎ አፅናንቶ ወደ ቀድሞው ቦታ ይመልሳቸዋል ምን ቢገጥመው ነው ብዬ በጣም ተጨነኩ ንገረኝ ብለው ቀለል አድርጎ አይጠቅምሽም አለኝ የነገሩ ከባድነት ገባኝ ና ላገኘው  ብዙ ለመንኩት እሰይ አንቺ ነሽ ጭራሽ ቀጣሪዋ አልኩኝ በውስጤ ቀጣዩን ወሬ ለመስማት እያቆበቆብኩ ከብዙ ልመና በኋላ ተስማማ ግን ጉዳዩን አልነገረኝም ሰው አስከፍቶኝ ነው አለኝ ማንነቱን እና ምን አድርጎ እንዳስከፋው ሊነግረኝ አልፈለገም ቆይ በፊት እኛን ስትመክረን አልነበር አልኩት ከማትጠብቂው ሰው ሲሆን ያማል አለኝ ዕፁ ወዲያው ባንቺ ምክኒያት እንደከፋው ገባኝ ታዲያ ነገሮችን ንቀን ካላለፍናቸው እኛኑ ነው የሚጎዱን ትለኝ አልነበር አልኩት ። ከዚህም በፊት እኮ ብዙ ግዜ ከፍቶኝ ያውቃል ግን በሰአቱ አዝንና ወዲያው ረሳው ነበር ግን ያስከፋኝ ሰው ከእኔ የሆነ ነገር በፈለገ ሰአት በመልካም መንገድ ቀርቦኝ ነበር የፈለገው ነገር ከተሟላለት በኋላ ግን ያልጠበኩት ነበር የሆነው ትንሽ ለዛ ነው ደግሞ በጣም ይቅርታ ጥቅስ መላኬን ማቆም አልነበረብኝም አሁን ከቀድሞው ይልቅ ህይወቴ ተሰርቶበታል የሆነ ነገር ተምሬያለሁ ሰዎች እኔን መጥላትም ለኔ መልካም አለማሰብም መብታቸው ነው እኔ ግን እነሱን መውደድም ለነሱ መልካም ማሰብም ግዴታዬ ነው ከጌታ የተቀበልኩት ትዕዛዝ የተማርኩት ትምህርት  ነውና አለኝ ።የዕውነተ ዕፁ አንጀቴ ስፍስፍ ነው ያለው የሆነ እዛው ላለቅስም ፈለኩ ብታይ በጣም ነው የሚያሳዝነው ዕፁ ለምን አሳዘንሽው ምን አድርገሽ አሳዘንሽው ምናምን አልልሽም እባክሽን ቢያንስ በቅንነትና በትህትና አዋሪው እንደ መልካም ጓደኛ እንኳን ብትቀርቢው ምን አለ እሱንም አልፈልግም ካልሽ ግን ቢያንስ አትጥዪው አጠገብሽ ያለውን ወንድም ሳትወጂ ጌታን እወዳለው ማለት ስላቅ ነው የእውነት ናኦድ ማንም ሰው ሚወደው ማንም ሰው ባወኩት ብሎ የሚመኘው ሰው ነው በዚህ ወጣትነት ሲሰብክ የሚሰብከውን ደግሞ ሲኖር የእውነት ስለሱ ጌታን የማያመሰግን የለም እኮ አውቃለሁ ጓደኛዬ የበፊት ስብራት ና ጉዳትሽ ሰውን እንዳታምኚ አድርጎሽ ይሆናል ናኦድ ማለት ብሩክ ነው ማለት አይደለም ከደረሰብሽ ብዙ ስቃይና የስነ ልቦና ጉዳት አንፃር ተቀይረሻል የበፊቷ እፁብ ሰው ወዳድ ሰው አክባሪ ትሁት የጌታ ቃል ከአንደበቷ የማይታጣ ነበረች አሁን በራስሽ ሙድ ነው ምትንቀሳቀሺው ስለ ሰዎች ግድ አይሰጥሽም ልወቅስሽ አይደለም ግን ቆም በይና ራስሽን ተመልከቺ በዚህ ከቀጠልሽ በዙሪያሽ ያሉትን ሰዎች ብቻ ሳይሆን ማንነትሽንም ታጪዋለሽ ። ንግግሯን ስትቋጭ ሳልፈልግ በዕንባ ርሻለሁ ሰው ተናግሮኝ አልቅሼ አላውቅም  ልክ እንዳልሆንኩ እያወኩ ብዙ ጥፋት አጥፍቻለው ። ከተቀመጠችበት ተነስታ አቀፈችኝ እፁዬ አታልቅሺ ተይኝ ማሂ እኔ ራስ ወዳድ ነኝ  አይደለም ከሰዎች ከጌታዬ ትዕዛዝ ራሴን ማስቀድም የማልጠቅም ሰው ነኝ  አንቺ እንኳን አሰንዲ እየሆንሽልኝ በውስጤ ሳማሽ ነበር እኔ ለማንም መሆን የማልችል ሴት ነኝ ተይኝ አልኳት እኔ ክፍተትሽን ካልነገርኩሽ ምኑ ላይ ነው ጓደኝነታችን እንጂ ፃዲቅ ሆኜ እየኮነንኩሽ አይደለም አንቺም እኔ ላይ ምታይውን ክፍተት ሳትደብቂ ንገሪኝ ብላ አፅናናችኝ ። እሺ ማሂ አሁን ምን ማድረግ አለብኝ አልኳት መጀመሪያ ሰዉ በአንቺ አዝኖ ጌታ አይደሰትምና ንሰሀ ግቢ ከዚያ ለራስሽ ይቅርታ አድርጊ ራስሽን መውቀስ አቁሚ ጌታ ይቅር ካለሽ የትኛውም ከሳሽ አይከስሽም ከዚያ ናኦድን ከልብሽ ይቅርታ ጠይቂው አለችኝ ። በሀሳቧ ተስማማው ስለ እርሷም ጌታን አመሠገንኩ ። አቤት ሄጄ ጌታዬ ፊት ከልቤ ነበር ያለቀስኩት ከንሰሀውም ጋር እንዲቀይረኝ ንፁህ ልብን ፍጠርልኝ ብዬ ለመንኩት ከእግሮቹ ስር አልቅሶ መነሳት ደስታና ብርሃንን ያጎናፅፋል ነፃነት ተሰማኝ  ። ማሚንም ተዐምርንም ይቅርታ ጠየኳቸው። ቀጣዩና ዋናው ናኦድን ይቅርታ መጠየቅ ነው የኔን ስልክ ስላላነሳልኝ በማሚ ስልክ ደወልኩለት..... ............ይቀጥላል......... @Gospel_literature @Gospel_literature
1 9620Loading...
27
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብ-ወለድ📘             #ክፍል_11 ......ማን እኔ? መቼ ? ግራ ተጋባው ማሚ በቁጣ አይን ስትመለከተኝ ተቀመጥኩ ልጁ እንደዚ ለየለት በዚህ ምሽት ጭራሽ ጠራሽኝ ብሎ ይመጣል እንዴ ምን አይነት ድርቅና ነው አናዶኛል መምጣቱ ባይሆንም ጠራሽኝ በሚል ሰበብ መምጣቱ ዕፁቤ አጫውቺው እንጂ እራት ይቅረብ ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳች ። ተዐምርም ልታግዛት ጉድ ጉድ ማለት ጀመረች ። አንተ መምጣት ከፈለክ በእኔ ነው ምታሳብበው ብዬ በሹክሹክታ አፈጠጥኩበት ምንም መልስ አልሰጠኝም ዝም አለ ወዲያው ነበር ስልክ ተደወለለት ሊያናግር መሠለኝ ወጣ እኔም ልብስ ለመቀየር ወደ ጓዳ ገባሁ ። ብቻዬን እየለፈለፍኩ ረጅም ደቂቃ ተቀምጬ ስወጣ ማሚ እስቲ ይሄን ልጅ ግባ በይው ምግቡ ቀዘቀዘ እኮ አለችኝ ተቀመጥኩና ተዐምር ሂጂ ጥሪው አልኳት እራስሽ አትጠሪውም እንዴ ብላ ስትነጫነጭ አንቺ ታላቅሽ እኮ ነኝ ታዘዢ ብዬ ሳፈጥባት ምላሷ ማቆሚያ የለው አንቺስ ማሚን አትታዘዢም እያለች እየተርጎመጎመች ወጣች ። የዚህች ሌጅ ጥጋብ እንዴት እንዴት ነው እሱ ቆይ ማሚ አንቺ ደግሞ ምን አለ ብትተያት ቢያንስ እንግዳ አታከብሩም እንዴ እኔንስ ከናቃቹኝ ቆቻችሁ ። እንዴ ማሚ የለም  እኮ አለች ተዐምር ምን ወዴት ሄደ እስቲ ደውይለት አለችኝ እንዴ ምን ብዬ ነው ምደውለው አስቸኩለውት ይሆናል አልኳት አቤት መከራዬ ፊት ነስተሽው ነው እንጂ ሄድኩ ሳይልማ አይሄድም እንደው እግዚአብሔርንም አትፈሪም እፁብ ማንስ ቢጠራው ምን አግብቶሽ እቤትሽ የተቀመጠን እንግዳ ለምን መጣህስ ይባላል ምነው ምነው አጥቶ እኮ አደለም የመጣው አክብሮን እንጂ ፊቷን ቅጭም አድርጋ ወይ ማሚ እሱ ፊት ሲነሱት ሲገባው አይደል ምንም ሆኖ አይደለም ባክሽ በራሱ ሰአት ይመጣል አልኳት እኔ ምንም አልልም ጌታ ይቅር ይበልሽ ይሄ አይደለም እንደ            እግዚአብሔር ቃል እንደ ሰው ራሱ ነውር ነው ስርአት አልበኝነት ብዬዋለው ብላ ተነስታ ወደ መኝታዋ ሄደች ። ተዐምርም የጣደችውን ቡና ትታ ተከተለቻት ኦኦ ነገሩ ከሯል ማለት ነው ትንሽ የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማኝ ና ቴክስት ልልክለት ስልኬን አነሳሁ ሰሙን ስፈልግ በፊት የተፃፃፍነውን መልዕክቶች አመጣልኝ ድንግጥ ነው ያልኩት መቼ ነው ደግሞ ያወራነው ብዬ ስከፍተው  "ናኦዴ ነገ እቤት እንድትመጣ ማሚ እራት ጋብዛሀለች" ይላል ልቤ ስንጥቅ የእሱ መልስ እሺ እፁቤ ስለ ግብዣው አመሠግናለሁ ነገ ከአብሮ አደግ ወንድሜ ጋ ቀጠሮ ነበረኝ ግን በቃ ሰርዤው እመጣለሁ ። ጌታ ሆይ ውሰደኝ ብዬ ከተቀመጥኩበት ብድግ አልኩ ። ጌታ ሆይ እየቃዠው መሆን አለበት መቼ ነው የፃፍኩት ሰማይ ምድሩ ዞረብኝ ማሚ እያበድሽ ነው ዘይኝ ብዬ ወደ እርሷ ሄድኩ ምንድነው አለችኝ ጭራሽ መች እንደ ሆነ አላስታውስም በቴክስት ጠርቼዋለሁ ኤጭ ሰላሜን ስጪኝ አለችኝ ተዐምር እንደ ተኛች እኛማ ደስ የሚልሽ መስሎን ነበር እኔ ነኝ የላኩለት አለችኝ ወይኔ እንዴት እንደ ተናደድኩ በተኛችበት ቆንጥጬ ልገላት ኡኡ ብላ በጩኸት አደበላለቀችው ማሚ ኸረ ባክሽ ባክሽ አንቺ ልጅ አድቢ ብላ አስለቀቀችኝ ። ባለጌ ልጅ አይደለሽ እንዴ እኔ ነኝ ጥፋተኛዋ ላንቺ ስልክ መስጠቴ ያዋርድሽ አዋረድሽኝ አልኳት ኡፍፍፍፍ በናንተ የተነሳ ጤናዬን ልጣ ብላ ስትቆጣ ነገ አገኝሻለዉ ብዬ አኔም ተኛዉ በምን አይኔ ነው የማየው ምን አይነት ችኩል ምን አይነት ስርአት የሌለኝ ነኝ እያልኩ ራሴን መውቀስ ጀመርኩ ሳልተኛ ነጋልኝ ። ስራ ገብቼም የእንቅልፉ ድካም ጭንቀቱ ተጫጭኖ ሰላም ነሳኝ ልደዉልለትም ብዬ ፈራሁ እሱ እስኪደውል በትዕግሥት ብጠብቅም የጠበኩት አልሆነም ። 3ቀን በመጠበቅ አሳለፍኩና በ4ተኛው ቀን አይኔን በጨው አጥቤ ደወልኩለት አላነሳልኝም ሁለት ሶስቴ ደወልኩ አላነሳልኝም ኸረ ለውጥማ አለ ብዬ ተውኩት ለማሂ ልነግራት ደወልኩላት እሷም አታነሳም ደጋግሜ ስደውል አነሳችልኝ ሄለው ማሂ ወዬ ዕፁ እንዴት ነሽ አለሁ እግዚአብሔር ይመስገን ምነው ስልክ አታነሺም አልኳት እእእ ከናኦዴ ጋር ሆኜ አላየሁትም ነበር አለችኝ አሀ ከአንቺ ጋር ሆኖ ነዋ ስልኬን የማያነሳው ብዬ ዘጋሁባት እንደሚመለከተው ሰው ራሴን እስክታዘብ ተናደድኩ እየተብሰለስልኩ ውዬ ከሰአታት በኃላ ማሂ መጣች አንቺ ምነው ጆሮዬ ላይ ዘጋሽው የሱን ንዴት እኔ ላይ ነው እንዴ ምትወጪው አለችኝ ባክሽ ወደዛ አትቀባጥሪ አልኳት ለምን እንዳገኘሁት ግን አውቀሻል አለችኝ ምን አገባኝ ስለሱ ይመለከተኛል አልኳት ኸረ እፁ እየተናደድሽ ባልሆነ አለችኝ ኦሆሆሆ ምን አናደደኝ አልኳን ንዴቴ እኮ ለራሴም ይታወቀኛል እና ማወቅ አልፈልግም ነው ምትይው ካልሽ እሺ አለችኝ የባሰ ተናደድኩ በገዛ እጄ ውይ ናዲ ግን ይለያል ምን አይነት ትሁት ነው እያለች ታሞግሰው ጀመር....... .........ይቀጥላል ......... @Gospel_literature @Gospel_literature
2 0150Loading...
28
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብ-ወለድ📘         #ክፍል_10 .....ናኦድን ለማግኘት ቸኩያለሁ ። ነገር ሳብሰለስል እንቅልፍ እምቢ ብሎኝ ሊነጋጋ ሲል ተኛሁ የስልክ ጥሪ ነበር ከእንቅልፌ ያነቃኝ ናኦድ ነበር ። ሄሎ ደህና አደርሽ እፁብ እግዚአብሔር ይመስገን እንዴት አደርክ አለሁ ክብሩ ይስፋ ተኝተሽ ነው እንዴ አለኝ ድምፄ አሳበቀብኝ መሠለኝ አዎን በግዜ አልተኛሁም ነበር አልኩት እኔ እኮ ስራ ቦታሽ መጥቼ ዝግ ሆኖብኝ ነው በቃ ስትመጪ ደውዪልኝ ብሎኝ ስልኩ ተዘጋ ። ኸረ ምን ጉድ ነው ፈልግሀለው ስለው ብቻ ለጥያቄው ምላሽ ጠብቆ እንዳይሆን አያፍርም እኮ እያልኩ ተነሳሁ ተጣጥቤ ልብሴን ለብሼ ወጣሁ ። ገና ሱቁንም ከፍቼ ጥቂት ሳልቆይ መጣ ሰላምታ ተለዋወጥን ተቀመጠ የጠራሁት ለሌላ ጉዳይ በሰበብ ባስባቡ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ሲሰብከኝ ሰአታት ነጎዱ የሆነ ሰአት ላይ ምርርር አለኝ አቁም አልለው ነገር  መፅሐፍ ቅዱሳዊ ነገር ነው የሚያወራው ኸረ ምን ጉድ ነው ይመፀዳደቅብኛል እንዴ አይሰለቸውም እያልኩ ከራሴ ጋር አወራለሁ ። አውርቶ ሲጨርስ ለምን ነበር ግን የፈለግሽኝ አለኝ ግዜ ሳላጠፋ ጉዳዩን ሁሉ ነገርኩት ያልጠበቀውን ነገር እንደነገርኩት ፊቱ ቢያሳብቅም በሁሉም ነገር ከጎኔ እንደሚሆን ነግሮኝ ሄደ ። ለማሂ ደወልኩላት እና መጣች ለሷም ሁሉንም ነገርኳት አይዞሽ እግዚአብሔር ይረዳናል ከእርሱ በታች ደግሞ በናኦድ ሙሉ በሙሉ እተማመናለሁ አለችኝ ። ግን አንቺ ደግሞ ለጉዳይሽ ብቻ ሳይሆን እሱም በሚፈልግሽ ግዜ ተገኚለት አለችኝ  ማሂ ደግሞ ያምሻል ከእርሱ ጋር ለደቂቃ ማሳለፍ ይጨንቀኛል ወሬዉ ሁሉ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ማውራት ነው በቃ ስልችት ነው ሚለኝ ኸረ እፁ ተይ ጌታን ይደብራል ለጥቅምሽ ብቻ እንደፈለግሽው ካወቀ ይጎዳል ቢያንስ እንደ ጥሩ እህት ቅረቢው ። ኸረ ማሂ እየነገርኩሽ ይጨንቀኛል ብዬ አፈጠጥኩባት አንቺ ታበዢዋለሽ እንደ እርሱ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው በስለትም አታገኚም እንኳን ሌላ አለች ውይ ውይ ይቅርብኝ ብዬ ሳኩኝ ምን አለች በይኝ በሳቅሽው ልክ ታለቅሺያለሽ ስታስጠዪ ብላኝ ሄደች ለንግግሯ ቦታም ሳልሰጥ ተውኩት ። ከ1ወር በኋላ በቤቱ ጉዳይ ሰበብ መገናኘት መደዋወል ጀመርን በትንሹም ቢሆን ስብከቱን እየለመድኩት ነው እዉነትም ንግግሩ ከልብ ላደመጠው ከራሱ እንደማይናገር ያስታውቃል በቤቱ ጉዳይ ክስ መስርተን ክርክር ላይ ናቸው ማሚ ነገሮችን ቸል ማለት ትወዳለች ክስ ተጀምሮ እንኳን ይቅር በቃ የምትል ሰው ናት እኔ ደግሞ እልኸኛ ከ3ወር ንትርክ በኋላ እናቴም ባለ ድርሻ እንደሆነች ታምኖ 1000,000 የተሸጠው ቤት  እኩል ተካፍለው የድርሻዋን በባንክ አስገቡላት አጎቶቼ እርር ብለዋል አንደኛውማ ዝቶብኝ አስፈራርቶኝ ነበር የተለያየነው ። ማሚ ናኦድን ስትመርቀው ስትመርቀው ምንም ገንዘብ አልቀበልም አለ ብትለምነው እኔም ብዙ ብለምነው አምቢ አለ ። ምን አስቦ ነው ደግሞ በውለታ ሊያስረኝ ባልሆነ ብዬ አሰብኩ ማሂም በጣም ደስ ብሏት እግዚአብሔርን አመሠገንን ስለ ናኦድ ስነግራት እርሱ ምን አይነት ፍጥረት ነው ብላ ተደነቀች እኔ ግን ምንም አይመስለኝም ። በፊት በቀን አስር ግዜ ምደውልለት አሁን ትዝም አልልሽ አለኝ  ከደወለልኝም እንደ ነገሩ ነው የማወራው  ማሚ ሁሌ ስለሱ ትጠይቀኛለች ተዐምርም በጣም ነው የምትወደው ጓደኛሽ አይመጣም እንዴ እያሉ ይጨቀጭቁኛል  ስራ ይበዛበታል ምናምን እያልኩ ዋሻቸዋለሁ ። በብሩ ምን አይነት ስራ መጀመር እንዳለብን ከማሚ ጋር መወያየት ጀመርን ተዐምር እፁ አንዴ ስልክሽን መዝሙር ልስማበት ብላ ተቀበለችኝ። ሰፈራችን ለንግድ ምቹ ስለሆነ የሸቀጣሸቀጥ ሱቅ ለመክፈት ተስማምተን ፀልየን ተኛን ቀኑ እሁድ ስለሆነ በጠዋቱ ተነስተው ቡና ተፈልቶ ቁርስ ሰርተው ቤቱ ሁሉ ፅዱ ሆኖ ተቀሰቀስኩ በፈገግታ ና በትህትና የታጀበ ቁርስ በልቼ ከማሂ ጋር ተደዋውለን ቸርች ሄድኩ ። ጌታ ደስ የሚል ግዜ ሰጥቶን ተጠናቀቀ ያው ሰላም ስንባባል እዛው እንሰነብታለን ጓደኞቻችንን እያወራን ናኦድ መጣ ኡፍፍፍፍ አልኩ ማሂ አንቺ ልጅ ኸረ ጌታን ፍሪ አይከብድሽም እንዴ አለችኝ እሱም አጠገባችን ደርሶ ሰላም ካለን በኋላ ለደቂቃዎች ነዝንዞን እፁ በቃ በኋላ እንገናኝ ብሎኝ ሄደ ሆሆሆሆ ጭራሽ ላግኝህ ልጁ ታሟል እንዴ አልኩ በቃ በሱ ጉዳይ ከማሂ ጋር ሁሌ                       እንደ ተጨቃጨቅን ነው ። ስንከራከር እነሱ ቤት ደረስን እዛው ውዬ አክስቷንም ታማ ነበርና እሷን መጠየቅ ሄደን አመሻሽቼ ወደ ቤት ሄድኩ እቤት ስደርስ ቤቱ ያለወትሮው አምሮበታል የምግብ መልካም መዓዛ እና የጥሩ እጣን ና ቡና ሽታ ከሩቅ ይጠራል ምን ተገኝቶ ነው ብዬ ከበር ወደ ውስጥ ስዘልቅ ናኦድ ከነ ማሚ ጋር ቁጭ ብሏል ደነገጥኩ ደግሞም ስላልጠበኩ አንተ ምን ትሰራለህ እዚ አልኩት ። ደነግጦ ከተቀመጠበት በመነሳት አንቺ እኮ ነሽ የጠራሽኝ አለኝ ማን እኔ ?........ ...........ይቀጥላል ........... @Gospel_literature @Gospel_literature
2 0620Loading...
29
🎬መዝሙር ለመስማት MB እየበዛ ተቸግረዋል ? የድምፅ ጥራት አንሶ ተቸግረዋል ? እንግዲያውስ መፍትሄ ይዘንላችሁ ቀርበናል ከታች ያለውን ሊንክ እና Button በመንካት HQ መዝሙር ያገኛሉ 👇 https://t.me/addlist/ZSxEk8-Vk3k3ZDJk https://t.me/addlist/ZSxEk8-Vk3k3ZDJk wave ለመግባት 👉 @wunuye_bot
10Loading...
30
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብ-ወለድ📘         #ክፍል_10 .....ናኦድን ለማግኘት ቸኩያለሁ ። ነገር ሳብሰለስል እንቅልፍ እምቢ ብሎኝ ሊነጋጋ ሲል ተኛሁ የስልክ ጥሪ ነበር ከእንቅልፌ ያነቃኝ ናኦድ ነበር ። ሄሎ ደህና አደርሽ እፁብ እግዚአብሔር ይመስገን እንዴት አደርክ አለሁ ክብሩ ይስፋ ተኝተሽ ነው እንዴ አለኝ ድምፄ አሳበቀብኝ መሠለኝ አዎን በግዜ አልተኛሁም ነበር አልኩት እኔ እኮ ስራ ቦታሽ መጥቼ ዝግ ሆኖብኝ ነው በቃ ስትመጪ ደውዪልኝ ብሎኝ ስልኩ ተዘጋ ። ኸረ ምን ጉድ ነው ፈልግሀለው ስለው ብቻ ለጥያቄው ምላሽ ጠብቆ እንዳይሆን አያፍርም እኮ እያልኩ ተነሳሁ ተጣጥቤ ልብሴን ለብሼ ወጣሁ ። ገና ሱቁንም ከፍቼ ጥቂት ሳልቆይ መጣ ሰላምታ ተለዋወጥን ተቀመጠ የጠራሁት ለሌላ ጉዳይ በሰበብ ባስባቡ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ሲሰብከኝ ሰአታት ነጎዱ የሆነ ሰአት ላይ ምርርር አለኝ አቁም አልለው ነገር  መፅሐፍ ቅዱሳዊ ነገር ነው የሚያወራው ኸረ ምን ጉድ ነው ይመፀዳደቅብኛል እንዴ አይሰለቸውም እያልኩ ከራሴ ጋር አወራለሁ ። አውርቶ ሲጨርስ ለምን ነበር ግን የፈለግሽኝ አለኝ ግዜ ሳላጠፋ ጉዳዩን ሁሉ ነገርኩት ያልጠበቀውን ነገር እንደነገርኩት ፊቱ ቢያሳብቅም በሁሉም ነገር ከጎኔ እንደሚሆን ነግሮኝ ሄደ ። ለማሂ ደወልኩላት እና መጣች ለሷም ሁሉንም ነገርኳት አይዞሽ እግዚአብሔር ይረዳናል ከእርሱ በታች ደግሞ በናኦድ ሙሉ በሙሉ እተማመናለሁ አለችኝ ። ግን አንቺ ደግሞ ለጉዳይሽ ብቻ ሳይሆን እሱም በሚፈልግሽ ግዜ ተገኚለት አለችኝ  ማሂ ደግሞ ያምሻል ከእርሱ ጋር ለደቂቃ ማሳለፍ ይጨንቀኛል ወሬዉ ሁሉ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ማውራት ነው በቃ ስልችት ነው ሚለኝ ኸረ እፁ ተይ ጌታን ይደብራል ለጥቅምሽ ብቻ እንደፈለግሽው ካወቀ ይጎዳል ቢያንስ እንደ ጥሩ እህት ቅረቢው ። ኸረ ማሂ እየነገርኩሽ ይጨንቀኛል ብዬ አፈጠጥኩባት አንቺ ታበዢዋለሽ እንደ እርሱ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው በስለትም አታገኚም እንኳን ሌላ አለች ውይ ውይ ይቅርብኝ ብዬ ሳኩኝ ምን አለች በይኝ በሳቅሽው ልክ ታለቅሺያለሽ ስታስጠዪ ብላኝ ሄደች ለንግግሯ ቦታም ሳልሰጥ ተውኩት ። ከ1ወር በኋላ በቤቱ ጉዳይ ሰበብ መገናኘት መደዋወል ጀመርን በትንሹም ቢሆን ስብከቱን እየለመድኩት ነው እዉነትም ንግግሩ ከልብ ላደመጠው ከራሱ እንደማይናገር ያስታውቃል በቤቱ ጉዳይ ክስ መስርተን ክርክር ላይ ናቸው ማሚ ነገሮችን ቸል ማለት ትወዳለች ክስ ተጀምሮ እንኳን ይቅር በቃ የምትል ሰው ናት እኔ ደግሞ እልኸኛ ከ3ወር ንትርክ በኋላ እናቴም ባለ ድርሻ እንደሆነች ታምኖ 1000,000 የተሸጠው ቤት  እኩል ተካፍለው የድርሻዋን በባንክ አስገቡላት አጎቶቼ እርር ብለዋል አንደኛውማ ዝቶብኝ አስፈራርቶኝ ነበር የተለያየነው ። ማሚ ናኦድን ስትመርቀው ስትመርቀው ምንም ገንዘብ አልቀበልም አለ ብትለምነው እኔም ብዙ ብለምነው አምቢ አለ ። ምን አስቦ ነው ደግሞ በውለታ ሊያስረኝ ባልሆነ ብዬ አሰብኩ ማሂም በጣም ደስ ብሏት እግዚአብሔርን አመሠገንን ስለ ናኦድ ስነግራት እርሱ ምን አይነት ፍጥረት ነው ብላ ተደነቀች እኔ ግን ምንም አይመስለኝም ። በፊት በቀን አስር ግዜ ምደውልለት አሁን ትዝም አልልሽ አለኝ  ከደወለልኝም እንደ ነገሩ ነው የማወራው  ማሚ ሁሌ ስለሱ ትጠይቀኛለች ተዐምርም በጣም ነው የምትወደው ጓደኛሽ አይመጣም እንዴ እያሉ ይጨቀጭቁኛል  ስራ ይበዛበታል ምናምን እያልኩ ዋሻቸዋለሁ ። በብሩ ምን አይነት ስራ መጀመር እንዳለብን ከማሚ ጋር መወያየት ጀመርን ተዐምር እፁ አንዴ ስልክሽን መዝሙር ልስማበት ብላ ተቀበለችኝ። ሰፈራችን ለንግድ ምቹ ስለሆነ የሸቀጣሸቀጥ ሱቅ ለመክፈት ተስማምተን ፀልየን ተኛን ቀኑ እሁድ ስለሆነ በጠዋቱ ተነስተው ቡና ተፈልቶ ቁርስ ሰርተው ቤቱ ሁሉ ፅዱ ሆኖ ተቀሰቀስኩ በፈገግታ ና በትህትና የታጀበ ቁርስ በልቼ ከማሂ ጋር ተደዋውለን ቸርች ሄድኩ ። ጌታ ደስ የሚል ግዜ ሰጥቶን ተጠናቀቀ ያው ሰላም ስንባባል እዛው እንሰነብታለን ጓደኞቻችንን እያወራን ናኦድ መጣ ኡፍፍፍፍ አልኩ ማሂ አንቺ ልጅ ኸረ ጌታን ፍሪ አይከብድሽም እንዴ አለችኝ እሱም አጠገባችን ደርሶ ሰላም ካለን በኋላ ለደቂቃዎች ነዝንዞን እፁ በቃ በኋላ እንገናኝ ብሎኝ ሄደ ሆሆሆሆ ጭራሽ ላግኝህ ልጁ ታሟል እንዴ አልኩ በቃ በሱ ጉዳይ ከማሂ ጋር ሁሌ                       እንደ ተጨቃጨቅን ነው ። ስንከራከር እነሱ ቤት ደረስን እዛው ውዬ አክስቷንም ታማ ነበርና እሷን መጠየቅ ሄደን አመሻሽቼ ወደ ቤት ሄድኩ እቤት ስደርስ ቤቱ ያለወትሮው አምሮበታል የምግብ መልካም መዓዛ እና የጥሩ እጣን ና ቡና ሽታ ከሩቅ ይጠራል ምን ተገኝቶ ነው ብዬ ከበር ወደ ውስጥ ስዘልቅ ናኦድ ከነ ማሚ ጋር ቁጭ ብሏል ደነገጥኩ ደግሞም ስላልጠበኩ አንተ ምን ትሰራለህ እዚ አልኩት ። ደነግጦ ከተቀመጠበት በመነሳት አንቺ እኮ ነሽ የጠራሽኝ አለኝ ማን እኔ ?........ ...........ይቀጥላል ........... @Gospel_literature @Gospel_literature
10Loading...
31
.        🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብ-ወለድ📘           #ክፍል_9 ........እርምጃዬን ገታ አድርጌ ሄለው አልኩ ምንም ምላሽ አላገኘሁም ። ከዝምታ በኋላ ስልኩ ተዘጋ ግራ መጋባቴን ያየችው ማሂ ምነው አለችኝ እንጃ የብሩክን ድምፅ የሰማሁ መሠለኝ ከዚያ ምንም መልስ አልመለሰልኝም አልኳት መስሎሽ ይሆናል ደግሞ ደህና የረሳሽውን ሆሆሆ ነይ በይ እንሂድ አለችኝ ።  እቤት ስገባ ተዐምር ቡና እያፈላች ነበር የኔ እህት አዋቂ እኮ ነሽ አንቺ ይመችሽ አልኳት ባክሽ እማዬ ራሷን አሟት ለእርሷ ነው ያፈላሁት አለችኝ እማ ምን ሆንሽ አልኩአት ዝም ብላ ነው የኔ ልጅ አላመመኝም  መክሰስ ብዪ አለችኝ ። እሷ ምግብ ልታመጣልኝ ጓዳ ስትገባ ተዐምር ምን ሆናለች አልኳት አገር ቤት ያለችው የድሮ ጓደኛዋ ደውላላት ነው አለችኝ እየተንሾካሾከች ምን ብላ አልኳት እማ ስትመጣ ሁለታችንም ዝም አልን እኔም ምግቤን መብላት ጀመርኩ ስልኳ ጮኸ አንስታ ማውራት ጀመረች ተይኝ ባክሽ ይቅርብኝ ድህነቴ ይሻለኛል ከነሱም አልጣላም እያለች ታወራለች ግራ የገባኝ እኔ እንደ ጆሮ ጠቢ ተመስጬ አዳምጣለሁ ትንሽ አናግራ አለች መጥታለች ብላ ስልኩን ሰጠችኝ ። ሄለው እፁብየ አቤት አልኩ አወቅሽኝ ፅጌ ነኝ አለችኝ ውይ አዎን ሰላም ነሽ አልኩ አለሁ እኔ እግዚአብሔር የተመሠገነ ይሁን ይኸውልሽ እፁብ ወንድ ልጅ ባይኖርም አንቺ ትልቅ ነሽ ታስተውያለሽ የአያቶቻችሁን መሬት አጎቶችሽ ለመቀራመቱት ነው እናትሽ አልሰማ ብላኛለች በምትችይው መንገድ አስረጂያት የድርሻዋን ትጠይቅ አትፍዘዢ አለችኝ ። ጭስስ አልኩ እሺ ፅግዬ አወራታለሁ አልኩ አዎን ዝም አትበይ እንደው እናንተን መርዳት ሲገባቸው ጭራሽ በድብቅ ሊሸጡት ነው  በተቻላቹ መጠን ተሟገቱ አለችኝ እሺ ብዬ ስልኩ ተዘጋ እማ ምን አሰብሽ አልኳት በልጅነቴ ተዐምር ሳትወለድ የማውቃቸው አጎቶች ናቸው የት ናችሁ የት ወደቃችሁ ተባብለን አናውቅም ምን አስባለው ሰይጣን ሊያውከኝ እንጂ አቅሜን አውቀዋለሁ አለችኝ ማለት ልተይላቸው አልኳት የኔ ልጅ የቤተሰቦቼ እንጂ እኔ የለፋሁበት አይደል ምን ይሁን ብዬ ያለ አቅሜ ልንጠራራ አለችኝ እና ለነዚ ጅቦች የለፉበት ነው አልኳት አንቺ ልጅ በቃ ተይኝ ወንድሞቼ እኮ ናቸው ከማይረባ ከጊዜያዊ መሬት የነሱ ወንድምነት ይበልጣል አለችኝ እማ ይሄ ክርስትናም የዋህነትም አደለም አለማወቅ ነው የሚባለው አነሱ ቤት ንብረት እያላቸው ይንገበገቡ የለ እንዴ ስረቂ አልተባልሽ የወላጆሽን ንብረት የድርሻሽን ነው እንጂ ተይኝ እፁብ በቃ በምን አቅማችን ነው እንከራከር ብንልስ ምንከራከረው ጠበቃ መቅጠር ስንት ዕዳ አለ በቃ ተይኝ ድህነቴ ይግደለኝ ሌላ ራስ ምታት አትሁኚብኝ አለችኝ ። አሷን ላለማስጨነቅ ዝም አልኩ በዝምታ ስብሰለሰል በLaw በማዕረግ የተመረቀው ናኦድ ትዝ አለኝ ። አንተ እኮ መንገድ አታጣም አልኩና  ልደውልለት ወጣሁ ሳስበው መጀመሪያ ማድረግ ያለብኝ ነገር እንዳለ አሰብኩ የማሚን ስልክ ወስጄ የሁለቱንም አጎቶቼን ስልክ ቁጥር ወሰድኩ እናቴ ለቤተሰቦቿ ብቸኛ ሴት ናት ሁለት ወንድሞች አሏት በመጀመሪያ ሰለሞን የሚባለው ጋር ነበር የደወልኩት ሰላምታ ተለዋውጠን ማንነቴን ስነግረው እንዴ አላችሁ እንዴ አለኝ እርር አልኩ አዎ እግዚአብሔር አልጣለንም  አለን ፈልጌህ ነበር አልኩት መቼም የቤቱን ጉዳይ የመንደር ወሬ ደርሷችሁ መሆን አለበት ለመሆኑ እናትሽ ደህና ናት አለኝ እሱን ማወቅ አስፈልጎህ ቢሆን እስከዛሬ በደወልክ አሊያም ባገኘሀት ነበር አልኩ አአ አንቺ ትንሽ በረሮ አጎትሽ ነኝ ያውም የእናትሽ  ታላቅ እንዴት ነው ስርዓት አላስተማረችሽም አለኝ ምንም አልተናገርኩም ዝም አልኩ ግምቴ ልክ ነው የደወልሽልኝ ለቤቱ ጉዳይ ነው አለኝ አዎን ለሱ ነው አልኩ እንግዲያውስ አርፈሽ ቁጭ በይ ገና ቤቱ ብዙ ጉዳይ ይቀረዋል ሌላ እንቅፋት አልፈልግም ብሎኝ ስልኩን ዘጋብኝ ። ሰራልሀለው እኔ እፁብ አይደለሁም አልኩ በውስጤ ሰው ቢሰማኝ ልክ የሆነ ምመካበት ነገር ያለኝ ነው ምመስለው ናኦድ ጋር ደወልኩና ነገ ላገኘው እንደምፈልግ ነገርኩት ምንም አላንገራገረም ኸረ ደስ ይለኛል አለኝ መልካም እደውላለሁ ብዬ ስልኩን ዘጋሁት አቤት ግን ራስ ወዳድነቴ ለጥቅሜ ሰአት መኖሩ ትዝ አለኝ በምኑ ሊያኖረኝ ብዬ ሳላግጥ የነበርኩበት ስራው ዛሬ ሊያስፈልገኝ ነው ተመልሼ ገባሁና ተቀመጥኩ ፊቴ ላይ ንዴቴ ይነበባል መሠለኝ ተዐምር ቡናውን ቀድታ ስትሰጠኝ እናቴ ምን ሁነሻል አለችኝ ምን ሆንኩ አልኳት ለመሆኑ ማንን አውርተሽ ነው የመጣሽው አለችኝ እእእ ማሂ ናት አልኳት በይ እኔን ጣጣ ውስጥ እንዳትከቺኝ የአንቺ እልኸኝነት ገደብ ያጣ ነው አለችኝ ምንም መልስ አልሰጠኋትም ነገ ነግቶ ናኦድን ለማግኘት ቸኩያለሁ ....... ...............ይቀጥላል............. @Gospel_literature @Gospel_literature
2 0540Loading...
32
.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብ-ወለድ📘         #ክፍል_8 ...........ይንገርሽ አለችኝ በቃ ለሞራሉ ስል ሱቅ እንዲመጣ ነገርኩት ። ደግሞ እንደጠራሁት ራሱ ረስቼ ሲመጣ ነው ትዝ ያለኝ አቤት አስመሳይ መሆኔን የተረዳሁት ያኔ ነው ወንበር ሰጠሁት ሻይ ቡና ካላልክ ብዬ ወከብኩ ለሚያየኝ ለሱ ጥሩ ቦታ ያለኝ ነው የምመስለው ። ስለ መፅሀፍ ቅዱስ ስለ አገልጋዮች ታሪክ ይተርክልኝ ጀመር የፈለገኝ ለምን እንደሆነ ሳይናገር 1:30 ሆነ ደንበኛ ሲመጣ ስነሳ ስቀመጥ ስልችት ሲለኝ እኔ የምልህ ናኦድ ለምንድነው የፈለከኝ አልኩ ። እእእእ ምን መሠለሽ  ለደቂቃዎች ዝም አለኝ አጠገቡ ያለውን ውሀ አንስቶ ይጠጣል ያስቀምጣል ናኦድ ምንድነዉ አልኩት ምን መሠለሽ እፁብ በቃ እኔ ለአንቺ ጥሩ አመለካከት አለኝ  በእግዚአብሄር ፊት ስፀልይ አንቺ የወደፊት ሚስቴ እንደሆንሽ አሳይቶኛል አለኝ ። በሳቅ ሞትኩ እሱ ተደናግጦ ዝም ብሎ ያየኛል ደግሜ ሳየው እስቃለሁ ምነው እፁብ አለኝ ናኦድ እየቀለድክ ነዋ ፕራንክ ነው በለኝ አልኩት  ማለት እኔ እውነቴን ነው አለኝ ኸረ አንተ ልጅ ያምሀል እንዴ እግዚአብሔር እንደው ሚያሳይህን አጣ ጭራሽ ይሄ ይሄ ነገራችሁ ነው ትውልድን ወደ ኋላ ሚጎትተው አልኩት እፁብ አልቀለድኩም እውነቴን ነው አለኝ ኸረ እፈር እኔ እንደሰማውህ ሌላ ሰው እንዳይሰማህ እንዴት ነው ነገሩ እግዚአብሔር መቀለጃ ሆነ እንዴ  አይተህም ከሆነ ከእግዚአብሄር ሳይሆን ቅዠት ነው የሚሆነው እኔ እውነቴን ነው አስቢበት ብሎ ከመቀመጫው ተነሳ እንግዲያውስ ለአንተ ያሳየህ እግዚያብሔር ለእኔም ያሳየኝ ። ብዬ እኔም ወደ ቦታዬ ተመለስኩ እሱም ወጣ ወይ ጉድ ይሄ ልጅ ጭራሽ እራሱን እንደ ነቢዩ ኤልያስ ነው እንዴ የሚያየው እያልኩ ሲያወራ የነበረውን የፊት ገፁን እያስታወስኩ በሳቅ ሞትኩ ከደቂቃዎች በኋላ ሚሂ መጣች ። ወይኔ ጓደኛዬ እንኳን መጣሽ እያልኩ ስስቅ ምነው ምን ተገኘ እያለች ሰላም አለችኝ በመጀመሪያ ተቀመጪ አልኳት ተቀመጠች ጆሮዋን አቆብቁባ እሺ ምን አዲስ አለችኝ ። ናኦድ ልነግራት እጀምርና እስቃለሁ እእእ ናኦድ ምን ሆነ አለች ሳቄን አላቆምኩም ውይ እስቲ ተናገሪ ዝም ብለሽ አትገልፍጪ አለችኝ እሺ እሺ አልኩና ናኦድ ወደ ፊት ሚስቴ እንደሆንሽ ጌታ አሳይቶኛል አለኝ ብዬ ሳኩ አትይኝም ገምቼ ነበር የኔ ምስኪን ምን አልሽው አለችኝ ኸኸኸ ምን እለዋለሁ አንቺ ስታስቢው እብድ ነኝ እንዴ የገረመኝ ደግሞ በዚህ በሰለጠነ ዘመን ፀልዬበት እግዚአብሔር አሳየኝ ምናምን ምኑ ፋራ ነው በስማም አፁብ ንቀሽው እንዳይሆን ብቻ አንቺ አግኝተሽ ነው በዚህ ዘመን እግዚአብሔርን ሚፈራ ሰው?  ኸረ ማሂ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰው አለ እንዴ ብዬ ስቃለሁ እስቲ ፌዝ ብቻ አይጠቅምም ቆም ብለሽ አስቢ እንኳን ፀልዬበታለው ይቅርና ትናንት ተዋውቀው ዛሬ ለስንት ነውር የሚጠይቁ ሰዎች ባሉበት ምድር ፋራ ሳይሆን የገባው ነው አለችኝ ። አንቺ ደግሞ ምታሽቃብጪው ነገር አለ በቃ እኔ አይመቸኝም ደግሞ በምኑ ሊያኖረኝ ነው አልኳት ። እግዚያብሔር ነው ሰውን የሚያኖረው አለችኝ አይደል እግዚአብሔር ከሰማይ ብር ይበትንልሻል አንቺ ደግሞ ታበዢዋለሽ አልኳት ለራሴ ስሙኒ የሌለኝ ሴት ገና ምን አለው ማለትም ጀመርኩ ስለማንኛውም ፀልይበት አለችኝ ሴትዮ ያምሻል እንዴ ከጊቢ ትምህርት ትቼ የመጣሁት ቤተሰቦቼን ማኖር ከቻልኩ ብዬ ነው ጭራሽ ሌላ ኑሮ ላስብ እንዴ ደግሞ ሲያስመስል ነው ጌታ ጌታ የሚለው እሱም ከሌሎቹ አይሻልም እንደውም ምፀልየው ትዳር ሚባል ነገር ውስጥ እንዳትከተኝ ብዬ ነው ቀልደኛ ነገ ላገባው ነው የተባለ ሰው የካደኝ ሰው እኮ ነኝ ምንም ትዳር ጋብቻ ምናምን ሚባል ነገር የለም ተውረገረኩባት ማሂ መናደዴ ገብቷታል መሠለኝ ዝም አለች  አሰሪዬም መጥታ ሱቁን ዘጋግቼ ወጣን በዝግታ ስንራመድ ስልኬ ጠራ አዲስ ስልክ ስለ ሆነ ማነው ደግሞ እያልኩ ቁጥሩን አንድ በአንድ ሳይ የውጪ ስልክ ነው  አነሳሁት  ሄለው አለኝ የብሩክ ድምፅ መሰለኝ ልቤ ተሰነጠቀ እርምጃዬን ገታ አድርጌ ሄለው አልኩ..... ..........ይቀጥላል ........ @Gospel_literature @Gospel_literature
2 1060Loading...
33
.        🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ             #ክፍል_7 .........ከዚያ በኋላ አልደወለም ስልኩን ደግሞ በቃሌ አላውቅም ለነገሩ የእነሱ መኖር ምንም ባይጠቅምም በሰው ወሬ አሳብቤ ነው ከቅዱሳን ህብረት የጠፋሁት ። ወደ እቤት እንደሄድኩ ተዐምርዬ ነገ ቸርች ይዘሽኝ አትሄጂም አልኳት እንዳዋራሽ ፈልገሽ ከሆነ ውሸታም እንደሆንሽ ስለማውቅ አትልፊ ስንት ዘመን ዛሬ ነገ ስትይኝ አልከረምሽም ነበር ጥናቴን ላጥናበት አለችኝ  እማም ፊት ነስታኛለች ምግብ አምጥታ ፊቴ ታስቀምጥና ፊቷን ግን አትፈታልኝም እነዚህ ሰዎች ምን እየሆኑ ነው እንደሌሎቹ በሱስ በክፉ ህይወት ውስጥ ቢያገኙኝ ምን ሊሆኑ ነበር አልኩና በሆዴ ምግቡን በልቼ ተኛሁ ። በጠዋቱ ነበር የነቃሁት በፊት እሁድ ቀንም እሰራ ነበር ያውም በራሴ ፍቃድ ለአሰሪዬ ዛሬ እንደማልመጣ ነግሬያት ቤት መስራት ያለብኝን ሰራሁና ልብሴን ቀይሬ ወጣሁ ። ተዐምር ቀድማኝ ሄዳለች መንገድ ላይ እያለሁ እፁብ አይንሽን በጨው አጥበሽ ልትሄጂ ነው ባለፈው እንደዛ አስደንግጠሻቸው ውስጤ ይለኛል  ምንም አይሆንም እንደውም መሄዴ ያስደስታቸዋል ከራሴ ጋር ስሟገት ደረስኩ ። ተዐምር አይታኝ ተዐምር ሆንኩባት መሠለኝ ፈዘዘች ሊፈልጉኝ የመጡ ጓደኞቼ ሁሉ መምጣቴ እንዳስገረማቸው ፊታቸው ያሳብቃል ። የአምልኮው መርሀግብር ተጠናቆ በፍጥነት ወጣሁ አንቺ እፁብ እፁብ ጥሪ ሰምቼ ዞር አልኩ ማሂ ነበረች የድሮ የልጅነት  ጓደኛዬ ቆሜ ጠበኳት ደስ ብሎኛል በመምጣትሽ ጌታ ይባረክ ብላ ደስታዋን ገለፀችልኝ ።  እኔም ስላገኘሁሽ ደስ ብሎኛል አልኳት ታዲያ የምን የጥድፊያ ነው ሌሎቹን አናግሪያቸው አለችኝ ሁሉንም ጠብቄ አናገርኳቸው አንዳቸውም ግን ፊታቸው አልጠቆረብኝም ከስብከቱ ደግሞ  ብዙ ነገር ተምሬያለሁ ። ከማሂ ጋር በዝግታ እየተራመድን ስለ አንድአንድ ነገሮች እያወራን ደረስኩ ስልክ ተለዋውጠን ተሰነባብተን ተለያየን። እቤት ስገባ ማሚ እውነቴን ነው ቸርች መታለች ትላለች ተዐምር የኔ ልጅ ሰው ተመሳስሎብሽ ወይም መንፈስ ነው ያየሽው  እሷ በፍፁም አለቻት በር ላይ ሆኜ ነበር ማደምጠው ቆይ ግን እኔ ከሰው የተለየ ምን አለብኝ አልኩ ሁለቱም ደነገጡ ሳያስቡት ስለገባሁ እኔማ የቤተሰቤ ታሪክ ይቀየራል ብዬ ስራ ስትለኝ መጥፎ ነገር ባለመገመቴ ነው ያን ቀን የሆነው ሁሉ የተፈጠረው እግዚያብሔር ደግሞ ያከበሩትን ያከብራል ሲባል እኔ በብዙ አይነት መንገድ ነበር ምተረጉመው መጠጥ ሲሰጡኝ ምቀሰፍ ነገር ነው የመሠለኝ በድካምም ሆኜ እግዚአብሔርን አላሳዘንኩትም እሱም አሳልፎ ለውርደት አልሰጠኝም ቆይ ከቸርች ቀረሁ እንጂ ምን ሳደርግ አይታችሁኛል ብዬ አለቀስኩ  የኔ ልጅ ወደ አጉል ህይወት እንዳትገቢብኝ ብዬ እንጂ ከልቤ ይመስልሻል ፊት የነሳሁሽ አንቺ  ለኔ ብለሽ ያልሆንሽው የለም እንደዚያ የምትወጂውን ትምህርት እንኳን ትተሻል የኔን ህይወት ለውጣለሁ ብለሽ በማይሆን ተስፋ ተሰብረሻል በቃ ይብቃሽ ወደ ትምህርትሽ ተመለሺ ብላ አቀፈችኝ ።  መመለሴ አይቀርም አንድ ቀን እግዚያብሔር ሁሉን ይለውጣል አንቺ አትጨነቂ አልኳት ተዐምር እና እህቴ ከዚህ በኋላ ሁሌ እንሄዳለን አለችኝ ። ኮስተር ብዬ ዘግተሽኝ አልነበረ እንዴ አልኳት እህህህ ከማሚ ጋር ታረቃቹአ እንዴ እሰይ እኔም የቀልዴን ነዋ በቃ አለችኝ አይ የኔ እህት አሽቃባጭ እኮ ነሽ አልኳት ። ታረቅን ቀናቶች ወራቶች ይነጉዳሉ በተአምር አምልኮ አልቀርም በቃ ሱቅም ቁጭ ብዬ መፅሀፍ ቅዱስ ነው የማነበው ናኦድ ወደ አገልግሎት እንድመለስ ይገፋፋኛል ከስራውም ጋር አይመቸኝም አልችልምም   የጊዜ ጉዳይ ነው ይቅር ይበለኝና ጉትጎታው ስለሰለቸኝ ይሁን ሲደውል ራሱ ራሴን ያመኛል ። ጭራሽ በጣም እንደሚፈልገኝ ነግሮኛል ጭቅጭቁ ስለሰለቸኝ ለማሂ ስነግራት ምን አለበት እሱ እኮ በቅንነት ነው ጊዜ ካጣሽ ሱቅ መጥቶ የተፈለግሽበትን ጉዳይ ይንገርሽ አለችኝ ........... ..................ይቀጥላል.............. @Gospel_literature @Gospel_literature
2 1400Loading...
34
በጣም ይቅርታ አድርጉልኝ 🥺🙏 Final exam ላይ ነበርኩ ...የጤና ተማሪዎች ካላችሁ ታቃላችሁ ትረዱኛላችሁ😭 sorry 🙏 ከእንግዲህ ሁሌ ጠብቁኝ
2 0940Loading...
35
.        🤔ጥያቄዬ🤔 Present by Hopeful_Tube 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብ-ወለድ📘             #ክፍል_6 ......ጨለማው እየበረታ መጣ ልቤ መተንፈስ አቅቶት ትንፋሼ ይቆራረጣል ጭር ብሎ አይደለም ሴት ልጅ ወንድ አይታይም አናቴ መደወሏን አላቆመችም ትንሿ ስልኬ ደግሞ ጩኸቷ ልታስደፋኝ ነው ። በፍጥነት ዘጋኋት እየተራመድኩ ነው የመጨረሻ ነብሴ እስክትጨነቅ ድረስ ኮቴ ተሰማኝ ለመዞር ካሰብኩ ከመቅፅበት የሆነ እጅ አፌን አፈነኝ እጮሀለሁ ብትይ ብሎ አንገቴ ስር ስለት ይመስለኛል የሚቀዘቅዝ ነገር አድርጓል እባክህን ምንም የለኝም ተወኝ ። ሌሎችም መጡ አእእእ ምን አገኘሽ ባክህ ወፍ የለም ይባባላሉ ቦርሳ አልያዝኩ ምን አልያዝኩ መፅናኛዬን ስልኬንም ወሰዷት እና እንዲሁ ልትፋታት ነው አለው ሁለቱን እጆቼን ወደ ኋላ ጥፍር አድርጎ አንደኛው ይዞኛል ሀሳባቸው ገባኝና ለመጮህ ብሞክር አፌን ግጥም አድርጎ አፍኖታል በቃ ነብሴ ልትወጣ ደረሰች ብዙ ተወራጨው እግዚያብሔር እንደ እኔ መች ክፉ ሆኖ የመኪና ባትሪ በትልቁ በራ ሶስቱም እዛው ትተውጭ በፍጥነት እሮጡ መኪናውም ፍጥነት ጨመሮ አጠገቤ አቆመ  ከወደኩበት ተነሳሁ ከመኪናው የወረደው ትልቅ ሰው ነበር የኔ ልጅ ምን አደረጉሽ ደህና ነሽ ጠየቀኝ አባቴ እስኪመስለኝ ድረስ ትከሻውን ተደግፌ አለቀስኩ ተረጋጊ ብሎ መኪናው ውስጥ እንድገባ አደረገ ምንም እንዳላደረጉኝ ካረጋገጠ በኋላ ተመስገን የኔ ጌታ ያ ሁሉ ፈተና ይህቺን ነብስ እንድታደግ ነው ብሎ አመሠገነ በዚህ ምሽት እዚህ ምን ትሰሪያለሽ እኔ ሴት ልጆች አሉኝ አንቺኑ የሚያህሉ ግን በዚህ ሰአት ከቤት ወጥተው አያውቁም እኔ እንኳን ከመንገድ ነው ምመጣው መኪና ተበላሽቶብኝ ቆሜ እንጂ ዘመኑ ከፍቷል በዚያ ላይ ሴት ልጅ ነሽ ብዙ ነገር ተናገረኝ እኔ ከማልቀስ ውጪ ምንም አልተናገርኩም እሺ የት ነው እቤትሽ አለ ነገርኩት የኔ ቤት ያ ነው ብሎ በእሩቁ አሳየኝ ወይ ከልጆቼ ጋር እደሪና ጠዋት እቤት ላድርስሽ አለኝ አይ እናቴ ትጨነቃለች እቤት እሄዳለው አልኩኝ ወደ ራሱ መኖሪያ ቤት መኪናውን አስጠጋና ክላክስ አደረገ ከደቂቃዎች በኋላ ሁለት ሴት ልጆች አንድ ደሞ ቲንሽዬ ወንድና ባለቤቱ መሠለችኝ ማሚን ምታክል ሴት ወጡ ከመኪናው ወርዶ ሁሉም በየተራ ሠላም አሉት የጫነውን እቃ አውርዶ ከባለቤቱ ጋር ቆመው ያወራሉ ስለ እኔ መሆኑን መገመት አልተሳነኝም። ልጆቹን አስገብተው እርሱም እሷም ወደ መኪናው ገቡ ጨበጠችኝ አስቴር እባላለሁ አለችኝ እፁብ አልኳት ለምንድነው ምታለቅሺው ሰዎቹ ምንም አላደረሱብሽም አይደል አለችኝ ግምቴ ልክ ነበር ነግሮአታል ድንጋጤው ይሆናል አታስጨንቂያት አላት አይዞሽ እግዚያብሔር መልካም ነው አለችኝ በጣም ተሰማኝ በራሴ አፈርኩ እግዚያብሔር እንደ ሰው ቢሆን ኖሮ ዛሬ ህይወቴ ተመሰቃቅሎ ነበረ ። እበር ላይ አደረሱኝ ስልኬን ተቀብለውኝ ተሰናበቱኝ ለማመስገን እንኳን ቃል አጣሁ እግዚአብሔር ብድራታችሁን ይክፈላችሁ አልኳቸው ፈገግታቸው ብቻ በቂ ነው ። ጊቢ እንደገባሁ መኪናውን አስነስተው ሄዱ እናቴና ተዐምር እበር ላይ ተቀምጠው በእንባ ብዛት የሉም ገና ሲያዩኝ ከተቀመጡበት ተነሱ የኔ ልጅ በህይወት አለሽ ምንድነው መታ ሰውነቴን ሁሉ መደባበስ ጀመረች ተዐምር አለባበሴ አስደንግጧት ከእግር ጥፍሬ እስከ ፀጉሬ ታየኛለች እናቴ ቆይታ ነው ያስዋለችው ምንድነው እፁብ ምን አይነት ህይወት ጀመርሽ አለች ። ተዐምር እየተመናቀረች ገባች ተከተልኳት እናቴም መጣች ።  በጣም ነው የማዝነው እህቴ ምሳሌዬ ናት እያልኩ በየደረስኩበት ሁሉ አወራ ነበር አንቺ ግን መጥፊያዬ ልትሆኚ ነው ብላ እንባ ተናነቃት እናቴ ቀጠለች እኛ ምን ገጠማት ምን ደረሰባት ብለን እንጨነቃለን እፁብ አንቺ የኔ ልጅ እራስሽ ነሽ ምነው ቀሚስሽ ረዘመ እኔ ፊት ልብስ መቀየር የምትፈሪ ልጅ በዚህ ውድቅት እንዲህ ሆነሽ ትመጪያለሽ ? ለመሆኑ የት ነበርሽ ከየትስ የተማርሽው ነው ሁለቱም ፋታ ሳይሰጡኝ ያወራሉ እባካችሁ አድምጡኝ ብዬ ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ የገጠመኝን ነገርኳቸው ምነው በቀረብኝ እናቴ እንደ ሞትሽ ነው ምቆጥረው ብላ አለቀሰች ተዐምርም ማፈሪያነቴን ነገረችኝ ለካ ትምህርቴ ይቅር ያልሽው ለአለሌነትሽ እንዲመችሽ ነው እግዚያብሔር ይቅር ይበልሽ ብላኝ ሁለቱም አልቅሰው ገብተው ተኙ እኔም እዛው ሳሎን ፍራሽ አምጥቼ ተኛሁ ህልምም ይመስለኝ ጀመር ሁሉንም ሳስታወስና እቤት በሰላም መድረሴን ሳስብ በቃ እንባዬን መግታት ተሳነኝ ። ይህ ከተፈጠረ ሳምንታት ተቆጠሩ እቤት ውስጥ ማሚም ተዐምርም አያዋሩኝም እንደ ቆሻሻ ነው የሚቆጥሩኝ ጌታ ባይታደገኝና የእነዛ አውሬዎች መጫወቻ ብሆን ምን ሊውጠኝ ነበር  ። ሰብለ በማግስቱ ሱቅ መጥታ አንቺ ድሮም ድሀ ሲያስቡለት አይወድም ምን ክብር አለሽና ነው ክብሬ ማዕረጌ ምናምን ብለሽ የተመለስሽው ስንት ብር እንዳመለጠሽ ታውቂያለሽ እኔንም አፌን እንዳበላሽ አደረግሽኝ ብላ ጮኸችብኝ ። የእናንተ ብር በአፍንጫዬ ይውጣ ደግሞ አታፍሪም  ታናሽ እህት የለሽም ደህና ስራ እንደሚያሰራ ሰው ወስደሽ ልትሸጪኝ ነበር እግዚያብሔር እንደ እኔም እንደ አንቺም ስላልሆነ ታደገኝ እንጂ ከብርሽ ጋር ብረሪ ድህነት በስንት ጣዕሙ አልኳት   ዋጋ ትከፍይበታለሽ ብላኝ ሄደች ። ከዚያ በኋላ ተመልሳ መጥታ አታውቅም ። ዛሬ ደግሞ ቀኑ አልገፋ ብሎኛል ተቀምጬ ጋዜጣ ላይ ተጣድኩ ሲሜን አዘግቼ እንደገና አወጥቼዋለው ካስወጣሁት በኋላ የባለፈው ሰው ደውሎልኝ ስልኬ አስቸግሮአቸው እንደነበረ ነገረኝ አዘግቼው መሆኑን ነገርኩት ብዙ መከረኝ አሁን ያለሁበትንም ሁኔታ ጠይቆ አፅናናኝ ባለቤቱም እንደዛው ። ነገ ቸርች ለመሄድ ወስኜአለሁ ስለኬ አዲስ ስለሆነ የማናቸውም ስልክ የለኝም ናኦድም ከዚያ በኋላ አልደወለም ስልኩን ደግሞ በቃሌ አላውቅም ............ ..................ይቀጥላል................
2 3160Loading...
.        🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘           #!#ክፍል 31 .......መከረኛ እንባዬ እየረገፈ ተቀመጠችና ውሀ ጠጣች እኔ በገዛ ቤቷ ፋታ አልሰጥ አልኳት ለመረጋጋት እየሞከረች እኔም ጩኸት ያጀበው ጥያቄዬን ሳላቆም አማን መጣ ሲያየን ተደናገጠ እፁብ ምን ትሰሪያለሽ አለኝ ናዲን ከዚህች ሰይጣን ውጪ ማንም ምንም ሊያደርገው አይችልም ከሰማችህ አንተ ጠይቃት አልኩት ። አንቺ ተረጋጊ ብሎ ወንበር ሰጠኝ ስለማከብረው ተቀመጥኩ ይኸውልሽ ማህሌት እኛ ትልልቅ ሰዎች ነን እንደዚህ አይነት ጨዋታ አያምርብንም እግዚአብሔርን መፍራት እንደሆነ አቁመሻል ግን ቢያንስ በዚህ ሰአት እድሜያቸው የገፋ ቤተሰቦቹ ክፉኛ ተጨንቀዋል እባክሽ እልህሽን ለጊዜው ተወት አድርጊውና ወንድሜ የት ነው ያለው አላት ። እንዴ ነገሩ እውነት ነው እንዴ ይሄቺ እብድ ስትበጠብጠኝ አእምሮዋ ተነክቶ መስሎኝ ነበር የታገስኳት የምሯን የው ናኦድን ውለጂ ምትለኝ አለችው አታስመስይ ማህሌት እስከዛሬ ጌታን ብዬ ስትጫወቺብኝ ዝም ብዬሻለሁ አሁን ገና በማይቀለደው ቀለድሽ አልኳት ተዐምር እየተንሾካሸከች ኸረ እፁ በናትሽ ዛሬስ ለጌታ ስትይ እንደ በፊቱ እሷን ተያትና ለጌታ ትተን ከእኛ ሚጠበቀውን እናድርግ አለችኝ አንቺ ልጅ ዝም በይ በእርሷ ቦታ ወደ አንቺ እንዳልዞር አልኳት ። አማን ቀጠለ እባክሽ ማህሌት በጨዋ ደንብ እናውራ ብዬ ነው ናኦድ የት ነው አላት ቆይ ለምንድነው የምትለምናት ህግ አፍንጫዋን ይዞ ያስለፈልፋት የለ አልኩት አንቺ አበዛሽው እንደ አንቺ ስላልሆንኩ ነው ቤቴ መተሽ ስትጨፍሪ ዝም ያልኩሽ አይ ካልሽ አሁን ያልሽው ለአንቺ ይሆናል በጥበቃ እየተጠፈጠፍሽ ትወጪያለሽ አሁን ቤቱን ለቀሽ ውጪ አለችኝ ። ብዙ ነገር ልናገራት አልኩና ራሴን ለመግዛት ሞከርኩ አማንም እፁ በቃ ነይ በዚህ መንገድ አይሆንም ብሎ አስወጣኝ እና ለፖሊስ እናመልክት አልኩት 24ሰአት ስላለፈው ቤተሰቡም ለፖሊስ አመልክቷል ሆስፒታል እያለሽ ከፖሊስ ጣቢያ ሲጠሩኝ የው ትቼሽ የሄድኩት ከሰዎች ጋር ግጭት አለው ብለው ሲጠይቁኝ ስለ ብሩክም ስለ ማህሌትም ያለውን ነገር ነግሬያቸዋለው አንቺ አትጨናነቂ መጥሪያ ሲደርሳት እዛው ትናዘዛለች አለኝ ። አማን ምኑን ልረጋጋ እሺ ምን እንዳደረጉት ምን አውቃለሁ  እኔ እኮ ነኝ ጦስ የሆንኩበት ምነው በእሱ ቦታ እኔን ባደረገኝ ብዬ አለቀስኩ ኸረ አንቺ ልጅ ምን እየሆንሽ ነው እኛ ሳናስብ ቀርተን ነው እኛ ሳንጨነቅ ቀርተን ነው ግን ማልቀስ ምንም መፍትሄ አይሆንም ጤና ስትሆኚ ነው ነገሮችን ምን ማድረግ እንዳለብሽ እንኳን መወሰን የምትችይው እኔ አይከፋኝም አብሮ አደግ ወንድሜ የት ምን ላይ እንዳለ ሳላውቅ ቆሜ ስሄድ ምንም የተፈጠረ አልመስልማ  ውስጤ ቢከስልም እሱን ማግኘት የምችለው ጠንክሬ ነገሮችን በጥንቃቄ ማድረግ ስችል ነው በሚል ነው አሁን እቤት ልሸኛቹ ይህቺን ትንሽ ልጅም ያለ እድሜዋ አታስጨንቂያት ለእናትሽም አስቢላቸው እንጂ ብሎ ተቆጣኝ እሺ አሙ እኔስ ምን ላድርግ አቅም ቢከዳኝ የማደርገው ባጣ እኮ ነው እንባ የሚቀድመኝ እሺ እንዳልከኝ ለመጠንከር እሞክራለሁ አልኩት ውስጤ እንደማይችለው እያወኩ እቤት ደረስን እሱ ወደ ናዲ ቤተሰቦች ተመለሰ ።  ወደ ጓዳ ገባሁና ጌታ ሆይ እኔ አቅም የለኝም ባለበት አንተ ጠብቀው አንዳች ክፉ ዜና መስማት አልፈልግም ብዬ ጌታ እግር ስር አለቀስኩ ። አማን ደወለልኝ..... .............ይቀጥላል......... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
Show all...
እውነተኛ የክርስቲያኖች ቻናል እነዝህ ብቻ ናቸው እናንተም ተቀላቀሉ
Show all...
1
🇪🇹 JOIN 🇪🇹
ሰላም ቅዱሳን በTELEGRAM ቻናል ተወዳጅ የሆኑትን በደረጃ አስቀምጠናል እናንተም JOIN በማለት በተሰብ ይሆኑ 🙏 ለማስታወቅያ ስራ👉@skat_kal
Show all...
YIKIRTYE
YE MEZMUR MAIKEL
KINE TUBE
MEZMUR CLUB
MERCY IN BERUA
SINETSUF BE WANGEL
WUNU PICTURE
JOIN US
.        🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘           #ክፍል30 ......መሞከር ጀመርኩ  በጭራሽ ስልኩ አይሰራም እንዳፈጠጥኩ ነጋልኝ ስልኩ አሁንም ዝግ ነው ወዲያው አማን ደወለልኝ አሙ ስልኩ ለሊቱን ሙሉ ዝግ ነው አሁንም እንደዚያው አልኩት ሰላምታም ሳልሰጠው አትጨናነቂ እፁ ምንም አይሆንም እኔ እቤት እሄድና ደውልልሻለሁ አለኝ የእርሱን ስልክ እየጠበኩ እዛው እንቅልፍ ወሰደኝ ። የተኛሁበት ክፍል በር ተከፈተ ተዐምር አትረብሺኝ ለሊቱን አልተኛሁም አልኩኝ በደከመ ድምፅ ምላሽ አልሰጠችኝም የእግሯ ኮቴ ቀረበኝ አጠገቤ ስትቆም ምን ፈልገሽ ነው ብዬ ብርድ ልብሱን ከፊቴ ላይ ሳነሳው ማሂ ነበረች በየሱስም አንቺ ምን ትሰሪያለሽ አልኩኝ አፍሽን ዝጊ ብላ አፈጠጠች የያዘችውን ትልቅ ሹል ቢለዋ እያሳየችኝ ። ማሂ ምን እያደረግሽ ነው እኔ እኮ ጓደኛሽ ነኝ አልኳት ከት ብላ ስቃ ጓደኛ እኮ አንቺ የኔ ጓደኛ የማይሆነውን ህይወቴን እንዳመሰቃቀልሽው ለዘላለሙ ናኦድን ወደማታዪበት አሰናብትሻለሁ ብላ ቢለዋውን ወደ ላይ አነሳችው ና ወደ ሆዴ ቁልቁል ሰደደችው ማሂ ብዬ ጮኹኩ ምንድነው በኢየሱስ ስም ተዐምርና ማሚ ነበሩ ምን አይተሽ ነው ። በርግጌ ስነሳ ምንም ነገር የለም ምን አይተሽ ነው አሉኝ ሰውነቴ በላብ ተጠምቋል እንጃ ማሚ ቅዠት አይሉት ህልም ብቻ መጥፎ ነገር ነው ያየሁት ናዲ ትናንት ከሸኘኝ ጀምሮ ስልኩ አይሰራም አማንም ደውላለሁ ብሎ ዝም አለ ብዬ በፍጥነት ፒጃማዬንም ሳልቀይር ክፍት ጫማ እንዳደረኩ ወደ እነ ናዲ ቤት  ሄድኩ የጊቢው በር  እስኪከፈት ነብሴ ተጨነቀች በሀይል ነበር የምደበድበው ታናሽ እህቱ በፍጥነት መጥታ ከፈተችልኝ እርሷም ከውጪ በጉጉት ምትጠብቀው ነገር አለ መሠል እኔ መሆኔን ስታይ ኤጭ ብላ ወደ ኋላ ተመለሰች ተከትለዋት ሙሉ ቤተሰቡና አማንም በረንዳውን ሞልተውት ነበር ። ናዲስ አልኩኝ ሁሉም አፍጠውብኛል ዝም አሉ ንገሩኝ እንጂ ናዲስ አልኩኝ አሁንም ዝም አማን ናዲስ ብዬ ጮኹኩኝ እናትየው አንቺን እንጠይቅሽ እንጂ ትናንት አንቺን ሊያገኝ ወጣ ከተባለበት መቼ ተመለሶ አሉኝ እንባ ባደከመው ድምፅ አማን ናዲ እዚህ የለም አልኩኝ አቅሜ ሲከዳኝ ይታወቀኛል እንባዎቼ እየረገፉ አዎን በለኝ ወይም ናዲን አሳየኝ አልኩት እፁ ተረጋጊ ነይ እስቲ ወደዚህ አረፍ በይ አለኝ ሰማይ ምድሩ ዞረብኝ እያኋቸው ሰዎቹ ብዥዥዥ ይሉብኝ ጀመር ። ከዚያ ራሴን ያገኘሁት የፈረደበት ሆስፒታል ነበር አጠገቤ ተዐምር ነበረች ግሉኮሱን ልነቅለው ስል ነርሶቹን ጠራቻቸው መሠለኝ ትንሽ ነው ይሄ ብቻ ይለቅ ብለው ከለከሉኝ ሆስፒታሉን በአንድ እግር አቆምኩት  ለእኔ አይታወቀኝም የናዲ ነገር ብቻ ነው የሚያሳስበኝ ለ4ሆነው ከአቅማቸው በላይ ስሆን መርፌ አምጥተው ወጉኝ በድጋሚ ስነቃ ጎረቤቶቻችን ነበሩ ግሉኮሱ ተነቅሎ ነበረ በፍጥነት ብድግ አልኩ ትንሽ እንደማዞር ሲያደርገኝ  አልጋው ላይ ቁጭ አልኩና ራሴን አረጋግቼ ተነስቼ ወጣሁ እፁ ተረጋጊ የት ነው የምትሄጂው አሁንም ትወድቂያለሽ እያለች ተዐምር ትከተለኛለች  እርምጃዬ ከአልጋ የተነሳ ሰው አልመስልም እልህ ና ንዴቴ ህመሜን አስረሱኝ ተዐምር አልቆም ስላት ከፊት ለፊቴ በሩጫ አልፋኝ ቆመች ዞር በይልኝ ብዬ ገፈተርኳት አሁንም ትከተለኝ ጀመር ጎረቤቶቻችን ለማሚ ደወሉላት መሠለኝ ደወለች ስልኬ ተዐምር ጋር ነበር ይኸው ማሚ ሰማችልሽ መሠለኝ እፁብ ቁሚ እያለከለከች ትለምነኛለች የሆስፒታሉ ርዝመት ከሀገር ሀገር ስደት ጉዞ መሠለኝ እንደወጣን ታክሲ ውስጥ ገባሁና ብር እንደያዘ ሰው ወደነ ማሂ ሱፐርማርኬት  እንዲነዳው ነገርኩትና ሄድን ተዐምር ብር ይዛ ነበር እንደወረድኩ ወደ ሱፐር ማርኬቱ በቀጥታ ገባሁ ተቀምጣ ስልኳ ላይ አፍጣ ነበር ብቻ በሁለት እጄ እንቅ አደረኳት ናዲን የት አደረስሽው አንቺ ክፉ የእስከዛሬው አንሶሽ ትንፋሽ አትሯት እንዴት ትተንፈስ የሱፐር ማርኬቱ ሰራተኞች እንደምንም አስለቀቁኝ ጥበቃ ኸረ የህግ ያለ እያለ አንዱ ሲንጣጣ ተው ብላ በእጇ ምልክት አሳየችው  እያሳለች መናገር ፈልጋለች ግን ደም ስሯ ተገታትሯል ከሞት አፋፍ ሳትመለስ አልቀረችም ። ተዐምር አንቺ እፁ አብደሻል እንዴ ሌላው ቢቀር ክርስትናሽን ረሳሽው አለችኝ ገላመጥኳት ና አንቺ ሰይጣን ናዲ የት ነው ያለው አልኩኝ መከረኛ እንባዬ እየረገፈ....... ............ይቀጥላል ........... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
Show all...
😱 16👍 8🥰 3😭 2
ሰላም ቅዱሳን በTELEGRAM ቻናል ተወዳጅ የሆኑትን በደረጃ አስቀምጠናል እናንተም JOIN በማለት በተሰብ ይሆኑ 🙏 ለማስታወቅያ ስራ👉@skat_kal
Show all...
👍 2
YIKIRTYE
YE MEZMUR MAIKEL
KINE TUBE
MEZMUR CLUB
MERCY IN BERUA
SINETSUF BE WANGEL
WUNU PICTURE
JOIN US
የዛሬው አጠር ስላለ 2 ክፍል ፖስቻለው enjoy it😊
Show all...
🥰 30👏 10👍 9 5
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘          #ክፍል_29 ........ድንግጥ ብሎ ቀረ ። ወዲያው ለማስቀየስ ማለት አለኝ ናዲ ብቻህን ለመጨነቅ እየሞከርክ ነው እኔ እድሌ ጠማማ ነው ባክህ ስንት ነገር አለፈ በቃ እፎይ ብዬ ሳላበቃ ሌላ ጣጣ ትናንት እህትህና እናትህ ሲጨቃጨቁ ሰምቼአቸዋለሁ አልኩትና በረጅሙ ተነፈስኩ በጣም ደነገጠ ፊቱ ልውጥውጥ አለ ምን እንደሚለኝ እንኳን ያጣ መሠለኝ ከእነርሱ ሀሳብ በላይ የእኔ መስማት አስጨነቀው ። አንዴ አፉን ይይዛል አንዴ ጭንቅላቱን ይይዛል ጭንቅንቅ ሲል  አሳዘነኝ ናዲ የኔ መስማት ከሆነ ያስጨነቀህ እሱ አያሳስብህ ። ከቤተሰቦችህ ጋር በእኔ ምክኒያት ባትጋጭ ደስ ይለኝ ነበር ግን ምን ማድረግ ይቻላል የኔ መዘዝ ሁሌም ላንተ እንደተረፈ ነው አልኩት ። ብስጭት ብሎ በሚያስፈራ አስተያየት አየኝ እኔና አንቺ መሀል የኔ ያንቺ ሚባል ነገር አለ እንደሱ እንዴት ታስቢያለሽ ደግሞ  እግዚአብሔርን አምነዋለሁ ቤተክርስቲያን እንኳን ምታውቀውን አይደለም ቤተ ክርስቲያን ራሱ ጌታ የሚያውቀውን የኔ ቤተሰቦች ቢሆኑ ብሩክ ቢሆን ማሂ ብትሆን ልፉ ሲላቸው ነው እድሌ ምናምን እያልሽ ይብሱን አታበሳጪኝ እግዚአብሔር ለእኔና ለአንቺ ስንት ነገር አላደረገልንም እንኳን ይህቺን ልጁን ሰጥቶን የለ ምን አስጨነቀሽ ለእርሱ እንተውለታለን በራሱ መንገድ ያሰማምረዋል አለኝ ተፅናናው ደግሞ አባቢ ራሱ እንዴት የተባረከች አስተዋይ ልጅ ነች ሲልሽ ነበር በጣም ነበር ደስ ያለኝ ማሚ መጥታ ደስታዬን አቀዘቀዘችው እንጂ ሁሉንም  ለምን እንዳደረገ ራሱ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ዝም ማለት ነው እሺ እፁዬ አለኝ ። አብረን እያለን ቴክስት ደረሰው መሠለኝ ይህቺ ልጅ ወሬ ከየት ነው ምታመጣው ጌታ ሆይ አለ የእኔም ስልክ የአዲስ የመልዕክት ድምፅ አሰማኝ ። ሳየው ብሩክ ነበር ስሚ አማች ይሆኑኛል ያልሻቸው ሰዎች አይኗን ላፈር አሉ ተባለ እና ምን ይሻልሻል መቼም ናኦድሽ በአንድ እናቱ እንደማይደራደር የታወቀ ነው ስሰማ እኔን ይመርጣል ብለሽ እንዳትሳሳቺ ይላል ። ይሄ ሰይጣን ብዬ ስልኩን ጠረጴዛው  ላይ ስወረውረው ምንድነው አለኝና ስልኩን አንስቶ አነበበው እኔም የእርሱን ስቀበለው ማሂ ነበረች ቤተሰቦችህ ያቺን መዘዘኛ ለቤቱ ክብር አትመጥንም አሉአ ገና ምን አይተህ የእኔ ግፍ 😂😂  ይላል እነዚህ አጋንኝቶች ምን አድርጉ ነው የሚሉን አሁንስ አበዙት ቆይ ባልሰራላቸው እንስሶች አልኩኝ ሳግና ንዴት እየተናነቀኝ እንዴ እፁ ስሜታዊ እየሆንሽ ነው የኔ እናት እንዴት ብትናደጂ ነው ከአንደበትሽ ክፉ ወጥቶ የማያውቅ መፅሀፍ ለሰነፍ እንደ ስንፍናው አትመልስለት ነው የሚለው እነርሱም የዘሩትን በሚያጭዱበት ጊዜ እኛም የዘራነውን መልካም እናጭዳለን እናቴ አትናደጂ በቃ ንቀሽ ተያቸው ስናወራ ስናወራ ሰአቱ ነጎደ እረ መሸ እኮ ተነሺ ብሎ እስከ እቤት አድርሶኝ ተመለሰ ። ከነማሚ ጋር ተጨዋውተን የተዐምርን ቡና ጠጥቼ ወደ ጓዳ ገባሁና አምላኬን አውርቼው ነገሬን አደራ ሰጥቼው መፅሀፍ ቅዱሴን አነሳሁ አንብቤ ስጨርስ ናዲ ሌላ ቀን በግዜ ነው የሚደውልልኝ ስደውልለት ስልኩ አይሰራም ለፀሎት ዘግቶት ነው የሚሆነው ብዬ ከአንድ ሰአት በኋላ ደወልኩለት አይሰራም ጌታ ሆይ ፍርሃት ፍርሃት አለኝ ለአማን ደወልኩና ከተኛበት ተነስቶ በደከመ ድምፅ አወራኝ አትጨናነቂ እኔ እደውልለታለሁ አለኝ ጠበኩ 30ደቂቃ አልደወለም አገኘኸው ብዬ ቴክስት አደረኩለት እፁ ይቅርታ ያልደወልኩት አስጨንቅሻለው ብዬ ነው ጠዋት እንሞክርለታለን ያው እሱ ረጅም ሰአት አይደል የሚፀልየው የተለመደ ነው ተኚና ጠዋት እንደውላለን አለኝ ። እኔ በየት በኩል እንቅልፍ ይውሰደኝ ደጋግሜ መሞከር ጀመርኩ...... ..........ይቀጥላል ........ @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
Show all...
👍 15🔥 2🥰 2😱 2
.     🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘          #ክፍል_28 .... ሸኙኝ ማሚና ተዐምር ከሱቅ አልገቡም ነበር መሄጃ የለኝ ጌታዬ ላይ ተነፋረኩኛ ጌታ ሆይ በእኔ ምክኒያት ይሄ ቤተሰብ ሰላም ማጣት የለበትም ናዲን ከተናገሩት በጣም ይጣላቸዋል እርግጠኛ ነኝ ከቤተሰቡ እንዲቂያቂያም አልፈልግም ያውም በእኔ ምክንያት ። መንፈስ ቅዱስ ከፋኝ አልኩት የተሰማኝን እየለፈለፍኩ ልክ ስሞታ እንደሚናገር ህፃን እርሱም ደግሞ አፅናናኝ ጭንቀቱን ረሳሁና ራሱን አየሁት ከቆይታ በኋላ ለናዲ ደወልኩለት አያነሳም በቃ ለጌታ ሰጥቼ ተኛሁ ከረጅም ደቂቃዎች በኋላ ደወለልኝ ። እፁዬ ይቅርታ የሆነ ጉዳይ ይዤ ነበር አለኝ በቃ ሲጨቀጭቁት ነበረ ብዬ ገባኝ ድምፁ ተረብሾ እንደሆነ ያሳብቃል ምን እንደሆነ መጠየቅ ሁሉ አስጠላኝ ገብቶኝ ለምን እንዳልገባው ሆናለሁ ብዙም አላወራንም ስልኩ ተዘጋ ። ማሚ  እንደመጣች ፊቴን ነው የምታየው ግንባሬን ነው የምትስመው ምንድነው ፊትሽ ምን ተፈጠረ አለችኝ እንደገና ተነፋረኩባታ ብዙ መከረችኝ አትፍሪ ጌታ ከእናንተ ጋር ከሆነ አይደለም ቤተሰቡ ሙሉ የአለም ህዝብ ቢያድምባቹ ምንም አይፈጠርም ለበጎ ነው የኔ ቆንጆ ልጅ አለችኝ ። በጠዋቱ ተነስቼ እቤት መስራት ያለብኝን ሁሉ ሰራሁና ናዲን አገኘሁት በጣም ተረብሾ ተጨናንቋል ምን እንደሆነ ብጠይቀው አልጋገር አለ ነው በድብብቆሽ  ነው ቸምንቀጥለው ስለው ትንሽ ከቤት ተጋጭቼ ነው አለኝ በምን አልኩት ሊያለቅስ ደረሰ አንቺ አታውቂውም የቤተሰብ ጉዳይ ነው አለኝ እየከፋው በእኔ ምክንያት ነዋ አልኩት ድንግጥ ብሎ ቀረ...... ...........ይቀጥላል ........ @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
Show all...
👍 18
.        🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘           #ክፍል_27 እሁድ እቤታቸው ተጋብዣለሁ  ቀናቶች አልሄድ ብለውኝ ስጓጓ ከርሜ አይደርስ የለ ቀኑ ደረሰና ያስደስታቸዋል ብዬ ያሰብኩትን አለባበስ ለብሼ ሄድኩኝ ናዲና አማን ነበር ይዘውኝ የሄዱት እቤታቸው ተውቧል እነርሱ አምረውና ደምቀው ነበር የጠበቁን የምግቡ ና የቡናው መዐዛ ቤቱን ድግስ ቤት ድግስ ቤት አሰኝቶታል እነዚህ ሰዎች በዚሁ ሊያስቀሩኝ አስበው ነው እንዴ ናዲ አልኩት ፈገግ አለና እኔም አልገባኝም እስቲ እንጠይቃቸዋለን አለኝ ሁሉንም በየተራ ሰላም አልኩ ሁለት እህትና ሶስት ወንድም አሉት አንዷ ታላቁ ስትሆን አንዷ ታናሹ ነች አንዱ ታላቁ ሲሆን ሁለቱ ታናናሾቹ ናቸው ። አባትየው ፈገግታቸው በቂ ነው እንደ በረዶ የነጣው ፀጉራቸው ና ፂማቸው ልዩ ውበትን ችሮአቸዋል አባትህ ደስ ሲሉ እኮ ውበታቸው ከፊት ይልቅ ጨምሯል እውይ ፀጉራቸው ገፅታቸው ሲያምር አልኩት እኔም በእርሱ እኮ ነው የወጣሁት አለኝ ጉረኛ የሳቸውን ያክል እንኳን አታምርም አልኩት አማን ቀስ ብሎ እናንተ ምን ትንሾካሾካላችሁ በጋራ ከቤተሰቡ ጋር አታወሩም እንዴ አለን ፋዘርን ካየኋቸው ቆየሁ ለዛ እኮ ነው አልኩት ። ለዛ ያለው ጨዋታ እየተጨዋወትን ቆየን ናዲማ የማላውቀው ናዲ ጨዋ ሆኖ አረፈው በጣም ነው የሚያከብራቸው ከጌታ ቀጥሎ  ለቤተሰቡ ባለው ክብር አይደራደርም ። ሴቶቹ  እየተንጎዳጎዱ ያስተናግዱናል  ። እናትየው በየመሀሉ እየተነሱ ይመለሳሉ ምን ጎደለ ብሉ ጠጡ ይሉናል ። መፀዳጃ ቤት መሄድ ፈለኩ ና አንዷን እህቱን ስጠይቅ ወደ ውስጥ እለፊ አለችኝ ። በግምት እየሄድኩ ጆሮዬ ውስጥ ሚሰቀጥጥ ወሬ ዘለቀ እርምጃዬን ገታ አድርጌ ቆምኩ አሁን የኔ ልጅ ሴት አጥቶ ነው እናቱ ነበሩ እማዬ ዝም በይ በጥልቀት ስለማታውቂያት ሴት እንዴት እንዲ ታወሪያለሽ ። አፍሽን ዝጊ ገና በ12ኛ ክፍል አልነበር እንዴ ልታገባ የነበረው የአሜሪካ ዳይስፖራ አስጠልቶት የተዋትን የኔ ልጅ በምን እዳው ነው? ገና ያለ እድሜዋ አይደል እንዴ መቅበጥ የጀመረችው እኔ  ስንት ነገር ቸርች ውስጥስ እንደተወራ አታውቂም እኔ በህይወት እያለው ልጄ እሷን አያገባም እንዴት እስከዛሬ አትነግሩኝም ወይኔ ዘውዲቱ እናትና ልጅ ይጨቃጨቃሉ እዛው አዙሮ ሊጥለኝ መከረኛ እንባዬ እርግፍ እርግፍ አለ  ከኋላዬ የእግር ኮቴ ሲሰማኝ ቶሎ እንባዬን ጠራረኩና ወደ ኋላ ተመለስኩ እፁዬ ግቢ አለችኝ ታናሹ ሊዲያ ነበረች ተመልሼ ተቀመጥኩ ። የሚያወሩትን ሁሉ አልሰማም ድንዝዝ ብዬ እነዚያን ቃላቶች በድግግሞሽ ያቃጭሉብኝ ጀመር አይደል እንዴ የኔ ልጅ አሉ አባቱ ህህህ ብዬ ከሄድኩበት የሀሳብ ማዕበል ተመለስኩ ልክ አይደለሁ ወይ አሉኝ ኸረ ልክ ኖት አልኩኝ ምን እንዳሉም ሳልሰማ እናትየው ተመልሰው መጥተው ተቀመጡ ሳያቸው አልቅሽ አልቅሽ አለኝ ሰው እንዴት በቀድሞ ማንነቱ ይለካል  ለነገሩ ጥሩ ስራ መልካም ነገር በህይወቴ ሆኖ ቢያልፍ ማንም አያስታውሰውም ነበር ሳልፈልገው በህይወቴ ለተፈጠረ ያውም እኔን ጎድቶ እኔን ሰብሮ ላለፈ ጉዳይ በየጊዜው መልኩን እየቀያየረ ያሰቃቸኛል ። ምን ሆነሻል ልክ አይደለሽም አለኝ ናዲ ደህና ነኝ አልኩ ሊወርድ ጥቂት የቀረውን ዕንባ ዋጥ ለማድረግ ከውስጤ ጋር ትንቅንቅ ገጥሜ ኸረ እፁብ አትዋረጂ ዋጪው ዋጪው ራሴን አበረታው ዘንድ ሞከርኩ  እንዴ አመመሽ እንዴ አለኝ ኸረ በጭራሽ ዝም ብዬ ነው አልኩት ። ወጥተሽ ጥፊ ጥፊ አሰኘኝ መከረኛዋ እናቴ እቅፍ ውስጥ መሆን አጓጓኝ ከመች መች ደረሰ ብዬ የጠበኩትን ቀን በምን ቀን እዚ ቤት መጣሁ ለማለት አበቃኝ እየመሸም ስለነበር አባትየው ከመፅሐፍ ቅዱስ ክፍል አካፈሉን ። የፈራኸው አይወርስህም በሚል ርዕስ አሁን ይሄ መልዕክት ለእናትየው ነው ለእኔ ነው ግራ ግብት ብሎኝ አሜን አንኳ እንዴት ልበል ተሳሰርኩ እናትየው አሜን አይወርሰኝም ቤቴ አይገባም እያሉ ይቀበሉ ነበር ግራ ግብት እንዳለን ፀልየውልን ናዲና አማን ሸኙኝ....... ........ይቀጥላል .......... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
Show all...
😢 26👍 11😁 3 2
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘            #ክፍል_26 .....እኮ እንዴት አልኩት በጣም በረጅሙ ተነፈሰና ጓደኞችሽ ደወሉልኝና በጣም መታመምሽን ነገሩኝ  የእውነት በራሴ በጣም ነበር የተናደድኩት እውነት ቢሆን ኖሮ እንኳን በቃ ስላልቻልኩ ልደውልልሽ ነበር ልክ ልደውል አልደውል ስታነሳ ምን ብዬ ልጀምር ይቅርታ አድርጌልሻለው ልበላት ወይስ እስክትደውል ጠብቄ ኮስተር ብዬ ላውራት እያልኩ ከራሴ ስሟገት አቤል ደወለልኝ በቃ ደስ አለኝ እንደሌላ ቀኑ በሰው ስልክ ደውላ ነው ብዬ አነሳሁት ሲነግረኝ እየቀለደም መስሎኝ ነበር ጭራሽ ራሷን ስታ አልነቃ ብላለች ሲለኝ ምሆነውን አጣሁ።   ደስ እያለኝ በፈገግታ ተመስጬ ስሰማው  ንግግሩን አቆመና ኸረ አትመሰጪ በቃ አላወራም አለኝ እሰይ ተጋደልናታ ብዬ ስኮሳተር ስቀልድ ነው ከዚያ የእግዚአብሔር ነገር ዝም ብዬ ብቻ ተነስቼ ልመጣ ስል አማን ደወለልኝ የት ን ደብሮኛል አለኝ ነገርኩት ደስ አለው በጣም እኔ ተናደድኩ ታማለች እያልኩህ ምን ሆነሀል ብዬ ስጣላው አይ ደስ ያለኝ ሰላም ሊወርድ በመሆኑ ነው ስጠብቀው ነበር አለኝ እኚህ ሰዎች አውቀው ነው እንዴ አልኩና ከሆነም ይሁን ብዬ ስነሳ በቃ አብረን እንሂዳ አለኝ መጣን የእውነት ባላይሽ ይሻለኝ ነበር በቃ ራሴን ይቅር አልለውም ነበር አለኝ ። ወሬ አታብዛ ወደዛ የፊልም አክተር አክተር አትጫወት አልኩት ጉዱ መች አለቀና አለኝ የምኑ ስለው አቤል ለአንቺ ሲል የማሂን የሶሻል ሚዲያዎች ሰርች አድርጎ ማውራት ከጀመሩ ሰነባብተዋል ለእኔ እንዳለኝ የድሮ ማንነቴን ተጠቅሜ ሙሉ እምነቷን ስትጥልብኝ ምንም አትደብቀኝም ብሎ የተፃፃፉትን አሳየኝ የእኔና የአንቺ አብሮ መሆን ሰላም እንደሚነሳት ከብሩክ ጋርም አብረው እንደሚያሴሩ ነገረችው ። ራሴን ጠላሁት ከአንቺ ይልቅ እነሱን አመንኳቸው ለስቃይና በሽታ ዳረኩሽ ክፉ ነኝ አይደል  እውነት ቢሆን እንኳን የስንት ቀን መልካምነትሽን በአንድ ጊዜ ስህተት ቀየርኩት እንዴት እንዳስቻለኝ ራሱ ይገርመኛል ጨካኝ ነኛ ?አለኝ ሳላስበው ለካ እየተነፋረኩ ነው  ቁስሌን አስታወሰኝ  ግን አሁን በዚያ ከመከፋት ይልቅ በጊዜው በሆነው መልካም ነገር ማመስገን ይሻላል ብዬ እምባዬን ጠራረኩኝ እፁ ይቅርታ የምልበት አቅም ራሱ የለኝም ምን እንደምልሽ ራሱ ሲል እንግዲ አታሽቃብጥ በቃ ያለፈው አልፏል በራሴው ታሪክ እንደ አሰለቃሽ ፊልም ልታስለቅሰኝ ነው እንዴ ብዬ ፈገግ አልኩ ። ከዚህች ከማሂ ጋር ግን ብዙ ማወራው ጉዳይ አለኝ በቁጭት ነው የሚያወራው እንግዲ አታናደኝ በቃ ንቆ መተው ነው አይሻልም ሰላም ለምን እናጣለን አማን በሩን ከፍቶ ገባ እናንተ ልጅቷ ማረፍ ሲኖርባት አፍጣቹ የሆድ የሆዳችሁን ታወራላችሁ ብሎ ተቀመጠ በል ሂድ አረፍ በል እኔ እጠብቃታለሁ አለው በስልኬ ሰአት ሳይ 10ሰአት  አዎ ሂድ አልኩት ግደሉኝ ከዚህ አልሄድም አለ ከደረቀ ስለማይሰማ ተውነው  ስለ እግዚአብሔር መልካምነት በሚገርም አገላለፅ ይሰብከን ጀመር አማንም በተራው ሲያወራ እንዳፈጠጥን ነጋ  እነ ሊዩም መጡ  ህክምናዬን ጨርሼ እንድወጣ ተፈቀደልኝ ። ጌታን አያመሠገንን ወጣን አቤሎና ሊየን አመሠገንኳቸው የራስ ሰው አይመሠገንም አለች ሂዩ ። እነ ናዲም ያን ቀን ሆቴል አርፈው ስራ ስለሚስተጓጎልባቸው ተመለሱ ። ቀኖች እየገፉ አመቶች እየተተካኩ ልመረቅ ደረስኩ በየእረፍቱ እነ ማሚ ጋር እየተመላለስኩ የብሩክ ዛቻና ጭቅጭቅ ሳይቆም የማሂም ሴራ ሳይቆም እግዚአብሔር እየረዳን ብዙ ቀናቶች አለፉ ሊዩና አቤሎም የሶስታችንም ጓደኝነት እንደተጠበቀ ሆነ እግዚአብሔር ከረዳቸው መጪ አመት የመጋባት እቅድ አላቸው ፊተኞች ኋለኞች ይሆናሉ እያሉ ያስቁኛል ቆይ በምን ልትኖሩ እያልኩ ሳናድዳቸው ከቤተሰቦቼ ጋር እሰራለሁ እሷ ምን በወጣት ደግሞ ተመርቀንስ ስራ የለ ማለት የሁሌ ንግግሩ  ነው አቤሎ ለቤተሰቡ በቸኛና የሀብታም ልጅ ነው ። የማይደርስ የለ እግዚአብሔርም ጤናችንን ጠብቆ ሰላማችንን ጠብቆ በድካማችን አግዞን ተመረቅን ማሚና ናዲ ተዐምር አማን መጥተው አስመረቁኝ የአቤሎና የሊዩ ቤተሰቦችንም በደንብ ተዋውቀናል ቤተሰቦቻችንም እርስ በእርስ ተዋውቀው አዳማ ላይ ደስ የሚል ግዜ አሳለፍን ከሊዩና አቤሎ ተለይቶ መኖርን ደግሞ ልጀምር ነው አሰንደእነርሱ መልካም ጓደኛ በዘመኔ ገጥሞኝ አያውቅም ። እንደዋወላለን ረጅም ሰአት አወራቸዋለው በቃ ቢከፋኝም ተላቅሰን ከተለያየን ቀን ጀምሮ እየኖርኩት ነው ያለ እነርሱ ። እንግዲ ተመርቆ ወዲያው ስራ የለ ከማሚ ጋር ንግዱን አጧጥፈው ጀመር ጀግናዋ እናቴ ከትንሹ ተነስታ ትልቅ ወደ ትልቅ ሱቅ አሳድጋዋለች ። በጅምላ ብቻ እቃዎችን ታስረክባለች ። ብሩክ ተብዬው አሁን ድር ይደውላል አላነሳም እርሱም ተስፋ አይቆርጥም ማሂ ስታየኝ እንኳን መንገድ ትቀይራለች ። የናዲ እህትና ወንድሞች ስለእኛ ቢያውቁም እናትና አባቱን እንድተዋወቅ እሁድ እቤታቸው ተጋብዣለሁ ........ ..........ይቀጥላል........... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
Show all...
🥰 28👍 16