cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

ስነፅሁፍ በወንጌል - Gospel Literature

◉ውድ የዚህ ቻናል ቤተሰቦች በዚህ ቻናል ላይ ፦ ➫ #አጭር_እና_ረጅም_ልብወለዶች ➫ #መንፈሳዊ_ተውኔት ➫ #መንፈሳዊ_ትረካዎች ➫ #መንፈሳዊ_ፅሁፎች ➫ #መንፈሳዊ_መነባነቦች ➫ #መንፈሳዊ_ድርሰቶች_ያገኛሉ። ለአስተያየት ጥያቄ 👉 @wunu_pa አጋር ቻናል 👉 @zema_sink 👉 @wunuye_picture Since Thursday 11-9-2014-

Show more
Advertising posts
9 973Subscribers
+3424 hours
+767 days
+61630 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘          #ክፍል_17 .......አላስጨረስኩትም ኸረ በጭራሽ ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ሲያየኝ ማለት እንደዚ ከቀለደብኝ ሰው ጋር የኔ ልብ ምን ይሰራል ። እነዚያ ግዜያት ታውሰውኝ ነው እንጂ ምንም አስቤ አይደለም የደበረኝ ሰዓቱ እኮ ሄዷል ለምን ወደ ቸርች አንሄድም አልኩት ምን እንደሚያርበተብተኝ ባይገባኝም ማወራውም ማስበውም ግራ የሆነ ነገር ነው ። እሺ ጥያቄዬስ ይኸው ለረጅም ግዜያት መልስሽን እየጠበኩ እፁብ አላሳዝንሽም አለኝ ወይኔ እንባ ተናነቀኝ ምንም ምናገርበት አቅም አጣሁ ፍርሃት ደስታ ስጋት አንደበቴን ቆላለፉት ለረጅም ደቂቃ ዝም አልኩና ራሴን ማዳመጥ ፈለኩ ውስጤ አንቺ ምን አይነት ሰው ነሽ ፀልየሽ አለቃቅሰሽ አሁንም የፀሎትሽን መልስ ልትገፊው ነው ምንም አትግደርደሪ  ይለኛል አንዴ ደግሞ ኸረ ሴት ልጅ እኮ ነሽ ወዲያው ስትነግሪው ይንቅሻል አንዴ ደግሞ ይሄ ሁሉ ጊዜ ጠበቀሽ ቢያንስ ጌታን ፍሪ ልክ ሰው እንደሚናገረኝ ከራሴ ሀሳብ ጋር ክርክር ገባሁ በመጨረሻም የመጨረሻ ቆርጦ ሀሳቡን የቀየረ ቀን እሮሮ ከማበዛ እነግረዋለው በሚለው ወሰንኩ ና በረጅሙ ተነፈስኩ እፁብ የዚህን ያክል የሚያስጨንቅሽ አልመሰለኝም ነበር ተይው በቃ ወደ ቸርች እንሂድ አትጨናነቂ አለኝ አንጀት በሚበላ ድምፅ ለመሄድ ከተቀመጠበት ሲነሳ ናኦድ አልኩት ግራ በመጋባት አይነት አስተያየት አየኝ ተቀመጥ አልኩት ትንፋሼን እየሰበሰብኩ ያነሳውን ስልክ መልሶ አስቀመጠና ተቀመጠ እውነት እነዚያ ግዜያት  ቀጥተውኛል እንደ አንተ አይነት ጌታን የሚፈራ፣ መልካም ፣ትሁት ፣ቅን ከዚህም በላይ የሆነ ሰው ማግኘት ዕድል ብቻ አይደለም እግዚአብሔር ለወደደው የሚሰጠው ስጦታ እንጂ የሴትነት ወጉ ይዞኝ እንጂ ጊቢ ባሳለፍኩአቸው ወራቶች ከዚያም በፊት ሁሉ ድጋሚ ጥያቄውን እንድታነሳልኝ ስሻውም ስፀልይበትም ነበር አሁን የፀሎቴ መልስ ነህ ማለት ነው አልኩት እያየሁት የፊቱ ፈገግታና ወገግታ ጨመረ እፁ እየቀለድሽ አይደለማ አለኝ ሁኔታው ፈገግ ያሰኛል ኸረ አንተ ልጅ ራስህን ግዛ እየሳኩ ። ከተቀመጠበት ተነስቶ አቀፈኝ የተቀመጥንበት ካፌ የሰዉ ብዛት አንተ ትኩረት እየሳብክ ነው ብዬ አረጋጋውት ደስታ ፊት ቢኖረው በእርሱ ይገለፅ ነበር ከአንቺ ጋ ገና ብዙ ማወራው ነገር አለ በይ ተነሽ ጌታዬን ላመስግንበት ወደ ቸርቻችን አለኝ ሲገረም ሲለፈልፍ ሲቀባጥር በሁኔታዎቹ ፈገግ እያልኩ ቸርች ደረስን እግዚአብሔር ድንቅ ና መልካም ጊዜ ሰጥቶን በቃሉ መክሮን በዝማሬ አረስርሶን እንደለመድነው ማሂ እና ሌሎች የቸርቻችን ልጆች ተሰባስበን ወደ ቤት ገባን ። ደስ ስላለኝ የሆነ ማወራለት ሰው ፈለኩ ደግሞ ከእናቴ ምደብቃት ነገር ስለሌለ ከጅምሩ አንስቼ እስከ ፍፃሜው ተረኩላት እና በጣም ተደሰተች የኔ ልጅ አሁን ገና መልካም ሰው ገጠመሽ አልዋሽሽም በቁም ነገር ልጄ ከዚህ ሰው ውጪ ሌላ ሰው ላይ እንዳትወድቅ ብዬ ጌታን ለምኜው ነበር ፀሎቴን ለሰማ ለእግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይሁንለት ብላ እልል አለች ። ተዐምርም ማሚ ድሮም እኔ ጠርጥሬ ነበር እኮ አለቻት አንቺ ልጅ ኸረ እባክሽ ቀስ ብለሽ እደጊ ማሚ አቺን ልጅ አንድ በያት እንጂ አልኳት ተይ የኔ ልጅ እሷ ለአንቺ ብላ እንጂ የኔ ልጅ ስርዐት አልባ ሆና አይደለም አለችኝ ና ተሳሳቁ ተጋገዛቹ ማለት ነው አልኳቸው አዎና ለአንቺ ናኦድ አለልሽ እኛ እርስ በእርስ ብንተጋገዝ አይሻለንም አለችኝ ፈገግ አልኩና ። ወደ ጓዳ ገብቼ ፀልዬ መፅሀፍ ቅዱስ አንብቤ ስነሳ ናኦድ ደወለልኝ ረጅም ሰአት ተወራሁት እና ተኛሁ ። የፍሬሽ ነገር ልክ ለዐመታት አይቼው እንደማላውቅ ሲነጋ እስካገኘው ጓጓሁ ለማሂ እንነግራታለን ብሎኝ ስራ ከመግባቱ በፊት ማሂን ልናገኛት ወደ ተለመደው ካፌ ሄድኩ... .......ይቀጥላል ...... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
Show all...
👍 11🏆 1
.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘          #ክፍል_16 .......ደንዝዤ ቀረሁ የዚያን ቀን ያዘንኩት ሀዘን የተሸማቀኩት ስሜት  የተዋረድኩት ውርደት ታወሰኝ ደግሞ ምን ሊሆን መጣ በሀሳቤ የኋላ ታሪኬን በሙሉ ቃኘሁት እንባዬ እየወረደ ነው ተዐምርም ናኦድም ተደናግጠው ከተቀመጡበት ተነስተው ተጠጉኝ ምነው እፁ ማነው የደወለው ? ምን ሆነሽ ነውበየተራ በጥያቄ ያጣድፉኝ ጀመር በተለይ ማሚ ይህንን መስማት እንደሌለባት አውቃለሁ ተዐምር ሰማች ማለት ደግሞ እናቴ ጋር መድረሱ አይቀሬ ነው የሆዴን በሆዴ እንደያዝኩ በዝምታ ተዋጥኩ የዚህኔ ለጥያቄው መልስ አልሰጥ ባይነቴ ያሰለቸው ናኦድ ስልኬን ተቀብሎኝ መደወል ጀመረ ። ሄሎ በዚህ ስልክ ተደውሎ ነበር አለ ቀጥሎም አዎ የእርሷ ነው ስልኩ ግን አንተ ማነህ አለው የብሩክን ምላሽ ባልሰማም የሆነ ነገር ግን ብሎታል ስልኩን ዘጋው ና እርሱም እንደ እኔው ቁጭ አለ እእእእእ ምንድነው አለች ተዐምር በተራው ወደ እርሱ እያፈጠጠች ዝም አላት እናንተ ሰዎች ደዋዩ አንደበት የሚቆልፍ ነው እንዴ ምን እየተካሄደ ነው ብላ ስትሄድ ተዐምር አልኳት እእእ ብላ ዞረች ዝም ብዬ አየኋት ምንድነው የሆንሽው እፁብ ነው እማዬን ልጥራት አለች እንዳትነግሪያት አልኳት ለምን አለችኝ በቃ አይመለከትሽም ምንም ነገር ብትነግሪያን የእውነት እንጣላለን አንቺ ህፃን አይደለሽም አልኳት ። አሁን ልጅ ነሽ ምናምን ስትይ አልነበር እንዴ የምን መገለባበጥ ነው ሲጀመር ምኑን ነው ምነግራት ስልክ ተደውሎላት ልሳኗ ተዘጋ ከዚያ ናኦድም በዚያ ስልክ ደውሎ ተለጎመ ይህን ነው ምነግራት ሆሆሆሆ እያለች ወጣች ሁኔታዋ ፈገግ አደረገኝ  ናኦድ አቀርቅሮ ምን እንደሚያስብ ባላውቅም በዝምታ ተውጠናል ። አንድም ሳናወራ በየመሀሉ ገዢ ሲመጣ እያስተናገድኩ ለሰአት ተቀመጥን ። ዝምታውን ለመስበር መሠለኝ እኔ የምለው ለምን ደነገጥሽ አለኝ በረጅሙ ተነፈስኩ ለምን አልደነግጥም እነዚያን ግዜያቶች ማስታወስ አልፈልግም ነበር ደግሞ ምክኒያቴን ላስረዳሽ ላግኝሽ ምናምን ይላል እንዴ ደፍረቱ አንተ ግን ለምን ደነገጥክ አልኩት ምላሽ አልሰጠኝም ዝም አለና ግን በቂ ምክኒያት ካለው ተቀብለሽው አብረሽው ትሆኛለሽ አለኝ እየቀለድክ ነው አልኩት በዚህ ይቀለዳል አለኝ ኸረ ጭራሽ እንዳታስበው አልኩት ማሚና ተዐምር መጡ እናንተ አስሬያቹ ጠፋው አይደል ይቅርታ ናኦድ ልጄ በሉ ተዐምር ቡና ታፍላላችሁ እቤት  ግቡ አለችን ኸረ ማሚ ያው አይደል እንዴ ውጪ ማኪያቶ እንጠጣለን በዚያውም ወደ ቸርች ስለምናልፍ አልኳት እሺ ይሁን ታዲያ በግዜ ተመለሺ የኔ ልጅ አለችኝ ወጣን ። እኔም በራሴ ሀሳብ እርሱም በራሱ ሀሳብ ተውጠን ፊት ለፊቱ ያለውን የማኪያቶ ብርጭቆ ያለማቋረጥ ያማስለዋል ኸረ አንተ ልጅ ልትቀደው ነው እንዴ ብዬ ፈገግ አልኩ  ቆይ ምን እየሆንክ ነው እኔ ራሱ እንደ አንተ አልተጨነኩም ነው ሌላ ምክኒያት አለህ ከእኔ ጉዳይ ውጪ አልኩት ምን ይኖረኛል አለኝ እና ተረጋጋ በቃ እኔን ለማስረሳት እንደ መሞከር ይባስ ታስጨንቀኛለህ እንዴ አልኩት ዕፁ ሰለቸኛ አለኝ ምኑ አልኩት ባንቺ ምክኒያት የሚፈራረቁብኝ ህመሞች እነዚያን የምትጠይኝን ግዜያቶች በስንት መከራ አልፈው አሁን ደግሞ ያውም ልታገቢው የነበረ እጮኛሽ ሲመጣ ደነገጥኩም ደስ አለኝም ግራ ገባኝም የሆነ በአንድ ግዜ የተደበላለቀ ስሜት ተሰማኝ  እንዴ ሀሳብህን የቀየርክ መስሎኝ አልኩት ። ለምን እቀይራለው እግዚአብሔር እንደማይዋሽ እኮ አይደለም እኔ ልጁ አጋንንት እንኳን ያውቃሉ ጊዜው ይርዘምም ፈተናው ይብዛም ያለኝ ነገር እንደሚፈፀም አንዳች ታክል አልጠራጠርም ምን አልባት አሁንም ልብሽ እዛ ይሆናል አላስጨረስኩትም ኸረ በጭራሽ አልኩ........ ...........ይቀጥላል........... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
Show all...
🥰 23👍 8 6🏆 4😁 2
.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘            #ክፍል_15 .....እንቅልፍ ከየት ይምጣ ስገላበጥ አድሬ በጠዋት ከማሚ ጋር ቁርስ ሰርተን አብረን በላን ቤተሰቦቼ አንዳች ሳይሆኑ የጠበቀልኝን ጌታ እያመሠገንኩ እንደዛ የጓጓሁለትንም ቀጠሮ አስረስተውኝ ከማታ የቀጠለ ወሬ እየተወራ ናኦድ ደወለልኝ ወይኔ ማሚ ምን አይነት ሰው ነኝ ብዬ ስደናገጥ ምነው አሉኝ ሁለቱም በቶሎ ልብስ ቀያይሬ ወጣሁ ። የተቀጣጠርንበት ካፌ ስደርስ ተቀምጧል አሁንም በሰአት ጉዳይ አይደራደርም ማለት ነው እያልኩ በውስጤ አጠገቡ ደረስኩ ። ሰላምታ ተለዋወጥን አረፍ አልኩ የሆነ ነገር ውሰጂ አለኝ ኸረ ከቤት አይደል የምመጣው ብዬ እምቢ አልኩ የግድ ሲለኝ ወተት አዘዝኩ አቤት ጉዳዩን ለመስማት ካለኝ ጉጉት የተነሳ የሚያወራቸው ወሬዎችና ጥያቄዎቹ ትርጉም አልባ ሆኑብኝ ከረጅም ደቂቃዎች ወሬ  በኋላ እና እፁብዬ ወደ ዋናው ጉዳዬ ስመጣ እእእ በነገርሽ ላይ ማሂ በጣም ትለያለች ትህትናዋ መንፈሳዊነቷ ብስለቷ ምን ልበላት በአጠቃላይ ልባም ሴት ብትባል አይበዛባትም ሙሉ አካሌ ሲዝለፈለፍ ይታወቀኛል ተመሳስጦ ማውራት አልጀመረም እንዴ ናኦድ ምን ሆነሀል ስለ ጓደኛዬ ባህሪ እንደ አዲስ ልትነግረኝ  ነው አልኩት ኦው ይቅርታ እና ምን ልልሽ ነው ሰርፕራይዝ ላደርጋት አሰብኩና አንቺ ታስፈልጊኛለሽ አለኝ የሆነ ነገር እንደ መታው ሰው አናቴ የተከፈለ እስኪመስለኝ ደነገጥኩ ጌታ ሆይ ውሰደኝ አልኩ በእኔ ቤት በውስጤ ነው ግን ሳላውቅ አውጥቼዋለሁ ለካ እንዴ ወዴት ብሎ ፈገግ አለ መልሼ በሆዴ ወደ ራሱ ነዋ ምን ቀረኝ አልኩ ቀለበት ሊያስርላት ሆኖ ብቻ ጨርቄን ሊያስጥለኝ ባልሆነ እያልኩ ክፍት አለኝ ቆይ እንዴት ሳትነግሩኝ ግን አልኩት ። እንዴ እስከ አሁን እንዴት አታውቂም አለኝ ካልነገረችኝ በምን አውቅልሃለሁ አልኩት ዕንባ እየተናነቀኝ እናንተን ብሎ ጓደኛሞች ያውም ሁለታችሁም ሴቶች ሆናችሁ አለኝ ማሂ ግን እንዴት ደበቀችኝ ብዬ ገረመኝ ለነገሩ ቀና ቀናውን ባስብስ ትምህርት ላይ ሆኜ እንደዚህ አይነት ወሬ ምን ያደርግላታል ብላ ይሆናላ አልኩት እንዴ እንደዚህ አይነት ወሬ ስትዪ ማለት በዚህ በጥቂት ግዜ ፍቅር ጀመርን ማለት ከብዷት ይሆናላ  አልኩት ። ምን ብሎ ሳቀ ምን አለብህ ሳቅ የኔን የውስጥ ለቅሶ ባየህልኝ አልኩ በሆዴ ማውራት እስኪያቅተው ይስቃል አንተ ልጅ ጤነኛ አይደለህም እንዴ ምንድነው የሚያስቅህ ዞር ዞር እያልኩ ከኋላ ከጎን የተቀመጡ ሰዎችን  እየቃኘሁ አንቺን ልጠይቅሽ እንጂ የምን ፍቅር ነው ምታወሪው አለኝ ሳቁን እንደ ቀጠለ እና ሰርፕራይዝ ልባም ሴት ምናምን ያልከኝ እራስህ አይደለህ እንዴ ይብሱን ይስቅ ጀመር አንቺ ልጅ ይሄ የዋህነትሽ እኮ ነው የሚገርመኝ ገና ተናግሬ ሳልጨርስ ከእህቴ ጋር አፋቅረሽኝ አረፍሽው ምንም አልልም ጌታ ይቅር ይበልሽ እፎይ አልኩ በአንዴ ፊቴ ወደ ደስታ ሲቀየር እየታወቀኝ ባክሽ ዛሬ ልደቷ ነው እሱን ነበር አታውቂም ያልኩሽ አለኝ ወይኔ እኔ ምን አይነተሰ ሰው ነኝ ጌታን ረስቼዋለሁ አልኩት እና አሁን ደውይላት አለኝ ። ደውዬ አወራኋት እና እቤት የሚገርም ዝግጅት አድርገን ማሚ አሞኛል ብላ እንድትጠራት አደረግን በጣም ነበር ደስ ያላት የገዛንላትን ስጦታ ሰጥተናት ደስ የሚል ግዜ አሳለፍን አባቷ ደውሎላት እሷ ሄደች ማሚን እረፊ ብለናት ልጀንም ስራ አስፈትቼ ሱቅ ቁጭ አልን ። ቅድም የቀባጠርኩት ትዝ እያለው ይስቃል ከዚያ ለተዐምር ነገራት እና ሳቁብኝ  ሂድ እዛ ጥርሳቹ ይርገፍ የእውነት ግን ከፍቶኝ ነበር አልኩት እና ደነገጥኩ እንዴ ለምን አለኝ ምለው ጠፍቶኝ እንትን ስላልነገራቹኝ ነዋ አልኩት ተዐምር ኸረ እፁ አትዋሺ ቀንተሽ ነው አለችኝ ሂጂ አንቺ ልጅ አይደለሽ እንዴ አይጥ አልኳት እያጉረመረመች ዝም አለች ተያት ታውራበት የአሁን ልጆች እኮ ሲፈጠሩም በስለው ነው አለኝ እሺ አባባ ያኔ በኛ ግዜ እያልክስ ምትነግረኝ ነገር የለም አልኩት እንዴ ንቀሽኛል ቆይ ከተመረኩ እንኳን ቆየው እኮ ምን ቀረኝ አለኝ  እቺ ምላሰኛ ልጅ ምንም ሚስት ነው የቀረህ  እኔ ነኝ ያልኩህ ናኦድ ቶሎ በልና አግባ ግዜ እኮ ቆሞ አይጠብቅም አለችው ደንግጬ ኸረ ባክሽ ባክሽ ተዐምር ጓደኛሽ አደረግሽው እንዴ ብዬ አፈጠጥኩባተ የእቺ ጓደኛ ማለት የኔ ጓደኛ ማለት አይደል እንዴ ነው አግባ ስላልኩትም ቀንተሽ ነው አለችኝ ። ወይኔ ጨጓራዬን ገለበጠችው ብነክሳት ሁሉ ደስ ይለኝ ነበር ። ወዲያው የባለፈው ስልክ ተደወለልኝ አንስቼ ሄሎ አልኩኝ ሄሎ እፁብ ደህና ነሽ ደህና ነኝ አልኩ ፊቴ ጭምድድ አንዳለ ታናግሪኛለሽ ብሩክ ነኝ አለኝ  ልቤ ተሰነጠቀ ዝም አልኩ አንቺን ለማግኘት ኢትዮጵያዊ መጥቻለው እባክሽ አንዴ ላግኝሽ እና የገጠመኝን ላስረዳሽ አለኝ ስልኩን ዘግቼው ደንዝዤ ቀረው......... ............ይቀጥላል ........ @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
Show all...
👍 26😱 12
.       🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘         #ክፍል_14 ..............ወደ ጊቢ የምመለስበት ቀን ደረሰ በጣም እየከፋኝ ነው እዚህ እነሱን  ለምጄ  በተለይ የናኦድ ጥቅም አሁን አሁን እየገባኝ ነው እየከበደኝም ቢሆን ወደ ግቢ ሄድኩ እነ ማሚ  እየናፈቁኝ ነው በጣም ማሂና ናኦድም ይደውሉልኛል እናቴ እንዴት አድርጋ እንዳስተማረችኝ ስለማውቅ ወጥሬ አነባለሁ እፀልያለሁ ፌሎ ህብረት አደርጋለሁ በቃ እግዚአብሔርም ሊቀርፀኝ ስለፈለገ በብዙ ሁኔታዎች እያለፍኩ ነው ። ዛሬ ፈተና ላይ ነን አንቺ እፁብ እፁብ አንቺን እኮ ነው ከፊት ለፊቴ አተኩሮ እያየኝ ያለው መምህር ፊቱ በቁጣ ቀልቷል የያዘውን ቀይ ብዕር እያገላበጠ አፍጦብኛል ከኋላ ጥሪው እየጨመረ ነው ጭራሽ ይጎትቱኝ ጀመረ አስተማሪው እንዳፈጠጠብኝ ነው  ራሴን ማዳን ስለነበረብኝ ቶሎ ቶሎ ሰርቼ ወጣሁ ። እየጠሩኝ የነበሩት እነማን እንደሆኑ እንኳን አላወኩም ። ሀገር ሰላም ብዬ እየጠሬጠርኩ ስለ ሰራኋቸው ጥያቄዎች እያሰብኩ ከኋላዬ መዶሻ የመታኝ ይመስል ትከሻዬ ላይ እጅ አረፈ ተደናግጬ ዞር አልኩ አንቺ ማን ስለሆንሽ ነው መልስ የከለከልሽኝ ብሎ አፈጠጠብኝ ። እኛ ክላስ መሆኑን እንኳን አስተውዬው የማላውቀው ፊት ይቅርታ እንተዋወቃለን አልኩት ። እውነትም አታውቂኝም ማለት ነው በደንብ እንተዋወቃለን ብሎ እጄን ጨመቀኝ ሰውዬ ያምሀል እንዴ አልኩት ሰማሽኝ አሁን ላጣሁት ፈተና እና ለዚህ ትቢትሽ ዋጋ ትከፍያለሽ ብሎኝ ሄደ ። ከቁም ነገርም አልቆጠርኩትም ዝም ብዬ መንገዴን ተጓዝኩ ሻይ ጠጥቼ ትንሽ አረፍኩና ወደ ላይብረሪ ተመለስኩ አንብቤ ስጨርስ እነ ተዐምር ስለ ናፈቁኝ ዶርም ተመልሼ ደወልኩላቸው በየተራ ሲያወሩኝ ሲያስቁኝ ሲያዝናኑኝ ቆይተን ተሰነባበትን ሱቁን በታታሪነት እየሰሩ ነው አንድም ነገር ሳይጎልብኝ እያስተማሩኝ ነው እኔም ማድረግ ያለብኝን ሁሉ በአግባቡ እከውናለው ማጥናት ባለብኝ ሰአት አላርፍም ማረፍ ባለብኝ ሰአት አላጠናም መፀለይ ባለብኝ ሰአት ሌላ ነገር አልከውንም እግዚአብሔር ብቻውን እየረዳኝ ነው የበቀደሙ ልጅ በየመንገዱ እየተከተለ ነገር ይፈልገኛል አሁንማ ከጓደኞቹ ጋር ተሰብስበው መንገድ ይከለክሉኛል አንዳንዴ እናደድና አንዳንዴም ከቁም ነገር አልቆጥራቸውም  የእነሱንም ዛቻና ፌዝ የትምህርቱንም ክበደት እንደምንም ጌታ አሳልፎኝ ከወራት በኋላ ወደ ቤት ተመለስኩ ከውጪ ሀገር  እንደሚመጣ ሰው በሚገርም አቀባበል ሰብሰብ ብለው ነበር የጠበቁኝ ማሂም ናኦድም ቤት ነበሩ በጣም ደስ አለኝ ያሳለፍኩትን ስነግራቸው ስንጨዋወት ቆይተን እነ ማሂ ወደ ቤት ሊሄዱ ልንሸኛቸው ስንወጣ ማሚና ማሂ ተመስጠው ሲያወሩ ናኦድ በሹክሹክታ ተሰናብተውን ሄዱ ነገ በጠዋት እንደሚፈልገኝ ነገረኝ ማሚና ተዐምር ሶለናፈቁኝ ረጅም ሰአት ስናወራ ስንስቅ አመሸን ።  እነሱ ሲተኙ ምን ሊነግረኝ ይሁን በሚል ጉጉት እንቅልፍ ከየት ይምጣ..... .........ይቀጥላል ......... @Gospel_literature @Gospel_literature ✍written by Aksan Adane
Show all...
🥰 28😁 5👍 2
.        🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ📘 ✍ፀሀፊት አክሳን አዳነ           #ክፍል_13 ..........በማሚ ስልክ ደወልኩለት ሁለቴ እንደጠራ ሄሎ ማዘር አለኝ ማሚ አይደለሁም እፁብ ነኝ አልኩት ወዲያው ስልኩን ይዘጋዋል ብዬ ነበር የጠበኩት እሱ ግን ዝምታን መረጠ ። ይኸውልህ ናኦድ ስልኬን አላነሳ ስላልከኝ ነው በማሚ የደወልኩት ብዬ ሳልቸርስ ችግር ገጥሞሽ ነው እሺ ምን ልርዳሽ አለኝ ። ጌታ ሆይ በጣም ደነገጥኩ በተዘዋዋሪ ለችግርሽ ነው ምትፈልጊኝ መሆኑ ገባኝና አዎን ትልቅ ችግር ገጠመኝ እና ላገኝህ ፈልጌ ነበር አልኩት ። በረጅሙ ተነፈሰና እሺ አለኝ የእውነት ይብሱን በራሴ እንዳፍር አደረገኝ ጭራሽ መልሼ ለችግሬ ፈለኩህ እያልኩት ምን አይነት ልብ ነው ያለው አልኩኝ በሆዴ እና ነገ ሱቅ ትመጣለህ አልኩት ጭራሽ ለጉዳዩ ፈልጎኝ ሚመጣ አስመሰልኩት  እሺ አለኝ እሺ በጣም አመሠግናለሁ አልኩት ና ስልኩ ተዘጋ ። በቃ ሰላሜን ነሳኝ አንዴ ያደረኩትን እያስታወስኩ አለቅሳለሁ አንዴ ደግሞ ስላለው ልብ እየተገረምኩ ጌታን አመሠግናለሁ አንዴ ድርጊቶቹ እየታወሱኝ እስቃለሁ ስጮህበት እንኳን በመልካም ትህትና ነበር ምላሽ የሚሰጠኝ እንዲሁ ሳወጣ ሳወርድ ሊነጋ አቀላልቷል ። ተኛሁ ነገር ግን እንደ ከዚህ በቀደሙ አርፍጄ አልነበረም የተነሳሁት ቀጠሮ አክባሪ ስለሆነ በጊዜ ይመጣል በሚል በግዜ ወጥቼ ሄድኩ 2ሰአት ሲል ሱቁን አፅድቼ ከፋፍቼ የፈረደበትን ሬድዮ ከፍቼ ተቀመጥኩ ግን የጠበኩት አልነበረም የሆነው ናኦድ ሳይመጣ 6ሰአት ሆነ ቁርስ እንዳልበላው እንኳን ትዝ ያለኝ የህዝቡን የምሳ ሰአት ትርምስ አይቼ ነበር ሰራተኛው ተማሪው ነጋዴው የታክሲ መጨናነቁን አላፊ አግዳሚውን በአይኔ እየቃኘሁ እበሩ ላይ ተቀምጬያለሁ ። በጣም እየራበኝ ሲመጣ ገባሁና ለማሚ ደወልኩላት እናቴ ምሳ ከደረሰ ላኪልኝ ቁርስ እንኳን አልበላሁም አልኳት ውይ ውይ አፈር ልብላልሽ የኔ ልጅ አሁን እልካለው እኔ እናትሽ ይራበኝ አለችኝ ኸረ ምን በወጣሽ በቃ እንዳትቆይ ብዬ ስልኩን ስዘጋው ናኦድ ገብቶ ቆሟል እንዴ ኮቴም የለህ እንዴ ብዬ ሰላም አልኩት ምንም እንዳልተፈጠረ ነው ፊቱ ጌታ ሆይ ብቻ በውስጡ አቂሞብኝ እንዳይሆን እያልኩ እንዲቀመጥ ጋበዝኩት እኔም ወንበር ይዤ ተቀመጥኩ ። የእውነት ልትረዳኝ ፈቃደኛ ስለሆንክ አመሠግናለሁ አልኩት ግራ ገብቶት አየኝ ከእኔ የትህትናን ቃል እንደማይጠብቅ ተረዳሁ። እና የፈለኩህ አላስጨረሰኝም ከዚያ በፊት ግን ቁርስ አልበላሁም ስትዪ የሰማሁ መሠለኝ ቴክ አድርጌ ምግብ ላምጣ ብሎ ተነሳ ኸረ በጌታ አይሆንም አልኩት ካልሄድኩ ብሎ ሲከራከረኝ ማሚ ትልካለች ብዬ በመከራ እሺ አለኝ ። ቆይ ለምንድነው እንደዚህ ምትሆነው አልኩት  አልገባኝም እንዴት ሆንኩ ሁል ጊዜ እያስከፋውህ እንደዛ አሳዝኜህ ቢያንስ መጥፎ ፊት አታሳየኝም ? ለምን መጥፎ ፊት አሳይሻለው ያን ያህል ደግሞ አላስቀየምሽኝም ባይሆን የማትፈልጊያቸውን ነገሮች ስላደረኩ ይሆናል እንደዛ ያደረግሽው አይደለም በጥፋቴ ያለ ጥፋቴም ብታስቀይሚኝ ከክርስቶስ የተካፈልኩት ፍቅር ከነገሩ አንቺ እንደምትበልጪ ነው አለኝ በላዬ ላይ ፍም ልትከምር ስቃዬን ልታበዛው አልኩት ኸረ ጌታ እኮ እንደ እኛ አይደለም ከሀጢያት በቀር እንደ እኛ ተፈትኖ የለ ይረዳናል ይራራል ያንን ለማድረግሽ ምክንያት አታጪም አለኝ የእውነት በጣም ከፋኝ በሰው ፊት በፍፁም የማላለቅሰው እዛው ቀወጥኩት ናኦድ ወድጄ አይደለም እንደዛ ክፉ የሆንኩት አልኩት አውቃለሁ የገጠመሽን በሙሉ ለዛም ነበር ልቀርብሽ የሞከርኩት አለኝ እሺ ይቀርታ አድርግልኝ አልኩት ይቅርታ ባላደርግልሽማ አጠገብሽ አልገኝም ነበር አለኝ በጣም አመሠግናለሁ ብዬው ተዐምር ያመጣችውን ምሳ ለሶስት በልተን ተጨዋውተን ተለያየን ። አዕምሮዬ ሰላም አገኘ በጣም ነበር ደስ ያለኝ ። ከበፊቱ በላይ ቸርች መሄድ ጀመርኩ ይሄንን ስራም አቁሜ የማሚን ሱቅ ከፈትን ጌታ እየረዳን ጥሩ እየሰራን ነው ቀጣይ አመት ላይ ዊዝድሮ ሞልቼ ያቆምኩትን ትምህርት ልጀምር ነው የበፊቷን እፁብ ለመሆን በጣም እየጣርኩ ነው ጌታም እየረዳኝ ነው ። ማሂና ናኦድምም እየመጡ ይጠይቁናል ጥሩ ጓደኛሞች ሆነናል ። ነገሩ ተገልብጦ በተራዬ ስለ ናኦድ መፀለይ ጀመርኩ እውነትም እግዚያብሔርን የሚፈራ አለች ማሂ ናኦድ የወደፊት ባሌ እንዲሆን ተመኘው  ግን ምን ያደርጋል በተራው እሱ ሀሳቡን ሳይቀይር አልቀረም ያኔ ስላቀረበልኝ ጥያቄ እንዲያነሳ መንገድ ስከፍት አስቀይሶ ሌላ ነገር ያወራል ለነገሩ ይበለኝ ለሱ እንደ እኔ አይነት ሴት አትገባውም እንደ ራሱ መልካምና ልባም ሴት ናት ምትገባው እያልኩ ራሴን እወቅሳለሁ እነዚያን ጊዜያት ናፈኩአቸው ያኔ ምን ነበረበት በዚያ ህይወት ውስጥ ባልሆን ግን ደግሞ በአንድ ነገር አምናለው በእኔ ህይወት የእግዚአብሔር ፈቃድ ብቻ መፈፀም እንዳለበት የወደድከውን አድርግ ብዬ ለጌታ ተውኩለት ቀናቶች ገፍተው ወደ ጊቢ የምመለስበት ቀን ደረሰ........ ............ይቀጥላል.......... @Gospel_literature @Gospel_literature
Show all...
🥰 27👍 9
.         🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልበ-ወለድ📘          #ክፍል_12 .......እያለች ታሞግሰው ጀመር አስተያየቴ ገባት መሠለኝ ምነው እፁ ፊትሽን ጥለሽዋል እኮ አለችኝ የዚህን ያክል አልኩና ንዴቴን ገትቼ ራሴን መቆጣጠር ጀመርኩ ። ታውቂያለሽ በፊት ሁል ጊዜ ጠዋት ጠዋት ለኳየራችን ልጆች በሙሉ የመፅሀፍ ቅዱስ ጥቅስ ይልክልናል አንድ ቀን ሳይሰላች ማለት ነው አስቢው ለዚያ ሁሉ ሰው እና ይህን ሁለት ሶስት ቀን ሳይደርሰኝ ቀረ እኔ ጋ ብቻ መስሎኝ ሌሎቹን ስጠይቃቸው ኸረ እኛ ጋርም አልላከም አሉኝ ደውዬ ስጠይቀው ትንሽ ደብሮኝ ነው አለኝ እሱ ሰዎች የፈለገ ያክል ቢከፋቸው ዋጋ ከፍሎ አፅናንቶ ወደ ቀድሞው ቦታ ይመልሳቸዋል ምን ቢገጥመው ነው ብዬ በጣም ተጨነኩ ንገረኝ ብለው ቀለል አድርጎ አይጠቅምሽም አለኝ የነገሩ ከባድነት ገባኝ ና ላገኘው  ብዙ ለመንኩት እሰይ አንቺ ነሽ ጭራሽ ቀጣሪዋ አልኩኝ በውስጤ ቀጣዩን ወሬ ለመስማት እያቆበቆብኩ ከብዙ ልመና በኋላ ተስማማ ግን ጉዳዩን አልነገረኝም ሰው አስከፍቶኝ ነው አለኝ ማንነቱን እና ምን አድርጎ እንዳስከፋው ሊነግረኝ አልፈለገም ቆይ በፊት እኛን ስትመክረን አልነበር አልኩት ከማትጠብቂው ሰው ሲሆን ያማል አለኝ ዕፁ ወዲያው ባንቺ ምክኒያት እንደከፋው ገባኝ ታዲያ ነገሮችን ንቀን ካላለፍናቸው እኛኑ ነው የሚጎዱን ትለኝ አልነበር አልኩት ። ከዚህም በፊት እኮ ብዙ ግዜ ከፍቶኝ ያውቃል ግን በሰአቱ አዝንና ወዲያው ረሳው ነበር ግን ያስከፋኝ ሰው ከእኔ የሆነ ነገር በፈለገ ሰአት በመልካም መንገድ ቀርቦኝ ነበር የፈለገው ነገር ከተሟላለት በኋላ ግን ያልጠበኩት ነበር የሆነው ትንሽ ለዛ ነው ደግሞ በጣም ይቅርታ ጥቅስ መላኬን ማቆም አልነበረብኝም አሁን ከቀድሞው ይልቅ ህይወቴ ተሰርቶበታል የሆነ ነገር ተምሬያለሁ ሰዎች እኔን መጥላትም ለኔ መልካም አለማሰብም መብታቸው ነው እኔ ግን እነሱን መውደድም ለነሱ መልካም ማሰብም ግዴታዬ ነው ከጌታ የተቀበልኩት ትዕዛዝ የተማርኩት ትምህርት  ነውና አለኝ ።የዕውነተ ዕፁ አንጀቴ ስፍስፍ ነው ያለው የሆነ እዛው ላለቅስም ፈለኩ ብታይ በጣም ነው የሚያሳዝነው ዕፁ ለምን አሳዘንሽው ምን አድርገሽ አሳዘንሽው ምናምን አልልሽም እባክሽን ቢያንስ በቅንነትና በትህትና አዋሪው እንደ መልካም ጓደኛ እንኳን ብትቀርቢው ምን አለ እሱንም አልፈልግም ካልሽ ግን ቢያንስ አትጥዪው አጠገብሽ ያለውን ወንድም ሳትወጂ ጌታን እወዳለው ማለት ስላቅ ነው የእውነት ናኦድ ማንም ሰው ሚወደው ማንም ሰው ባወኩት ብሎ የሚመኘው ሰው ነው በዚህ ወጣትነት ሲሰብክ የሚሰብከውን ደግሞ ሲኖር የእውነት ስለሱ ጌታን የማያመሰግን የለም እኮ አውቃለሁ ጓደኛዬ የበፊት ስብራት ና ጉዳትሽ ሰውን እንዳታምኚ አድርጎሽ ይሆናል ናኦድ ማለት ብሩክ ነው ማለት አይደለም ከደረሰብሽ ብዙ ስቃይና የስነ ልቦና ጉዳት አንፃር ተቀይረሻል የበፊቷ እፁብ ሰው ወዳድ ሰው አክባሪ ትሁት የጌታ ቃል ከአንደበቷ የማይታጣ ነበረች አሁን በራስሽ ሙድ ነው ምትንቀሳቀሺው ስለ ሰዎች ግድ አይሰጥሽም ልወቅስሽ አይደለም ግን ቆም በይና ራስሽን ተመልከቺ በዚህ ከቀጠልሽ በዙሪያሽ ያሉትን ሰዎች ብቻ ሳይሆን ማንነትሽንም ታጪዋለሽ ። ንግግሯን ስትቋጭ ሳልፈልግ በዕንባ ርሻለሁ ሰው ተናግሮኝ አልቅሼ አላውቅም  ልክ እንዳልሆንኩ እያወኩ ብዙ ጥፋት አጥፍቻለው ። ከተቀመጠችበት ተነስታ አቀፈችኝ እፁዬ አታልቅሺ ተይኝ ማሂ እኔ ራስ ወዳድ ነኝ  አይደለም ከሰዎች ከጌታዬ ትዕዛዝ ራሴን ማስቀድም የማልጠቅም ሰው ነኝ  አንቺ እንኳን አሰንዲ እየሆንሽልኝ በውስጤ ሳማሽ ነበር እኔ ለማንም መሆን የማልችል ሴት ነኝ ተይኝ አልኳት እኔ ክፍተትሽን ካልነገርኩሽ ምኑ ላይ ነው ጓደኝነታችን እንጂ ፃዲቅ ሆኜ እየኮነንኩሽ አይደለም አንቺም እኔ ላይ ምታይውን ክፍተት ሳትደብቂ ንገሪኝ ብላ አፅናናችኝ ። እሺ ማሂ አሁን ምን ማድረግ አለብኝ አልኳት መጀመሪያ ሰዉ በአንቺ አዝኖ ጌታ አይደሰትምና ንሰሀ ግቢ ከዚያ ለራስሽ ይቅርታ አድርጊ ራስሽን መውቀስ አቁሚ ጌታ ይቅር ካለሽ የትኛውም ከሳሽ አይከስሽም ከዚያ ናኦድን ከልብሽ ይቅርታ ጠይቂው አለችኝ ። በሀሳቧ ተስማማው ስለ እርሷም ጌታን አመሠገንኩ ። አቤት ሄጄ ጌታዬ ፊት ከልቤ ነበር ያለቀስኩት ከንሰሀውም ጋር እንዲቀይረኝ ንፁህ ልብን ፍጠርልኝ ብዬ ለመንኩት ከእግሮቹ ስር አልቅሶ መነሳት ደስታና ብርሃንን ያጎናፅፋል ነፃነት ተሰማኝ  ። ማሚንም ተዐምርንም ይቅርታ ጠየኳቸው። ቀጣዩና ዋናው ናኦድን ይቅርታ መጠየቅ ነው የኔን ስልክ ስላላነሳልኝ በማሚ ስልክ ደወልኩለት..... ............ይቀጥላል......... @Gospel_literature @Gospel_literature
Show all...
24👍 9🥰 3👏 2💔 2
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብ-ወለድ📘             #ክፍል_11 ......ማን እኔ? መቼ ? ግራ ተጋባው ማሚ በቁጣ አይን ስትመለከተኝ ተቀመጥኩ ልጁ እንደዚ ለየለት በዚህ ምሽት ጭራሽ ጠራሽኝ ብሎ ይመጣል እንዴ ምን አይነት ድርቅና ነው አናዶኛል መምጣቱ ባይሆንም ጠራሽኝ በሚል ሰበብ መምጣቱ ዕፁቤ አጫውቺው እንጂ እራት ይቅረብ ብላ ከተቀመጠችበት ተነሳች ። ተዐምርም ልታግዛት ጉድ ጉድ ማለት ጀመረች ። አንተ መምጣት ከፈለክ በእኔ ነው ምታሳብበው ብዬ በሹክሹክታ አፈጠጥኩበት ምንም መልስ አልሰጠኝም ዝም አለ ወዲያው ነበር ስልክ ተደወለለት ሊያናግር መሠለኝ ወጣ እኔም ልብስ ለመቀየር ወደ ጓዳ ገባሁ ። ብቻዬን እየለፈለፍኩ ረጅም ደቂቃ ተቀምጬ ስወጣ ማሚ እስቲ ይሄን ልጅ ግባ በይው ምግቡ ቀዘቀዘ እኮ አለችኝ ተቀመጥኩና ተዐምር ሂጂ ጥሪው አልኳት እራስሽ አትጠሪውም እንዴ ብላ ስትነጫነጭ አንቺ ታላቅሽ እኮ ነኝ ታዘዢ ብዬ ሳፈጥባት ምላሷ ማቆሚያ የለው አንቺስ ማሚን አትታዘዢም እያለች እየተርጎመጎመች ወጣች ። የዚህች ሌጅ ጥጋብ እንዴት እንዴት ነው እሱ ቆይ ማሚ አንቺ ደግሞ ምን አለ ብትተያት ቢያንስ እንግዳ አታከብሩም እንዴ እኔንስ ከናቃቹኝ ቆቻችሁ ። እንዴ ማሚ የለም  እኮ አለች ተዐምር ምን ወዴት ሄደ እስቲ ደውይለት አለችኝ እንዴ ምን ብዬ ነው ምደውለው አስቸኩለውት ይሆናል አልኳት አቤት መከራዬ ፊት ነስተሽው ነው እንጂ ሄድኩ ሳይልማ አይሄድም እንደው እግዚአብሔርንም አትፈሪም እፁብ ማንስ ቢጠራው ምን አግብቶሽ እቤትሽ የተቀመጠን እንግዳ ለምን መጣህስ ይባላል ምነው ምነው አጥቶ እኮ አደለም የመጣው አክብሮን እንጂ ፊቷን ቅጭም አድርጋ ወይ ማሚ እሱ ፊት ሲነሱት ሲገባው አይደል ምንም ሆኖ አይደለም ባክሽ በራሱ ሰአት ይመጣል አልኳት እኔ ምንም አልልም ጌታ ይቅር ይበልሽ ይሄ አይደለም እንደ            እግዚአብሔር ቃል እንደ ሰው ራሱ ነውር ነው ስርአት አልበኝነት ብዬዋለው ብላ ተነስታ ወደ መኝታዋ ሄደች ። ተዐምርም የጣደችውን ቡና ትታ ተከተለቻት ኦኦ ነገሩ ከሯል ማለት ነው ትንሽ የጥፋተኝነት ስሜት ተሰማኝ ና ቴክስት ልልክለት ስልኬን አነሳሁ ሰሙን ስፈልግ በፊት የተፃፃፍነውን መልዕክቶች አመጣልኝ ድንግጥ ነው ያልኩት መቼ ነው ደግሞ ያወራነው ብዬ ስከፍተው  "ናኦዴ ነገ እቤት እንድትመጣ ማሚ እራት ጋብዛሀለች" ይላል ልቤ ስንጥቅ የእሱ መልስ እሺ እፁቤ ስለ ግብዣው አመሠግናለሁ ነገ ከአብሮ አደግ ወንድሜ ጋ ቀጠሮ ነበረኝ ግን በቃ ሰርዤው እመጣለሁ ። ጌታ ሆይ ውሰደኝ ብዬ ከተቀመጥኩበት ብድግ አልኩ ። ጌታ ሆይ እየቃዠው መሆን አለበት መቼ ነው የፃፍኩት ሰማይ ምድሩ ዞረብኝ ማሚ እያበድሽ ነው ዘይኝ ብዬ ወደ እርሷ ሄድኩ ምንድነው አለችኝ ጭራሽ መች እንደ ሆነ አላስታውስም በቴክስት ጠርቼዋለሁ ኤጭ ሰላሜን ስጪኝ አለችኝ ተዐምር እንደ ተኛች እኛማ ደስ የሚልሽ መስሎን ነበር እኔ ነኝ የላኩለት አለችኝ ወይኔ እንዴት እንደ ተናደድኩ በተኛችበት ቆንጥጬ ልገላት ኡኡ ብላ በጩኸት አደበላለቀችው ማሚ ኸረ ባክሽ ባክሽ አንቺ ልጅ አድቢ ብላ አስለቀቀችኝ ። ባለጌ ልጅ አይደለሽ እንዴ እኔ ነኝ ጥፋተኛዋ ላንቺ ስልክ መስጠቴ ያዋርድሽ አዋረድሽኝ አልኳት ኡፍፍፍፍ በናንተ የተነሳ ጤናዬን ልጣ ብላ ስትቆጣ ነገ አገኝሻለዉ ብዬ አኔም ተኛዉ በምን አይኔ ነው የማየው ምን አይነት ችኩል ምን አይነት ስርአት የሌለኝ ነኝ እያልኩ ራሴን መውቀስ ጀመርኩ ሳልተኛ ነጋልኝ ። ስራ ገብቼም የእንቅልፉ ድካም ጭንቀቱ ተጫጭኖ ሰላም ነሳኝ ልደዉልለትም ብዬ ፈራሁ እሱ እስኪደውል በትዕግሥት ብጠብቅም የጠበኩት አልሆነም ። 3ቀን በመጠበቅ አሳለፍኩና በ4ተኛው ቀን አይኔን በጨው አጥቤ ደወልኩለት አላነሳልኝም ሁለት ሶስቴ ደወልኩ አላነሳልኝም ኸረ ለውጥማ አለ ብዬ ተውኩት ለማሂ ልነግራት ደወልኩላት እሷም አታነሳም ደጋግሜ ስደውል አነሳችልኝ ሄለው ማሂ ወዬ ዕፁ እንዴት ነሽ አለሁ እግዚአብሔር ይመስገን ምነው ስልክ አታነሺም አልኳት እእእ ከናኦዴ ጋር ሆኜ አላየሁትም ነበር አለችኝ አሀ ከአንቺ ጋር ሆኖ ነዋ ስልኬን የማያነሳው ብዬ ዘጋሁባት እንደሚመለከተው ሰው ራሴን እስክታዘብ ተናደድኩ እየተብሰለስልኩ ውዬ ከሰአታት በኃላ ማሂ መጣች አንቺ ምነው ጆሮዬ ላይ ዘጋሽው የሱን ንዴት እኔ ላይ ነው እንዴ ምትወጪው አለችኝ ባክሽ ወደዛ አትቀባጥሪ አልኳት ለምን እንዳገኘሁት ግን አውቀሻል አለችኝ ምን አገባኝ ስለሱ ይመለከተኛል አልኳት ኸረ እፁ እየተናደድሽ ባልሆነ አለችኝ ኦሆሆሆ ምን አናደደኝ አልኳን ንዴቴ እኮ ለራሴም ይታወቀኛል እና ማወቅ አልፈልግም ነው ምትይው ካልሽ እሺ አለችኝ የባሰ ተናደድኩ በገዛ እጄ ውይ ናዲ ግን ይለያል ምን አይነት ትሁት ነው እያለች ታሞግሰው ጀመር....... .........ይቀጥላል ......... @Gospel_literature @Gospel_literature
Show all...
👍 25 7
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብ-ወለድ📘         #ክፍል_10 .....ናኦድን ለማግኘት ቸኩያለሁ ። ነገር ሳብሰለስል እንቅልፍ እምቢ ብሎኝ ሊነጋጋ ሲል ተኛሁ የስልክ ጥሪ ነበር ከእንቅልፌ ያነቃኝ ናኦድ ነበር ። ሄሎ ደህና አደርሽ እፁብ እግዚአብሔር ይመስገን እንዴት አደርክ አለሁ ክብሩ ይስፋ ተኝተሽ ነው እንዴ አለኝ ድምፄ አሳበቀብኝ መሠለኝ አዎን በግዜ አልተኛሁም ነበር አልኩት እኔ እኮ ስራ ቦታሽ መጥቼ ዝግ ሆኖብኝ ነው በቃ ስትመጪ ደውዪልኝ ብሎኝ ስልኩ ተዘጋ ። ኸረ ምን ጉድ ነው ፈልግሀለው ስለው ብቻ ለጥያቄው ምላሽ ጠብቆ እንዳይሆን አያፍርም እኮ እያልኩ ተነሳሁ ተጣጥቤ ልብሴን ለብሼ ወጣሁ ። ገና ሱቁንም ከፍቼ ጥቂት ሳልቆይ መጣ ሰላምታ ተለዋወጥን ተቀመጠ የጠራሁት ለሌላ ጉዳይ በሰበብ ባስባቡ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ሲሰብከኝ ሰአታት ነጎዱ የሆነ ሰአት ላይ ምርርር አለኝ አቁም አልለው ነገር  መፅሐፍ ቅዱሳዊ ነገር ነው የሚያወራው ኸረ ምን ጉድ ነው ይመፀዳደቅብኛል እንዴ አይሰለቸውም እያልኩ ከራሴ ጋር አወራለሁ ። አውርቶ ሲጨርስ ለምን ነበር ግን የፈለግሽኝ አለኝ ግዜ ሳላጠፋ ጉዳዩን ሁሉ ነገርኩት ያልጠበቀውን ነገር እንደነገርኩት ፊቱ ቢያሳብቅም በሁሉም ነገር ከጎኔ እንደሚሆን ነግሮኝ ሄደ ። ለማሂ ደወልኩላት እና መጣች ለሷም ሁሉንም ነገርኳት አይዞሽ እግዚአብሔር ይረዳናል ከእርሱ በታች ደግሞ በናኦድ ሙሉ በሙሉ እተማመናለሁ አለችኝ ። ግን አንቺ ደግሞ ለጉዳይሽ ብቻ ሳይሆን እሱም በሚፈልግሽ ግዜ ተገኚለት አለችኝ  ማሂ ደግሞ ያምሻል ከእርሱ ጋር ለደቂቃ ማሳለፍ ይጨንቀኛል ወሬዉ ሁሉ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ማውራት ነው በቃ ስልችት ነው ሚለኝ ኸረ እፁ ተይ ጌታን ይደብራል ለጥቅምሽ ብቻ እንደፈለግሽው ካወቀ ይጎዳል ቢያንስ እንደ ጥሩ እህት ቅረቢው ። ኸረ ማሂ እየነገርኩሽ ይጨንቀኛል ብዬ አፈጠጥኩባት አንቺ ታበዢዋለሽ እንደ እርሱ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው በስለትም አታገኚም እንኳን ሌላ አለች ውይ ውይ ይቅርብኝ ብዬ ሳኩኝ ምን አለች በይኝ በሳቅሽው ልክ ታለቅሺያለሽ ስታስጠዪ ብላኝ ሄደች ለንግግሯ ቦታም ሳልሰጥ ተውኩት ። ከ1ወር በኋላ በቤቱ ጉዳይ ሰበብ መገናኘት መደዋወል ጀመርን በትንሹም ቢሆን ስብከቱን እየለመድኩት ነው እዉነትም ንግግሩ ከልብ ላደመጠው ከራሱ እንደማይናገር ያስታውቃል በቤቱ ጉዳይ ክስ መስርተን ክርክር ላይ ናቸው ማሚ ነገሮችን ቸል ማለት ትወዳለች ክስ ተጀምሮ እንኳን ይቅር በቃ የምትል ሰው ናት እኔ ደግሞ እልኸኛ ከ3ወር ንትርክ በኋላ እናቴም ባለ ድርሻ እንደሆነች ታምኖ 1000,000 የተሸጠው ቤት  እኩል ተካፍለው የድርሻዋን በባንክ አስገቡላት አጎቶቼ እርር ብለዋል አንደኛውማ ዝቶብኝ አስፈራርቶኝ ነበር የተለያየነው ። ማሚ ናኦድን ስትመርቀው ስትመርቀው ምንም ገንዘብ አልቀበልም አለ ብትለምነው እኔም ብዙ ብለምነው አምቢ አለ ። ምን አስቦ ነው ደግሞ በውለታ ሊያስረኝ ባልሆነ ብዬ አሰብኩ ማሂም በጣም ደስ ብሏት እግዚአብሔርን አመሠገንን ስለ ናኦድ ስነግራት እርሱ ምን አይነት ፍጥረት ነው ብላ ተደነቀች እኔ ግን ምንም አይመስለኝም ። በፊት በቀን አስር ግዜ ምደውልለት አሁን ትዝም አልልሽ አለኝ  ከደወለልኝም እንደ ነገሩ ነው የማወራው  ማሚ ሁሌ ስለሱ ትጠይቀኛለች ተዐምርም በጣም ነው የምትወደው ጓደኛሽ አይመጣም እንዴ እያሉ ይጨቀጭቁኛል  ስራ ይበዛበታል ምናምን እያልኩ ዋሻቸዋለሁ ። በብሩ ምን አይነት ስራ መጀመር እንዳለብን ከማሚ ጋር መወያየት ጀመርን ተዐምር እፁ አንዴ ስልክሽን መዝሙር ልስማበት ብላ ተቀበለችኝ። ሰፈራችን ለንግድ ምቹ ስለሆነ የሸቀጣሸቀጥ ሱቅ ለመክፈት ተስማምተን ፀልየን ተኛን ቀኑ እሁድ ስለሆነ በጠዋቱ ተነስተው ቡና ተፈልቶ ቁርስ ሰርተው ቤቱ ሁሉ ፅዱ ሆኖ ተቀሰቀስኩ በፈገግታ ና በትህትና የታጀበ ቁርስ በልቼ ከማሂ ጋር ተደዋውለን ቸርች ሄድኩ ። ጌታ ደስ የሚል ግዜ ሰጥቶን ተጠናቀቀ ያው ሰላም ስንባባል እዛው እንሰነብታለን ጓደኞቻችንን እያወራን ናኦድ መጣ ኡፍፍፍፍ አልኩ ማሂ አንቺ ልጅ ኸረ ጌታን ፍሪ አይከብድሽም እንዴ አለችኝ እሱም አጠገባችን ደርሶ ሰላም ካለን በኋላ ለደቂቃዎች ነዝንዞን እፁ በቃ በኋላ እንገናኝ ብሎኝ ሄደ ሆሆሆሆ ጭራሽ ላግኝህ ልጁ ታሟል እንዴ አልኩ በቃ በሱ ጉዳይ ከማሂ ጋር ሁሌ                       እንደ ተጨቃጨቅን ነው ። ስንከራከር እነሱ ቤት ደረስን እዛው ውዬ አክስቷንም ታማ ነበርና እሷን መጠየቅ ሄደን አመሻሽቼ ወደ ቤት ሄድኩ እቤት ስደርስ ቤቱ ያለወትሮው አምሮበታል የምግብ መልካም መዓዛ እና የጥሩ እጣን ና ቡና ሽታ ከሩቅ ይጠራል ምን ተገኝቶ ነው ብዬ ከበር ወደ ውስጥ ስዘልቅ ናኦድ ከነ ማሚ ጋር ቁጭ ብሏል ደነገጥኩ ደግሞም ስላልጠበኩ አንተ ምን ትሰራለህ እዚ አልኩት ። ደነግጦ ከተቀመጠበት በመነሳት አንቺ እኮ ነሽ የጠራሽኝ አለኝ ማን እኔ ?........ ...........ይቀጥላል ........... @Gospel_literature @Gospel_literature
Show all...
👍 22🏆 4🥰 3👏 1
🎬መዝሙር ለመስማት MB እየበዛ ተቸግረዋል ? የድምፅ ጥራት አንሶ ተቸግረዋል ? እንግዲያውስ መፍትሄ ይዘንላችሁ ቀርበናል ከታች ያለውን ሊንክ እና Button በመንካት HQ መዝሙር ያገኛሉ 👇 https://t.me/addlist/ZSxEk8-Vk3k3ZDJk https://t.me/addlist/ZSxEk8-Vk3k3ZDJk wave ለመግባት 👉 @wunuye_bot
Show all...
🎶በ አንስተኛ MB መዝሙር ለማግኘት🎶
🎶ከፍተኛ ጥራት ያለው መዝሙር ለማግኘት🎶
🎶በ KB size መዝሙር ለማግኘት🎶
🎶በትንሽ MB ቪዲዮ መዝሙር ለማግኘት🎶
🎶በትንሽ MB ኦዲዮ መዝሙር ለማግኘት🎶
🎶አዳዲስ ሙሉ አልበሞችን ለማግኘት🎶
🎶ቆየት ያሉ ሙሉ አልበሞችን ለማግኘት🎶
🎶Live worship መዝሙር ለማግኘት🎶
🎶የ Cover song መዝሙር ለማግኘት🎶
🎶🎶አሁኑኑ ይቀላቀሉን🎶🎶
.      🤔ጥያቄዬ🤔 📘ተከታታይ መንፈሳዊ ልብ-ወለድ📘         #ክፍል_10 .....ናኦድን ለማግኘት ቸኩያለሁ ። ነገር ሳብሰለስል እንቅልፍ እምቢ ብሎኝ ሊነጋጋ ሲል ተኛሁ የስልክ ጥሪ ነበር ከእንቅልፌ ያነቃኝ ናኦድ ነበር ። ሄሎ ደህና አደርሽ እፁብ እግዚአብሔር ይመስገን እንዴት አደርክ አለሁ ክብሩ ይስፋ ተኝተሽ ነው እንዴ አለኝ ድምፄ አሳበቀብኝ መሠለኝ አዎን በግዜ አልተኛሁም ነበር አልኩት እኔ እኮ ስራ ቦታሽ መጥቼ ዝግ ሆኖብኝ ነው በቃ ስትመጪ ደውዪልኝ ብሎኝ ስልኩ ተዘጋ ። ኸረ ምን ጉድ ነው ፈልግሀለው ስለው ብቻ ለጥያቄው ምላሽ ጠብቆ እንዳይሆን አያፍርም እኮ እያልኩ ተነሳሁ ተጣጥቤ ልብሴን ለብሼ ወጣሁ ። ገና ሱቁንም ከፍቼ ጥቂት ሳልቆይ መጣ ሰላምታ ተለዋወጥን ተቀመጠ የጠራሁት ለሌላ ጉዳይ በሰበብ ባስባቡ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ሲሰብከኝ ሰአታት ነጎዱ የሆነ ሰአት ላይ ምርርር አለኝ አቁም አልለው ነገር  መፅሐፍ ቅዱሳዊ ነገር ነው የሚያወራው ኸረ ምን ጉድ ነው ይመፀዳደቅብኛል እንዴ አይሰለቸውም እያልኩ ከራሴ ጋር አወራለሁ ። አውርቶ ሲጨርስ ለምን ነበር ግን የፈለግሽኝ አለኝ ግዜ ሳላጠፋ ጉዳዩን ሁሉ ነገርኩት ያልጠበቀውን ነገር እንደነገርኩት ፊቱ ቢያሳብቅም በሁሉም ነገር ከጎኔ እንደሚሆን ነግሮኝ ሄደ ። ለማሂ ደወልኩላት እና መጣች ለሷም ሁሉንም ነገርኳት አይዞሽ እግዚአብሔር ይረዳናል ከእርሱ በታች ደግሞ በናኦድ ሙሉ በሙሉ እተማመናለሁ አለችኝ ። ግን አንቺ ደግሞ ለጉዳይሽ ብቻ ሳይሆን እሱም በሚፈልግሽ ግዜ ተገኚለት አለችኝ  ማሂ ደግሞ ያምሻል ከእርሱ ጋር ለደቂቃ ማሳለፍ ይጨንቀኛል ወሬዉ ሁሉ ከዘፍጥረት እስከ ራዕይ ማውራት ነው በቃ ስልችት ነው ሚለኝ ኸረ እፁ ተይ ጌታን ይደብራል ለጥቅምሽ ብቻ እንደፈለግሽው ካወቀ ይጎዳል ቢያንስ እንደ ጥሩ እህት ቅረቢው ። ኸረ ማሂ እየነገርኩሽ ይጨንቀኛል ብዬ አፈጠጥኩባት አንቺ ታበዢዋለሽ እንደ እርሱ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው በስለትም አታገኚም እንኳን ሌላ አለች ውይ ውይ ይቅርብኝ ብዬ ሳኩኝ ምን አለች በይኝ በሳቅሽው ልክ ታለቅሺያለሽ ስታስጠዪ ብላኝ ሄደች ለንግግሯ ቦታም ሳልሰጥ ተውኩት ። ከ1ወር በኋላ በቤቱ ጉዳይ ሰበብ መገናኘት መደዋወል ጀመርን በትንሹም ቢሆን ስብከቱን እየለመድኩት ነው እዉነትም ንግግሩ ከልብ ላደመጠው ከራሱ እንደማይናገር ያስታውቃል በቤቱ ጉዳይ ክስ መስርተን ክርክር ላይ ናቸው ማሚ ነገሮችን ቸል ማለት ትወዳለች ክስ ተጀምሮ እንኳን ይቅር በቃ የምትል ሰው ናት እኔ ደግሞ እልኸኛ ከ3ወር ንትርክ በኋላ እናቴም ባለ ድርሻ እንደሆነች ታምኖ 1000,000 የተሸጠው ቤት  እኩል ተካፍለው የድርሻዋን በባንክ አስገቡላት አጎቶቼ እርር ብለዋል አንደኛውማ ዝቶብኝ አስፈራርቶኝ ነበር የተለያየነው ። ማሚ ናኦድን ስትመርቀው ስትመርቀው ምንም ገንዘብ አልቀበልም አለ ብትለምነው እኔም ብዙ ብለምነው አምቢ አለ ። ምን አስቦ ነው ደግሞ በውለታ ሊያስረኝ ባልሆነ ብዬ አሰብኩ ማሂም በጣም ደስ ብሏት እግዚአብሔርን አመሠገንን ስለ ናኦድ ስነግራት እርሱ ምን አይነት ፍጥረት ነው ብላ ተደነቀች እኔ ግን ምንም አይመስለኝም ። በፊት በቀን አስር ግዜ ምደውልለት አሁን ትዝም አልልሽ አለኝ  ከደወለልኝም እንደ ነገሩ ነው የማወራው  ማሚ ሁሌ ስለሱ ትጠይቀኛለች ተዐምርም በጣም ነው የምትወደው ጓደኛሽ አይመጣም እንዴ እያሉ ይጨቀጭቁኛል  ስራ ይበዛበታል ምናምን እያልኩ ዋሻቸዋለሁ ። በብሩ ምን አይነት ስራ መጀመር እንዳለብን ከማሚ ጋር መወያየት ጀመርን ተዐምር እፁ አንዴ ስልክሽን መዝሙር ልስማበት ብላ ተቀበለችኝ። ሰፈራችን ለንግድ ምቹ ስለሆነ የሸቀጣሸቀጥ ሱቅ ለመክፈት ተስማምተን ፀልየን ተኛን ቀኑ እሁድ ስለሆነ በጠዋቱ ተነስተው ቡና ተፈልቶ ቁርስ ሰርተው ቤቱ ሁሉ ፅዱ ሆኖ ተቀሰቀስኩ በፈገግታ ና በትህትና የታጀበ ቁርስ በልቼ ከማሂ ጋር ተደዋውለን ቸርች ሄድኩ ። ጌታ ደስ የሚል ግዜ ሰጥቶን ተጠናቀቀ ያው ሰላም ስንባባል እዛው እንሰነብታለን ጓደኞቻችንን እያወራን ናኦድ መጣ ኡፍፍፍፍ አልኩ ማሂ አንቺ ልጅ ኸረ ጌታን ፍሪ አይከብድሽም እንዴ አለችኝ እሱም አጠገባችን ደርሶ ሰላም ካለን በኋላ ለደቂቃዎች ነዝንዞን እፁ በቃ በኋላ እንገናኝ ብሎኝ ሄደ ሆሆሆሆ ጭራሽ ላግኝህ ልጁ ታሟል እንዴ አልኩ በቃ በሱ ጉዳይ ከማሂ ጋር ሁሌ                       እንደ ተጨቃጨቅን ነው ። ስንከራከር እነሱ ቤት ደረስን እዛው ውዬ አክስቷንም ታማ ነበርና እሷን መጠየቅ ሄደን አመሻሽቼ ወደ ቤት ሄድኩ እቤት ስደርስ ቤቱ ያለወትሮው አምሮበታል የምግብ መልካም መዓዛ እና የጥሩ እጣን ና ቡና ሽታ ከሩቅ ይጠራል ምን ተገኝቶ ነው ብዬ ከበር ወደ ውስጥ ስዘልቅ ናኦድ ከነ ማሚ ጋር ቁጭ ብሏል ደነገጥኩ ደግሞም ስላልጠበኩ አንተ ምን ትሰራለህ እዚ አልኩት ። ደነግጦ ከተቀመጠበት በመነሳት አንቺ እኮ ነሽ የጠራሽኝ አለኝ ማን እኔ ?........ ...........ይቀጥላል ........... @Gospel_literature @Gospel_literature
Show all...