en
Feedback
University of Gondar Students' Union

University of Gondar Students' Union

Open in Telegram

ይህ የቴሌግራም ቻናል ለጎንደር ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ተአማኒነት እና ወቅታዊ የሆኑ መረጃዎችን የሚያደርስ ሲሆን አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ https://t.me/+oUv5_G-huC5kYmM0 OR @henok2727

Show more
3 808
Subscribers
+1324 hours
+1237 days
+43530 days
Posts Archive
ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 40.65 በመቶዎቹ የማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ! ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 40 ነጥብ 65 በመቶዎቹ የማለፊያ ነጥብ ማስመ
ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 40.65 በመቶዎቹ የማለፊያ ነጥብ አስመዘገቡ! ለዩኒቨርሲቲ መውጫ ፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ውስጥ 40 ነጥብ 65 በመቶዎቹ የማለፊያ ነጥብ ማስመዝገባቸውን የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። የትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ ከሰኔ 30 ቀን ጀምሮ ለስድስት ቀናት ሲሰጥ የቆየው የዩኒቨርሲቲ ትምህርት መውጫ ፈተና በስኬት መጠናቀቁን ገልፀዋል። ለመውጫ ፈተና ሊቀመጡ ይችላሉ ተብሎ ተገምቶ ከነበረው 240 ሺህ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን 194 ሺህ 239 ተማሪዎች ብቁ ሆነው ለፈተና መመዝገባቸውንም ነው የተናገሩት። ከዚህ ውስጥ ከ48 የመንግስት ተቋማት 84 ሺህ 627 ተማሪዎች እና ከ171 የግል ተቋማት 109 ሺህ 612 ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ መመዝገባቸውም ነው የገለጹት። የመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ ከተመዘገቡት ውስጥ ከመንግስት ተቋማት 77 ሺህ 981 ተማሪዎች እንዲሁም ከግል ተቋማት 72 ሺህ 203 ተማሪዎች በድምሩ 150 ሺህ 184 ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል ብለዋል፡፡ ከእነዚህ ውስጥ 61 ሺህ 54 ተማሪዎች ወይም 40 ነጥብ 65 በመቶ የማለፊያውን ነጥብ አስመዝገበዋል ነው የተባለው፡፡ ለተቋማትም የተማሪዎቻቸውን ውጤት የመላክ ሥራ መጀመሩንም ጠቁመዋል። ለኢንትራንስ ተፈታኞች👇 https://t.me/ATC_UEE ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot ➡️ https://t.me/atc_news

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሲካሄድ የቆየው የመውጫ ፈተና/ Exit Exam/ ተጠናቀቀ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ እንደሚታወቀው የትምህርት ጥራትን ለማምጣት አንዱ እና ዋነኛው የመውጫ ፈተና መስጠት እንደሆነ በማመን የኢፌዴሪ ትምህርት ሚኒስቴር ከመንግስትና ከግል የትምህርት ተቋማት ጋር በመሆን ፈተናውን ለተመራቂ ተማሪዎች ለመስጠት አበክሮ ሲሰራ ቆይቷል። ስለሆነም የ2015ዓ/ም ተመራቂ ተማሪዎች/በመንግስትና በግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከተሰተሉ የነበሩ ከሰኔ 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በየተመደቡበት በ5ቱም ግቢዎች የመውጫ ፈተናውን በተያዘላቸው የፈተና መርሀ- ግብር ሀምሌ 7/2015ዐሰ/ም በሰላም አጠናቀዋል። ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ለልህቀት እንተጋለን! ህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ሀምሌ 7/2015ዓ/ም

ከምርቃት እና የምረቃ መርሀግብር ተሳትፎ ጋር በተገናኘ በቅርቡ የኢት/ከፍ/ት/ተቋ/ተ/ህብረት መግለጫ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መግለጫ ከምርቃት ፕሮግራም ጋር በተያያዘ የተነሳውን ሀሳብ በተመለከተ ማስተካከያ ማድረግ አስፈላጊ ሆኗል። በመሆኑም ሁሉም ተማሪ ጊዜያዊ የትምህርት ማስረጃውን ከማግኘቱ አስቀድሞ የመውጫ ፈተናን ማለፍ የሚጠበቅበት ሲሆን የምርቃት መርሀ-ግብር ተሳትፎን በተመለከተ በተቋማት ሴኔት ብቻ የሚወሰን መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ሀምሌ 05/2015 ዓ.ም         https://t.me/UoGStudentUnionOffice

Final exit exam schedule_Thursday and Friday.pdf

Share Final exit exam schedule_Thursday and Friday.pdf

Share UoG-Mgt Session 3 Hamle 6.xls

Share Final exit exam schedule_Thursday and Friday.pdf

Share UoG- Mgt Session 2 Hamle 6.xls

Share UOG Mgt Session 1 Hamle 6.xlsx

urgent notice! your exit exam time for Economics and business management has been modified as : business management =6:30-9:30 local time Economics=9:30-12:00 local time University of Gondar student union

#ለመውጫ_ተፈታኝ_እጩ_ምሩቃን_በሙሉ:- በመውጫ ፈተና ወቅት ቀይ የባንዲራ ምልክት ማድረግ ተመልሳችሁ ለማረጋገጥ ያሰባቹኃቸው ጥያቄዎች በቀላሉ ለማግኘት እንዲረዳችሁ እንጂ ከእርማቱ ጋር ፍፁም የማይገናኝ መሆኑን እንዲሁም የመልስ ቅያሪ ስታደርጉ ሳትሰርዙ (Clear my choice) የሚለውን ሳትጫኑ የቀየራችሁትን መልስ ብታጠቁሩም መልሳችሁ የሚያዝ መሆኑን እንገልፃለን::

#ማስታወቂያ #ለመውጫ_ተፈታኝ_እጩ_ምሩቃን_በሙሉ:- በመውጫ ፈተና ወቅት ቀይ የባንዲራ ምልክት ማድረግ ተመልሳችሁ ለማረጋገጥ ያሰባቹኃቸው ጥያቄዎች በቀላሉ ለማግኘት እንዲረዳችሁ እንጂ ከእርማቱ ጋር ፍፁም የማይገናኝ መሆኑን እንዲሁም የመልስ ቅያሪ ስታደርጉ ሳትሰርዙ (Clear my choice) የሚለውን ሳትጫኑ የቀየራችሁትን መልስ ብታጠቁሩም መልሳችሁ የሚያዝ መሆኑን እንገልፃለን:: የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት

Exit Exam Schedule Hamle 3-5,2015 E.C (1).pdf

ከኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት የተሰጠ መግለጫ! በቅድሚያ በዩኒቨርሲቲ ቆይታችሁ ማሟላት የሚጠበቅባችሁን አሟልታችሁ ለዚህ ለበቃችሁ ውድ እጩ ምሩቃን እና ክቡራን የምሩቃን ቤተሰቦች እንኳን ደስ አላችሁ እያልን በዚህ አመት በሁሉም የትምህርት ክፍሎች የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና፤ ተመራቂ ተማሪዎች ያላቸውን ብቃት ለመለካት የተዘጋጀ እና ለት/ት ጥራት የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ቢሆንም የነበሩ ክፍተቶችን እና በቅድሚያ መሟላት የነበረባቸው ሁኔታዎችን በዝርዝር በማስቀመጥ ቢያንስ ቁጥራቸው በዛ ያሉ ተመራቂዎች በሚገኙባቸው የት/ት ፕሮግራሞች በዚህ አመት እንዲጀመር አልያም በሙከራ ደረጃ እንዲሰጥ ያላሳለሰ ጥረት አድርገናል። ሆኖም የት/ት ጥራትን ለማምጣት በሁሉም የት/ት ክፍሎች እንዲጀመር በመወሰኑ፤ ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎችን ከግምት በማስገባት በትግበራው ተማሪው ተጎጂ እንዳይሆን እያደረግን ቆይተናል። በቅርቡ በተሰጡት የመለማመጃ እና የሙከራ ፈተናዎች ወቅት የነበሩ ክፍተቶችን ከየዩኒቨርሲቲው የተማሪ ህብረቶች በመሰብሰብ እና በዋናው ፈተና ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ችግሮችን በመለየት እንዲስተካከሉ ለት/ት ሚኒስቴር ከወዲሁ አሳውቀናል። በተጨማሪም ምርቃት እና የመውጫ ፈተናን በተመለከተ ከት/ት ሚኒስቴር ጋር በነበረን ቅድመ ውይይት የምረቃ  መርሀ-ግብር ላይ የሚሳተፉ ተማሪዎችን በተመለከት ዩኒቨርሲቲዎች የቀደመ አሰራራቸውን መከተል እንደሚችሉ ስምምነት ላይ ደርሰን የነበረ ቢሆንም፤ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ “የመውጫ ፈተናን ያላለፉ ተማሪዎች የምርቃት ፕሮግራም ላይ አይሳተፉም” በማለት በድንገት አሳውቆ የነበረ መሆኑ ይታወቃል። ውሳኔው ከተገለፀበት እለት ጀምሮ እንደ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ጉዳዩ አግባብነት የሌለው፣ በህግ ለተቋማት ሴኔት በተሰጠ ስልጣን ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ያለ አግባብ ጣልቃ መግባቱን እንዲሁም ውሳኔው ከ4-7 አመታት የተማረው ተማሪን ብቻ ሳይሆን የሀገር መሰረት የሆነውን ቤተሰብንም ጭምር የሚጎዳ፤ ለት/ት ጥራቱም ምንም ፋይዳ የሌለው መሆኑን በመግለፅ በተደጋጋሚ ውይይት ያደረግን ሲሆን በዚህም መሰረት ት/ት ሚኒስቴር በግብታዊነት ያስተላለፈውን ውሳኔ በማሻሻል ወደቀድሞ ሀሳብ ተመልሷል። ለዚህም በተመራቂ ተማሪዎች ስም ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ምስጋናችንን እናቀርባለን። በዚህም መሰረት በሀገራችን የሚገኙ ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አንድ/ሁለት ያልተሟላ ውጤት ኖሯቸው ከግማሽ በላይ ጠቅላላ ድምር ውጤት(CGPA>=2.00) ያላቸውን ተማሪዎች የምርቃት መርሀ-ግብር እንዲሳተፉ አድርገው ሲያሟሉ ዲግሪ የሚሰጡ ሲሆን አሁንም በተመሳሳይ የመውጫ ፈተናውን የማያልፍ ተማሪ ካለ የምርቃት መርሀ-ግብር ላይ በመሳተፍ ለምዘናው ብቁ በሆነ ጊዜ በየሶስት ወሩ በሚሰጠው ፈተና ያለገደብ መመዘን ብሎም ድጋሚ የመፈተን ፍላጎት የሌለው እጩ ምሩቅ በደረጃ ዝቅ ያለ የት/ት ማስረጃ መውሰድ እንደሚችል በመመሪያ ተቀምጧል። በመሆኑም ውድ እጩ ምሩቃን በምርቃት መርሀ-ግብር ዙሪያ ሲነሱ የነበሩ ነገሮችን ታግሳችሁ ከሚመለከታቸው አካላት መልስ እስኪሰጥ በትግስት ስለጠበቃችሁ ምስጋናችንን እያቀረብን፤ ጥያቄያችን መልስ አግኝቶ ሁሉም ተመራቂ ተማሪ የምርቃት መርሀ-ግብር ላይ የሚሳተፍ በመሆኑን እንገልፃለን። በተያያዘም የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች በትምህርት ማስረጃቸው ላይ ከ100 ያመጡት ውጤት የሚገለፀው በጊዜያዊው ማስረጃቸው(Tempo) ላይ ሳይሆን በትራንስክሪፕት ማለትም የወጪ መጋራታቸውን ከፍለው ሲያጠናቅቁ በሚሰጣቸው፤ የወሰዱትን የት/ት አይነቶች ከነውጤታቸው በሚያሳየው ማስረጃ ላይ መሆኑን እየገለፅን መንግስት አዲስ ቅጥር ማቆሙን ካሳወቀ 2 አመታት ያለፉ ቢሆንም በግሉ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በመንግስት መስሪያ ቤቶችም የተለያዩ አዲስ ቅጥሮች ሲፈፀሙ የቆዩ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን። በመጨረሻም ክቡራን እጩ ምሩቃን፦    1) የምትፈተኑበት ኮምፒውተር ፈተና ከመጀመሩ በፊት ሙሉ አገልግሎት እንደሚሰጥ ፈትሻችሁ እንድትቀመጡ፤ 2) ፈተናውን በምትሰሩበት ወቅት የኮምፒውተር ገመዶች በሰውነታችሁም ሆነ በሌላ ነገሮች እንዳይነኩ እና እንዳይቋረጡ ጥንቃቄ እንድታደርጉ፤ 3) ወደ መፈተኛ ክፍሎች ስትገቡ እና ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ መመሪያዎችን እንድታከብሩ፤ 4) ምዘናው በበይነመረብ የሚሰጥ እንደመሆኑ በፈተናው ወቅት ችግሮች ካጋጠሙም ወድያው መፍታት ስለሚቻል እንከን ሲያጋጥማችሁ በየመፈተኛ አዳራሹ ለተመደቡ የአይሲቲ ባለሙያዎች በፍጥነት እንድታሳውቁ እንዲሁም የሚያጋጥሟችሁን የትኛውም ተግዳሮቶች በግቢያቹ ላለው ህብረታችሁ በማመልከት ከግቢው ከአቅም በላይ ከሆነ በእኛ በኩል በሚመለከተው አካል እንዲፈታ የምናደርግ መሆኑን እየገለፅን በቅርቡ በተሰጠው የሙከራ ፈተና ልክ በመዘጋጀት ያለምንም ፍርሀት እና ጭንቀት የፈተና ስነ-ምግባርን በጠበቀ መልኩ እንድትፈተኑ አደራ እያልን መልካም ፈተና እንዲሆንላችሁ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ት/ት ተቋማት ተማሪዎች ስም አብዝተን እንመኛለን።              መልካም እድል! የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ፅ/ቤት https://t.me/UoGStudentUnionOffice

የመውጫ ፈተና(Exit-Exam) ለምትፈተኑ..... ወድ ዕጩ ተመራቂ ተማሪዎች እንደሚታወቀው ከነገ 03/11/2015 ጀምሮ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሁሉም ተመራቂ ተማሪዎች የመዉጫ ፈተና ይሰጣል። ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በማግስቱ ፈተና የሚፈተን ሰው በቂ የሆነ እንቅልፍ መተኛት አለበት (ከ8፡00 -- 10:00) ሰዓት። ይህን በማድረጋችሁ የሚከተለውን ታተርፋላችሁ። ⚪️ It improves your memory, ⚪️ Strengthens your concentration, ⚪️ Relaxes your mind, ⚪️ helps to think critically, ⚪️ Improves problem solving abilities, ⚪️ Reduces stress, ⚪️ Manages anxiety, ⚪️ Maximizes your performance, አመጋገበችሁም የተሻለ፣ ጨጓራችሁን የማይነካ ይሁን። ቁርስም አትዝለሉ። ስትመገቡ ምቾት በማይሰጣችሁ ልክ ጠግባችሁ አትብሉ። ውሃም አብዝታችሁ አትጠጡ። ፈተና ላይ ሆናችሁ ጥያቄ በምትሰሩ ሰዓት የከበዳችሁን ጥያቄ ለመስራት በመታገል ብዙ ጊዜ አትግደሉ፤ እሱን ለመስራት ስትታገሉ ሌሎች ቀላል ጥያቄዎችን ሳትሰሩ ሰዓት ሊያልቅባችሁ ይችላልና።  ከባዱን ጥያቄ ዝለሉትና ቀለል ቀለል የሚሉትን ሰርታችሁ ስትጨርሱ ሰዓት ስለሚተርፋችሁ ወደከበዳችሁ ጥያቄ ትመጡና ትሰሩታላችሁ። ከዚህ በተጨማሪ ሁላችሁም ተፈታኝ ተማሪዎች በዕለቱ ከተመደቡ ፈታኝ መምህራን እና ከ ICT ባለሙያዎች የሚሰጣችሁን አቅጣጫ ብቻ በመከተል ተረጋግታችሁ በተቻለ መጠን የድስፒሊን ግድፈት እንዳይኖርባችሁ የብዙ ዓመት ልፋታችሁ ከንቱ እንዳይሆን የምትችሉትን ሁሉ በማድረግ ፈተናዉን በድል ጨርሳችሁ ጥሩ ውጤት እንድታስመዘግቡ ከወዲሁ መልካም ምኞታችንን እንገለጻለን። መልካም ፈተና ይሁንላችሁ! Good Luck! የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት!!! መልካም ፈተና!!!

የመውጫ ፈተና በሚሰጥባቸው ቀናት የሚኖሩ ዲስፕሊንና የምንከተለው ፕሮቶኮል👆 ©ት/ት ሚኒስቴር @EHEISUOfficialChannell

Exit Exam schedule.pdf

University of Gondar Exit Exam schedule for Hamle 3 and 4, 2015 E.C.

Final Exam Schedule July 6.xlsx0.85 KB