University of Gondar Students' Union
Open in Telegram
ይህ የቴሌግራም ቻናል ለጎንደር ዩንቨርሲቲ ተማሪዎች ተአማኒነት እና ወቅታዊ የሆኑ መረጃዎችን የሚያደርስ ሲሆን አስተያየት እና ጥቆማ ለመስጠት ይህንን ሊንክ ይጠቀሙ https://t.me/+oUv5_G-huC5kYmM0 OR @henok2727
Show more3 808
Subscribers
+1324 hours
+1237 days
+43530 days
Posts Archive
✍✍ውድ የጎንደር ዩኒቨርስቲ የ2015 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች እና ሁሉም የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች በያላችሁበት ሰላማችሁ ይብዛ እያልን ወደ ግቢ መግቢያ ጊዜ እስካሁን ምንም አይነት የተቀየረ ነገር የለም። ማለትም ለተመራቂዎችም ሆነ ለሁሉም ህ/ጤ/ሳ/ኮ ተማሪዎች ነሃሴ 01/2015 ዓ.ም ወደ ግቢ መግቢያ መሆኑን ለማሳወቅ እንወዳለን ።
https://t.me/+oUv5_G-huC5kYmM0
https://t.me/UoGStudentUnionOffice
#ለወዳጅዎ_ያጋሩ
Remedial students can see their grade via this portal http://213.55.79.200
Dear all,
I am sending a survey to assess the need for occupational therapy services at the University of Gondar's student clinic. Thank you so much in advance for taking the time to complete it.
Best Regards
Sara
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSce4O3sH0UOsf_qZ92BPEsvApJWVTwU5ROsvMOJhUzVlKysuw/viewform?usp=sf_link
#Remedial
የሪሚዲያል ተማሪዎች ውጤት የመታውቂያ ቁጥራችሁን በማስገባት ነገ ረቡ ማየት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን ። ነው የሚለቀቅ ብላችሁ በተደጋጋሚ እየጠየቃችሁን ትገኛላችሁ ። ስለሆነም ፈተናችሁ ታርሞ እና የውጤት ትንተናውም ተሰርቶ የተጠናቀቀ በመሆኑ ውጤታችሁ በቅርቡ የሚለቀቅ ይሆናል። የማለፍ ምጣኔያችሁም አመርቂ እንደሆነ የውጤት ትንተናችሁ ላይ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ፅ/ቤት
🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺
join our channel
https://t.me/UoGStudentUnionOffice
Dear all,
I am sending a survey to assess the need for occupational therapy services at the University of Gondar's student clinic. Thank you so much in advance for taking the time to complete it.
Best Regards
Sara
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSce4O3sH0UOsf_qZ92BPEsvApJWVTwU5ROsvMOJhUzVlKysuw/viewform?usp=sf_link
When: Friday, August 11 - Sunday, August 13, 2023 .
Register as early as possible with this link https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSe1GL6goJQJN9lNUmlJQzlGQOF6DziAeOw2uPENjhDqIV-4vw/viewform?usp=sf_link
መች፡ ነሐሴ 5-7, 2015 E.C
ከዚህ በታች በሰፈረው ማስፈንጠሪያ ቀድመው ይመዝገቡ
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSe1GL6goJQJN9lNUmlJQzlGQOF6DziAeOw2uPENjhDqIV-4vw/viewform?usp=sf_link
ለ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች‼
🔻🔺 ለተፈታኞች የተከለከሉ ነገሮች🔺🔻
በፈተና ማዕከል (ዩኒቨርሲቲ) እና መፈተኛ ክፍሎች ውስጥ የተከለከሉ ነገሮች የሚከተሉት ናቸው ...👇
1. ማንኛውንም ዓይነት የጦር መሣሪያ፣ ስለት እና ሹልነት ያላቸውን ብረታ ብረቶችና ጠንካራ ፕላስትኮች ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው፡፡
2 ማንኛውም ድምጽ የሚቀዳ፣ ፎቶ የሚያነሳ፣ ቪዲዮ የሚቀርጽ፣ ከቴሌ መስመርም ሆነ ከቴሌ መስመር ውጭ መልዕክት በዲጂታል መንገድ የሚሰጥ ወይም የሚቀበል የግል ዕቃ/መሳሪያ/ የቴክኖሎጂ ውጤት፣ ስልክ፣ አይፓድ፣ ታብሌት፣ ኮምፒዩተር፣ ላፕቶፕ፣ ስማርት ሰዓት፣ ማጂክ ብዕር/ እስክሪብቶ፣ ማጂክ ኮት/ ጃኬት እና ሌሎች ማንኛቸውም ፎቶ ምስል እና ድምጽ የሚቀርጹ የኤሌክትሮኖክስ መሣሪያዎችን በዩኒቨርሲቲው ግቢ ውስጥም ሆነ ግቢ ዙሪያ ይዞ መግኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
3 በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ማንኛውንም ዓይነት የግል ፍላሽ ዲስክ፣ ሃርድ ዲስክ፣ ሲዲ፣ ሚሞሪ፣ ሚሞሪ ሪደር፣ ኦ-ቲጂ ኮንቨርተርና መሰል ዕቃዎችን ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው፡፡
4 ማንኛውም አደንባዥ እጾች (ጫት፣ ሲጋራ፣ በሐኪም ማዘዣ የሌለው መድኃኒት (በሽሮፕም ይሁን በታብሌት) ህክምና መስጫ መርፌ))መያዝ ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው።
5. ማንኛውም ዓይነት የአልኮል መጠጥ ይዞ መገኘት ወይም መጠቀም የተከለከለ ነው።
6. ማንኛውም ዓይነት የአንገት ሐብል፣ የጸጉር ጌጥ፣ የጆሮ ጌጥ፣ የጣት ቀለበት፣ የእጅ አንባር አድርጎ ወይም ይዞ መገኘት የተከለከለ ነው። (ከልሙጥ የጋብቻ ቀለበት በስተቀረ)
7. ፈተና ከተጀመረ ከ30 ደቂቃ በኋላ ወደ ፈተና ክፍል መግባት እና ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ከፈተና ክፍል መውጣት የተከለከለ ነው።
8 ተፈታኙ ፈተናው ሳይጠናቀቅ ከፈተና ክፍል የሚወጣ ከሆነ የፈተና ጥያቄ የያዘውን ቡኩለት ይዞ መውጣት ተከለከለ ነው፡፡
9. በፈተና ሰዓት በመፈተኛ ክፍል ውስጥ ማስቲካ መያዝም ሆነ መጠቀም የተከለከለ ነው።
10. በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ በግልም ሆነ በቡድን መጮህ ወይም በጣም ከፍተኛ ድምጽ ማሰማት የተከለከለ ነው።
የ 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ቻናል👇
https://t.me/+bsiFkfN1DSwxNDFk
Share share🙏🙏
ለተጨማሪ መረጃ👇👇👇👇
╔═══════════╗
♨️ ♦️ @ethiouniversity1 ♨️
♨️ ♦️ @ethiouniversity1 ♨️
♨️ ♦️ @ethiouniversity1 ♨️
╚═══════════╝
" ዘንድሮ በመደበኛው 667 ሺህ 483 ፤ በግል፣ በማታ እና በርቀት 200 ሺህ 691 ተፈታኞች ፈተና ይወስዳሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
ከ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ጋር በተያያዘ ባለፈው ዓመት የተስተዋሉ የተለያዩ እንከኖች በዚህኛው ዓመት መስተካከላቸውን የትምሕርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል።
ምዝገባው በማንዋል በመሆኑ ተፈጥሮ የነበረውን የተፈታኞች መረጃ አያያዝ ጥራት ጉድለት ለማረም ዘንድሮ ምዝገባው በበይነ መረብ መካሄዱን አገልግሎቱ ገልጿል።
በተጨማሪም ከዩኒቨርሲቲ ድልድል፣ ዝግጅት እና አቀባበል ጋር በተያያዘ እክሎች የነበሩ ሲሆን ዘንድሮ ችግሩ መቀረፉን አረጋግጧል።
አምና ካጋጠመው ጉድለት በመማር የፈተና ማስፈጸሚያ ማንዋል እና መመሪያውን በማዘጋጀት እና በመከለስ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተደርጓል።
ባለፈው ፈተና ወቅት ተፈታኞችን ማዘጋጀት አለመቻሉ ዋና ችግር እንደነበር የጠቀሰው አገልግሎቱ በዚህ ዓመት በቂ ዝግጅት ስለመደረጉ ገልጿል።
በዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከተመዘገቡት 869 ሺህ 802 ትክክለኛውን የምዝገባ ሂደት ያላሟሉ 1 ሺህ 213 ተፈታኞች ምዝገባ መሠረዙንም ተገልጿል።
ዘንድሮ ፦
- በመደበኛ 667 ሺህ 483
- በግል፣ በማታ እና በርቀት 200 ሺህ 691 ተፈታኞች ፈተና ይወስዳሉ።
ፈተናው በሁለት ዙር በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ይሳጣል።
የመጀመሪያው ዙር ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 21 ቀን፤ ሁለተኛው ዙር ፈተና ደግሞ ከሐምሌ 25 እስከ 28 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚሰጥ አገልግሎቱ አረጋግጧል።
የማኅበራዊ ሣይንስ ተፈታኞች ከሐምሌ 16 እስከ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ እ
የሚገቡ ሲሆን ሐምሌ 18 ገለጻ ይሰጣቸዋል።
የተፈጥሮ ሣይንስ ተፈታኞች ደግሞ ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ገብተው ሐምሌ 24 ቀን ገለጻ ይሰጣቸዋል።
ተፈታኞች ፈተናውን በራሳቸው ጥረት እንዲሠሩ አሳስበው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ባለፈው ዓመት የፈተና ደንብ ጥሰት የፈጸሙ 17 ሺህ ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሠረዙን አስታውሷል።
Credit : #ኤፍቢሲ
#Remedial
የሪሚዲያል ውጤት መች ነው የሚለቀቅ ብላችሁ በተደጋጋሚ እየጠየቃችሁን ትገኛላችሁ ። ስለሆነም ፈተናችሁ ታርሞ እና የውጤት ትንተናውም ተሰርቶ የተጠናቀቀ በመሆኑ ውጤታችሁ በቅርቡ የሚለቀቅ ይሆናል። የማለፍ ምጣኔያችሁም አመርቂ እንደሆነ የውጤት ትንተናችሁ ላይ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት ፅ/ቤት
🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺🔺
join our channel
https://t.me/UoGStudentUnionOffice
Repost from Career Development Center--UOG
We are excited to share a wonderful opportunity.
The Career Development Centre, in collaboration with Dereja, planed three days of employability skills and job readiness training.
When: Friday, August 11 - Sunday, August 13, 2023
We are going to come to each campus—Maraki, Tewodros, Fasil, GC, and Tseda.
A certificate will be issued for those attending strictly, and there is also an incentive for participation.
Register as early as possible with this link https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSe1GL6goJQJN9lNUmlJQzlGQOF6DziAeOw2uPENjhDqIV-4vw/viewform?usp=sf_link
እጅግ አስደሳች ዜና
የጎንደር የኒቨርሲቲ የሞያ ማጎልበቻ ማዕከል ከደረጃ ጋር በመተባበር የ3 ቀናት ተከታታይ የሥራ ፍለጋ ክህሎትና ዝግጁነት ሥልጠና ለሁሉም ተመራቂ ተማሪዎች በጎንደር የኒቨርሲቲ
መች፡ ነሐሴ 5-7, 2015 E.C
በሁሉም ግቢዎች እንመጣለን፡ ማራኪ፣ቴዎድሮስ፣ፋሲል፣ጤና ሳይንስ፣ጠዳ
3ቱንም ቀናት በንቃት ለተሳተፉ ሰርትፊኬትና ማበረታቻ ይሰጣል
ከዚህ በታች በሰፈረው ማስፈንጠሪያ ቀድመው ይመዝገቡ
https://docs.google.com/forms/d/e/1FAIpQLSe1GL6goJQJN9lNUmlJQzlGQOF6DziAeOw2uPENjhDqIV-4vw/viewform?usp=sf_link
#Remedial
በሬሚዲያል ፈተና 30% የተቋም ውጤታቹህ እና 70% የማዕከል ፈተና ውጤታቹህ አንድ ላይ ተደምሮ ከ50% በላይ ማለትም ድምሩ ከ300 ሲሆን 150 እና ከዚያ በላይ ያመጣቹህ እንዲሁም ድምሩ ከ400 ሲሆን 200 እና ከዚያ በላይ ያመጣቹህ ተማሪዎች #2016 የትምህርት ዘመን ላይ ሬሚድያል #በተማራችሁበት የመንግስት ዩንቨርስቲ ላይ ፍሬሽማን ሆናቹህ ትቀጥላላቹህ።
የሬሚድያል ውጤት ሲለቀቅ ለማየት ➡️ Click
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news
#ጎንደር_ዩኒቨርሲቲ
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ በመውጫ ፈተና በአጠቃላይ ካስፈተናቸው 3,089 ተማሪዎች ውስጥ 2,760 (89.35%) ተፈታኞች በብቃት ማለፋቸውን አሳውቋል።
ፈተናውን ከወሰዱ 73 ትምህርት ክፍሎች መካከል 34 ትምህርት ክፍሎች ሙሉ በሙሉ (100%) አሳልፈዋል።
ከአጠቃላይ ተፈታኞች መካከል በመደበኛ መርሐግብር ካስፈተናቸው 2,919 ተማሪዎች 2,703 (92.6%) ያለፉ ሲሆን ቀሪዎቹ 170 ተማሪዎች በተከታታይ መርሐግብር ተፈተነው 57(33.53%) ፈተናውን በብቃት አልፈዋል።
ይህም ውጤት በአገሪቱ ካሉ አቻ ተቋማት ቀዳሚ እንደሚያደርገው ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።
@tikvahethiopia
እንኳን ደስ ያላቹሁ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ዩኒቨርሲቲያችን "የጎንደር ዩኒቨርሲቲ" ለመውጫ ፈተና ካስፈተናቸው ተማሪዎች ውስጥ በአጠቃላይ 89.2% በማስመስገብ በጥሩ ውጤት አልፈዋል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን
እስካሁን ውጤት ማየት ያልቻላችሁ ተመራቂ ተማሪዎች የመዉጫ ፈተና ውጤታችሁን ከዛሬ 10 ሰአት ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣችሁን Username በመጠቀም በዚህ ሊንክ በ https://result.ethernet.edu.et በመግባት ማወቅ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን ።
#የመውጫ_ፈተና
- የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ብቁ ሆነው የተመዘገቡት ከ48 የመንግስት ተቋማት 84,627 ተማሪዎች እና ከ171 የግል ተቋማት 109,612 ተማሪዎች ፤ አጠቃላይ በድምሩ 194,239 ተማሪዎች ናቸው።
- ለፈተናው ከተመዘገቡት ከመንግስት ተቋማት 77,981 ተማሪዎች / 92.15 በመቶ ከግል ተቋማት 72,203 ተማሪዎች / 65.87 ከመቶ ተማሪዎች ፈተናውን ወስደዋል።
- አጠቅላይ ፈተናውን የወሰዱ 150,184 ተማሪዎች ናቸው። (ከመንግሥት 77,981 ከግል 72,203)
- በመንግስት ተቋማት ለፈተናው ከተቀመጡት 77,981 ተማሪዎች ውስጥ 48,632 ተማሪዎች ወይም 62.37 በመቶ የማለፊያውን 50 እና ከዚያ በላይ አስመዝግበዋል።
- በግል ተቋማት ለፈተና ከተቀመጡት 72,203 ተማሪዎች ውስጥ 12,422 ተማሪዎች ወይም 17.2 በመቶ የማለፊያውን 50 እና ከዚያ በላይ አስመዝግበዋል።
- በድምሩ ከአጠቃላይ 150,184 የመውጫ ፈተና ተፈታኞች ፈተናውን ያለፉት 61,054 ብቻ ናቸው ይህም ማለት 40.65 ነው።
ተፈታኞች ውጤታቸውን #ከእሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣቸውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/ ገብተው ማወቅ ይችላሉ።
(ከትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ)
" የ2015 የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን ከእሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣቸውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/ ገብተው ማወቅ ይችላሉ " - ትምህርት ሚኒስቴር
የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተና መጠናቀቅን አስመልክቶ መግለጫ ልኮልናል።
ለመውጫ ፈተና ሊቀመጡ ይችላሉ ተብሎ ተገምቶ የነበረው 240 ሺህ ተማሪዎች ሲሆኑ የመውጫ ፈተናን ለመውሰድ ብቁ ሆነው የተመዘገቡት ከ48 መንግስት ተቋማት 84,627 እና ከ171 የግል ተቋማት 109,612 በድምሩ 194,239 ተማሪዎች ናቸው፡፡
የመውጫ ፈተናን ለመውስድ ከተመዘገቡት ውስጥ ከመንግስት ተቋማት 77,981 ተማሪዎች ከተመዘገቡት 92.15 ከመቶ እንደዚሁም ከግል ተቋማት 72, 203 ተማሪዎች 65.87 ከመቶ በድምሩ 150,184 ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን ወስደዋል፡፡
በመንግስት ተቋማት ለፈተና ከተቀመጠት ውስጥ 48,632 ተማሪዎች 62.37 በመቶ የማለፊያውን 50 እና ከዚያ በላይ አስመዝግበዋል፡፡
በተመሳሳይ ከግል ተቋማት ለፈተና ከተቀመጡት ውስጥ 12,422 ተማሪዎች 17.2 በመቶ የማለፊያውን 50 እና ከዚያ በላይ አስመዝግበዋል፡፡
በድምሩ ለፈተና ከተቀመጡት ውስጥ 61,054 ተማሪዎች 40.65 በመቶ የማለፊያውን ነጥብ አስመዝገበዋል፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር በላከልን መግለጫ የ2015 የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤታቸውን #ከእሁድ ማታ ጀምሮ ለፈተናው የተሰጣቸውን User Name በመጠቀም በዚህ ሊንክ https://result.ethernet.edu.et/ ገብተው ማወቅ ይችላሉ ብሏል።
(ትምህርት ሚኒስቴር የላከልን ሙሉ መግለጫ ከላይ ተያይዟል)
@tikvahethiopia
