210
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 28/ 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን)
"እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በፍቅር አደረሳችሁ"
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የጌታችንን የመድሃኒታችንን የእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓልን ከታካሚዎችና ቤተሰቦቻቸው ጋር እጅግ በደመቀ መልኩ አከበረ።
በዛሬው ደማቅና አስደሳች የገና በዓል ዝግጅት ላይ የተቋሙ ሃላፊዎች የተቋሙ ታካሚዎችና ቤተሰቦቻቸው የተቋሙ ሰራተኞች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በመገኘት መልካም የሚባል ጊዜን አሳልፈዋል።
በኘሮግራሙ "የትሩፋት ቤተሰብ ማህበር" የተባለ ግብረ ሰናይ ድርጅት ከየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሲአርሲ (CRC) ክፍል ጋር በመተባበርና በመቀናጀት ከተቋሙ ታካሚዎች ጋር በጋራ የገናን በዓል አክብረዋል።
በበዓል ዝግጅት ላይ ለ150 (አንድ መቶ ሃምሣ) ታካሚዎች ምሳ የማብላት ዝግጅት ነበረ እንዲሁም ለተቸገሩ ታካሚዎች 50,000 ( ሃምሳ ሺህ) ብር በስጦታ መልክ አበርክተዋል።
በተጨማሪም ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ ለተቋሙ ተረኛ ሰራተኞች በዓልን በስራ ሲያሳልፉ ደስ ብሎአቸው እንዲያሳልፉ በሬ በማረድ የምሳ ግብዣ አድርጎላቸዋል።
በደመቀው ልዩ የገና በዓል አከባበር ላይ የተገኙት የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ዋና ኘሮቮስት ዶ/ር ኤልያስ ተዋበ እንደገለፁት በዓልን እንዲህ በደመቀ መልኩ ከታካሚዎቻችን ጋር ማሳልፍ እጅግ ደስታን የሚሰጥ ነገር ነው ብለዋል።
አያይዘውም ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ በሚሰጠው አገልግሎት ላይ መሟላት መስተካከል ያለባቸው ነገሮች ቢኖሩ ከእናንተ ደንበኞቻችን ፣ ታካሚዎቻችን ጋር በመመካከር የምናስተካክል ይሆናል ብለዋል። የእንኳን አደረሳችሁ መልዕታቸውንም አስተላልፈዋል።
በተቋሙ ውስጥ አገልግሎት እያገኙ ያሉ ታካሚዎችና የታካሚ ቤተሰቦቻቸው በበኩላቸው እየተሰጣቸው ባለው አገልግሎት በጣም ደስተኛ እንደሆኑ እንባ እየተናነቃቸው ገልፀዋል። የገናን በዓልም እንደዚህ ስናከብ እቤታችን ያለን ያክል እንዲሰማን ስላደረጋችሁን እናመሰግናችኋለን ብለዋል።
በዛሬው የገና በዓል አከባበር በየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አበበች ጎበና እናቶችና ህፃናት ህክምና ማእከል እንዲሁ በደመቀ መልኩ ተከብሮ ውሏል።
በተያያዘ ገናን በዓል በማስመልከት ለመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማህበረ ከተቋሙ ሶፍት ፣ የገላ ሳሙና የልብስ ሳሙና እና ሌሎች ስጦታዎችን አበርክተዋል
በስጦታው መርሃግብር ላይ የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የምርምርና ጥናት ም/ ኘሮቮስት ዶ/ር መረርቱ ተመስገን ፣ የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አበበች ጎበና የእናቶችና ህፃናት ህክምና ማእከል ሃላፊ ዶ/ር አናንያ ሰለሞ እንዲሁም የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አበበች ጎበና የእናቶችና ህፃናት ህክምና ማእከል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶ/ር ዱረቲ ጀማል በመገኘት በመገኘት ስጦታውን አበርክቷል።
የአበበች ጎበና ሰራተኞች ሰብሰብ ብለው ከታካሚዎቻቸው ጋር ጥሩ የበዓል ጊዜን አሳልፈዋል። በበዓል ዝግጅቱ ላይ የተገኙት የማእከሉ ሃላፊ ዶ/ር አናንያ ሰለሞን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው የተሰናዳውን ማዕድ ለሰራተኞች ጋብዘዋል።
"ሰላም አይለየን"
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበሃገራችን ስ 27/ 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን)
በቅድሚያ ለመላው የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሰራተኞችና በመላው ዓለም ለምትገኑ የክርስስትና እምነት ተከታዮችና ኢትዮጵያውያን በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም በፍቅር በጤና አደረሳችሁ ።
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ፅህፈት ቤት ለየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አበበች ጎበና እናቶችና ህፃናት ህክምና ማእከል ለገና በዓል የሚውል 3 (ሶስት) በሬዎችን በስጦታ መልክ አበረከተ።
የበሬ ስጦታውን ያበረከቱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፅህፈት ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ ሞገስ ባልቻ ፣ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ፅህፈት ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ ታረቀኝ ገመቹ ፣ የለሚኩራ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ተስፋዬ ደንድር የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ጤና ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ታደሰ ወዳጆ እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት በአበበች ጎበና ቅጥር ግቢ ውስጥ በመገኘት በሬዎችን አስረክበዋል።
በርክብክቡ ላይ የተገኙት የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አበበች ጎበና እናቶችና ህፃናት ህክምና ማእከል ሀላፊ የሆኑት የማህፀን ፅንስ ስፔሻሊስት ሃኪም ዶ/ር አናኒያ ሰለሞን እንደተናገሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሁሌም ለሚያደርግልን ድጋፍ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው በማለት ተናግረዋል። አያይዘውም የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
በተጨማሪም የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሶሻል ኮሚቴ 2 (ሁለት) በሬዎችን ለገና በዓል ሰራተኛው ከታካሚው ጋር ደስ ብሎት እንዲውል በስጦታ አበርክቷል።
ለካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ለገና በዓል ተረኛ ሰራተኞችና ታካሚዎች በጋራ ሆነው የገና በዓልን የሚያከብሩበት የበሬ ስጦታ መበርከቱ እጅግ ደስ የሚያሰኝ መሆኑ ተጠቁሟል።
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሃገራችን ከፈራቻቸው ቀደምትና ግዙፍ ሆስፒታሎች መካከል በዋናነት የሚጠቀስ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ነው።
"መልካም የገና በዓል"
"ሰላም አይለየን"
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 26/ 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን)
በካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ Integrated Pharmaceuticals Logistics System (IPLS) ስለሰጠና ተሰጠ።
በሁለት ተከፍሎ በተሰጠው ስልጠና ላይ የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አበበች ጎበና የእናቶችና ህፃናት ህክምና ማዕከል ባለሙያዎችም ተሳትፈውበታል።
ከተሳታፊዎች መካከል ሁሉም ኬስቲም አስተባባሪዎች ፣ ነርስ፣ፋርማሲስት እና የላቦራቶሪ ባለሙያ እንዲሁም የተወሰኑ ሀኪሞች ይገኙበታል።
76 የተቋቋሙ ሰራተኞች የተሳተፉበት ስልጠና እጅግ ጠቃሚ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
በአጠቃላይ ስልጠናው አግባባዊ የተቀናጀ የመድሃኒትና የህክምና መገልገያ ግብአቶች አሰራር ሲስተም/ዘዴ በሁለቱም ሆስፒታል ያሉ ባለሙያዎች በቂ ግንዛ እንዲያገኙ ማድረግ ሲሆን ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁም ይህንን የተቀናጀ ስራ ለመስራት ስልጠናውን ሰጥቷል።
ስልጠናው IPLS ምንነት የIPLSዋና ዋና ኮምፖነንቶች ምንነት ፤ በ IPLS ዉስጥ የባለ ድርሻ አካላት ሚና ምን እንደሆነ መድሃኒቶችንና ግብአቶች እንዴት መያዝ እንዳለባቸው በስፋት ይተነትናል።
በተጨማሪም የዳታ ሪኮርድንግ ፣ የዳታ ሪኮረዲን ቱልስ(Bin card,stock card,Model-19,model-22,);
እንዲሁም ዶክመንተ እንዴት መያዝ እንዳለበት
ዲስፔንሰሪ ዩኒት(Des Unit(DUs)ና ሌሎች ክፍሎች እንዴት መድሀኒትና ግብአቶች ከስቶር እንደዳለባቸው ፤መቼ ማዉጣት እንዳለበት
በአጠቃላይ በተቋሙ ላይ የመድሃኒት አያያዝና አጠቃቀም ዙሪያ እንዲሁም የህክምና መገልገያ እቃዎች አጠቃቀምን በተመለከተ ያጠነጠነው ስልጠና ውጤታማ እንደነበረር ከሰልጣኞች ማወቅ ተችሏል ።
የፋርማሲ ዳይሬክቶሬት ሁሌም በሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ የሚሰራቸው ጠንካራ ስራዎች የፋርማሲ ዳይሬክቶሬትን በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደገ ይገኛል። ይህ ስልጠናም ተቋሙ መድሃኒትን አስመልክቶ የሚሰራቸውን ስራዎች በተጠና እና ሳይንሳዊ በሆነ መልኩ እንዲተገብር ይረዳዋል ተብሏል።
"ሰላም አይለየን"
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 26/ 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን)
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የፋርማሲ ዳይሬክቶሬት ለቆዳ ላይ ህመሞች የሚውል
(dermatological extemporaneous compounding preparation) መድሃኒት መቀመም ጀመረ።
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ የፋርማሲ ዳይሬክቶሬት የህብረተሰቡን የመድኃኒት ፍላጎትና አቅርቦት ጥራቱን በጠበቀ መልኩ በተመጣጣኝ ዋጋ አገልግሎቱን ለማድረስ ጠንክሮ እየሰራ ይገኛል።
የየካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ማህበረሰብ አቀፍ የመድሃኒት አቅርቦት የአገልግሎት አድማሱን በማስፋት ለህብረተሰቡ የሚውሉ መድሃኒቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረበ ይገኛል
ይህም ማህበረሰብ አቀፍ ፋርማሲ አገልግሎት ማህበረሰቡ በአቅራቢያው መድሃኒቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ ያገዘው ሲሆን ተቋሙም በራሱ የሚያገኘውን ገቢ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የፋርማሲ ዳይሬክቶሬት ለመጀመሪያ ጊዜ ለቆዳ ህመሞች የሚውል የመድሃኒት ቅመማ (dermatological extemporaneous compounding preparation) በማዘጋጀት ወደ ስራ ገብቷል።
ይህ የመድኃኒት ቅመማ አገልግሎት ለተቋሙም ይሁን ለአከባቢው ማህበረሰብ እጅግ ጠቃሚ በመሆኑ የህብረተሰቡን እንግልትና ድካም እንደሚቀንስ ታምናል።
በተቋሚዠሙ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የመድሃኒት ቅመማ (dermatological extemporaneous compounding preparation) መዘጋጀቱ ለተቋሙ ተጨማሪ የአገልግሎት አድማስ ማስፋፍያ እንደሚሆን ይታመናል።
በዚህ የመድኃኒት ቅመማ ማስጀመሪ ሂደት ላይ ትልቁን አስተዋጽኦ ያበረከቱት ከዶክመንቴሽን እስከ ክፍል ዝግጅት ግብአቶችን በማሟላት እና ስልጠናዎችን በማዘጋጀት ረገድ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተሳትፈውበታል።
የፋርማሲ ዳይሬክቶሬት ፣ የቆዳና አባላዘር ዲፓርትመንት የማኔጅመንት አባላት የኮሞፓወንዲን ኬስ ቲም አባላት እንዲሁም ሌሎች በዚህ የመድሃኒ ቅመማ ማስጀመሪ ላይ በሰፊው በመሳተፋቸው የከበረ ምስጋናችን ይድረሳችሁ ብለዋል ።
"ሰላም አይለየን"
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ታህሳስ 25 / 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን)
የሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ "ሶሻል ኮሚቴ" ለገና በዓል የሚሆን አስቤሳ እያከፋፈለ ይገኛል።
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ሶሻል ኮሚቴ ሁሌም እንሚያደርገው በዓላት ሲቃረብም ይሁን በአዘቦት ቀን የተቋሙን ሰራተኛ የሚያስደስት ነገሮችን እንደሚያደርግ ይታወቃል።
ሶሻል ኮሚቴው የተቋሙ ሰራተኛ በዓልን ደስ ብሎት እንዲያሳልፍ የተለያዩ አስቤዛ እያከፋፈለ ይገኛል በዛሬው እለትም ዱቄትና ዘይት ለሰራተኞች አከፋፍሏል።
ሶሻል ኮሚቴው በራሱ ተነሳሽነት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል ቀን ከለሊት እየሰራ ይገኛል ለዚህም ድካምና ልፋታቸው በዕውነት የከበረ ክብርና ምስጋና ይገባቸዋል።
የሶሻል ኮሚቴ አባላት እንደተናገሩት ከሆነ ለተቋማችን ሰራተኞች ይጠቅሳሉ ይበጃሉ ያልናቸውን ሁሉ ከማድረግ ወደኋላ አንልሞ ሲሉ ተደምጠዋል።
ሶሻል ኮሚቴ ከወዲሁ ለመላው የተቋማችን ሰራተኞች መልካም የገና በአል ይሁንላችሁ ሲል መልካም ምኞቱን ተመኝቷል።
"ሰላም አይለየን"
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ አዲስ አበባ ህዳር 19 / 2016 (ኮሚኒኬሽን ቡድን)
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የጠቅላላ ቀዶ ጥገና ሃኪሞችን Final External Exam አስፈተነ።
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በሃገር አቀፍ ደረጃ ሰፊ ከጤና አገልግሎት አሰጣጡም በተጨማሪም የተማሩ እጅግ የበቁ አንቱታን ያተረፉ ሁሉም በአንድ ድምፀ የሚመሰክሩላቸው የጤና ባለሙያዎችን እያፈራ የሚገኝ አንጋፋና ትልቅ ተቋም እንደሆነ ይታመናል።
ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ ትምህርትን በተመለከተ ከሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ውስጥ የቀዶ ጥገና ህክምና ክፍል አንዱ ክፍል ነው።
በዛሬው ዕለት የተቋቋሙ ከሚኮራበት ዲፓርትመንት መካከል አንዱ የሆነው የቀዶ ጥገና ህክምና ክፍል ብዛታቸው 11የሆኑ የ4ኛ ዓመት የጠቅላላ ቀዶ ጥገና ሬዚዳንት ሃኪሞች በዛሬው ዕለት ከተቋሙ ውጪ በመጡ መዛኛች ተመዝነው አመርቂ ውጤት አምጥተዋ።
የ4ኛ ዓመት የጠቅላላ ቀዶ ጥገና ሬዚዳንት ምዘናውን የሰጡት ከተለያዩ የሃገራችን ክፍል የተወጣጡ ሙሁራኖች ሲሆኑ ከሃገር ውጭም የመጡ መዛኞች ተገኝተውበታል
ምዘናው ጠዋትና ከሰዓት የዘለቀ ሲሆን 11 ዱም የ4ተኛ ዓመት የጠቅላላ ቀዶ ጥገና ፕሬዚደንት ሃኪሞች የተሻለ ውጤት በማምጣት ለሆስፒታሉ ኩራት ሆነዋል ተብሏል።
በሆስፒታሉ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በጠቅላላ ቀዶ ጥገና ስፔሻሊስት ህክምናውን የተከታተሉት ሃኪሞቹ የተሰማቸውን ደስታ ገልፀዋል ።
ምዘናውን አስመልክቶ ከሃገር ውጪ እንዲሁም ከሃገር ውስጥ የተገኙት ሙሁራኞች ተመዛኞቹ የተሻለ ብቃት እንዳላቸው መስክረዋል።
ከምዘናው በኃላ የሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ ከውጭ የመጡ መዛኞች ኘሮቮስቶች ስፔሻሊስት ሃኪሞች የቀዶ ጥገና ህክምና ክፍል ሃላፊዎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በፓዮኔር ዳያግኖስቲክ ሴንተር ስፖንሰር ባደረገው በካሶፒያ ሆቴል የእራት ግብዣ ተከናውነዋል።
በካሶፒያ ሆቴል በተከናወነ የእራት ግብዣ የተለያዩ የሽልማት መርሃግብር የተለያዩ ንግግሮች በተቋሙ ሃላፊዎች እና እንግዶች ተከናውኗል።
የቀዶ ጥገና ክፍል ሃላፊ የሆኑት ዶ/ር ጌታቸው ደስታ ለሁሉም 4ተኛ ዓመት የጠቅላላ ቀዶ ጥገና ሬዘደንቶች የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን ካስተላለፉ በኃላ በነበራቸው የትምህርት ቆይታ ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል። ወደፊትም በሚኖረው የቀዶ ጥገና የትምህርት ክፍል ጠንክረን የምንሰራ ይሆናል ብለዋል።
በእራት ግብዣው ላይ የተገኙት የሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጁ ኘሮቮስቶች እንደተናገሩት ዛሬ ለ4 ዓመታት ለመጀመሪያ ጊዜ የጠቅላላ ቀዶ ጥገና ህክምና የተከታላችሁ ሁሉ በየደረሳችሁበት የተቋማችን አንባሳደር ናችሁ ስሉ ተደምጠዋል።
"ሰላም አይለየን"
