en
Feedback
የማርያም ልጆች ነን

የማርያም ልጆች ነን

Open in Telegram

ማርያም ብሂል መርህ ለመንግስተ ሰማያት

Show more
316
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
-830 days
Posts Archive
ልብሰ ተክህኖን ክህነት የሌለው ሰው መንካትና ማጠብ አይችልም። ሥርዓት አይደለም። በቅንነት አንዳንድ የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት አድርጋችሁት ከነበረ ከእንግዲህ እንዳታደርጉ ትምህርት ይሁናችሁ። ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ ፰ ላይ ከዲያቆናት፣ ከቀሳውስትና፣ ከዚያ በላይ ከሆኑት በስተቀር ንዋየ ቅድሳትን እንዲነኩ አልተፈቀደም። ስለዚህ ካህናት ሆይ ክህነት የሌላቸው ሰዎች ንዋየ ቅድሳትን እንዲነኩና እንዲያጥቡ አታድርጉ። © በመምህር በትረ ማርያም አበባው https://t.me/dn_mezmur

ማቴዎስ 27 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ሲነጋም የካህናት አለቆችና የሕዝቡ ሽማግሎች ሁሉ ሊገድሉት በኢየሱስ ላይ ተማከሩ፤ ² አስረውም ወሰዱት፥ ለገዢው ለጴንጤናዊው ጲላጦስም አሳልፈው ሰጡት። ³ በዚያን ጊዜ አሳልፎ የሰጠው ይሁዳ እንደ ተፈረደበት አይቶ ተጸጸተ፥ ሠላሳውንም ብር ለካህናት አለቆችና ለሽማግሎች መልሶ፦ ⁴ ንጹሕ ደም አሳልፌ በመስጠቴ በድያለሁ አለ። እነርሱ ግን፦ እኛስ ምን አግዶን? አንተው ተጠንቀቅ አሉ። ⁵ ብሩንም በቤተ መቅደስ ጥሎ ሄደና ታንቆ ሞተ። ⁶ የካህናት አለቆችም ብሩን አንሥተው፦ የደም ዋጋ ነውና ወደ መባ ልንጨምረው አልተፈቀደም አሉ። ⁷ ተማክረውም የሸክላ ሠሪውን መሬት ለእንግዶች መቃብር ገዙበት። ⁸ ስለዚህ ያ መሬት እስከ ዛሬ ድረስ የደም መሬት ተባለ። ⁹ በዚያን ጊዜ በነቢዩ በኤርምያስ የተባለው፦ ከእስራኤል ልጆችም አንዳንዶቹ የገመቱትን፥ የተገመተውን ዋጋ ሠላሳ ብር ያዙ፥ ¹⁰ ጌታም እንዳዘዘኝ ስለ ሸክላ ሠሪ መሬት ሰጡት የሚል ተፈጸመ። ¹¹ ኢየሱስም በገዢው ፊት ቆመ፤ ገዢውም፦ የአይሁድ ንጉሥ አንተ ነህን? ብሎ ጠየቀው፤ ኢየሱስም፦ አንተ አልህ አለው። ¹² የካህናት አለቆችም ሽማግሎችም ሲከሱት ምንም አልመለሰም። ¹³ በዚያን ጊዜ ጲላጦስ፦ ስንት ያህል እንዲመሰክሩብህ አትሰማምን? አለው። ¹⁴ ገዢውም እጅግ እስኪደነቅ ድረስ አንዲት ቃል ስንኳ አልመለሰለትም። ¹⁵ በዚያም በዓል ሕዝቡ የወደዱትን አንድ እስረኛ ሊፈታላቸው ለገዢው ልማድ ነበረው። ¹⁶ በዚያን ጊዜም በርባን የሚባል በጣም የታወቀ እስረኛ ነበራቸው። ¹⁷ እንግዲህ እነርሱ ተሰብስበው ሳሉ ጲላጦስ፦ በርባንን ወይስ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤ ¹⁸ በቅንዓት አሳልፈው እንደ ሰጡት ያውቅ ነበርና። ¹⁹ እርሱም በፍርድ ወንበር ተቀምጦ ሳለ ሚስቱ፦ ስለ እርሱ ዛሬ በሕልም እጅግ መከራ ተቀብያለሁና በዚያ ጻድቅ ሰው ምንም አታድርግ ብላ ላከችበት። ²⁰ የካህናት አለቆችና ሽማግሎች ግን በርባንን እንዲለምኑ ኢየሱስን ግን እንዲያጠፉ ሕዝቡን አባበሉ። ²¹ ገዢውም መልሶ፦ ከሁለቱ ማንኛውን ልፈታላችሁ ትወዳላችሁ? አላቸው፤ እነርሱም፦ በርባንን አሉ። ²² ጲላጦስ፦ ክርስቶስ የተባለውን ኢየሱስን እንግዲህ ምን ላድርገው? አላቸው፤ ሁሉም፦ ይሰቀል አሉ። ²³ ገዢውም፦ ምን ነው? ያደረገው ክፋት ምንድር ነው? አለ፤ እነርሱ ግን፦ ይሰቀል እያሉ ጩኸት አበዙ። ²⁴ ጲላጦስም ሁከት እንዲጀመር እንጂ አንዳች እንዳይረባ ባየ ጊዜ፥ ውኃ አንሥቶ፦ እኔ ከዚህ ጻድቅ ሰው ደም ንጹሕ ነኝ፤ እናንተ ተጠንቀቁ ሲል በሕዝቡ ፊት እጁን ታጠበ። ²⁵ ሕዝቡም ሁሉ መልሰው፦ ደሙ በእኛና በልጆቻችን ላይ ይሁን አሉ። ²⁶ በዚያን ጊዜ በርባንን ፈታላቸው፥ ኢየሱስን ግን ገርፎ ሊሰቀል አሳልፎ ሰጠ። ²⁷ በዚያን ጊዜ የገዢው ወታደሮች ኢየሱስን ወደ ገዢው ግቢ ውስጥ ወሰዱት ጭፍራውንም ሁሉ ወደ እርሱ አከማቹ። ²⁸ ልብሱንም ገፈው ቀይ ልብስ አለበሱት፥ ²⁹ ከእሾህም አክሊል ጎንጉነው በራሱ ላይ፥ በቀኝ እጁም መቃ አኖሩ፥ በፊቱም ተንበርክከው፦ የአይሁድ ንጉሥ ሆይ፥ ሰላም ለአንተ ይሁን እያሉ ዘበቱበት፤ ³⁰ ተፉበትም መቃውንም ይዘው ራሱን መቱት። ³¹ ከዘበቱበትም በኋላ ቀዩን ልብስ ገፈፉት፥ ልብሱንም አለበሱት ሊሰቅሉትም ወሰዱት። ³² ሲወጡም ስምዖን የተባለው የቀሬናን ሰው አገኙ፤ እርሱንም መስቀሉን ይሸከም ዘንድ አስገደዱት። ³³ ትርጓሜው የራስ ቅል ስፍራ ወደሚሆን ጎልጎታ ወደሚባለው ስፍራ በደረሱ ጊዜም፥ ³⁴ በሐሞት የተደባለቀ የወይን ጠጅ ሊጠጣ አቀረቡለት፤ ቀምሶም ሊጠጣው አልወደደም። ³⁵ ከሰቀሉትም በኋላ ልብሱን ዕጣ ጥለው ተካፈሉ፥ ³⁶ በዚያም ተቀምጠው ይጠብቁት ነበር። ³⁷ ይህ ኢየሱስ የአይሁድ ንጉሥ ነው የሚል የክሱን ጽሕፈት ከራሱ በላይ አኖሩ። ³⁸ በዚያን ጊዜ ሁለት ወንበዶች አንዱ በቀኝ አንዱም በግራ ከእርሱ ጋር ተሰቀሉ። ³⁹ የሚያልፉትም ራሳቸውን እየነቀነቁ ይሰድቡት ነበርና፤- ⁴⁰ ቤተ መቅደስን የምታፈርስ በሦስት ቀንም የምትሠራው፥ ራስህን አድን፤ የእግዚአብሔር ልጅስ ከሆንህ ከመስቀል ውረድ አሉት። ⁴¹ እንዲሁም ደግሞ የካህናት አለቆች ከጻፎችና ከሽማግሎች ጋር እየዘበቱበት እንዲህ አሉ። ⁴² ሌሎችን አዳነ፥ ራሱን ሊያድን አይችልም፤ የእስራኤል ንጉሥ ከሆነ፥ አሁን ከመስቀል ይውረድ እኛም እናምንበታለን። ⁴³ በእግዚአብሔር ታምኖአል፤ የእግዚአብሔር ልጅ ነኝ ብሎአልና ከወደደውስ አሁን ያድነው። ⁴⁴ ከእርሱ ጋር የተሰቀሉት ወንበዶች ደግሞ ያንኑ እያሉ ይነቅፉት ነበር። ⁴⁵ ከስድስት ሰዓትም ጀምሮ እስከ ዘጠኝ ሰዓት ድረስ በምድር ሁሉ ላይ ጨለማ ሆነ። ⁴⁶ በዘጠኝ ሰዓትም ኢየሱስ፦ ኤሎሄ ኤሎሄ ላማ ሰበቅታኒ? ብሎ በታላቅ ድምፅ ጮኸ። ይህም፦ አምላኬ አምላኬ፥ ስለ ምን ተውኸኝ? ማለት ነው። ⁴⁷ በዚያም ከቆሙት ሰዎች ሰምተው፦ ይህስ ኤልያስን ይጠራል አሉ። ⁴⁸ ወዲያውም ከእነርሱ አንዱ ሮጠ፤ ሰፍነግም ይዞ ሆምጣጤ ሞላበት፥ በመቃም አድርጎ አጠጣው። ⁴⁹ ሌሎቹ ግን፦ ተው፥ ኤልያስ መጥቶ ያድነው እንደ ሆነ እንይ አሉ። … ⁵¹ እነሆም፥ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ከላይ እስከ ታች ከሁለት ተቀደደ፥ ምድርም ተናወጠች፥ ዓለቶችም ተሰነጠቁ፤ ⁵² መቃብሮችም ተከፈቱ፥ ተኝተው ከነበሩትም ከቅዱሳን ብዙ ሥጋዎች ተነሡ፤ https://t.me/dn_mezmur

ለካስ ሰይጣን የልብን ያውቃል! ልብ ሁሉንም ነገር ያደርጋል። እምነታችን ሳይቀር ከልብ ነው። አቨው እንደሚናገሩት "ልብ ካላየ አይን አያይም" ሲሉ ይደመጣሉ። ለዚህም ምሳሌ የሚሆነን በአብነት ትምህርት ቤት ውስጥ ልጆች መልእክተ ዮሐንስን ሲማሩ "ነ" ን "ኀ" እንዲሁም "ሸ"ን "ቨ" አድርጎ መጥራት የተለመደ ነው። ምክንያቱም የፊደላቸው ቅርጽ ስለሚመሳሰል ይሆናል ብየ እገምታለሁ። ይህን ይዘው ነው አባቶች ተማሪው ከአንድ ሁለቴ ነገረውት ካላስተካከለ ፊደሉን ከልብህ እየው "ልብ ካላየ አይን አያይም" የሚሉበት ምክንያት ።ሌላ ብዙ ምክንያት ቢኖረውም። ልብ የመልካም ሥራዎችም የክፍ ሥራዎችም ቋት ነው። ይህን ታላቅ ልብ ሰይጣን ያውቀዋል ሲሉኝ ግራ ገባኝ። መጽሐፍ "እግዚአብሔር ልብንና ኩላሊትን ይመረምራል" ይላል ይህ ደግሞ ሰይጣን ያውቃል ይላል። አሁንም በድጋሜ ሰይጣን ክርስቶስ በልብህ መሆን አለመሆኑን ያውቃል። ምክንያቱም ስትቆጣ ስትጮህ የማይረባ ነገር ስትናገር ሲያይህ እግዚአብሔር በአንተ ዘንድ እንደሌለ ያውቃል።ከነፍስ ምኞት ለሥጋ ምኞት ስትገዛ አዎ ሰይጣን ልቡናህን ያውቃል። ያን ጊዜ ወደ ልብህ ገብቶ ውስጥህን ይበረብረዋል። ያን ጊዜ ልብህን ከማወቅ ባሻገር ልብህን ይቆጣጠረውና በአንተ ልብ እንዳታስብ፤ምንም አይነት መልካም ሥራ እንዳትሠራ ያደርግሃል።ታዲያ ልቤን ሰይጣን አያውቀውም ትለኛለህ! ማንኛውም ሰው መልካም ነገር አላደረገም ማለት ልቡን ለሰይጣን መነሃሪያ አስረክቧል ማለት እንደሆነ ጥርጥር የለውም። ምናልባትም ሰዓትን ፣ቀናትን ፣ዓመታትንና ዘመናትን እያፈራረቀ እየኖረ ሊሆን ይችላል። ነገር ግን "መኖር" የሚለው ቃል በራሱ ትርጓሜ ያሻዋል። ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ "በመንፈሳዊው መንገድ ላይ የምትጓዙ ከሆነ እንዳትወድቁ በራሳችሁ አትደሰቱ፤ ትዕቢትን የምንፈራው እድገታችንን እንዳያቆመው ብቻ ሳይሆን እንዳይጥለንም ነው። ዲ/ን መዝሙር 14-01-17 ዓ.ም ኢትዮጵያ https://t.me/dn_mezmur

የነፍስ ምግብ ማውጫ ሁሉም በየተራ ስለሚተረክ ሸር አድረጉ ለሌሎችም እንዲዳረስ

የነፍስ ምግብ ቁጥር 1.m4a5.44 MB

ትረካ

ሉቃስ 1 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁶ በስድስተኛውም ወር መልአኩ ገብርኤል ናዝሬት ወደምትባል ወደ ገሊላ ከተማ፥ ²⁷ ከዳዊት ወገን ለሆነው ዮሴፍ ለሚባል ሰው ወደ ታጨች ወደ አንዲት ድንግል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ፥ የድንግሊቱም ስም ማርያም ነበረ። … ²⁹ እርስዋም ባየችው ጊዜ ከንግግሩ በጣም ደነገጠችና፦ ይህ እንዴት ያለ ሰላምታ ነው? ብላ አሰበች። ³⁰ መልአኩም እንዲህ አላት፦ ማርያም ሆይ፥ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋ አግኝተሻልና አትፍሪ። ³¹ እነሆም፥ ትፀንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ፥ ስሙንም ኢየሱስ ትዪዋለሽ። ³² እርሱ ታላቅ ይሆናል የልዑል ልጅም ይባላል፥ ጌታ አምላክም የአባቱን የዳዊትን ዙፋን ይሰጠዋል፤ ³³ በያዕቆብ ቤትም ላይ ለዘለላም ይነግሣል፥ ለመንግሥቱም መጨረሻ የለውም። ³⁴ ማርያምም መልአኩን፦ ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል? አለችው። ³⁵ መልአኩም መልሶ እንዲህ አላት፦ መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል። ³⁶ እነሆም ዘመድሽ ኤልሳቤጥ፥ እርስዋ ደግሞ በእርጅናዋ ወንድ ልጅ ፀንሳለች፥ ለእርስዋም መካን ትባል ለነበረችው ይህ ስድስተኛ ወር ነው፤ ³⁷ ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና። ³⁸ ማርያምም፦ እነሆኝ የጌታ ባሪያ እንደ ቃልህ ይሁንልኝ አለች። መልአኩም ከእርስዋ ሄደ።

የክርስቲያን የቅድስና ማዕረግ 1አንብዕ እንባ ከአይናቸው እንደ ሰንውሀ ሳያቋርጥማፍሰስ ነው 2 ኩነኔ በማዕረጋት ሂደት ኩነኔ ማለት ስጋን ለነፍስ ማስገዛት ነው 3 ፍቅር እግዚአብሄር ከመፍጠር ያልናቀውን ፍጥረት ሁሉንም እኩል መውደድ 4 ሑሰት ካሉበት ቦታ ሁነው ካሰቡት መድረስ ነው እነዚህ በንፅሐ ነፍስ የሚገኙ አራቱ ማዕረጋት ሲሆኑ 5 ንፃሬ መላእክት በአፀደ ስጋ ሆነው መላእክትን በየከተማቸውና በየቦታቸው ያያሉ 6 ተሰጥሞ ብርሀን ይህ ደግሞ የእግዚአብሔር የባህሪ ገንዘብ የሆነው በሚያስደንቅ ብርሀን ውስጥ መዋኘት ነው 7 ከዊነ እሳት የመጨረሻ ማእረግ ሲሆን እዚህ ደረጃ የደረሱ ቅዱሳን ሰውነታቸው ለአጋንንት  የሚያቃጥልና የማይቀርብ ይሆናል እነዚህ ደግሞ በንፅሐ ልቦና የሚገኙ ሶስቱ መዓረጋት ናቸው 8 ጽማዌ ዝም ፀጥ ማለት መናገር መቀባጠር መተው 9 ልባዌ ልብ ማድረግ ማስተዋል በጥልቀት ነገሮችን መረዳት ማለት ነው 10 ጣዕመ ዝማሬ ሳይሰለቹና ሳይቸኩሉ ምስጢርና ትርጓሜውን እያወጡ እና እያወረዱ በንቁ ህሊና ማመስገን መፀለይ ነው እነዚህ ደግሞ በንፅሀ ስጋ የሚገኙ ሶስቱ መአረጋት ናቸው

በስድስተኛውም ወር .m4a18.06 MB

መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ዶግማ፡ እግዚአብሔር (ፈጣሪ) የአካል ሦስትነት አለው፡፡በ መለኮት፣ በመፍጠር፣ በሥልጣን፣ በአገዛዝ፣ በፈቃድ  አንድ ነው፡፡ በሦስትነቱ አብ፤ ወልድ፤ መንፈስ ቅዱስ ሲባል በአንድነቱ አንድ መለኮት አንድ እግዚአብሔር ይባላል፡፡ ቀኖና  በሃይማኖት አባቶች ወይም በቅዱስ ሲኖዶስ አማካኝነት እንደጊዜው ሁኔታ የሚሻሻል_በመሆኑ_የሚጨመርበት_የሚቀነስለት_ነው፡፡ ለምሳሌ እኛ ኦርቶዶክሳውያን የምንጠመቀው ሴት በሰማንያ ወንድ በአርባ ቀናችን ነው፡፡ የተወለዱ ሕጻናት ሴቷ ሰማንያ ወንዱም አርባ ቀን ሳይሞላቸው ቢታመሙና በሽታው አስጊ ከሆነ በ10፣ በ20፣ በ30…ቀናቸው መጠመቅ ይችላሉ ቀኖና ነውና፡፡ ትውፊት አንድ ሰው ከእርሱ በፊት ከነበረው ማኅበረሰብ የሚቀበለውና የሚወርሰው እምነት፣ ባህል፣ የአኗኗር ዘይቤ፣ …ወዘተ ሲሆን ሒደቱም በዚህ ሳያበቃ እርሱም በተራው ለተተኪው የሚያስተላልፈው ነው፡፡ ለምሳሌ በሚዳሰስ መንገድ የሚተላለፍ ትውፊት በሆነ ዘመን ተሠርተው አገልግሎት የሚሰጡ አብያተ ክርስቲያናት፣ ንዋየተ ቅድሳት እና ቅዱሳት መጻሕፍትን የመሳሰሉት ቅርጻቸውንና ይዘታቸውን ሳይለውጡ ከትውልድ ወደ ትውልድ ተጠብቀው የሚተላለፉበት የትውፊት መተላለፊያ መንገድ ነው፡፡ ከእህታችን ሰላም ተሰማ 09-01-17 ዓ.ም https://t.me/dn_mezmur

“ሰዎች ሁሉ የሚያውቁትና የሚያነቡት በልባችን የተጻፈ መልእክታችን እናንተ ናችሁ።” — 2ኛ ቆሮ 3፥2 https://t.me/dn_mezmur

#እርቃን_ገላዎች       አንብቡት  #ሼር ሁለት ወጣት ሴቶች ግማሽ አካላታቸውን ብቻ የሚሸፍን ልብስ ለብሰው ስብሰባ ቦታ ደረሱ ። የስብሰባው መሪ በጥሩ ፈገግታ ተመለከታቸውና እንዲቀመጡ ጋበዛቸው ። ከዚያም እነዚህ ሴቶች በህይወት ዘመናቸው ሁሉ ሊረሱት የማይችሉትን መልዕክት ተናገራቸው ። ትኩር ብሎ አይናቸውን እያየ እንዲህ አላቸው ፣ "ሴቶች ፈጣሪ የፈጠራቸው በጣም አስፈላጊ ነገሮች ሁሉ በሚገባ የተሸፈኑና እንዲሁም ለማየትና ለማግኘት ብዙ ጥረት የሚጠይቁ ናቸው ። ፩ አልማዞችን የት ነው የምታገኙአቸው ? ከመሬት በታች ከብዙ ጥልቀት በኋላ ተሸፍነውና ተደብቀው ። ፪ ወርቆችን የት ነው የምታገኟቸው ? ከማዕድናቶች በታች በትላልቅ ድንጋዮች ተሸፍነው ነው ። እነሱን ለማግኘት ወደታች ብዙ ርቀት ጠንክራችሁ መቆፈር ፣ መስራትና መፈለግ አለባችሁ ። ከዚያም ፊታቸውን ትኩር ብሎ እያየ ንግግሩን ቀጠለ ። "የእናንተ ሰውነት አስፈሪና ልዩ ነው ። የእናንተ ሰውነት ከአልማዝ ፣ ከወርቅና ከሌሎች የበለጠ ውድና ማራኪ ነው ። ስለዚህ እናንተም በሚገባ ልትሸፈኑ ይገባል ። ንግግሩን ቀጠለ ፣ ይህንን ውድ ሃብታችሁን ልክ እንደ አልማዝና ወርቅ በሚገባ ከሸፈናችሁና በቀላሉ እንዳይገኝ ካደረጋችሁ ታማኞችና አስፈላጊውን የማዕድን ማውጫ መሳሪያዎች ያላቸው ማዕድን አውጪ ድርጅቶች እናንተን ለማግኘትና ለዘመናት የማዕድን ማውጣት ስራቸውን ለመስራት ወደ እናንተ ይጎርፋሉ ። በመጀመሪያ ከሃገራችሁ መንግስት( ቤተሰባችሁ) ጋር ይገናኛሉ ፣ ፕሮፌሽናልና ህጋዊ ፊርማ (ህጋዊ ጋብቻ) ይፈራረማሉ ። ነገር ግን የህንን ውድና ማራኪ ሃብታችሁን በሚገባ ባትሸፍኑትና ባትጠብቁት ሁልጊዜ ህገወጥ ማዕድን አውጪዎች ወደ እናንተ እንዲመጡና ውድ ማዕድናችሁን በህገወጥ መንገድ እንዲያወጡት ትማርካላችሁ ። ከዚያም ምንም ሳይጥሩና ሳይደክሙ በቀላሉ ውድ ሃብታችሁን ይወስዳሉ ማለት ነው ። ስለዚህ ሴቶች እባካችሁ ሰውነታችሁን በሚገባ ሸፍኑ ። ይህን ካደረጋችሁ ፕሮፌሽናሎችና ህጋዊ ማዕድን አውጪዎች እናንተን ያሳድዳሉ ።"  እህታቹሁ ፍቅርተ ኢየሱስ እስቲ ሁላችንም ወንዶች እህቶቻቹሁ፤ሚስቶቻችንን ፣ ጓደኞቻችንንና ልጆቻችንን እንድሸፍኑ አስተምራቸው ።       የቅዱሳን አምላክ ማስተዋልን ይስጠን

ውድ
"የዝጉ መንገድ"
እና
"የማርያም ልጆች ነን"
ቻናል ተከታታዮች በእግዚአብሔር ስም እንደምን አላችሁ? በእነዚህ በሁለቱ ቻናሎች የሚለቀቁትን ዘና ሳቅ እያደረጉ እውቀት የሚያስጨብጡትን ቻናሎች ስለተቀላቀላችሁ ከልብ እናመሰግናለን። "ምንም ሳትደክሙ የሰጠኋችሁን ትምህርት በነጻ ስጡ" እንዲል መጽሐፍ እናንተም እንዲሁ በነጻ ያገኛችሁትን ትምህርት ለሰዎች ይዳረስ ዘንድ ሸር ማድረጋችሁን እንዳትረሱ። በዚህ ቻናል ውስጥ እስካሁን ሲለቀቁ ከነበሩት በተጨማሪ በተጠናከረ መልኩ ቻናሉን እና የሚለቀቁ ጽሑፎችን ለማሳደግ ስላሰብን እገዛችሁን ከአሁን እንጠይቃለን። የሚለቀቁ መልክቶች 1. ሰኞ፦   ምክረ አበው፣ ብሒለ አበው ፣ምሳሌያዊ አነጋገሮች 2. ማክሰኞ፦ ሥነ ልቦናዊ የሆኑ ጽሑፎች 3. ዕሮብ፦    ጥያቄ እና መልስ 4. ሐሙስ፦ የቤተ ክርስቲያን ዶግማ፣ቀኖና እና ትሩፋት 5. አርብ፦     ነገረ ክርስቶስ እና  ነገረ አርብ 6. ቅዳሜ፦  እመቤታችን እና ቅዱሳት አንስት 7. እሑድ፦ መጽሐፍ ቅዱስ ጽሑፍ እና ነገረ ሰንበተ ክርስቲያን እነዚህንና በስም ያልተጠቀሱ በርካታ መልዕክቶችን የምናስተላል ይሆናል። የሚተላለፈውም በጽሑፍ መልክ፤በ Audio፣በ Video በሌሎች ነገሮችም ስለሆነ በምትፈልጉት ሁሉ ማገዝ የምትፈልጉ በውስጥ መስመር አናግሩኝ። ዲ/ን መዝሙር ንጉሴ 0929181733 @mezwell በእነዚህ አድራሻዎች ማግኘት ትችላላችሁ። መልካም ቀን ተመኘሁላችሁ። https://t.me/dn_mezmur

መክብብ 11 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እንጀራህን በውኃ ፊት ላይ ጣለው፥ ከብዙ ቀን በኋላ ታገኛዋለህና። ² ለሰባት ደግሞም ለስምንት እድል ፈንታን ክፈል፥ በምድር ላይ የሚሆነውን ክፉ ነገር ምን እንደሆነ አታውቅምና። ³ ደመናት ዝናብ በሞሉ ጊዜ በምድር ላይ ያፈስሱታል፤ ዛፍም ወደ ደቡብ ወይም ወደ ሰሜን ቢወድቅ፥ ዛፉ በወደቀበት ስፍራ በዚያ ይኖራል። ⁴ ነፋስን የሚጠባበቅ አይዘራም፥ ደመናንም የሚመለከት አያጭድም። ⁵ የነፋስ መንገድ እንዴት እንደ ሆነች አጥንትም በእርጉዝ ሆድ እንዴት እንድትዋደድ እንደማታውቅ፥ እንዲሁም ሁሉን የሚሠራውን የእግዚአብሔርን ሥራ አታውቅም። ⁶ ወይም ይህ ወይም ያ ማናቸው እንዲበቅል ወይም ሁለቱ መልካም እንዲሆኑ አታውቅምና በማለዳ ዘርህን ዝራ፥ በማታም እጅህን አትተው። ⁷ ብርሃን ጣፋጭ ነው ፀሐይንም ማየት ለዓይን መልካም ነው። ⁸ ሰው ብዙ ዘመን በሕይወት ቢኖር በሁሉም ደስ ይበለው፤ ሆኖም የጨለማውን ዘመን ያስብ፥ ብዙ ቀን ይሆናልና። የሚመጣው ነገር ሁሉ ከንቱ ነው። ⁹ አንተ ጐበዝ፥ በጕብዝናህ ደስ ይበልህ፥ በጕብዝናህም ወራት ልብህን ደስ ይበለው፥ በልብህም መንገድ ዓይኖችህም በሚያዩት ሂድ፤ ዳሩ ግን ስለዚህ ነገር ሁሉ እግዚአብሔር ወደ ፍርድ እንዲያመጣህ እወቅ። ¹⁰ ሕፃንነትና ጕብዝና ከንቱዎች ናቸውና ከልብህ ኀዘንን አርቅ፥ ከሰውነትህም ክፉን ነገር አስወግድ። https://t.me/dn_mezmur