en
Feedback
ትብል ተዋሕዶ

ትብል ተዋሕዶ

Open in Telegram

🔊 "ለእመ ረሳእኩኪ ቤተክርስቲያን ለትርስአኒ የማንየ" ❖ የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ✞ ትምህርቶችን፥ ✞ እለታዊ ዜናዎችን፥ ✞ የየዕለቱን ስንክሳር፥ ✞ ቅዱሳን ስዕላት፥ ✞ ዝክረ ቅዱሳን እና ✞ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን የሚያገኙበት ቻናል ነው። በዚህ ቦት ያገኙናል ፤ @demesetewahedo_bot

Show more
521
Subscribers
No data24 hours
+37 days
+2230 days
Posts Archive
🌹እንኳን ለኅዳር ጽዮን ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!🌹 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድ
🌹እንኳን ለኅዳር ጽዮን ማርያም አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!🌹 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ሃያ አንድ በዚች ቀን የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓልዋ መታሰቢያ ነው።እንዲሁም አክሱም ጽዮን የእመቤታችን ጽላት የገባችበት ዓመታዊ ታላቅ በዓል ነው፤ በዚህች ዕለት ታቦተ ጽዮን ከነበረችበት ድንኳን ወጥታ ማንም ካህን ሳይሸከማት በተአምራት አብርሃና አጽብሓ ወዳሠሩላት ቤተ መቅደስ ራሷ በመንፈስ ቅዱስ ገብታ ተገኘች። ሰላም ለኪ ማርያም እምነ ፥ ዘሰመይናኪ ጸወነ፥ ሶበ እምርኁቅ ርእየ ዘጽላሎትኪ ስነ፥ ለቢሶ ዳዊት ልብሰ ክብር ዘየሐይድ ዐይነ፥ ቅድመ ታቦተ ሕግ ኀለየ ወዓዲ ዘፈነ። የብርሃን እናቱ ድንግል ወላዲተ አምላክ ክብርት እመቤታችን ጽዮን ማርያም ከበዓሏ ረድኤት በረከት ትክፈለን፤ የዓሥራትን ሀገሯን ቅድስት ኢትዮጵያን ትጠብቅልን ሰላም ፍቅር ታድርግልን። አሜን! ╔═══════ ✞ ═══════╗ 📚JOIN: @demesetewahedo ╚═══════ ✞ ═══════╝

🔔 ዘኬዎስ አጭር ባይሆን? ዘኬዎስ በማጠሩ ምክንያት በኢያሪኮ እያለፈ ያለውን ክርስቶስን ለማየት ተቸገረ:: ሕዝቡ ብዙ ነውና የቆሙት ሁሉ ጌታን ከማየት ከለሉት:: የሾላ ዛፍ ላይ ወጥቶ ጌታን ለማየት ሲሞክር ጌታ አሻቅቦ አየው:: እሱ ዛፍ ላይ ጌታን ሊያይ እንጂ ሊታይ አልወጣም:: ጌታ ሊታዩ ከሚሞክሩ ይልቅ ሊያዩት የሚሹትን ይወዳልና ዘኬዎስን ጠራው:: ከምድር ቆመን ዓይናችንን አንጋጥጠን ማረን የምንለው ጌታ ዘኬዎስን ከምድር ሆኖ ወደ ላይ እያየ ና ልማርህ አለው:: "ዛሬ በቤትህ እውል ዘንድ ይገባኛል" አለው:: ጌታ ወደ ቤቱ ገባ:: ለዘኬዎስ ቤት መዳን ሆነለት:: ዘኬዎስ አጭር ባይሆን ኖሮ ከሰዎች ጋር እየተጋፋ ጌታን ያይ ይሆናል እንጂ በጌታው ዓይን ለመታየት የሚያበቃ ትጋት አያሳይም ነበር:: ምናልባትም ሰዎችን ገለል በሉ እያለ በኩራት ሲጋፋ ከአንዱ ጋር ሲጣላ ሊቆይ ይችል ነበር:: ዘኬዎስ አጭር ባይሆን ከዛፍ ላይ አይወጣም ነበር::  ዘኬዎስ አጭር ባይሆን የሠራዊት አምላክ ወደ ቤቱ አይገባም ነበር:: በኪሩቤል ላይ የሚቀመጠው ንጉሥ በቤቱ ወንበሮች ላይ የተቀመጠው ዘኬዎስ በማጠሩ ምክንያት ነው:: የዘኬዎስ ነፍስ የዳነው በቁመቱ ማጠር ነበር:: እግዚአብሔር የመዳኑን ቀን የቆረጠለት ቁመቱን ሲያሳንሰው ነበር:: በምድር በመጽሐፍ ቅዱስ በሰማይ በሕይወት መዝገብ ስሙ የተጻፈው ዘኬዎስ አጭር በመሆኑ ነው:: ስለ ቁመት የማወራ እንዳይመስልህ:: እግዚአብሔር ለነፍሳችን መዳን የሚያሳጥርብን ብዙ ነገር አለ:: እንደ ዘኬዎስ ቁመትህ አጭር ባይሆን የሚያጥርህ ነገር ግን አይጠፋም:: ይሄ ጎደለኝ የምትለው ከሰዎች አነስኩበት የምትለው ነገር አንዳች ነገር የለም? እሱን ማለቴ ነው:: ይሄ ይጎድለኛል ከሰው አንሳለሁ እያልክ አትማረር:: እጥረትህ መክበሪያህ ነው:: ጉድለትህም መዳኛህ ነው:: እግዚአብሔር ያጎደለብህ የመሰለህ ነገር ወደ ዛፍ እንድትወጣ ምክንያትህ ይሁን:: በጉድለትህ እንደ ዘኬዎስ ከፍ በልበት:: ያኔ ሰዎች አንተን አንጋጠው ከማየት ውጪ አማራጭ አይኖራቸውም:: ፈጣሪ በፍቅሩ ይይህ እንጂ ሰዎች ወዳንተ ያዘነብላሉ::  በቤትህ መዳን ይሆንልሃል:: ከዚያም ስላጠረህ ስለጎደለህ ነገር ፈጣሪህን ስታመሰግነው ትኖራለህ:: እመነኝ አንዳንድ ጉድለቶች እድሎች ናቸው:: ዘኬዎስ አጭር ባይሆን ይሄኔ በሾላው ዛፍ ጥርሱን እየፋቀ ይቀር ነበር::      ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

photo content
+1

✞✞✞ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ፡፡ አሜን ፡፡ ✞✞✞ ✞✞✞ እንኩዋን ለኃያል ሰማዕት "ማር ቴዎድሮስ" እና "ቅዱስ አንያኖስ" ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✞✞✞ +"+ ቅዱስ ቴዎድሮስ ማር ሰማዕት +"+ =>በቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት አለቅነት ከተሰጣቸው ሰማዕታት አንዱ የሆነው ማር ቴዎድሮስ የተወለደው በምድረ አንጾኪያ (ሶርያ) በ3ኛው መቶ ክ/ዘ ነው:: አባቱ ዮሐንስ በትውልድ ግብጻዊ የሆነ ክርስቲያን ነው:: እናቱ ግን አስቸጋሪና ጣዖት አምላኪ ሶርያዊት ነበረች:: +ባልና ሚስት አብረው ሲኖሩ ሚስት ባሏ ክርስቲያን መሆኑን አታውቅም ነበር:: ቴዎድሮስ (የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው) በተወለደ ጊዜ ግን ጠብ ተነሳ:: እሱ ክርስትና ለማስነሳት: ሚስት ደግሞ ወደ ጣዖት ቤት ለመውሰድ ተጋጩ:: ሚስት ወገኖቿ ባለስልጣኖች ናቸውና ልጁን ቀምታ ባሏን ዮሐንስን ወደ ግብፅ አሳደደችው:: +ዮሐንስ በስደት ባለበት ሃገር ስለ ልጁ ፈጽሞ ይጸልይ: ያለቅስም ገባ:: እግዚአብሔር ደግሞ ልመናውን ሰማ:: ማር ቴዎድሮስ ወጣት በሆነ ጊዜ ማንም ሳይጠራው ወደ ቤተ ክርስቲያን ሔዶ ተማረ: ተጠመቀ:: ዕለት ዕለትም ጾምና ጸሎትን ከምጽዋት ጋር ያበዛ: ድንግልናውን ለመጠበቅ ይተጋ ነበር:: +በዛው ልክ ደግሞ ገና በ20 ዓመቱ በጉልበቱ ኃያል: በውበቱም ደመ ግቡ: በጠባዩም ገራገር ነበርና ተወዳጅ ነበር:: ነገሥታቱም የአንጾኪያ የጦር ሠራዊት አለቃ አድርገው ሾሙት:: እነሆ እስከ ዛሬ "የሠራዊት አለቃ" ተብሎ ይጠራል:: +ማር ቴዎድሮስ በተሳተፈባቸው ጦርነቶች ሁሉ ተሸንፎ አያውቅም:: ይልቁኑ የነገሥታቱን (የጠላት) ልጆች በመማረክ ነው የሚታወቀው:: እንዲያውም አንድ ጊዜ ከአሕዛብ ጋር በተደረገ ጦርነት ብቻውን አሸንፏቸዋል:: +የፋርስ ሰዎች ሊዋጉ ሲመጡ መልአክ ከሰማይ ወርዶ ሰይፍ ሰጠው:: ፋርሶችን "በከንቱ ከምትጠፉ ወደ ሃገራችሁ ተመለሱ" አላቸው:: እነርሱ ግን ተሳለቁበት:: ከፈረሱ ወርዶ ወደ ምስራቅ ዙሮ ጸልዮ በመስቀል አማተበ:: በመካከላቸው ገብቶም በመልአኩ ሰይፍ ለወሬ ነጋሪ ሳያስቀር አጠፋቸው:: +አንድ ቀን ወደ አንድ ከተማ ቢገባ ዘንዶ ሲመለክ አገኘ:: ይባስ ብሎ የአንዲት ክርስቲያን ልጆችን ለመስዋዕትነት ሲያቀርበቧቸው ተመለከተ:: በስመ ሥላሴ አማትቦ: በፈረሱ ላይም ተቀምጦ ዘንዶውን በጦር ገደለው:: የዘንዶውም ርዝመት 24 ክንድ ነበር:: +ከነገር ሁሉ በሁዋላ ቅዱስ ቴዎድሮስ ስለ አባቱ ወሬ ሰምቶ: ካለበት ሥፍራ አፈላልጎ አግኝቶ ደስ አሰኘው:: እስኪያርፍ አብሮት ቆይቶ: ቀብሮት ወደ አንጾኪያ ሲመለስ ግን የሚያሳዝን ነገር ጠበቀው:: +ክርስቶስ ተክዶ: ጣዖት ቁሞ: አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለው: የክርስቲያኖች ደም ፈሶ: ከተማዋ በግፍ ተሞልታ ተመለከተ:: እርሱም በዚያች ሰዓት መወሰን ነበረበትና አደረገው:: የሁሉ ሠራዊት አለቃ ቢሆንም የክብር ልብሱን አውልቆ: ባጭር ታጥቆ በንጉሡ ዲዮቅልጢያኖስ ፊት ቆመ:: +ማር ቴዎድሮስ በአደባባይ እንዲህ ተናገረ:- "አንሰ አመልኮ ለክርስቶስ ንጉሠ ስብሐት በኩሉ ልብየ: ወእሠውዕ ሎቱ - እኔስ የክብር ባለቤት ክርስቶስን በፍጹም ልቤ አመልከዋለሁ: ለእርሱም ብቻ እሠዋለሁ::" ንጉሡ በቁጣ መሬት ላይ ጥለው እንዲደበድቡት አዘዘ:: ወታደሮቹ ደሙ እስኪንጠፈጠፍ ገረፉት:: +በብዙ መክፈልተ ኩነኔ አሰቃይተው በእሳት አቃጠሉት:: እርሱ ግን በጸሎቱ እሳቱን ውሃ አደረገው:: ወታደሮቹ እርሱን በብዙ አሰቃዩ:: እርሱ ግን በእግዚአብሔር ኃይል ጸና: ታገሠ:: +በመጨረሻም ጌታችን በግርማ ወርዶ "ወዳጄ ቴዎድሮስ ስምህን የጠራ: መታሠቢያህን ያደረገ: ገድልህን (ዜናህን) የጻፈ: ያጻፈ: ያነበበ: ገዝቶ በቤቱ ውስጥ ያኖረውን ሁሉ እምርልሃለሁ" አለው:: +በስሙም ረድኤት እንደሚደረግ ነግሮት ዐረገ:: ወታደሮቹም በዚህ ቀን አንገቱን ሰይፈው የክብር አክሊልን ተቀብሏል:: እጅግ ብዙ ሺህ ሰዎችም አብረውት ተሰይፈዋል:: +"+ ቅዱስ አንያኖስ ዘግብጽ +"+ =>ይህ ቅዱስ አባት ውለታው ከፍ ያለ ነውና በምድረ ግብጽ እጅግ ይከበራል:: በተለይ ክርስትናን ከሐዋርያት ተቀብሎ ለምዕመናን ያስረከበ አባት በመሆኑ ልዩ ቦታ ይሰጠዋል:: ይህስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- +ወንጌላዊው ሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስ በሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ዼጥሮስ ተመድቦ: በፈቃደ እግዚአብሔር ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ በ50ዎቹ ዓ/ም አካባቢ ወደ ምድረ ግብጽ ወረደ:: +እስክንድርያ ከተማ በሜዲትራኒያን ባሕር ዳርቻ እንደ መኖሯም መጀመሪያ ወደ እርሷ ደረሰ:: ልክ ወደ ከተማ ሲገባ ገና አንደበቱ ለወንጌል ሳይከፈት እንቅፋት መትቶት ጫማው ተበጠሰ:: ያን ሁሉ በርሃ የቻለች ጫማ በእንቅፋት በመበጠሷ እያዘነ ወደ ጫማ ሰፊ ዘንድ ደርሶ "ሥራልኝ?" ይለዋል:: +ይህ ጫማ ሰፊ አንያኖስ (አንያኑ) ይባላል:: ጣዖት አምላኪ: ግን ደግሞ ቅንና ገር የሆነ ሰው ነበር:: "እሺ" ብሎ ሲሰፋለት መሳፈቻው (መስፊያው) ስቶ መሐል እጣቱን ስለ ወጋው "ኢታስታኦስ (አታኦስ)" ብሎ ጮኸ:: ትርጉሙም "አንድ አምላክ" ማለት ነበር:: +ይህንን የሰማው ቅዱስ ማርቆስ ቀና ብሎ "ጌታየ ሆይ! ጐዳናየን ስላቀናህልኝ አመሰግንሃለሁ!" ብሎ: ምራቁን እትፍ ብሎ በጭቃ የአንያኖስን እጅ ቀባው:: +ወዲያውም ደሙ ቁሞ: ቁስሉም ድኖ እንደ ነበረው ሆነ:: በዚህ ተአምር ድንጋጤም: ደስታም ቢሰማው "ማነህ አንተ?" ሲል ቅዱሱን ጠየቀው:: ወንጌላዊውም መልሶ "እኔ የክርስቶስ ሐዋርያ ነኝ" አለው:: +አንያኖስም "እባክህ ወደ ቤቴ እንሒድ" ብሎ ሐዋርያውን ጋበዘው:: እቤት ሲደርሱም ከሚስቱና ከልጆቹ ጋር አስተናግደውት የሕይወትን ቃል ለመኑት:: ቅዱስ ማርቆስም ከስነ ፍጥረት እስከ ጌታችን የማዳን ሥራ አስተምሯቸው አመኑ:: አጥምቆ ሥጋውን ደሙን አቀበላቸው:: +ይህቺው የቅዱስ አንያኖስ ቤትም በምድረ ግብጽ የመጀመሪያዋ ጉባኤ ቤትና ቤተ ክርስቲያን ሆነች:: ቅዱሱ ሐዋርያ በ60 ዓ/ም አካባቢ በቅዱስ አንያኑ ቤት ሆኖ በርካቶችን አሳመነ:: በሰማዕትነት ከማረፉ በፊትም ቅዱስ አንያኖስን የምድረ ግብጽ ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) አድርጐ ሾመው:: +ቅዱስ አንያኖስም ለ12 ዓመታት የክርስቶስን መንጋ እያበዛ ተጋደለ:: ከሐዋርያው የተቀበለውን ንጹሕ ዘር ዘራ:: የድኅነት የምሥራቹንም አዳረሰ:: ይሔው ይህ መልካም ተክል ዛሬም ድረስ ሳይጠወልግ አለ:: +የአሁኑ ፓትርያርክ አቡነ ታውድሮስም ከቅዱስ ማርቆስ 118ኛ ሲሆኑ ከቅዱስ አንያኖስ 117ኛ ናቸው:: ቅዱሱ ለእኛ ኢትዮዽያውያንም የክህነት አባታችን ነው:: ይህች ቀንም ዕለተ ዕረፍቱ ናት:: =>አምላከ ቅዱሳን ክፉውን አርቆ ከበጐው ዘመን ያድርሰን:: ከበረከታቸውም ይክፈለን:: =>ኅዳር 20 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት= 1.ማር ቴዎድሮስ ኃያል ሰማዕት 2.ቅዱስ አንያኖስ (አንያኑ) =>ወርኀዊ በዓላት 1..ቅዱስ ዮሐንስ ሐፂር 2.ቅዱስ አክሎግ ቀሲስ 3.ቅዱስ አፄ ካሌብ ጻድቅ (ንጉሠ ኢትዮዽያ) 4.አባ አሞንዮስ ዘሃገረ ቶና 5.ቅድስት ሳድዥ የዋሒት =>+"+ በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኩዋ መከራን ብትቀበሉ ብጹዓን ናችሁ:: ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ: አትናወጡም:: ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት:: +"+ (1ዼጥ. 3:13) <<< ወስብሐት ለእግዚአብሔር >>>

ሰላም ለከ ኀበ ድንግል ተፈናዊ፤ ሰላም ለከ #ገብርኤል ብሥራታዊ፤ ሰላም ለከ ፆፈ እሳት አርያማዊ፤ ሰላም ለከ ፅንሰ ቃል አለባዊ፤ ሰላም ለከ እምዕደ ሞት ቤዛዊ፤ በተአምኖ ንሴፎ ትንባሌ ዚአከ መዓል
ሰላም ለከ ኀበ ድንግል ተፈናዊ፤ ሰላም ለከ #ገብርኤል ብሥራታዊ፤ ሰላም ለከ ፆፈ እሳት አርያማዊ፤ ሰላም ለከ ፅንሰ ቃል አለባዊ፤ ሰላም ለከ እምዕደ ሞት ቤዛዊ፤ በተአምኖ ንሴፎ ትንባሌ ዚአከ መዓልተ ወሌሊተ ዕቀበነ አንተ። ╔═══════ ✞ ═══════╗ 📚JOIN: @demesetewahedo ╚═══════ ✞ ═══════╝

#ዝማሬ_ተዋሕዶ ይለይብኛል ሚካኤል ጠብቆ አሳድጎ ከልጅነቴ አባት እየሆነኝ ሚካኤል አባቴ ይለይብኛል ሚካኤል ይለይብኛል(2) በክንፉ ሸፍኖ በቤቱ አሳድጎኛል (2) አያምርብኝ ብዘነጋው ታሪኬን ሚካኤል ነው ያስጌጠልኝ ህይወቴን አረሳብኝ እርሱ አትርሳብኝ ያልኩትን ለካስ ሰምቶኝ ኖሯል የልጅነት ጸሎቴን ሚካኤል ያን ሁሉ ዘመን የታገሰኝ ሚካኤል===ፍሬ ጠብቆ ያልቆረጠኝ ሚካኤል===የከፍታዬ መሰላል ሚካኤል===መነሻዬ ሆነሀል አዝ...... እንዳይከፋኝ እንዳልደፋ አንገቴን እንዳላለቅስ እንዳለፈስ እንባዬን እንዳይርቀኝ ደስታ በመንፈሴ እንዳልዝል ካጠገቤ አይርቅም ያሳደገኝ ሚካኤል ሚካኤል ቀኔም ቀን አይሆን ሳልጠራህ ሚካኤል===ና ድረስልኝ ሳልልህ ሚካኤል===እንዳስጀመርከኝ ጅማሬዬን ሚካኤል===አሳምረው ፍፃሜዬን አዝ...... ውድቅ አረገው የጠላቴ ክፉ እቅድ አራመደኝ በከፍታዬ መንገድ ሊያስቀረኝ አልቻለም ሊጎትተኝ ባላጋራ ተጥሎ ስላለ በእግዚአብሔር ድንቅ ስራ ሚካኤል===እሳታዊ ነው ነበልባል ሚካኤል===ጠላቴ ፊትህ ይቀልጣል ሚካኤል===ለኔ አይኔ ነው መከታዬ ሚካኤል===የዘለዓለም ጠባቂዬ አዝ...... እንዳይከፋኝ እንዳልደፋ አንገቴን እንዳላለቅስ እንዳለፈስ እንባዬን እንዳይርቀኝ ደስታ በመንፈሴ እንዳልዝል ካጠገቤ አይርቅም ያሳደገኝ ሚካኤል ሚካኤል ቀኔም ቀን አይሆን ሳልጠራህ  ሚካኤል===ና ድረስልኝ ሳልልህ ሚካኤል===እንዳስጀመርከኝ ጅማሬዬን ሚካኤል===አሳምረው ፍፃሜዬን ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

🌹እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሲመት በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን! 🌹 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን ለሰው ወገን የሚያዝን
🌹እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በዓለ ሲመት በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን! 🌹 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ዐሥራ ሁለት በዚች ቀን ለሰው ወገን የሚያዝንና የሚራራ በእግዚአብሔር ጌትነት ዙፋን ፊት ሁልጊዜ በመቆም ለፍጥረቱ ሁሉ የሚማልድ የመላእክት አለቃ በሰማያትም ለሚኖሩ ኃይሎች ሁሉ አለቃቸው ለሆነ ለቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው ። ሰላም እብል ኪያከ መልአክ፥ ርኅሩኅ ልብ ለኩሉ እንተ ኢኮንከ ድርከ፥ ሚካኤል ሊቅየ ለለእቤለከ፥ ኅብአኒ በጽላሎትከ ነግህ ወሠርከ፥ እስመ እምንእስየ እፈርህ ሀከከ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም ገናና የሆነ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ልመናውና አማላጅነቱ ፈጽሞ ይጠብቀን፡፡ ከጽኑ ጠላት እጅ በክንፎቹ ጋርዶ ይሰውረን፡፡ ለዘለዓለሙ አሜን! ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

" የገና ጾም በልዩ ሁኔታ እንዲጾም መንፈሳዊ አዋጅ ተላልፏል " ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄
+3
" የገና ጾም በልዩ ሁኔታ እንዲጾም መንፈሳዊ አዋጅ ተላልፏል " ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

በምጸልይበት ጊዜ ልቤ አይሰበሰብም እንዲህ ከሆነ መጸለይ ቢቀርብኝስ ❓ ልቡናውን ሰብስቦ መጸለይ ያቃተው አንድ ደቀ መዝሙር አረጋዊውን አባት እንዲህ ሲል ይጠይቃቸዋል።   "አባቴ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ስጸልይ ልቡናዬ አይሰበሰብልኝም፤ አፌ ቢያነበውም ልቡናዬ ግን ይበታተናል፤ እኔ ደግሞ ዝም ብዬ ሳስበው ቅዱሳን በፍጹም ሐሳባቸው እያሰቡና እያራቀቁ እንባንና ጸጸትን እየጨመሩ የጻፉትን እኔ በልቤ ሌላ እያሰብኩ በአፌ ብቻ ባነበንበው እንደ ገደል ማሚቶ ፊደሉ አፌ ላይ  እየነጠረ ይሄዳል እንጅ ጸሎትም አይሆንልኝም፤ ስለዚህ አባቴ የአፍ ብቻ ጸሎቴ ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ባልተወው ይሻላል?" ብሎ ጠየቃቸው።    አረጋዊው አባትም እንዲህ ሲሉ አስረዱት “አየህ ልጄ ዐይነ ስውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከመንገድ ላይ ያለ እባብ ለጊዜው የበትሩን ድምጽ ሰምቶ ይመታኛል ብሎ ይሸሻል እንጅ ዐይነ ስውር ነው አላየኝም ብሎ ባለበት አይጠብቀውም ስለዚህ አንተም አስተውለህ ብትጸልይ መልካም ቢሆንም ለጊዜው ግን ጭራሽ ከምታቆመው በአፍህ ውስጥ ያለው የቃለ እግዚአብሔርን መንኳኳት የሚሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና መቼም ቢሆን ጸሎትህን አትተው፤ አጋንንትንም ማባረር አንድ ታላቅ ጥቅም ነውና፤ ብዙ ከመጸለይህም አንጻር አንዳንድ ጊዜ ልብህ የሚወድቅባት ቃል ተጠራቅማ ወደ እግዚአብሔር ታደርስሃለች። እናም ልጄ ልብህ ምንም ዝርው ቢሆንም አፍህም የእግዚአብሔር ፍጥረት ነውና ይህንንም እንዳታቆመው፤ አሁን አንዱን ይዘህ ወደፊት ደግሞ ሁለቱንም ለማገናኘት መጣር ይኖርብሃል እንጅ አንተው በዳይ አንተው አኵራፊ ሆነህ ጭራሽ ከአምላክ ርቀህ የጠላት ሰይጣን መጫወቻ እንዳትሆን።" ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

🌹እንኳን ለደብረ ቁስቋም ኣመታዊ ክብረ በዐል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!🌹 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ስድስት በዚች ቀን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክ
🌹እንኳን ለደብረ ቁስቋም ኣመታዊ  ክብረ በዐል በሰላም  አደረሳችሁ! አደረሰን!🌹 አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ስድስት በዚች ቀን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከአረጋዊ ዮሴፍና ከሰሎሜ ጋር ከስደት በሚመለሱ ጊዜ ወደ ደብረ ቊስቋም ገባ በመንገድ ጉዞ ካገኛቸውም ድካም አረፉ። ሰላም ለአእጋሪከ ውስተ ደብረ ቊስቋም እለ ጌሣ፤ ሕፃነ ማርያም ክርስቶስ አመ ጐየይከ ደወለ ንሒሳ፤ ወአመ በጽሐ ህየ እንዘ ይነሥእ ኃይለ አንበሳ፤ እንተ ሠመርከ በኀድዓት ለነፍሱ ታፍልሳ፤ ሰላም ሰላም ለወልደ ዮሴፍ ዮሳ። ክብርት እመቤታችን ከበዓሉ በረከት ረድኤት ትክፈለን፤ ሀገራችንን ሰላም ፍቅር ታድርግልን። ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

ኅዳር 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም (ሚጠታ ለማርያም) 2.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ 3.ቅድስት ሰሎሜ ቡርክት 4.ቅዱስ ዮሳ (ወልደ ዮሴፍ) 5.ቅዱስ ቴዎፍሎስ ሊቅ
ኅዳር 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም (ሚጠታ ለማርያም) 2.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ 3.ቅድስት ሰሎሜ ቡርክት 4.ቅዱስ ዮሳ (ወልደ ዮሴፍ) 5.ቅዱስ ቴዎፍሎስ ሊቅ 6.አባ ጽጌ ድንግል ዘወለቃ 7.አባ ፊልክስ ዘሮሜ ወርሐዊ በዓላት 1.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን 2.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል 3.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ 4.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ 5.አባ አርከ ሥሉስ 6.ቅድስት አርሴማ ድንግል "ዘንዶውም ሴቲቱ በወለደች ጊዜ ሕፃንዋን እንዲበላ ልትወልድ ባላት ሴት ፊት ቆመ፤ አሕዛብንም ሁሉ በብረት በትር ይገዛቸው ዘንድ ያለውን ልጅ: ወንድ ልጅ ወለደች ፤ ልጇም ወደ እግዚአብሔርና ወደ ዙፋኑ ተነጠቀ፤ ሴቲቱም ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን በዚያ እንዲመግቧት በእግዚአብሔር ተዘጋጅቶላት ወደ ነበረው ሥፍራ ወደ በረሀ ሸሸው " 📖ራዕይ 12፥4-6 ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 🌹 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

“የትዕቢት መጀመሪያ ሰውን ከእግዚአብሔር ትለየዋለች” /ሲራክ 10፡12/ ሳጥናኤል ከቀደመ ክብሩ ተዋርዶ ዲያብሎስ የኾነው “ይኽ ሕዝብ ፈጣሪውን አጥቶ ተጨንቋል፡፡ እኔ ፈጠርኋችኁ በማለትም ፈጣሪነትን በእጄ ልያዝ” ብሎ በታበየ ጊዜ ነው፡፡ ዲያብሎስ ዲያብሎስ የኾነ  አስቀድሞ ዲያብሎስ ኾኖ ስለተፈጠረ አይደለም፡፡ በትዕቢት ከመውደቁ በፊት የዐሥሩ ነገደ መላዕክት የአጋዕዝት አለቃ ንዑድ ክቡር መልዐክ ነበርና፡፡ ከዚኽ ክብሩና ሹመቱ ያዋረደው ትዕቢቱ ነው፡፡ እሳቱ ወደማይጠፋ ትሉ ወደማያንቀላፋ እሳት የጣለው ትዕቢቱ ነው፡፡ ወደ ዘለዓለማዊ ሐሳር የጣለው ትዕቢቱ ነው፡፡ ተወዳጆች ሆይ! ትዕቢት የነበረንን መልካም ምግባር ኹሉ የሚየሳምም ደግሞም የሚገድል ክፉ ደዌ ነው፡፡ ወንጌላዊው፡- “በሰው ዘንድ የከበረው በእግዚአብሔር ዘንድ ግን የተዋረደ ነው” እንዲል /ሉቃ.16፡15/ ውስጣችን በትዕቢት የተሞላ ከኾነ በአፍአ ብንመጸውትም፣ ብንጸልይም ምጽዋታችን ወይም ጸሎታችን በእግዚአብሔር ዘንድ ርኵስ መሥዋዕት ነው፡፡ ትዕቢት ካለብን ውስጣችን ንጽሕ የለውም፡፡ ስለዚኽ ሰው ንጽሕናውን እንዲያጣ የሚያደርገው ዝሙት ወይም ማመንዘር ብቻ አይደለም ማለት ነው፤ ትዕቢት ጭምር እንጂ፡፡ እንደዉም ትዕቢት ከዝሙት ወይም ከማመንዘር በላይ እኛን ያቆሽሻል፡፡ ለምን? ምንም እንኳን ዝሙት ንስሐ ካልገቡበት ሥርየተ ኀጢአት የሌለው በደል ቢኾንም በዝሙት የቆሸሸ ሰው ንስሐ ለመግባት ቅርብ ነው፡፡ በትዕቢት የታመመ ሰው ግን እንዲኽ እንደ ዘማዊው ያለ ዓቅምን አያገኝም፡፡ ስለዚኽ ትዕቢት እጅግ አደገኛ ደዌ ዘነፍስ ነው ማለት ነው፡፡ ከትዕቢተኛ ሰው በላይ ጐስቋላ ሰው የለም፡፡ የፈለገ ያኽም ብዕል (ሃብት)፣ የዚኽን ዓለም ዕውቀት ቢኖሮውም ከትዕቢተኛ ሰው የባሰ ጐስቋላ ሰው የለም፡፡ በንግሥና ወንበር ቢቀመጥ፣ በሰዎች ዘንድ እጅግ “የተከበረ” ቢኾንም ከዚኽ ሰው በላይ ጐስቋላ ሰው የለም ብዬ በእውነት እነግራችኋለኁ፡፡ እስኪ ንገሩኝ! የዚኽን ከንቱ ደግሞም ኀላፊና ጠፊ ዓለምን ነገር ይዞ ከመታበይ በላይ ምን አላዋቂነት አለ? ነገ የሚጠወልገውን የመስከረም አደይ አበባን (የዚኽን ዓለም ክብር) ይዞ ከሚታበይ ሰው በላይ ማን ነው ጐስቋላ? ሕልምን ይዞ እውኑን ዓለም ከሚያጣ ከዚኽ ትዕቢተኛ ሰው በላይ ማን ጐስቋላ ሰው አለ ልትሉኝ ትችላላችኁ? አኹን በወርቅ አልጋ ላይ ስለተኛ ከሚታበይ ሰው በላይ ማን ድኻ አለ ልትሉኝ ትችላላችኁ? ከቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ገብረ እግዚአብሔር ኪደ ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

#ዜና ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ኅዳር 1 ቀን 2016 ዓ.ም በአገልግሎት ላይ ሳሉ በጥይት የተመቱትን መልአከ መንክራት ቆሞስ አባ ኤርምያስ ገ/ጻድቅ በሆስፒታል ተገኝ
+2
#ዜና ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ኅዳር 1 ቀን 2016 ዓ.ም በአገልግሎት ላይ ሳሉ በጥይት የተመቱትን መልአከ መንክራት ቆሞስ አባ ኤርምያስ ገ/ጻድቅ በሆስፒታል ተገኝተው ጎብኝተዋል። መልአከ መንክራት ቆሞስ አባ ኤርምያስ ገ/ጻድቅ የቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አቡነ ሳሙኤል ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ሲሆኑ በደብሩ ለሁለት ቀን በተዘጋጀው ጉባኤ ላይ ኅዳር 1 ቀን 2016 ዓ.ም ምሽት የዓውደ ምህረት አገልግሎት ላይ ማንነቱ ባልታወቀ ግለሰብ በጥይት ተመተው ሆስፒታል መግባታቸውን ተከትሎ ነው ብፁዕነታቸው ለጥየቃ በላንሴት አጠቃላይ ሆስፒታል የተገኙት። ብፁዕነታቸው ሀገረ ስብከቱ ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር እንደሚነጋገር ገልጸው ለአገልጋዮች ነገ ዋስትና እንዲኖራቸው መሠራት እንዳለበት አስገንዝበዋል። በተፈጸመው ድርጊት የተደፈረችው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ናት ብለዋል ብፁዕነታቸው አቡነ ሄኖክ ፤ ብፁዕነታቸው በሆስፒታሉ የሚገኙ ሌሎች ሕሙማንንም የጎበኙ ሲሆን ቡራኬ በመስጠት ሕሙማኑ ፈጥነው ያገግሙ ዘንድ ጸሎት አድርሰዋል። ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

“ሕብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወጸአድዒድ አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር፥ ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር፥ ተፈጸመ ናሁ ማሕሌተ ጽጌ ሥሙር፥ አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት ወምድር፥ ከመ በሕጽንኪ ያሰምክ ፍቁር
“ሕብረ ሐመልሚል ቀይሕ ወጸአድዒድ አርአያ ኰሰኰስ ዘብሩር፥ ተአምርኪ ንጹሕ በአምሳለ ወርቅ ግቡር፥ ተፈጸመ ናሁ ማሕሌተ ጽጌ ሥሙር፥ አስምኪ ቦቱ ንግሥተ ሰማያት ወምድር፥ ከመ በሕጽንኪ ያሰምክ ፍቁር።” ትርጓሜ "የሚያብረቀርቅ ቀይና ነጭ ቀለም ያለው አርአያው የብር ዝንጒርጒር ጠቃጠቆ የኾነ ንጹሕ ተአምርሽ በወርቅ አምሳል የተሠራ ነው፤ እነሆ የተወደደ (መልካም) ማሕሌተ ጽጌ ደረሰ ተፈጸመ፤ የሰማይና የምድር ንግሥት ማርያም ሆይ የተወደደ ልጅሽ በጒያሽ (በዕቅፍሽ) እንዲጠጋ (እንዲደገፍ፣ እንዲንተራስ) በርሱ ዐማጽኚ፡፡" 📖አባ ጽጌ ድንግል (ማህሌተ ጽጌ) ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 🌹 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

🌹🌷🌹ሥርዓተ ማሕሌተ ጽጌ (መጨረሻ ሳምንት)🌹🌷🌹 ኅዳር 2/2016 ዓ.ም 💐እንኳን ለዘመነ ጽጌ የመጨረሻ ሳምንት ማኅሌተ ጽጌ በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን !💐 ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»
+3
🌹🌷🌹ሥርዓተ ማሕሌተ ጽጌ (መጨረሻ ሳምንት)🌹🌷🌹 ኅዳር 2/2016 ዓ.ም 💐እንኳን ለዘመነ ጽጌ የመጨረሻ ሳምንት ማኅሌተ ጽጌ በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን !💐 ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

+++ወጣት ነህን? +++ ወጣት ነህን ወጣት በመሆንህ ገና ብዙ ዘመን አለኝ ዕድሜዬ ገና ነው ብለህ አትተማመን ተለክቶ የታወቀ ቀሪ ጊዜ ያለህም አድርገህ አታስብ ‹‹የጌታ ቀን ድንገት እንደ ሌባ በሌ
+++ወጣት ነህን? +++ ወጣት ነህን ወጣት በመሆንህ ገና ብዙ ዘመን አለኝ ዕድሜዬ ገና ነው ብለህ አትተማመን ተለክቶ የታወቀ ቀሪ ጊዜ ያለህም አድርገህ አታስብ  ‹‹የጌታ ቀን ድንገት እንደ ሌባ በሌሊት ይመጣልና›› 1ኛ ተሰ5፤2 ስለዚህ ምክንያት የእድሜያችንን መጨረሻ አስቀድመን እንዳናውቀው አደረገ ከዛሬ ዕለት ጀምሮ በትጋት ዝግጅታችንን እንጀምር ዘንድ በለጋ ዕድሜያችን ሲቀጩ በየቀኑ አታይምን ስለዚህም አንዱ ሲመክር እንዲህ ብሏል “ወደ እግዚአብሔር ለመመለስ አትዘግይ ከዛሬ ነገ እመለሳለሁ እያልህ አትቁጠር” ሲራ 5፤8 ዛሬ ነገ እመለሳለሁ ስትል አንድ ቀን ባቋራጭ እንዳትወሰድ፤ ስለዚህ ሽማግሌውም ይህንን ምክር ልብ ይበል ወጣቱም ይህንን ነገር ተረድቶ ተግባራዊ ያርግ ዘንድ ይሁን ወይስ በምቾትና ሁሉ ነገር ተሟልቶልህ የምትኖር እስካሁን ችግር የሚባል ደርሶብህ የማታውቅ ባለጸጋ ነህን እንዲህም ቢሆን ቅዱስ ጳውሎስ የሚለውን ስማው “ሰላምና ደኅንነት ነው ሲሉ ጥፋት በድንገት ይመጣባቸዋል” 1ኛ ተሰ 5፤3 የዚህ ዓለም ነገሮች ሁሉ ተለዋዋጮች ናቸው እኛ በራሳችን የወደፊት ሕይወትና ሁኔታ ላይ ማዘዝ የምንችልና የሰለጠን አይደለንም ነገር ግን በጽድቅ ሥራ ላይ የሰለጠንን እንሁን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቸርና ሰውን ወዳጅ ነውና›› ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ

ጥቅምት 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.አባ ይምዓታ ጻድቅ (ከተስዓቱ ቅዱሳን) 2.ቅዱሳን መርትያኖስ ወመርቆሬዎስ (ሰማዕታት) 3.አባታችን ያፌት (የኖኅ ልጅ) ወርኀዊ በዓላት 1.አማኑኤል ቸር አምላካችን 2.ቅዱሳን አበው (አብርሃም: ይስሐቅና ያዕቆብ) 3.ቅዱስ እንድራኒቆስና ሚስቱ ቅድስት አትናስያ 4.ቅድስት ዓመተ ክክርስቶስ 5.ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ (ሰማዕት) 6.ቅዱስ አባዲርና ቅድስት ኢራኢ "በጐንም ለማድረግ ብትቀኑ የሚያስጨንቃችሁ ማን ነው? ነገር ግን ስለ ጽድቅ እንኩዋ መከራን ብትቀበሉ ብጹዓን ናችሁ:: ማስፈራራታቸውንም አትፍሩ: አትናወጡም:: ዳሩ ግን ጌታን እርሱም ክርስቶስን በልባችሁ ቀድሱት::" 📖1ዼጥ.3:13 ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

🌹እንኳን ለፈጣሪያችን መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ እና ለቅዱሳኑ አባ መቃርስ፣ አቡነ መብዓ ጽዮን ፣ወአባ ጽጌ ድንግል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!🌹 ሰላም ሰላም ለፈያታዊ ዘቀ
🌹እንኳን ለፈጣሪያችን መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ እና ለቅዱሳኑ አባ መቃርስ፣ አቡነ መብዓ ጽዮን ፣ወአባ ጽጌ ድንግል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! አደረሰን!🌹 ሰላም ሰላም ለፈያታዊ ዘቀደሶ። ሀገረ ጽጌ የአኅዝ ምስለ ጻድቃን በተዋርሶ። ተዘከረኒ ክርስቶስ አመ ትመጽእ ለተዋቅሶ። በእንተ መቃርስ ጻድቅ እንተ መጠወ ነፍሶ። ወበበትረ መስቀል ዘይዘብጥ ርእሶ። ከጥንተ ስቅለቱ ረድኤት በረከት ያካፍለን፤ እኛ ከማናቀው እሱ ከሚያቀው መከራ ስጋ ወነፍስ ይሰውረን፤ ሀገራችን ሰላም ፍቅር ያድርግልን ። አሜን! ╔═══════ ✞ ═══════╗ 📚JOIN: @demesetewahedo ╚═══════ ✞ ═══════╝

ጥቅምት 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ 2.ቅዱስ መቃርስ ብጹዓዊ 3.አቡነ መብዓ ጽዮን ጻድቅ 4.አባ ጽጌ ድንግል ዘወለቃ ወርኀዊ በዓላት 1.ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት ሁሉ አለቃ) 2.ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ 3.ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት (ንጉሠ ኢትዮዽያ) 4.ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት 5.ማር ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት "በእውነት ደዌአችንን ተቀበለ:: ሕማማችንንም ተሸክሟል:: እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቆጠርነው:: እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ:: ስለ በደላችንም ደቀቀ:: የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ:: በእርሱም ቁስል እኛ ተፈወስን::" 📖ኢሳ. 53:4 ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄

"ሰላም ለያቆብ እኁሁ ለእግዚእነ በሥጋ ዘቀደመ ተሠይሞ ውስተ አብያተ ክርስቲያናት ወተጰጰሰ እምኀበ ሐዋርያት"። ትርጓሜ ከሐዋርያት ጵጵስናን የተቀበለ በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ መሾሙ የቀደመ በሥጋ
"ሰላም ለያቆብ እኁሁ ለእግዚእነ በሥጋ ዘቀደመ ተሠይሞ ውስተ አብያተ ክርስቲያናት ወተጰጰሰ እምኀበ ሐዋርያት"። ትርጓሜ ከሐዋርያት ጵጵስናን የተቀበለ በአብያተ ክርስቲያናት ውስጥ መሾሙ የቀደመ በሥጋ ዝምድና የጌታችን ወንድም ለኾነ ለያዕቆብ ሰላምታ ይገባል። 📖ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄ 📖 @demesetewahedo ┄┉✽‌»‌༺ ═ ✞ ═ ༻»‌✽‌┉┄