ኦርቶዶክስ መዝሙር(Ortodox Mezmur)
Open in Telegram
በእንግድነቴ አገር ሥርዐትህ መዝሙር ሆነችኝ።መዝ-118:54 ሸር በማድረግ ተባበሩን👇👇👇 https://t.me/OrtoMezmur21 https://t.me/OrtoMezmur21 https://t.me/OrtoMezmur21
Show more7 107
Subscribers
+1524 hours
+357 days
+10830 days
Posts Archive
✞ ማር ሚካኤል
ማር ሚካኤል ልበል ማር ሚካኤል ልበልህ/2/
ባርከህ አሳደከኝ በቅኔ በዜማ
መዝሙር አልሰስትም አባቴ ለአንተማ
ጅማሬዬ ታናሽ ያልበቃሁ ብሆንም
እንድፀና አውቃለሁ ከፊቴ ስትቀድም
ፍፄሜዬ እንዲያምር እንዲዋብ በቤትህ
አበርታኝ ልበርታ አፅናኝ ልፅና ልጅህ
ባህሩን ክፈለው በደረቅ እንዳልፈው
እንዳልፈራ አበርታኝ እጄን በእጅህ ያዘው
አዝ----------------
ከእንቅልፍ ያነቃኛል የደጅህ ደወል
በሌሊት መጥቼ ቤትህ እንድውል
በሄድኩበት ሁሉ ካፌ አትነጠልም
የማር ወለላ ነው ሚካኤል ያንተ ስም
ማር ሚካኤል ስልህ ማር ማር አለ አፌ
መውደዴ እወነት ነው በምልጃህ ተርፌ
አዝ----------------
በሞቱ ቀጠሮ ሰርግ የደገስክለት
ምን አለ ባህራን ስታተርፈው ከሞት
ዛሬም ተዐምርህን ትድግናህን አይተው
ብዙዎች ይሉሀል ሚካኤል ሙት አንሳው
ረዳኤ ምንዱባን በስደት ደጋፊ
ከክፉ ከልለህ በድል አሳላፊ
አዝ----------------
አለቱን ከፍለኸው በበትረ መስቀል
ከጭንጫው ሰጠኸኝ ማርና ፀበል
ቀድሞ ለእስራኤል ያኔ እንዳደረከው
የሰማነውን ዛሬ ሆኖ አየነው
የብርሀኑን አምድ ፋና ተከትለን
ከቅዱሳን ስፍራ ዛጅርማኤል ደርሰን
አዝ----------------
ከእንቅልፍ ያነቃኛል የደጅህ ደወል
በሌሊት መጥቼ ቤትህ እንድውል
በሄድኩበት ሁሉ ካፌ አትነጠልም
የማር ወለላ ነው ሚካኤል ያንተ ስም
ማር ሚካኤል ስልህ ማር ማር አለ አፌ
መውደዴ እወነት ነው በምልጃህ ተርፌ
መዝሙር
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
✥••┈┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈┈••✥
https://t.me/OrtoMezmur121
https://t.me/OrtoMezmur121
https://t.me/OrtoMezmur121
✥••┈┈┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈┈┈••✥
✞ ማር ሚካኤል
ማር ሚካኤል ልበል ማር ሚካኤል ልበልህ/2/
ባርከህ አሳደከኝ በቅኔ በዜማ
መዝሙር አልሰስትም አባቴ ለአንተማ
ጅማሬዬ ታናሽ ያልበቃሁ ብሆንም
እንድፀና አውቃለሁ ከፊቴ ስትቀድም
ፍፄሜዬ እንዲያምር እንዲዋብ በቤትህ
አበርታኝ ልበርታ አፅናኝ ልፅና ልጅህ
ባህሩን ክፈለው በደረቅ እንዳልፈው
እንዳልፈራ አበርታኝ እጄን በእጅህ ያዘው
አዝ----------------
ከእንቅልፍ ያነቃኛል የደጅህ ደወል
በሌሊት መጥቼ ቤትህ እንድውል
በሄድኩበት ሁሉ ካፌ አትነጠልም
የማር ወለላ ነው ሚካኤል ያንተ ስም
ማር ሚካኤል ስልህ ማር ማር አለ አፌ
መውደዴ እወነት ነው በምልጃህ ተርፌ
አዝ----------------
በሞቱ ቀጠሮ ሰርግ የደገስክለት
ምን አለ ባህራን ስታተርፈው ከሞት
ዛሬም ተዐምርህን ትድግናህን አይተው
ብዙዎች ይሉሀል ሚካኤል ሙት አንሳው
ረዳኤ ምንዱባን በስደት ደጋፊ
ከክፉ ከልለህ በድል አሳላፊ
አዝ----------------
አለቱን ከፍለኸው በበትረ መስቀል
ከጭንጫው ሰጠኸኝ ማርና ፀበል
ቀድሞ ለእስራኤል ያኔ እንዳደረከው
የሰማነውን ዛሬ ሆኖ አየነው
የብርሀኑን አምድ ፋና ተከትለን
ከቅዱሳን ስፍራ ዛጅርማኤል ደርሰን
አዝ----------------
ከእንቅልፍ ያነቃኛል የደጅህ ደወል
በሌሊት መጥቼ ቤትህ እንድውል
በሄድኩበት ሁሉ ካፌ አትነጠልም
የማር ወለላ ነው ሚካኤል ያንተ ስም
ማር ሚካኤል ስልህ ማር ማር አለ አፌ
መውደዴ እወነት ነው በምልጃህ ተርፌ
መዝሙር
ዘማሪ ዲ/ን አቤል መክብብ
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
https://t.me/OrtoMezmur121
https://t.me/OrtoMezmur121
https://t.me/OrtoMezmur121
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
ጾመ ሐዋርያት (የሰኔ ጾም) መቼ ይገባል ?
ለምንስ ይጾማል ?
❖ ጾመ ሐዋርያት ወይም ሰኔ ጾም ሰኔ #2 ይገባል (ይጀምራል) ሐምሌ 5 ቀን ይፈታል።
❖ ይህ ጾም ከቤተ ክርስቲያናችን የአዋጅ አጽዋማት ውስጥ አንዱ ሲሆን ቅዱሳን ሐዋርያት ጌታችንን ምሣሌ አድርገው የጾሙት ጾም ነው።
❖ የሰኔ ጾም ይህ ጾም የሐዋርያት ጾም በመባል ይታወቃል ስለ ምን የሐዋርያት ጾም ተባለ ቢሉ በበዓለ ጰራቅሊጦስ ሐዋርያት መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ የጾሙት ጾም ስለሆነ ነው።
የሰኔ ጾም የሚጾምበት ጊዜያት
❖ የሰኔ ጾም ቢያንስ 15 ቢበዛ 45 ቀናት ያህል ይጾማል
❖ የሰኔ ጾምን እስከ 9 ሰአት እንድንጾም ቤተክርስቲያን አውጃለች ።
❖ ጾሙ የሚገባበት ቀን በየዓመቱ የተለያየ ቢሆንም የጾሙ ማብቂያ ዕለት ግን ሐምሌ 5 ድረስ ነው ።
❖ ቅዱሳን ሐዋርያት የአምላካቸውን የመምህራቸውን አርአያ ተከትለው እርሱ ወደ ማዳን ሥራው ማለትም ህሙማነ ሥጋን በተዓምራት ሕሙማነ ነፍስን
በትምህርት ከማዳን አስቀድሞ የስራውን መጀመሪያ በገዳመ ቆሮንቶስ ገብቶ 40 ቀን 40 ሌሊት እንደ ጾመና እንደጸለየ ሁሉ ቅዱሳን ሐዋርያትም አብነቱን ተከትለው ጾመዋል፡፡
❖ ጸጋ መንፈስ ቅዱስን ከተቀበሉ በኋላ ዓለምን ዕጣ ተጣጥለው (ተከፈፍለው) ዞረው ከማስተማራቸው አስቀድመው የሥራቸው መጀመሪያ ጾምን አድርገዋል፡፡
❖ ሐዋርያትም ይህንን ጾም እንደሚጾሙ ጌታችን አስቀድሞ የዮሐንስ ደቀመዛሙርት ወደ እርሱ ቀርበው በጠየቁት ጊዜ ተናግሮ ነበር፡፡
✍️‹‹ እኛና ፈሪሳውያን ብዙ ጊዜ የምንጦመው ደቀመዛሙርትህ ግን የማይጦሙት ስለምንድን ነው? አሉት
✍ ኢየሱስም እንዲህ አላቸው ሚዜዎች ሙሽራው ከእነርሱ ጋር ሳለ ሊያዝኑ ይችላሉ? ነገር ግን ሙሽራው ከእነርሱ የሚወስድበት ወራት ይመጣል በዚያን ጊዜም ይጦማሉ›› ማቴ 9፥15-16
❖ እኛም ይህን ጾም የምንጾመው የሐዋርያትን በረከት ለመላበስ፣ እነርሱ ድል ያደረጉትን ዓለም እንድናሸንፈው አምላካችንን ለመማጸን በመሆኑ ይህንን ‹‹መሣሪያ›› አንጣለው ጾሙም ለመላው ክርስቲያን የተሰጠ ነው፤ አንድ አንዶች እንደሚሉት የቀሳውስት ብቻ አይደለም ለቄስና ለምዕመናን ተብሎ በክህነት ደረጃ የተለየ ጾምም የለም፡፡
ፆሙን የበረከት ፆም ያድርግልን በሰላም ያስፈፅመን አሜን በእውነት
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያበመልጣል"
ምሳ 1፥33
https://t.me/OrtoMezmur121
Bybit's 70M & Rising! Trade to claim 7 USDT and invite friends to double your bonus!https://www.bybit.com/promo/campaign/70MANDRising?quality=80&format=webp&ref=ZZQXVMY
❖ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የዕርገት በዓል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ።
#ዕርገት
ቤተክርስትያናችን ከምታከብራቸው በዓላት ውስጥ አንዱ የጌታችን የመድኃኒታችን የእየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ነው።ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ በ፵ኛው ቀን ማረጉን በማሰብ ቤተክርስትያናችን ዕርገትን ትንሳኤን በተከበረ በ፵ኛው ቀን ታከብራለች።በዚህ ዓመትም ቤተክርስትያናችን ዕርገትን ግንቦት21 ታከብረዋለች።
ዕርገት ልክ እንደ ትንሳኤ ሁሉ ቀኑ ይለዋወጣል። ነገር ግን ምንጊዜም ዕርገት ሐሙስን አይለቅም።ልክ ትንሳኤ እሁድን ስቅለት አርብን እደማይለቅ ሁሉ እርገትም ሐሙስን አይለቅም።
ዐረገ በስብሐት
ዐረገ በስብሐት ዐረገ በእልልታ
በስብሐት በእልልታ ዐረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
ሞትን ደል አድርጎ የሰራዊት ጌታ
አረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
እየዘመሩለት መልአክት በደስታ
አረገ በስብሐት በእልልታ
❖ መልካም በዓል
❖ እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ የዕርገት በዓል በሰላም አደረሰን/አደረሳችሁ።
#ዕርገት
ቤተክርስትያናችን ከምታከብራቸው በዓላት ውስጥ አንዱ የጌታችን የመድኃኒታችን የእየሱስ ክርስቶስ ዕርገት ነው።ጌታችን መድኃኒታችን እየሱስ ክርስቶስ ከሞት ከተነሳ በ፵ኛው ቀን ማረጉን በማሰብ ቤተክርስትያናችን ዕርገትን ትንሳኤን በተከበረ በ፵ኛው ቀን ታከብራለች።በዚህ ዓመትም ቤተክርስትያናችን ዕርገትን ግንቦት21 ታከብረዋለች።
ዕርገት ልክ እንደ ትንሳኤ ሁሉ ቀኑ ይለዋወጣል። ነገር ግን ምንጊዜም ዕርገት ሐሙስን አይለቅም።ልክ ትንሳኤ እሁድን ስቅለት አርብን እደማይለቅ ሁሉ እርገትም ሐሙስን አይለቅም።
ዐረገ በስብሐት
ዐረገ በስብሐት ዐረገ በእልልታ
በስብሐት በእልልታ ዐረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
ሞትን ደል አድርጎ የሰራዊት ጌታ
አረገ በስብሐት በእልልታ
አዝ
እየዘመሩለት መልአክት በደስታ
አረገ በስብሐት በእልልታ
❖ መልካም በዓል
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
