ዳዊት ጌታቸው።(እይታ)
Open in Telegram
452
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ለ እያንዳንዱ እርምጃህ ቀልብ ግዛ....የት ይደርስልኛል ብላ ነጋ ጠባ የምትፀልይ ነጠላ የለበሰች ወጣትነቷን ላንተ የሰዋች እናት የለችህም?የ እኔም እናት ያንተኑ ነው የምትመስለው።የት ትደርስልኛለች ብሎ ጉብዝናውን ላንቺ የሰጠ ያለ እድሜው የሸበተ፣መንገድ ለይ በሀሳብ ብቻውን የሚባዝን፣እሱ እየራበው በኮቱ ደብቆ የምትወጂውን ቀሚስ እና ስታምር ብለሽ ያለፍሻትን ጫማ የገዛልሽ አባት የለሽም? አለሽ!!!
እነዚህን ምስኪኖች ብናስብ ዛሬ የምናደርጋትን ነገር ምንኛ እንጠነቀቅላት ነበር?!(its not about being advisor about the messed up life..its just telling of the little portion of truth)ሰላም ሁኑ!!
የወርቅ ቀለበት *በእርያ አፍንጫ እንደሆነ ሁሉ ከጥበብ የተለየች ሴትም እንዲሁ ናት"።ምሳሌ11:22 መፅሀፍ ቅዱስ ውበት ያለ ጥበብ በተለይም ሴት ልጅ ያለ ብልሀት እና ጥበብ መኖሯ ከንቱ እንደሆነ ከሚያስረዳባቸው ትምህርቶቹ መካከል አንዱ ነው።
*እርያ=አሳማ።የሚለውን ቃል ይተካል መልካም ምሽት
ያቃጠላትን ፀሀይ ቅርቧ ባገኘችው ትልቅ ዛፍ ስር ተደግፋ እያሳለፈች ነው!ዛሬ ስሩ ብትሆንም አንድ ቀን ሆዱ እንደምትገባ ስታስብ ዘገነናት..."የተረገመ እንጨት" ጉዞዋን ቀጠለች....
"ሳለቅስ ላየኝ ሁሉ ስለ ሴት አይደለም"።
ይልቅ ፖለቲካው
ወገቤን ደከመው
ጥይት የጎረሰ
የህፃናት ግንባር
ደረቷን ቀስት ነድሎት
ስትለቅም ምስር
[እናት አለሜን]
አርሶ ደክሞት ገብቶ
እራቱን ሲጠብቅ
በ መድፎች አሎሎ
ጣሪያው ሲሰነጠቅ
[የ አባት ድንጋጤ]
ለ ሞተ ሠው ፍትሀት
ሲሆንበት ቅብጠት
የወረደው እንባ
አይደለም ስለ ሴት።
ሳንባቸው ሳይጠና
ባሩድ ለታፈኑ
እሩቅ እያሰቡ
ወደ ሞት ላቀኑ
ዘጠኝ ወር ጠብቀው
በ አምስቷ ቀን ብቻ
ፅንሳቸውን ላጡ ምንድነው መበርቻ??
ዝም ብለን አብረን እናልቅስ
original verse[ዝም ብለን አብረን ዝም እንበል]
ዳዊት ጌታቸው
@yefkrgtmdawit
