en
Feedback
ዳዊት ጌታቸው።(እይታ)

ዳዊት ጌታቸው።(እይታ)

Open in Telegram

ፍቅር!ሰላም!ግጥም!እይታ! sad! ለ አስተያየት @addemiinilik

Show more
452
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
ብታውቂ ስትስቂ! ጠፈርን እንደምታደምቂ መንፈስን ካ'ዚም እስራት እንደምታላቅቂ ብታውቂ! ስትስሚ! አጥንት እንደምታለመልሚ ታማሚ ልብ እንደምታክሚ ብታውቂ! ስታወሪ! ዱዳ እንደምታናግሪ መነኩሴውን ከሱባኤ፣ ፈላስፋውን ከጉባኤ እንደምትጠሪ ብታውቂ! እንኳንስ በ'ኔ ልትስቂ ከራስሽ ጋር ፍቅር ይዞሽ አይሽ ነበር ስትማቅቂ። በእውቀቱ ስዩም

ለመሸነፍ እንኳን ብርታት ያስፈልጋ!!!!!!!

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ " በጦርነቱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ አምራች አርሶ አደሮች፣ ሃኪሞችን ጨምሮ ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሰውተዋል " - ጊዜያዊ አስተዳደሩ በተለያዩ የማህበራዊ የትስስር ገፆ
+1
#ትግራይ " በጦርነቱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ አምራች አርሶ አደሮች፣ ሃኪሞችን ጨምሮ ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሰውተዋል  " - ጊዜያዊ አስተዳደሩ በተለያዩ የማህበራዊ የትስስር ገፆች በትግራዩ  ደም አፋሳሽ ጦርነት ስለ ተሰው ታጋዮች " እንደ ተራ ነገር የሚነገረው ቁጥር የሃቅ መሰረት ስለሌለው ትርጉም አንሰጠውም " አሉ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ። ፕረዚደንቱ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ቀን ስነ-ሰርአት በይፋ መታወጅ አስመልክተው ጥቅምት 2/2016 ዓ.ም ለክልሉ የመንግስት ፣ የግልና የውጭ ሚድያዎች ሰፊ ቃለ-መጠይቅና ማብራሪያ ሰጥተዋል። ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ ፤ በክልሉ በተካሄደው ደም አፋሳሽና እልህ አስጨራሽ ጦርነት የተሰው ታጋዮች ቁጥር እንዲገልፁ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ " ... በትግሉ ስለተሰውት ታጋዮች ቁጥር ብዙ ተረት ነው የሚወራው ፤ የተሰውት ታጋዮች ቁጠር እንገልፃለን። ለጊዜው ግን መግለፁ አስፈላጊ ሆኖ ስላልታየን እናቆየዋለን "  ብለዋል።  " ... ለትግራይ ህልውና የተከፈለ ዋጋ የሚመጥነው ደረጃና ዋጋ መስጠት አለብን ሲባል ለያንዳንዱ የተሰዋ ታጋይ ፤ ለያንዳንዱ የተሰዋበት ቤተሰብ የክብር የምስክር ወረቀት ልከናል " ያሉት አቶ ጌታቸው ፤ " የተሰውት ታጋዮች ቁጥር በእጃችን ይገኛል። ከቁጥሩ ባሻገር ግን እጅግ ከባድና ውድ ዋጋ ከፍለናል። ለህልውናችን የተከፈለ በመሆኑም  ግን የሚያስቆጨን አይሆንም ሊባል ይችላል " ሲሉ አክለዋል። አቶ ጌታቸው ፤ " ብዙ ልጆቻችን ከፍለናል። ጠላቶች (ፕሬዜዳንቱ ጠላቶች ያሏቸውን በስም አልገለጿቸውም) የኛ የመስዋእት ኪሳራ በማብዛት የነሱ ለማሳነስ እንደማነፃፀሪያ በማቅረብ ብዙ ይናገራሉ። በበኩሌ አሁን ካለው የተሰዋ ታጋይ ቁጥር ሩብ ፤ ከሩብ በታች ፤ አንድ መቶኛው እንኳን ብንከፍል ዋጋው ከባድ ነው የሚል እምነት አለኝ። " ብለዋል። " አልተሳካልንም እንጂ ያለ አንድ ታጋይና ያለ አንድ ወጣት መስዋእት ፣ ራሳችን በራሳችን የማስተዳደር መብታችን የምናረጋግጥበት ዕድል ቢኖር እመርጥ ነበር " ሲሉ አክለዋል። ፕሬዜዳንቱ በስም ያልጠሯቸውና " ጠላቶች " ሲሉ የጠሯቸው ኃይሎች " አሁን ላይ መጥራት በጀመሩት የተዛባና የተጋነነ ቁጥር በመደናገር ሌላው ያልሆነ ቁጥር ሲጠራ ቢውል ለኔ 20 ሺህ ተባለ ፣ 10 ሺህ ተባለ ፣ ህልውናችን ለማረጋገጥ አንድ ሰው ይሰዋ 20 ሺህ ዋጋው እጅግ ከባድ ነው " ብለዋል። " በተሰውት ታጋዮች ዝርዝር ፦ - የዩኒቨርስቲ መምህራንና ተማሪዎች ፣ - ጥሩ አምራች አርሶ አደሮች - ሃኪሞች ሁሉም አይነት የህብረተሰብ ክፍሎች አሉ። በአጠቃላይ ትግራይን በሰላም ጊዜ ወደ ተሻለ የእድገት ደረጃ የማሸጋገር አቅም የነበራቸው በመስዋእትነት አጥተናል " ያሉት አቶ ጌታቸው ፤ " ይህንን መስዋእትነት ዋጋ መስጠት እንዳለ ሆኖ ፤ ቁጥሩ ጠላት በሚለው ደረጃ እንዳልሆነ መረዳቱ ስጋታችን ቀንሶ ያረጋጋናል " ማለታቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል። የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ቀን ሰነ-ሰርዓት ከጥቅምት 3 አስከ 5 በተለያዩ ዝግጅቶች ታጅቦ በመካሄድ  ፤ ጥቅምት 6/2016 ዓ.ም " በሃዘን አንገታችን እንደፋም "  በሚል መሪ ቃል በሚካሄድ የህዝብ ሰልፍ እንደሚጠቃለል ከወጣው መርሃ ግብር ለመረዳት ተችሏል።    መረጃው በቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የተዘጋጀ ነው። @tikvahethiopia

ከ ድሎትህ ጀርባ ከ ድሎትሽ ጀርባ አንድ ምስኪን አለ ደግፎን በ እንባ ገድሉ ያልተፃፈ ቆሌው ያላረፈ እድሜውን ሳይሰስት ቆንጥሮ የሰጠ ጎንሽ እንዲደላው ጎኑን ያጎበጠ ሳቅሽ እንዲበዛ ጥርሱን ያረገፈ

Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#MoE ሚኒስትሩን ያስደናገጣቸው ቁጥር ? ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦ " ከዚህ ፈተና አንድ #ሊያስደነግጠን የሚገባ ነገር ከተፈተኑት ጠቅላላ ተማሪዎች ውስጥ 50 ከመቶ የሚሆኑት እና ከዛ በላይ 26 ከመቶ
+1
#MoE ሚኒስትሩን ያስደናገጣቸው ቁጥር ? ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፦ " ከዚህ ፈተና አንድ #ሊያስደነግጠን የሚገባ ነገር ከተፈተኑት ጠቅላላ ተማሪዎች ውስጥ 50 ከመቶ የሚሆኑት እና ከዛ በላይ 26 ከመቶ ነው ያገኙት። ከ845 ሺህ ፤ 422,500 ሺህ ተማሪ ከ26 በታች ነው ያገኘው። እንደው ዝም ብሎ አንድ ተማሪ ፈተናውን በግምት ቢሞላ እንኳን ሊያገኘው የሚችለው ውጤት ነው። ለዚህ ነው ከታች ጀምሮ በደንብ አጥርተን መስራት አለብን የምንለው። " ስለ 2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ቁጥሮች ምን ይላሉ ? - በ2015 የተፈተኑ ተማሪዎች ብዛት 845,099 ፤ 50 በመቶና በላይ ያመጡ 27,267 ተማሪዎች (3.2%) ብቻ ናቸው። ከነዚህ ውስጥ ፦ • ከተፈጥሮ ሳይንስ ያለፉ 19,017 ተማሪዎች • ከማህበራዊ ሳይንስ ያለፉ 8,250 ተማሪዎች - በማታ የተፈተኑ 16,541 ያለፉ 12 ተማሪዎች ብቻ - በግል የተፈተኑ 169,502 ያለፉ 498 ተማሪዎች ብቻ - በመደበኛ የተፈተኑ 659,056 ያለፉ 26,757 ተማሪዎች ብቻ - የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑ 3,106 ት/ቤቶች፤ 1,328 ትምህርት ቤቶች #አንድም_ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም / ምንም ተማሪ አላሳለፉም። - በሀገሪቱ ካሉትና የ12ኛ ክፍል ፈተና ካስፈተኑት ትምህርት ቤቶች 42.8 በመቶ የሚሆኑት አንድም እንኳን ተማሪ ማሳለፍ አልቻሉም። - 27 ሺህ 267 ተማሪዎች በቀጥታ ፍሬሽ ማን ሆነው ወደ ዩኒቨርሲቲ ሲገቡ 160 ሺህ ገደማ ተማሪ በሬሜዲያል ይገባሉ። #TikvahEthiopia @tikvahethiopia

አስራ ሁለተኛ ክፍሎች መልካም እድል

የኛን መጨካከን እና ክፋት ሲያይ ሳይቀድሙኝ ልቅደማቸው ብሎ እኮ ነው😂😂
የኛን መጨካከን እና ክፋት ሲያይ ሳይቀድሙኝ ልቅደማቸው ብሎ እኮ ነው😂😂

ስም ያለው ሞኝ ነው 😂😂

ዛሬ የግራ አቅጣጫዬን ይዜ ስንት suzuki dzire እንዳለፈኝ ስቆጥር ድንገት ይህችን ድንቅ ወጣት አየሁዋት እናም ሳታየኝ ተጠንቅቄ ይህን ምስል አስቀረሁት...ምን አልባትም ይህ ድርጊቷን ማንም እ
ዛሬ የግራ አቅጣጫዬን ይዜ ስንት suzuki dzire እንዳለፈኝ ስቆጥር ድንገት ይህችን ድንቅ ወጣት አየሁዋት እናም ሳታየኝ ተጠንቅቄ ይህን ምስል አስቀረሁት...ምን አልባትም ይህ ድርጊቷን ማንም እንዳያይ ትፈልግ ይሆናል ለሱም ይቅርታ ጠይቃለው!ግና እኔና ውሽማዬ እንዴት እንደምናደርግ እዩ ብለው ምስል የሚያጋሩም አሉ እና አንቺ ደስ ይበልሽ!!!በነገራችን ለይ ጥላው የኔ ነው!ከኔ ይወፍራል😂😂

የ ኢንጂነሪንግ ሄልሜት አርጎ ሲሄድ ቄስ ነህ ብለው ገደሉት😂😂

ቅን መሆን መልሶ ይከፍላል በእጥፍ።ቅን ሁኑ!!!

ልክ የዛሬ አመት ማዲንጎ ሞተ...ሀውልቱ ዛሬ ተመረቀ

እንኳን አደረሰን!!
እንኳን አደረሰን!!

አንድ አንድ ሰዎች ደግሞ አሉ ገና በደጉ ግዜ ፤ስንጣላቸው የሚሉንን አስበው የሚያስቀምጡ!! @dawitview ዳዊት ጌታቸው

ያሰባችሁት ይሳካ!!!!

ይህ post ላስቆጣችሁ ሰዎች ምላሽ አጤ ቴዎድሮስ ጦርነት ቀረ ሊሉ ይችላሉ ብዬ ያሰብኩት አሁን ያለውን የጦርነት ይዘት አይቼ ነው ጦርነት ማለት በ ሁለት ተቃራኒ ሀይላት መካከል በተፈጠረ አለመግባባት ወይም የጥቅም መፋለስ ምክንያት የሚመጣ አካላዊ ወይም ሀሳባዊ ሰጣገባ ነው።ጦርነት ግዴታ ሁሌ ቃታ እና ጦር መስበቅ የለበትም።መጥሀፍ ገልፆ የጦፈ ክርክር ማድረግ እና እውቀትን ተጠቅሞ እውነታውን ይዞ መገኘት እና ማሸነፍም ራሱን የቻለ ጦርነት ነው።ሀገራችን ውስጥ ተዘግበው የሚገኙ ጦርነቶች ቃታ እና ገጀራን በገፍ ጥቅም ለይ የዋሉበት አይነት እንጂ ሀሳባዊ ፍትጊያ(friction)የ ሌለባቸው ናቸው።የኔ ትውልድ እንዳለው ሮፍናን በኔ ትውልድ ያለው ጦርነት ደግሞ አብዛኛውን የጦርነት መስፈርት አያሟላም ምክንያቱም ቃታዎች የሚሳቡት ተቃራኒ ሀይል በሌለበት ሁኔታ ነው የገዛ ዘመዳሞች መሀል እንደማለት ነው ሲቀጥል ለአፍታ ጦርነቱ ቆም ብሎ ምንድነው የግጭቱ መንስኤ ቢባል አብዛኛው ተዋጊ ረስቶታል ምክንያቱም እዚ ግባ የማይባል እና በሀሳብ ጦርነት ሊፈታ የሚችል ነበርና። እና ምንይልክ ጣሊያንን አድዋ ለይ ትልቅ ምክንያት ይዞ አጤ ቴዎድሮስም መቅደላ ለይ የውጭ ጠላትን መክቶ ነው የወደቀው አሁን ያለውን የተንበጫበጨ ጦርነት ቢያዩ "ጦርነት ድሮ ቀረ አይሉም ነው የምትሉኝ"? @dawitview

ላንቺ "መሄድ"ማለት እኔን ትቶ መሄድ ትዝታን ረግጦ ጣፎ እንደ መግባት የባስ ትኬት ቆርጦ ላንቺ ቀላል ነው። ስቴጅ ስትኮበልይ ስቴጅ ስትኮበልይ መንገድሽን እንጂ ምን ረገጥኩ አትይ! ላንቺ መሄድ ማለት ሻንጣ እንደመጎተት ፈረስን በአርጩሜ ለጉዞ እንደመግራት ቀላል ነው። ጉልበትሽ በረታ አቅምን ሸመተ መካሪ እየጠፋ ሸኚ በረከተ ጨዋታው ፈረሰ ቀረ መዋደዱ ታኮሽ ያረፈበት ተወግቷል መንገዱ። ተወግቷል ተወግቷል የኔን ልብ ይመስላል!!😥 ዳዊት ጌታቸው @dawitview