ዳዊት ጌታቸው።(እይታ)
Open in Telegram
452
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
#ጥንቃቄ: ቴሌግራም ላይ ከተለያዩ ሰዎች አጭር ጹሑፍና ሊንክ እየተላከሎት ነው?
ቴሌግራም ላይ ከተለያዩ ሰዎች ጹሑፍና ሊንክ ያለው መልዕክቶች እየተላኩ ነው። ብዙዎች ይህ ጉዳይ በተደጋጋሚ እየደረሳቸው እንደሆነና የጥንቃቄ መልዕክቱን እንድናስተላልፍ ጠይቀውናል።
በመልዕክት የሚላከው ሊንክ ምንድን ነው?
በመልዕክቱ አብሮ የሚደርሶት ሊንክ የቴሌግራም አካውንቶን ለመጥለፍ የተዘጋጀ ቴሌግራምን የሚመስል ድረ-ገጽ ነው። ሊንኩን ሲከፍቱት ስልክ ቁጥር አስገብተው ወደ ቴሌግራም እንዲገቡ ይጠይቆቃል።
ቁጥሮን አስገብተው የሚመጣው ሌላኛው ገጽ በቴሌግራሞት የተላከሎትን አጭር የማረጋገጫ ቁጥር እንዲያስገቡ የሚጠይቅ ነው። ይህንን ቁጥር ካስገቡ የእርሶን ቴሌግራም በቀጥታ ይህን የሚጠቀሙት ሰዎችም መጠቀም ይጀምራሉ። መልዕክቶችን ለሌሎች መላክና እርሶ እንደላኩት አድርገው ይልካሉ።
ይህ ገጽ ልክ ቴሌግራምን እንዲመስል ተደርጎ የተሰራ ሲሆን የሚያስገቡት መረጃ ግን ወደ ቴሌግራም ሳይሆን ይህንን ወደ ሚቆጣጠሩት ሰዎች የሚላክ ነው። ይህ አይነቱ ማጭበርበር ማጥመድ(Phishing) በመባል ይታወቃል።
ምን ማድረግ እችላለሁ?
ይህ ችግር ካጋጠሞት ቀጥታ ቴሌግራሞት ላይ Setting ላይ በመግባት #Device የሚለውን በመጫን የእርሶ አካውንት በምን በምን ስልኮች ላይ እየሰራ እንደሚገኝ ማየት ይችላሉ። በዚህም ከእርሶ ቁጥጥር ያሉ ስልኮችን በሙሉ ማስወጣትና እርሶ የሚጠቀሙበትን ብቻ ማስቀረት ይችላሉ።
ሁለተኛው መንገድ ይህ ችግር ከተመፈጠሩም በፊት የሚያገለግል ሲሆን ሁለተኛ ዙር የደኅንነት ማረጋገጫ (Two-Step verification ) መጠቀም ድንገት ለእንደዚህ አይነት ችግሮች ብንጋለጥ ተጨማሪ የደኅንነት ማረጋገጫ ይሆነናል። (ስለዚህ ዝርዝር ሊንኩን ተጭነው ያንብቡ)
#StaySafeOnSocialMedia
#DigitalLiteracy
👋 @TikvahethMagazine
ተማጽኖ
(በእውቀቱ ስዩም)
አቤቱ
የጠፈር ባለቤቱ
በየብስ ነህ፥ በባህር፥ በምድር ነህ በሰማይ?
በቅጡ ለማናውቅህ ፥ በድንግዝግዝ ለምናይ
አቤቱ የፍጥረት አባት
ከሰማኸኝ ምናልባት
ኮረብታውን ሜዳ አድርገው ፤ ኮረኮንቹን አለስልሰው
የፎይታየን አድራሻ፥ ርቀቱን ቀንሰው
አልልህም!
ጽናት ስጠኝ ፤ ብርቱ አድርገኝ! በየርምጃው እንዳይደክመኝ
ከቀንበሮች ሁሉ መርጠህ፥ ምችለውን አሸክመኝ
አቤቱ! የጠፈሮች ሁሉ መስራች
አፈራርቀህ የምትሰጥ፥ መርዶና የምስራች !
ተወስነህ የማትገኝ ፤ በጊዜና በቦታ
ወሰን የሌለህ ዝምታ
እኔ ልጅህ-ሲመቸኝ ፤ ሲመቸኝ አማኝ
ባይመችህም ስማኝ
ካደፈጠው እዳ ሁሉ፥ በየበስ፥ ባየር በቀላይ
ከአውሎ ነፋስም በላይ
ከመሬት መራድም ይልቅ
ሰው ነው ሰውን ሚያሳቅቅ
ሰው ነው የሰው አደጋ
ደግሞ በሌላ ገጹ፥ ሰው ነው ለሰው ልጅ ጸጋ
ከስጦታው አካፍለኝ ፥ ካደጋው አስመልጠኝ
አልሳሳት አልልህም፥ የሚታረም ስህተት ስጠኝ !
@getem
@getem
@paappii
By bewuketu seyoum
ዛሬ ጫማዬን ሳስጠርግ አንዱ ጮክ ብሎ ኦሮሞ ምን ብሎ ይርታል መሰለህ "Mukkeen sirratti bu'uu qaba moo namni sirratti bu'uu qaba jedhanii yommuu gaafatan, yoo mukaan natti bu'e namni na kaasa jedhe"አለው እና ተሳሳቁ።
ትርጉም በ ስለሺ:-ግንድ ይውደቅብህ ወይስ ሰው ይውደቅብህ ሲሉት ግንድ ይውደቅብኝ ሰው ያነሳልኛል አለ።
የሰው ጥቅም ይግባን መልካም እሁድ!!
አብዛኛው ኢትዮጵያዊ በሚያንኮራፋበት ሰአት እኔ መሀል ቦሌ አልያም ደብረ ዘይት የማስተዳድረው ድርጅት ያለኝ ይመስል እንቅልፍ ከድቶኝ እገላበጣለው...ለሊት 7 ሰአት ከ39 ደቂቃ።አላስችል ሲለኝ ተነሳው፣የምሰራው ጠፋኝ።በ አልባሌ ሀሳብ ተዋጥሁ።እውነት እስራኤል ጨክና ጋዛን አሳሯን ማብላት ትቀጥል ይሆንን?ወይስ ደግሞ በጋዛ መደብደብ ተናዶ የሰፈራችን ባለ ሱቅ ሁሴን ዱቤ አልሰጥም ይለናልን?free palestine in order to get credit ቢለን ጦርነቱ እኛንስ ጎዳን ማለት አይደል?
በማያገባኝ ሀሳብ ስዋዥቅ 40 ደቂቃ ነጎደ!!ከ ሀሳቤ ቢገላግለኝ ብዬ ሙዚቃ ለመስማት የዶሴ አስተዳደሬን(file manager) መበርበር ጀመርኩ!!!ከ Jason derulo "wiggle" እስከ ሳንጃው ሰው በላ ዘለሰኛ ከተደረደሩት ዘፈኖች መሀል የ ገነት ማስረሻን እዋዋ ጎጃም ከፍቼ ዘና ማለት ጀመርኩ።ዜማው ጠንካራ ነው መነኩሴ ይፈትናል!!ሳልፈልግ እነቃነቃለሁ።መሀል ለይ ግን ገነት ማስረሻ አንድ ግጥም ስትቀልፅ ሰማሁዋት!!ረጅም ሰአት ስለ ትርጉሙ አሰብሁ፣ቅኔ ሆነብኝ።ከ ሀሳብ ለመሸሽ የጀመርኩት ሙዚቃ ለሌላ ሀሳብ ዳረገኝ!! ለማንኛውም ገነት ማስረሻ ያለችው እንዲህ ነው:-
በግንባር ሳላየው ደርሼ ስፍራው
ወንድነቱ ብቻ ዘለቀ ስራው...
ምን ማለት ፈልጋ ይሆን!!!
እኔም እንዲህ ነው ግራ የገባኝ😂😂
ደህና ሁኑ
ዳዊት ጌታቸው
@dawitview
ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም (ልጅ ያሬድ) ማረሚያ ቤት እንዲወርድ ታዘዘ‼️
ትዕዛዙን የሰጠው የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት 1ኛ የፀረ-ሽብርና የሕገ-መንግስት ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ነው።
የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ወንጀል ጉዳዮች ዳይሪክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ኮሜዲያን ያሬድ ዘላለም ባልቻ በቅጽል ስሙ( ልጅ ያሬድ) በተባለ ግለሰብ ላይ ተደራራቢ ክሶችን አቅርቧል።
በተለይም በኮምፒዩተር የሚፈጸም ወንጀል ድንጋጌን መተላለፍ፣ የቤተክርስቲያንና የሰዎችን ክብርና መልካም ስም በማጉደፍ፣ ጥላቻ ንግግር ማሰራጨት የሚሉ ነጥቦች ይገኙበታል።
ክሱ ከደረሰው በኋላ ተከሳሹ ያቀረበውን የዋስትና ጥያቄው ፍርድ ቤቱ ውድቅ በማድረግ በማረሚያ ቤት ሆኖ ጉዳዩን እንዲከታተል አዟል።
ይሁንና ተከሳሹ ችሎት በቀረበበት ጊዜ ዐቃቤ ሕግ ለቤተክርስቲያን ክብር፣ ለማህበረሰቡ ስነልቦና፣ እሴትና ባህል ሲባል በክሱ ላይ የቀረቡ ዝርዝር ነጥቦች እንዳይታተም በሚዲያ እንዳይቀርብ እንዲሁም ችሎቱ በዝግ እንዲሆን አቤቱታ አቅርቧል።
አቤቱታውን የመረመረው ፍርድ ቤቱም የማህበረሰቡን ክብርና ስነልቦናን ከግምት ውስጥ በማስገባት የክሱ ዝርዝር ጉዳይ በሚዲያ እንዳይሰራጭ ችሎቱ በዝግ እንዲሆን ብይን ሰጥቷል።
@Esat_tv1
@Esat_tv1
ብታውቂ
ስትስቂ!
ጠፈርን እንደምታደምቂ
መንፈስን ካ'ዚም እስራት
እንደምታላቅቂ
ብታውቂ!
ስትስሚ!
አጥንት እንደምታለመልሚ
ታማሚ ልብ እንደምታክሚ
ብታውቂ!
ስታወሪ!
ዱዳ እንደምታናግሪ
መነኩሴውን ከሱባኤ፣
ፈላስፋውን ከጉባኤ
እንደምትጠሪ
ብታውቂ!
እንኳንስ በ'ኔ ልትስቂ
ከራስሽ ጋር ፍቅር ይዞሽ
አይሽ ነበር ስትማቅቂ።
በእውቀቱ ስዩም
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ
" በጦርነቱ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፣ መምህራን ፣ አምራች አርሶ አደሮች፣ ሃኪሞችን ጨምሮ ሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች ተሰውተዋል " - ጊዜያዊ አስተዳደሩ
በተለያዩ የማህበራዊ የትስስር ገፆች በትግራዩ ደም አፋሳሽ ጦርነት ስለ ተሰው ታጋዮች " እንደ ተራ ነገር የሚነገረው ቁጥር የሃቅ መሰረት ስለሌለው ትርጉም አንሰጠውም " አሉ የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ።
ፕረዚደንቱ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ቀን ስነ-ሰርአት በይፋ መታወጅ አስመልክተው ጥቅምት 2/2016 ዓ.ም ለክልሉ የመንግስት ፣ የግልና የውጭ ሚድያዎች ሰፊ ቃለ-መጠይቅና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ ፤ በክልሉ በተካሄደው ደም አፋሳሽና እልህ አስጨራሽ ጦርነት የተሰው ታጋዮች ቁጥር እንዲገልፁ ከጋዜጠኞች ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት መልስ " ... በትግሉ ስለተሰውት ታጋዮች ቁጥር ብዙ ተረት ነው የሚወራው ፤ የተሰውት ታጋዮች ቁጠር እንገልፃለን። ለጊዜው ግን መግለፁ አስፈላጊ ሆኖ ስላልታየን እናቆየዋለን " ብለዋል።
" ... ለትግራይ ህልውና የተከፈለ ዋጋ የሚመጥነው ደረጃና ዋጋ መስጠት አለብን ሲባል ለያንዳንዱ የተሰዋ ታጋይ ፤ ለያንዳንዱ የተሰዋበት ቤተሰብ የክብር የምስክር ወረቀት ልከናል " ያሉት አቶ ጌታቸው ፤ " የተሰውት ታጋዮች ቁጥር በእጃችን ይገኛል። ከቁጥሩ ባሻገር ግን እጅግ ከባድና ውድ ዋጋ ከፍለናል። ለህልውናችን የተከፈለ በመሆኑም ግን የሚያስቆጨን አይሆንም ሊባል ይችላል " ሲሉ አክለዋል።
አቶ ጌታቸው ፤ " ብዙ ልጆቻችን ከፍለናል። ጠላቶች (ፕሬዜዳንቱ ጠላቶች ያሏቸውን በስም አልገለጿቸውም) የኛ የመስዋእት ኪሳራ በማብዛት የነሱ ለማሳነስ እንደማነፃፀሪያ በማቅረብ ብዙ ይናገራሉ። በበኩሌ አሁን ካለው የተሰዋ ታጋይ ቁጥር ሩብ ፤ ከሩብ በታች ፤ አንድ መቶኛው እንኳን ብንከፍል ዋጋው ከባድ ነው የሚል እምነት አለኝ። " ብለዋል።
" አልተሳካልንም እንጂ ያለ አንድ ታጋይና ያለ አንድ ወጣት መስዋእት ፣ ራሳችን በራሳችን የማስተዳደር መብታችን የምናረጋግጥበት ዕድል ቢኖር እመርጥ ነበር " ሲሉ አክለዋል።
ፕሬዜዳንቱ በስም ያልጠሯቸውና " ጠላቶች " ሲሉ የጠሯቸው ኃይሎች " አሁን ላይ መጥራት በጀመሩት የተዛባና የተጋነነ ቁጥር በመደናገር ሌላው ያልሆነ ቁጥር ሲጠራ ቢውል ለኔ 20 ሺህ ተባለ ፣ 10 ሺህ ተባለ ፣ ህልውናችን ለማረጋገጥ አንድ ሰው ይሰዋ 20 ሺህ ዋጋው እጅግ ከባድ ነው " ብለዋል።
" በተሰውት ታጋዮች ዝርዝር ፦
- የዩኒቨርስቲ መምህራንና ተማሪዎች ፣
- ጥሩ አምራች አርሶ አደሮች
- ሃኪሞች ሁሉም አይነት የህብረተሰብ ክፍሎች አሉ። በአጠቃላይ ትግራይን በሰላም ጊዜ ወደ ተሻለ የእድገት ደረጃ የማሸጋገር አቅም የነበራቸው በመስዋእትነት አጥተናል " ያሉት አቶ ጌታቸው ፤ " ይህንን መስዋእትነት ዋጋ መስጠት እንዳለ ሆኖ ፤ ቁጥሩ ጠላት በሚለው ደረጃ እንዳልሆነ መረዳቱ ስጋታችን ቀንሶ ያረጋጋናል " ማለታቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ዘግቧል።
የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ቀን ሰነ-ሰርዓት ከጥቅምት 3 አስከ 5 በተለያዩ ዝግጅቶች ታጅቦ በመካሄድ ፤ ጥቅምት 6/2016 ዓ.ም " በሃዘን አንገታችን እንደፋም " በሚል መሪ ቃል በሚካሄድ የህዝብ ሰልፍ እንደሚጠቃለል ከወጣው መርሃ ግብር ለመረዳት ተችሏል።
መረጃው በቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የተዘጋጀ ነው።
@tikvahethiopia
