Dire Dawa Comprehensive Secondary School
Open in Telegram
566
Subscribers
+424 hours
+127 days
+1930 days
Posts Archive
የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዉጤታችሁን በምን መመልከት ትችላላችሁ?🤔
⚡️ የ2015 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ነገ መስከረም 29/2016 ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በሚከተሉት አማራጮች ውጤታችሁን ማየት እንደምትችሉ የትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
በዚህም መሰረት ተማሪዎች፦
> በዌብ ሳይት - https://eaes.edu.et/
>በአጭር የጽሑፍ መልዕክት - 6284
> በቴሌግራም - https://t.me/eaesbot ላይ ተማሪዎች ዉጤታችሁን መመልከት እንደምትችሉ ሚኒስቴሩ ገልጿል።
እንኳን አደረሳችሁ !
ውድ የክርስትና እምነት ተከታይ የስራ ባልደረቦቼ በሙሉ እንኳን ለትንሳኤ በዓል አደረሳችሁ ።
በዓሉ የሰላም ፣ የደስታ ፣ የፍቅር ፣ የመተሳሰብ ይሆን ዘንድ እየተመኘሁ።
በዓሉ ሲከበር ፤ የተቸገሩ ወገኖቻንን አለንላችሁ በማለት ፣ የወደቁትን በማንሳት ፣ በሀዘን ላይ ያሉ ወገኖችን በማፅናናት፣ ከክፉ ድርጊትና ሀሳብ ርቀን ፤ በዓሉን በሰላም እጦት ፣ በግጭት ፣ በጥቃት፣ በድርቅ ክፉኛ የተጎዱ ወገኖቻችንን እያሰብን ፤ በገዛ ቄያቸው ከሞቀው ቤታቸው ተፈናቅለው ሜዳ ላይ የወደቁትን ፤ በፀሃይና ዝናብ የሚንከራተቱትን ፤ የሚወዱትን ተነጥቀው በጥልቅ ሀዘን ላይ የሚገኙትን ፣ ታመው በየሆስፒታሉ የተኙትን ፣ በየሰው ሀገር በስደት ስቃያቸውን እያዩ ያሉ ወገኖቻችንን እያሰብን ፤ በግልም ፤ በሀገርም ላለብን ችግር ሁሉ ፈጣሪ መፍትሄ እንዲያበጅልን እየተማፀንን እንድናሳልፍ አደራ እያልኩ።
የሰላም፣ የመተሳሰብና የበረከት በዓል ያድርግላችሁ!
ፈጣሪ ሀገራችን ሰላም ያድርግልን !
መልካም በዓል !
# ሳላሐዲን ❤️
ለትምህርት ቤታችን ማህበረሰብ በሙሉ
እንኳን ደስ አላችሁ
በሀገር አቀፍ ደረጃ በሰሜን ኢትዩጲያ ተከስቶ በነበረው ግጭት ወቅት የት/ቤታችን ማህበረሰብ በ 2014ዓ.ም በተደረገው ሀገራዊ ጥሪ ለጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ማድረጋችን የሚታወስ ነው።
በዚህ መሰረት ትምህርት ቤታችን በገንዘብና በአይነት ግምቱ 1.73 ሚሊየን ብር ድጋፍ በማድረግ ትምህርት ቤቱ ላበረከተው አስተዋፅኦ የሀገር ወገንና የዜግነት ሀላፊነት በመወጣት ከአስተዳደሩ ትምህርት ቤቶች ቀዳሚ በመሆን የዋንጫ እና የሰርተፊኬት ተሸላሚ ሆኗል በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን ።
