en
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Open in Telegram
916
Subscribers
-124 hours
+47 days
-330 days
Posts Archive
ሚያዝያ 13/2018 ዓ.ም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ጉባኤ ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ያለፉት 9ወራት ያከናወናቸው ተግባራትና የቀሪ ዓመታት ዕቅድ ማፅደቅ ላይ ያተኮረ ከምክር ቤቱ አባላት ጋር ውይይት አደረገ። የዕለቱ የመወያያ ዕቅድና ሪፖርት በአቶ ናስር ጫካ ቀርቦ ባለፉት 9 ወራት በእስልምና ጉዳይ ምክር ቤት  የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት በወረዳው ውስጥ የሚገኙ መስጂዶች ፣የመቃብር ስፍራ የዳዕዋ ትምህርት ተቋማትና መርከዞች ያሉበት ሁኔታ ቅኝት በማድረግ ሀይማኖታዊ አስተምህሮት ለማጠናከር  የቁራዓን፣ የሀዲችና ሀይማኖታዊ መፅሐፍት እጥረት በማሰባሰብ እጥረት ላለባቸው አከባቢዎች ተደራሽ ማድረግ መቻሉ ፤ሙስሊም የህብረተሰብ በአገልግሎት እጦት እንዳይገላታ የቀብርና የመስጂዶች በመጡ ጥያቄዎች መሰረት ምላሽ መስጠት መቻሉ፤ከሁሉ ቤተ እምነቶች ጋር የተቀናጀ ውይይት መደረጉ በሪፖርቱ ተመላክቷለ። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ ሼህ አብድልበር ዘይኑ በጉባኤው ባስተላለፉት መልዕክት ባለፉት ዓመታት ለሕዝበ ሙስሊሙ ብቻ ሳይሆን እንደ ወረዳ  የሚጠቅሙ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። በወረዳች ውስጥ ያሉ መስጂዶች ያለባቸው የግብዓት እጥረት ለማሟላት ሁሉም የምክር ቤቱ አባል ወክለው ከመጡበት አከባቢና ህብረተሰብ ጋር ሀብት የማሰባሰብ ስራ ግንዛቤ በመፍጠርና ሀብት የማሰባሰብ ስራ መሰራት መቻል እንዳለባቸው ፤ተናግረው እንደ ወረዳ ምክር ቤት የራሱ መስሪያ ቤት እንዲሁም የቲሞች ዚያራ ለተለያዩ ተግባራትን ለማስፈፀም እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው ይህንን ለማሳካት አቅም በፈቀደ መልኩ  ጥረት ማድረግ እንደሚገባ አስታውቀዋል ። ምክር ቤቱ ቀጣይ ላይ በተጠናከረ መልኩ ሪፖርትቶች ተገምግመው ውሳኔ ለማሳለፍ የሚካሄደውን ጉባኤ ወሳኝ በመሆን ለጉባኤው መሳካት የምንሰራቸው ሀይማኖታዊ  ተግባር አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል። በገጠሩ የህብረተሰብ ክፍል እና በወረዳችን ያሉትን የእስልምና ልህቀት ማእከላትን የማጠናከር ስራ ለነገ የማይባል በመሆኑ ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም የወረዳችን ሰላም እና ደህንነት ለመጠበቅ የሀይማኖት ተቋማት ኃላፊነት የጎላ በመሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ በሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለጸው በገ/ጉ/ወ/ወረዳ በሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት አማካኝነት የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በቀበሌ ለሚገኙ የሀይማኖት አባቶችና ባለድርሻዎች ያሳተፈ የግንዛቤ መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው። የፅህፈት ቤቱ የሃይማኖት ዕምነት ጉዳዮች እሴት ግንባታ ዋና ስራ ሂደት አስተባባሪ ወይዘሮ አስቴር ዮሐንስ ለመድረኩ የተዘጋጀ መወያያ ሰነድ አቅርበው ውይይት የተደረገ ሲሆን ከሌሎች እምነት ተከታዮች ጋር በምንም ምክንያት ወደ ግጭት መግባት እንደማያስፈልግ፣ መከባበርን ይበልጥ አጠናክረን በማስቀጠል ለሰላም እሴቶች ግንባታ የሚጠበቅብንን እንወጣለን፣ሰርግ ቤቶች እስከ ሌሊት ጭፈራ መኖሩን፣ስለ ሰላም መስበክ የዕለት ተዕለት ተግባር መሆን እንደሚገባና ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስፈልግ እንደሚገባ ተሳታፊዎች ጠይቀዋል የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ፅፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙሰማ በድሩ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ለወረዳችን እድገት መሰረት የሆነውን ሰላም ለመጠበቅ ፀጥታን የሚያደፈርሱ ጉዳዮች አስቀድሞ በመለየትና የመፍትሄ እርምጃ በመውሰድ ረገድ ከሀይማኖት ተቋማትና ከህብረተሰቡ ጋር በቅርበትና በቅንጅት እየተሰራ  መሆኑን ገልፀዋል ። አቶ ሙሰማ አክለው ህግ ለማስከበር የዕምነት ተቋማት ለመንግስት አጋዥ በመሆናቸው ከዘረኝነትና ጎጠኝነት ገለልተኛ መሆን አንደሚገባቸው አስታውሰው ፤መንግስት አጥፊዎችን የመቅጣት ህግን የማስከበር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል። የወረዳው የሃይማኖት ተቋማት ህብረት ሰብሳቢና የእስልምና ምክር ቤት ሰብሳቢ ሼህ አብድልበር ዘይኑ ከመድረክ ለተነሱት ሃሳብና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መካሄድ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰው ፣ሴት ልጅ ጠለፋ ላይ የተሰማሩ ደላሎች መኖራቸውና ይህ ለሰው ልጅ ክብር የሚነካ ተግባር በመሆኑ የእምነ አባቶች መሰል ድርጊቶችን ለመካከል ሚናቸው ከፍተኛ በመሆኑ በትኩረት መስራት አንደሚገባ አሳስበዋል ሁለንተናዊ ትብብር በማጎልበት የወረዳችንና የሃገራችን ልዕልና ከዳር ማድረስ ይጠበቃል ያሉት ሼኸ አብድልበር ዕምነታችን የማይፈቅደው ተግባር በመተው ፤ሁሉም በየ እምነቱ በመከባበር እምነቱ መጠበቅ እንደሚገባ ጠቅሰው ዕምነትን እንደ ሽፋን በመጠቀም የራሳቸው አጀንዳ ለማራመድ የሚንቀሳቀሱ አካላት በተለያዩ አከባቢዎች ለሚፈፀመው ግፍና በደል በፅኑ አውግዘዋል። የወረዳው የሃይማኖት ተቋማት ህብረት ምክትል  ሰብሳቢ መጋቢ ሀይማኖት ሀብታሙ የኔው በበኩላቸው ጉባኤተኞች የግንኙነት አግባባቸውን በማጠናከር ጸረ-ሰላም ሃይሎች ሊያስከትሉ የሚችሉትን የሰላም እጦት አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል። ፈጣሪ የሚያዘውን መልካም ስራ ልንሰራ እንደሚገባ የጠቆሙት ሀብታሙ የኔው፣በያለንበት እምነት ለሰዎች ሁሉ በጎ ስራን ልንሰራ ያስፈልጋል ሲሉ ምክራቸውን ለግሰዋል።

ሚያዚያ 12/2018 ዓ/ም ከአጎራባች ወረዳዎች ጋር በቅንጅት መስራት ወንጀልን አስቀድሞ ለመከላከልና የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ ተገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለጸው በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምእራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ ወረዳ፣ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቀቤና ልዩ ወረዳና በጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ አዋሳኝ ቀበሌያት ዘላቂ ሰላምና ወንጀልን አስቀድሞ ለመከላከልና የህግ የበላይነት ዙሪያ በጋራ በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል የሶስትዮሽ ውይይት በዛሬው ዕለት ኢንጌ ከተማ ላይ በተከሄደበት ወቅት ነወ። ከአጎራባች ወረዳዎች በድንበር አከባቢ በተለያዩ ምክንያቶች የሚፈጠሩ ወንጀሎችና የጸጥታ መደፍረስ ለመቆጣጠርና ቀጠናዊ ሰላምን ለማስፈን የውይይት መድረኩ ወሳኝ መሆኑ በመድረኩ የገለጸ ሲሆን ይህ አይነት የምክክር መድረክ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተመላክቷል። የጋራ ጉዳይ የሆነውን ሰላምን ለማረጋገጥ ሁሉ ዓቀፍ ትብብርን አጠናክሮ ማስቀጠል ከሶስቱም አጎራባች ወረዳዎች እንደሚጠበቅ እና  የማህበረሰቦችን በጋራ አብሮ የመኖር መስተጋብር በፅኑ መሰረት ላይ የተገነባ እንዲሆን ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በውይይት መድረኩ ተገልጿል፡፡ በምክክር መድረኩ ላይ የደቡብ ምእራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ ወረዳ፣ የቀቤና ልዩ ወረዳና የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የፖሊስ አመራሮች፣የቀበሌ ሚሊሻዎች እንዲሁም የቀበሌ አመራሮች ተሳትፈዋል። መረጃው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ነው።

ሚያዚያ 11/2018 ዓ/ም በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በኢንጌ ከተማ ለሚገነባው የኢርሻድ ኢስላማዊ ኮሌጅ የመሠረት ድንጋይ በዛሬው እለት ተቀመጠ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ፣ ኢንጌ ከተማ በ10 ሺህ ካሬ ሜትር መሬት ላይ ለሚያርፈው አዲስ ኢስላማዊ ኮሌጅ ግንባታ የሚያስችል የመሠረት ድንጋይ በዛሬው ዕለት በይፋ ተቀምጧል። የኮሌጁን የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጡት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይህ አብዱልከሪም በድረዲን ሲሆኑ፤ የአዲስ አበባ እና የወረዳው መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ታላላቅ ኡለሞች እና የወረዳው አመራሮች በስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል። በዚህ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይህ አብዱልከሪም በድረዲን በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የመብት ጥሰት እየፈጸሙ የሚገኙ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በጥብቅ አሳስበዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታህ ሁሴን ባስተላለፉት መልዕክት በመንፈሳዊ ትምህርት የታገዘ ዜጋ ለሀገሪቱ እድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው በማስገንዘብ፣ አስተዳደሩ የኮሌጁን ግንባታ በሁሉም መስክ ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን ቃል ገብተዋል። የዚህ ግዙፍ ኢስላማዊ ኮሌጅ መገንባት፤ የዲን ትምህርት ፍለጋ ወደ አዲስ አበባ እና የተለያዩ አካባቢዎች የሚንከራተተውን የአካባቢውን ህዝበ ሙስሊም በአቅራቢያው እውቀትን እንዲያገኝ ከማስቻሉም በላይ፣ ማህበረሰቡን ሃይማኖታዊ እውቀት የሚያስጨብጡ ብቁ ዳኢዎችን ለማፍራት የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው በዕለቱ ተብራርቷል። የፌደራል እና የአዲስ አበባ መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የሚገኙትን ኢስላማዊ ተቋማት እና መስጂዶች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን፤ በተለይም የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አህመድ ለአባታቸው መታሰቢያ ያስገነቡትን የበይተል ሙሀባ መስጂድና መድረሳን እንዲሁም የቁባ መስጂድን በዕለቱ ጎብኝተዋል።

የሳምንቱ አበይት ዜናዎች ሚያዚያ 11/2018 ዓ.ም 🎤 በጉራጌ ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በኢንጌ ከተማ ለሚገነባው የኢርሻድ ኢስላማዊ ኮሌጅ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በባለፉት 5 አመታት በወረዳው በሁሉም የማዘጋጃ ከተሞች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች ማከናወኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የሚወዳደሩ የብልጽግና ፓርቲ እጩዎች በወረዳው የተለያዩ ቀበሌዎች የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን በመዘዋወር ጎበኙ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የተማሪዎች ስነ-ምግባር በማሻሻል ተወዳዳሪና ብቁ ዜጋ ለመፍጠር የመምህራን ሚና ከፍተኛ መሆኑ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ፅህፈት ቤት ገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ባለፉት 5 አመታት ከ24,081 በላይ ወጣቶችን በቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉ የገደባኖ ጉታዘር  ወለኔ ወረዳ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ፅ/ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በባለፉት 5 አመታት በህበረተሰቡ፣ በተወላጅ ባለሀብቶች፣ በመንግስትና ከ620 ሚልዮን ብር በላይ ሀብት በማሰብሰብ የትምህርት መሰረተ ልማት ማሻሻል መቻሉን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅህፈት ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨

ሚያዚያ 10/2018 ዓ/ም በባለፉት 5 አመታት በወረዳው በሁሉም የማዘጋጃ ከተሞች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች ማከናወኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በባለፉት 5 አመታት በወረዳው መንግስት 112 ሚሊዩን በላይ በ6ቱም የማዘጋጃ ከተሞች እና በህብረተሰብ ተሳትፎና በልማታዊ ባለሀብት ከ234 ሚሊዮን ብር በላይ በአጠቃላይ 346 ሚሊዮን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መከናወናቸውን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት አክሎ ገለጿል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተማም አደም በባለፉት 5 አመታት የተከናወኑ ተግባራት አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ፅ/ቤቱ  በባለፉት 5 አመታት በሁሉም የማዘጋጃ ከተሞች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች ተሰርቷል ብለዋል። በወረዳው በባለፉት 5 አመታት በማህበረሰብ ተሳትፎ በባለፉት 5 አመታት በማህበረሰብ ተሳትፎ በጥሬ ገንዘብ፣ በቁሳቁስና በጉልበት በ2013 ዓ.ም 28 ሚሊዮን ብር ከነበረበት በ2018 ዓ.ም እስከ አሁን 234 ሚሊየን ሚሊዮን ብር ማድረስ መቻሉን ገልጸዋል። በዚህም በመንግስት፣ በማህበረሰቡና በባለሃብቶች በርካታ ስራዎች መሰራቱን ጠቅሰው በ6ቱም የማዘጋጃ ከተሞች ከመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎቸ አንጻር 26 ኪ.ሜትር የመንገድ ከፈታ በማድረግ ጠጠር የማልበስ ስራ ፣ 22 የተለያዩ የመንገድ እስትራክቸር ከልቨርት፣ ቱቦ ፣ ፎርድ ፣ 8 ኪ.ሜትር ዲች ስራ ፣1.8 ኪ/ሜትር መሀል አምባ ከተማ የጌጥ ድንጋይ ንጠፍ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። ከውሃ ዝርጋታ አንጻር 16 ኪሎ ሜትር ዝርጋታ በማከናወን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። የኤሌክትሪክ ሀይል አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ 21.6 ኪ.ሜትር የከፍተኛ እና ዝቅተኛ መስመር በመዘርጋት 4 ባለ 50KW ፣ 2 ባለ 100KW እና 2 ባለ 200 KW በጥቅሉ 8 ትራንስፎርመር በመትከል ህብረተሰብ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል:: የመሀል አምባ የቄራ ግንባታ፣ መሀል አምባ የማዘጋጃ ቤት ፅ/ቤት ግንባታ ፣ወ/ዲሴ የማዘጋጃ ፅ/ቤት ግንባታ ፣ የኢንጌ ሁለ ገብ አደራሽ ፣ መሀል አምባና ጅማ ቆሻሻ ጉድጓድ ግንባታ ስራ፣ ፣ጎርፍ መቀልበሻ ስራ እና ለከተሞች ለመሬት ካሳ ክፈያ ስራዎች ባለፉት 5 አመታት በከተሞች ከተከናወኑ ስራዎች ተጠቃሽ መሆናቸውን አቶ ተማም ገልጸዋል። በከተሞች 17.25 ሄ/ር ለተለያዩ አገልግሎት የሚውል ማለትም በማህበራት ቤት ልማት ፕሮግራም የቤት የዜጎች የመኖራያ ቤት ችግር ለመቅረፍ 41 በመሰረታዊ ህብረት ስራ በማደረጃት 398 አባለት 6.5 ሄ/ር መሬት በማስተላከፍ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፣ለግል መኖራያ ቤት 3.5ሄ/ር ፣ለንግድና ኢንቨስትመንት አገልግሎት 2.15 ሄ/ር ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞቸ 0.1ሄ/ር ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት 5.5 ሄ/ር መሬት መተላለፉን አስታውቀዋል። የአየር ንብረት ለመቆጣጠር ለውበትና ለምግብነት የሚውሉ ከ800 መቶ ሺህ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል። በወረዳው ማዘጋጃ ቤቶች 4 ከነበሩበት ወለጋዲሴ እና ጎራ ማዘጋጃ ቤት በማሳደግ ወደ 6 የማዘጋጃ ቤት የማሳደግ ስራ መሰራቱን ገልጸው ከፈርጅ ሽግግር አንጻር አምስት ከተሞች ወደ ፈርጅ አራት መሀል አምባ ከተማ ከፈርጅ አራት ወደ ፈርጅ ሶስት ለማስገባት በልዩ ትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋለ። የመሀል አምባ ከተማ ከፈርጅ ጥያቄ የማአከለዊ ኢትዮጰያ ክልል ጥናት እያካሄደ ሲሆን የመሀል አምባ ማዘጋጃ ቤት የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን  በዲጅታል አገልግሎት ለመስጠት 1,380,000 የሶፍት ዌር ዲዛይን እና ዴቨሎፕመንት ከተሰኘ ድርጅት ውል በመግባት የቅ/ዝግጅት ስራ እየተሰራ መሆኑን የጽ/ቤቱ ኃላፊ ተናግረዋል። የገጠር እስኬጅ ማእከላት 18 የገጠር ቀበሌዎች የመሰረታዊ ፕለን የተስራላቸው ሲሆን መሰረታዊ ፕላን ከተሰራለቸው የግንባታ ፍቃድ ወስደው የጀመሩ 4 የእስኬጅ ማእከላት ፈንጀሌ፣አረዳ፣ሙጆ እና ኩራሮ ሲሆኑ 4 የእስኬጅ ማእከላት የግንባታ ፍቃድ ተሰጥቷቸው ወደ ተግባር ያልገቡ ደነብ፣ቲቲሌ፣ቤደር እና ጠይባ ሲሆኑ ቀሪ የእስኬጅ ማአከላት በእቅድ ተይዘው የሚለሙ ይሆናል። ከዚህም ባለፈ አዲስ ኢንሼቲቭ የሆነው የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት ማለትም የመሀል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፓቲል ግብዓት የሟሟለት ስራ ፣ ወ/ዲሴ ፅ/ቤት ግንባታ እና በኢንጌ መዋለ ህፃነት ግንባታ ስራው ፣የመሀል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፓቲል የካፌ ግንባታ እና በሚድሮክ ኢንቨስትመነት ግሩፕ አማከሰኝነት የተሰራው ለመሀል አምባ እና በዙሪያው ለሚገኙ ማህበረሰቦች የንፅህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት 3 ጥልቅ ጉድጓድ ቁፎሮ ፣12 ቦኖዎች የሀይድሮ ኤሌክትሪካል ስራ ተጠናቆ ለህብረተሰብ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፣ የመሀል አምባ፣ ኮንበል እና ጅማ ከተሞች መዋለ ህፃነት አንድ መማሪያ ክፍል ግንባታ የጥናትና ዲዘየን ስራ በመስራት ጨረታ አሸናፊ ተለይቶ ውል የተገባ ሲሆን በመንግስት፣ህ/ሰቡ እና በልማታዊ ባለሀብት እንዲሳተፍ በማድረግ የጋራ አካውንት በመክፈት ሀብት የማሰባሰብ ስራ በመጀመር የልማት ስራዎች ለመስራት እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆናቸውን አስታውቀዋል።