ch
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

前往频道在 Telegram
917
订阅者
+124 小时
+57 天
-330 天
帖子存档
ሚያዚያ 10/2018 ዓ/ም በባለፉት 5 አመታት በወረዳው በሁሉም የማዘጋጃ ከተሞች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች ማከናወኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በባለፉት 5 አመታት በወረዳው መንግስት 112 ሚሊዩን በላይ በ6ቱም የማዘጋጃ ከተሞች እና በህብረተሰብ ተሳትፎና በልማታዊ ባለሀብት ከ234 ሚሊዮን ብር በላይ በአጠቃላይ 346 ሚሊዮን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎች መከናወናቸውን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት አክሎ ገለጿል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ተማም አደም በባለፉት 5 አመታት የተከናወኑ ተግባራት አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ፅ/ቤቱ  በባለፉት 5 አመታት በሁሉም የማዘጋጃ ከተሞች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች ተሰርቷል ብለዋል። በወረዳው በባለፉት 5 አመታት በማህበረሰብ ተሳትፎ በባለፉት 5 አመታት በማህበረሰብ ተሳትፎ በጥሬ ገንዘብ፣ በቁሳቁስና በጉልበት በ2013 ዓ.ም 28 ሚሊዮን ብር ከነበረበት በ2018 ዓ.ም እስከ አሁን 234 ሚሊየን ሚሊዮን ብር ማድረስ መቻሉን ገልጸዋል። በዚህም በመንግስት፣ በማህበረሰቡና በባለሃብቶች በርካታ ስራዎች መሰራቱን ጠቅሰው በ6ቱም የማዘጋጃ ከተሞች ከመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎቸ አንጻር 26 ኪ.ሜትር የመንገድ ከፈታ በማድረግ ጠጠር የማልበስ ስራ ፣ 22 የተለያዩ የመንገድ እስትራክቸር ከልቨርት፣ ቱቦ ፣ ፎርድ ፣ 8 ኪ.ሜትር ዲች ስራ ፣1.8 ኪ/ሜትር መሀል አምባ ከተማ የጌጥ ድንጋይ ንጠፍ ስራ መሰራቱን ተናግረዋል። ከውሃ ዝርጋታ አንጻር 16 ኪሎ ሜትር ዝርጋታ በማከናወን ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል ብለዋል። የኤሌክትሪክ ሀይል አገልግሎት ተጠቃሚ ለማድረግ 21.6 ኪ.ሜትር የከፍተኛ እና ዝቅተኛ መስመር በመዘርጋት 4 ባለ 50KW ፣ 2 ባለ 100KW እና 2 ባለ 200 KW በጥቅሉ 8 ትራንስፎርመር በመትከል ህብረተሰብ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል:: የመሀል አምባ የቄራ ግንባታ፣ መሀል አምባ የማዘጋጃ ቤት ፅ/ቤት ግንባታ ፣ወ/ዲሴ የማዘጋጃ ፅ/ቤት ግንባታ ፣ የኢንጌ ሁለ ገብ አደራሽ ፣ መሀል አምባና ጅማ ቆሻሻ ጉድጓድ ግንባታ ስራ፣ ፣ጎርፍ መቀልበሻ ስራ እና ለከተሞች ለመሬት ካሳ ክፈያ ስራዎች ባለፉት 5 አመታት በከተሞች ከተከናወኑ ስራዎች ተጠቃሽ መሆናቸውን አቶ ተማም ገልጸዋል። በከተሞች 17.25 ሄ/ር ለተለያዩ አገልግሎት የሚውል ማለትም በማህበራት ቤት ልማት ፕሮግራም የቤት የዜጎች የመኖራያ ቤት ችግር ለመቅረፍ 41 በመሰረታዊ ህብረት ስራ በማደረጃት 398 አባለት 6.5 ሄ/ር መሬት በማስተላከፍ ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል፣ለግል መኖራያ ቤት 3.5ሄ/ር ፣ለንግድና ኢንቨስትመንት አገልግሎት 2.15 ሄ/ር ለጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞቸ 0.1ሄ/ር ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት 5.5 ሄ/ር መሬት መተላለፉን አስታውቀዋል። የአየር ንብረት ለመቆጣጠር ለውበትና ለምግብነት የሚውሉ ከ800 መቶ ሺህ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል። በወረዳው ማዘጋጃ ቤቶች 4 ከነበሩበት ወለጋዲሴ እና ጎራ ማዘጋጃ ቤት በማሳደግ ወደ 6 የማዘጋጃ ቤት የማሳደግ ስራ መሰራቱን ገልጸው ከፈርጅ ሽግግር አንጻር አምስት ከተሞች ወደ ፈርጅ አራት መሀል አምባ ከተማ ከፈርጅ አራት ወደ ፈርጅ ሶስት ለማስገባት በልዩ ትኩረት እየተሰራ ይገኛል ብለዋለ። የመሀል አምባ ከተማ ከፈርጅ ጥያቄ የማአከለዊ ኢትዮጰያ ክልል ጥናት እያካሄደ ሲሆን የመሀል አምባ ማዘጋጃ ቤት የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን  በዲጅታል አገልግሎት ለመስጠት 1,380,000 የሶፍት ዌር ዲዛይን እና ዴቨሎፕመንት ከተሰኘ ድርጅት ውል በመግባት የቅ/ዝግጅት ስራ እየተሰራ መሆኑን የጽ/ቤቱ ኃላፊ ተናግረዋል። የገጠር እስኬጅ ማእከላት 18 የገጠር ቀበሌዎች የመሰረታዊ ፕለን የተስራላቸው ሲሆን መሰረታዊ ፕላን ከተሰራለቸው የግንባታ ፍቃድ ወስደው የጀመሩ 4 የእስኬጅ ማእከላት ፈንጀሌ፣አረዳ፣ሙጆ እና ኩራሮ ሲሆኑ 4 የእስኬጅ ማእከላት የግንባታ ፍቃድ ተሰጥቷቸው ወደ ተግባር ያልገቡ ደነብ፣ቲቲሌ፣ቤደር እና ጠይባ ሲሆኑ ቀሪ የእስኬጅ ማአከላት በእቅድ ተይዘው የሚለሙ ይሆናል። ከዚህም ባለፈ አዲስ ኢንሼቲቭ የሆነው የአንድ ከተማ አንድ ፕሮጀክት ማለትም የመሀል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፓቲል ግብዓት የሟሟለት ስራ ፣ ወ/ዲሴ ፅ/ቤት ግንባታ እና በኢንጌ መዋለ ህፃነት ግንባታ ስራው ፣የመሀል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፓቲል የካፌ ግንባታ እና በሚድሮክ ኢንቨስትመነት ግሩፕ አማከሰኝነት የተሰራው ለመሀል አምባ እና በዙሪያው ለሚገኙ ማህበረሰቦች የንፅህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት 3 ጥልቅ ጉድጓድ ቁፎሮ ፣12 ቦኖዎች የሀይድሮ ኤሌክትሪካል ስራ ተጠናቆ ለህብረተሰብ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፣ የመሀል አምባ፣ ኮንበል እና ጅማ ከተሞች መዋለ ህፃነት አንድ መማሪያ ክፍል ግንባታ የጥናትና ዲዘየን ስራ በመስራት ጨረታ አሸናፊ ተለይቶ ውል የተገባ ሲሆን በመንግስት፣ህ/ሰቡ እና በልማታዊ ባለሀብት እንዲሳተፍ በማድረግ የጋራ አካውንት በመክፈት ሀብት የማሰባሰብ ስራ በመጀመር የልማት ስራዎች ለመስራት እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

ሚያዚያ 09/2018 ዓ/ም በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የሚወዳደሩ የብልጽግና ፓርቲ እጩዎች በወረዳው የተለያዩ ቀበሌዎች የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን በመዘዋወር ጎበኙ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በሰባተኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የሚወዳደሩ እጩዎች እና የወረዳው ተወላጅ አመራሮች በወረዳው የተለያዩ ቀበሌዎች የተገነቡና እየተገነቡ የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን በመዘዋወር ጎበኙ። ጎራ እና ቤደር 1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ፣ኢንጌ ከተማ የስብሰባ አዳራሽና መዋለ ህጻናት ግነባታ እንዲሁም ደነብ የግብርና መስኖ ልማት እንቅስቃሴን የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ እጩዎችና ተወላጅ አመራሮች የመስክ ምልከታ በዛሬው እለት አካሂደዋል። በጉብኝቱ የጉራጌ ዞን ሴቶችና ህጻናት መምሪያ ኃላፊ እና የኢፌድሪ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እጩ ወይዘሮ ነጅብያ ማህሙድ ፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የመሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ኤጀንሲ ስራስኪያጅ እና የክልል ምክር ቤት እጩ  አቶ አ/ሃፊዝ ሁሴን ፣የጉራጌ ዞን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና የክልል ምክር ቤት እጩ  አቶ ኸይሩ መሀመድ እንዲሁም የጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙራድ ረሻድ ተገኝተዋል።

ሚያዝያ 07/2018ዓ.ም የተማሪዎች ስነ-ምግባር በማሻሻል ተወዳዳሪና ብቁ ዜጋ ለመፍጠር የመምህራን ሚና ከፍተኛ መሆኑ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ፅህፈት ቤት ገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለፀው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ፅ/ቤት ከገደባኖ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችና መምህራን በተማሪዎች ስነ-ምግባርና ውጤት ማሻሻል ዙሪያ ውይይት በተደረገበት ወቅት ነው። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደር አቶ ሚፍታ ሁሴን በውይይቱ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት መንግስት ልዩ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራባቸው ከሚገኝባቸው ዘርፎች አንዱ ትምህር እንደሆነ ተናግረው በተስጠው ልዩ ትኩረት ልክ የሚፈልገው ውጤት ማምጣት እንዳልተቻለ አስታውሰው ተማሪዎች በውጤታቸው ላይ ትኩረት ሰጥተው መማር እንዳለባቸው ጠቅሰው የትምህርትጊዜያቸው በተገቢው በመጠቀም መምህራን የሚሰጡት የድጋፍ ትምህርት ፣ወርክ ሺት በመሰራትና ላይብረሪ ገብተው በማንበብ ሀገር አቀፍ በሚሰጡ ፈተናዎች ላይ የሚፈልገውን ከፍተኛ ውጤት ማምጣት እንደሚችሉ አስገንዝበዋል። ዋና አስተዳዳሪው አክለው መወ ተማሪዎች ውጤታቸው ለማሻሻል ስነ ምግባር ከፍተኛ ሚና እንደሚጪወት ገልፀው የትምህርት ቤቱ ህግና ደንብ በማክበር  ሀገር የምትጠብቀው ውጤት ማምጣት እንደሚገባቸው አስታውቀዋል። ትምህርት ለአንድ ሀገር ሁለንትናዊ ብልፅግና መሰረት በመሆኑ መምህራን ተማሪዎቻቸውን በማገዝ ፣ወርክሺት በመስጠት ፣ የድጋፍ ትምህርት በመስጠት ትኩረት ስጥተው በመስራት እንዳለባቸው ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ ከመምህራን ብዙ መስራት እንደሚጠበቅባቸው በየደረጃው የሚዘጋጁ ፈተናዎች ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት የተማሪዎች የንባብ ክህሎት ለማሻሻል የቤተ መፅሐፍ የአገልግሎት አሰጣጥ ጊዜ ማሻሻል እንደሚገና የተማሪዎች ፍላጎት ያማከለ ስነ ዘዴ በመጠቀም ውጤታቸው ማሻሻል እንደሚገባ ገልጸዋል። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ኬኔ በበኩላቸው የተማሪዎች ውጤት እና ስነምግባር ለማሻሻል ትኩረት ሰጥተው እየሰሩ መሆኑን ገልፀው፤ተማሪዎች ለትምህርታቸው ጊዜ ሰጥተው መማር እንዳለባቸ ተናግረዋል። በስነ ምግባር የታነፀ ዜጋ ለመፍጠር የመምህራን ድርሻ የጎላ  በመሆኑ ውጤታቸውን እዲያሻሽሉ ልዩ እገዛ በማድረግ ፣ተማሪዎች በማብቃት የዕረፍት ቀናትን በመጠቀም ውጤታቸው ማሻሻል እንዲችሉ ተገቢውን ድጋፍ መስጠት ከመምህራን ይጠበቃል ብለዋል።

ሚያዝያ 07/2018 ዓ.ም ባለፉት 5 አመታት ከ24,081 በላይ ወጣቶችን በቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉ የገደባኖ ጉታዘር  ወለኔ ወረዳ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ፅ/ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ጂላሉ ወራቄ እንደገለፁት ባለፉት አምስት አመታት ስራ አጥ ወጣቶች በመለየት፣ግንዛቤ በመፍጠር፣በማደራጀትና የስራ ባለቤት በማድረግ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መምጣቱን ገልፀዋል። አቶ ጂላሉ አክለውም የስራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ባከባቢያችን ያሉ ፀጋዎችን መጠቀም እንደሚገባ አውስተው በዚህም ባለፉት 5 አመታት 26,436 ስራ አጥ ወጣቶች በመለየት አጫጭር የክህሎት ስልጠና በመስጠት 24,081 ወጣቶች በከተማና በገጠር ስራ እድል መፈጠሩን ጠቅሰው በግብርና ዘርፍ በመኸር ሠብል ልማት ፣መስኖ ፣ማደለብና ማሟከት እንዲሁም በዶሮ ሃብት ፣በንብ ማነብ፣በንግድ ዘርፍ እና በእንጨትና ብረታ ብረት ዘርፍ መሰማራታቸውን ገልጸዋል። መንግስት ያመቻቸላቸው ከኦሞ ባንክ ከ47 ሚሊዮን ብር በላይ ብድር በመውሰድ ቢዝነስ ፕላን በመስራት ለተደራጁ ስራ አጥ ወጣቶች መሰራጨት መቻሉን የገለጹት አቶ ጅላሉ ወራቄ በከተማ ለተደራጁ ወጣቶች 22 የማምረቻና መሸጫ ሼድ በመገንባት ለተደራጁ ወጣቶች ማስተላለፍ እንደተቻለ ጠቅሰው በገጠር ስራ ዕድል ፈጠራ ለተደራጁ ወጣቶች 1 ሺህ  ሄክታር በላይ መሬት በቤተሰብ፣በኪራይና የውል መሬት በማስተላለፍ ማስጠቀም መቻሉን ገልፀዋል። ለኢንተርፕራይዞች ከ119 ሚሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር የተፈጠረ ሲሆን ባለፉት 5 አመታት በገጠርና ከተማ ከተደራጁ ስራ አጥ ወጣቶች ከ38 ሚሊዮን ብር በላይ ዕዳ ማስመለስ መቻሉን ጠቅሰው የወጣቶች ሁለንትናዊ ተጠቃሚነት ሚያረጋግጡ የመንግስት ድጋፎች በማጠናከር ኢንተርፕራይዞች እንዲያሻሽሉ ለማድረግ  በተሰራው ስራ በ5 አመታት ውስጥ ከ314 በላይ ኢንተርፕራይዞች የደረጃ  ሽግግር ማድረግ መቻላቸውን አቶ ጅላሉ ተናግረዋል። በመጨረሻም አቶ ጅላሉ ወራቄ ባስተላለፉት መልዕክት ቋሚ ስራ ዕድል ፈጠራ ፣ ብድር አመለለስ ፣ ብድር ስርጭት፣ቁጣባ እና ኢንተርፕራይዞችን በELMIS ምዝገባ ተግባራት በጠንካራ ቅንጅታዊ አሰራር መተግበር እንዳለበት ገልጸው በአከባቢያችን ያሉ ጸጋዎቻችንን በአግባቡ በመለየት ወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ በተጨባጭ ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ ሲሆን ዜጎች በሚፈጠሩት የስራ ዕድሎች ከራሳቸው ባለፈ ሌሎችንም ተጠቃሚ በማድረግ የስራ አጥነትን ችግር መቅረፍ እንዳለባቸው አሳስበዋል።