en
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

Open in Telegram
912
Subscribers
-124 hours
+37 days
-730 days
Posts Archive
ሐምሌ 14/2018 ዓ/ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል ወረዳዊ የችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ በጥላሞ ቀበሌ ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በጥላሞ ቀበሌ አራጭ ተፋሰስ "ተስፋን እንትከል" በሚል መሪ ቃል ወረዳዊ የችግኝ ተከላ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሄደ። በዛሬው እለት በጥላሞ ቀበሌ አራጭ ተፋሰስ ላይ 1መቶ 37  ሺህ በላይ ለአካባቢ ስነ ምህዳር ተስማሚና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች ተዘጋጅተው በዛሬው ዕለት ተተክለዋል። የአረንጓዴ አሻራ ልማት የተፈጥሮ ሀብትን ከመጠበቅ ባለፈ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እና ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር ኢኮኖሚ ለመገንባት የማይተካ ሚና አለው። በመርሃ ግብሩ ላይ የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ፣የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የጥላሞ ቀበሌ አርሶ አደሮች ተሳትፈዋል።

ሐምሌ 14/2018 ዓ/ም የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልል አቀፍ ፈተና ከፍተኛ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች:-

ሐምሌ 13/2018 ዓ/ም ወቅታዊና ዋና ዋና የክረምት ስራዎች በጥራትና በፍጥነት በማጠናቀቅ ማህበረሰቡን ይበልጥ ተጠቃሚ ማድረግ እንደሚያስፈልግ የጉራጌ ዞን አስተዳደር አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የጉራጌ ዞን ወቅታዊና ዋና ዋና የክረምት ወራት ተግባራት አፈፃፀም በወልቂጤ ከተማ ተገመገመ። የጉራጌ ዞን ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አበራ ወንድሙ ወቅታዊና ዋና ዋና የክረምት ወቅት ስራዎች በልዩ ትኩረት መምራት ያስፈልጋል። በግብርና ዘርፉ የገጠሙ ፈተናዎች በመቋቋም ፣ለችግሮች ደግሞ መፍትሄ በመስጠት የታረሱ መሬቶች በአፋጣኝ ማልማት እንደሚገባ ተናግረዋል። ከተረጂነት ወደ ምርታማነት ወቅቱን በማገናዘብ በቂ በጀት መመደብና እርሻዎችን ማረስ ያስፈልጋል። የመከላከያ ሰራዊት ምልመላ ተግባር የህብረተሰቡን አመለካከት በመቀየር፣ ወጣቶቹን በማወያየትና አመራሩ ልዩ ትኩረት በመስጠት ሊሰራበት እንደሚገባ ተናግሯል። ስራዎች ትኩረት በተደረገባቸው አክል አፈጸማቸው ከፍ ይላል ያሉት አቶ አበራ በመሆኑም ለህብረተሰቡ ተጠቃሚነት ትጋት፣ቁርጠኝነትና ተነሳሽነት መፍጠር  እንደሚገባ መክረዋል። በስራ ላይ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮች በማስተካከል ጠንካራዎችን ማስቀጠል ይገባል ነው ያሉት። የጉራጌ ዞን ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ ናስር ሀሰን ወቅታዊ የክረምት ስራዎቻችን በትኩረት ከሰራንባቸው የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት የምናረጋግጥባቸው ናቸው። በተለይ የመኸር ወቅት፣የሌማት ትሩፋትና የገጠር ኮሪደር ስራዎችን የቤተሰብ ብልጽግና በሚያረጋግጥ ሁኔታ መስራት እንደሚገባ ተናግረዋል። የገቢ አፈጻም በተለይ በከተሞች አካባቢ የታየው ዝቅተኛ ውጤት በአፋጣኝ ወደ ውጤት መቀየር ያስፈልጋል ሲሉ አቶ ናስር አስገንዝበዋል። ወቅታዊ ስራዎቻችን በተቀመጠላቸው ጊዜ በማጠናቀቅ ማህበረሰባችን የሚመጥን ስራ መስራት ይጠበቅብናል ሲሉ ተናግረዋል። በመከላከያ ሰራዊት ተግባር የተዛቡ አመለካከቶችን  መቅረፍ ይገባል ያሉት አቶ ናስር አላማው ወደፊት በሀገርና በዞኑ ጠንካራ የጸጥታ አካል ለመፍጠር መሆኑን ታሳቢ ማድረግ ያስፈልጋል። የገጠር ሞዴል መንደሮች ግንባታ የተጀመሩት አጠናክሮ ማስቀጠልና ያልጀመሩ መዋቅሮች በአፋጣኝ ወደ ተግባር እንዲገቡ አስገንዝበዋል አቶ ናስር። አመራሩ በሚሰራው ስራ ውጤት ለማስመዝገብ በአጽንኦት መስራት እንዳለበት አሳስበዋል። በውይይቱ የተሳተፉ የስራ ኃላፊዎች በበኩላቸው የመኸር ስራና የገቢ አፈጻጸም እንቅስቃሴዎች አበረታች ቢሆኑም የፋይዳ መታወቂያ፣የሞዴል መንደሮች ግንባታ ፣የመከላከያ ሰራዊት ምልመላ ስራ ላይ ገና በዙ መስራት ይጠይቃል። የንግድ ፍቃድ እድሳት ዲጂታላይዝ ከማድረግ አንጻር በትኩረት እንዲሰራበት አንስተዋል። ስራዎች ይበልጥ ውጤታማ ለማድረግ አመራሩ የአመለካከትና የተግባር አንድነት በመያዝ በኃላፊነትና በቁርጠኝነት መስራት እንዳለበት አብራርተዋል። ወቅታዊ የክረምት ወቅት ስራዎች በሁሉም ዘርፎች በስኬት ለማጠናቀቅ በቁርጠኝነት እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል።

የሳምንቱ ዓብይት ዜናዎች ሐምሌ 12/2018 ዓ.ም 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የተጀመረው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገለልግሎት ስራ ተጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን!! የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ከመሀል አምባ ዋና የአስፓልት መንገድ እስከ መስጂደል ቁባ መስጂድ የ84 ሜትር የአስፓልት መንገድ ግንባታ ስራ መጀመሩን ተከትሎ ለመላው የወረዳችን ህዝቦችና ልማት ወዳዶች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ በአቶ ሚፈታ ሁሴን የተመራ የወረዳ አስተባባሪ አካላት ከሼሽት ማዴ- አመቶ ፣ቀቻ-ዋቦን የጠጠር መንገድ  ስራዎች ያሉበት ደረጃ የመስክ ምልከታ አካሄዱ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የወንጀል ቅድመ መከላከል ዙሪያ ለህበረተሰቡ ግንዛቤ በመፍጠር ረገድ በቁርጠኝነት እየተሰራ እንደሚገኝ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ገለፀ፡፡ ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የሀገር ዳር ድንበር እንዲከበርና የሀገር ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ውጤታማ የሆነ የመከላከያ ሰራዊት ምልመላ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ2018 በጀት ዓመት ማጠቃለያ የአመራር ግምገማና የምዘና መድረክ ተጠናቀቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን የ2018 በጀት አመት የዓመቱ ማጠቃለያ ምዘና እና ግምገማ መድረክ ተካሂዷል።     ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨                   🎤 ለትምህርት ጥራት መረጋገጥና የተማሪዎች ስነ ምግባር ለማሻሻል የርዕሰ መምህራን የመሪነት ሚና ከፍተኛ መሆኑነን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅህፈት ቤት አስታወቀ ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤  የቤት አባወራውን በአሰቃቂ ሁኔታ በዱላ ቀጥቅጠው የገደሉ 11 ተከሳሾች በጽኑ እስራት ተቀጡ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ጠቅላላ አመራር የ2018 ዓ.ም ዓመታዊ የስራ አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄድ  ይገኛል። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 ተማሪዎች የክረምት ወራትን በበጎ ፍቃድ ተግባራትና በማጠናከሪያ ትምህርት ላይ በመሳተፍ ሊያሳልፉ እንደሚገባ በጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ አስተዳደር አሳሰበ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 የመሃል አምባ መዋለ ህጻናት ትምህርት ቤት ለ5ተኛ ጊዜ ያስተማራቸው 94 ተማሪዎችን በታላቅ ድምቀት በዛሬው ዕለት አስመረቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨

"የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዜጎችን የአብሮነትና የእርስ በርስ የመረዳዳት ባህልና እሴትን የሚያጎለብት በመሆኑ በሁሉም ዘርፎች የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል"              አቶ አብድረሂም ርዳ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የበጎ ፍቃድ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ

ሐምሌ 11/2018 ዓ.ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የተጀመረው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገለልግሎት ስራ ተጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ ተገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለጸው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የክረምት ወራት የበጎ ፍቃድ  አብይ ኮሚቴ የውይይት መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው። የውይይት መድረኩን የመሩት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የበጎ ፍቃድ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አብድልረሂም ርዳ እንደገለጹት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ  በተለይም የአቅመ-ደካሞችን፣ የአረጋውያንና የሀገር ባለውለታ ዜጎችን ተጠቃሚነት በማሳደግ የአብሮነትና የእርስ በርስ የመረዳዳት ባህልና እሴትን የሚያጎለብት በመሆኑ በሁሉም ዘርፎች የተጀመሩ ተግባራት ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተናግረዋል። "በጎነት ለኢትዮጵያ ከፍታ" በሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ያለው የክረምት ወራት የወጣቶች አገልግሎት በሁሉም ዘርፍ እኩል ተግባራዊ ለማድረግ የባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ መሆኑ ተመላክቷል። ‎ ‎የክረምት ወራት በጎ ፍቃድ አገልግሎት በ16 ዘርፎች ላይ ውጤታማ ስራ ለመስራት ከወትሮ በበለጠ በትኩረት መሰራት እንዳለበት ከመድረኩ አቅጣጫ ተቀምጧል። በመድረኩ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የበጎ ፍቃድ አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ አብድልረሂም ርዳ እንዲሁም የወረዳው የክረምት በጎ ፍቃድ አብይ ኮሚቴ አባላት ተገኝተዋል።