912
Subscribers
-124 hours
+37 days
-730 days
Posts Archive
ሐምሌ 08/2018 ዓ/ም
የሀገር ዳር ድንበር እንዲከበርና የሀገር ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ውጤታማ የሆነ የመከላከያ ሰራዊት ምልመላ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ2019 የ1ኛ ዙር
የመከላከያ ሠራዊት አባላት ምልመላን በተመለከተ የግንዛቤ የኦረንቴሽንና የንቅናቄ መድረክ በመሀልአምባ ከተማ ተካሂዷል።
የወረዳው ሚሊሻ ፅ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አምዲሳ ከበደ በመደረኩ የመከላከያ ሰራዊት ምልመላ የተዘጋጀውን ሰነድ አቅርበው ጥልቅ ውይይት ተካሂዷል።
የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን በመድረኩ ተገኝተው እንዳሉት ምልመላው እንደ ወረዳ በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ያለንን ተሳትፎ የሚያሳድግና የስራ ዕድል ፈጠራ መስክ መሆኑን በተለያዩ አማራጮች በቂ ግንዛቤ በመፍጠር ማህበረሰባችን ተጠቃሚ እንዲሆን ለማስቻል ለተግባሩ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት መስራት ይገባል ብለዋል።
ከመሳተፍ አንጻር ወረዳው በባለፈው አመት የነበሩበት ጉድለቶች ማረም እንደሚገ በመጠቆም አመራሩ በልዩ ትኩረት ሊያሳካ እንደሚገባ አፅንዎት ሰጥተዋል።
አያት አባቶቻችን የፀናችን ሀገር ለእኛ ያስተላለፉት በወሬ ሳይሆን በተግባር ዋጋ ከፍለው መሆኑን ጠቁመው እኛም ለቀጣይ ትውልድ የፀናች ሃገር የማስተላለፍ ኃላፊነታችንን በተግባር ልንወጣ ይገባናል በማለት የተሰጠው የጊዜ ገደብ ሳያልፍ በተቀናጀ መልኩ ሁሉም ባለድርሻ አካላት ውጤታማ ምልመላ ማካሄድ ይጠበቅበታል ብለዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን በበኩላቸው የሀገር ዳር ድንበር እንዲከበርና የሀገር ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ ሀገር ወዳድ በስነ-ምግባር የታነጸ ወጣት ለሀገር ዘብ የሚቆም በመሆኑ ለወጣቶች ግልጽ መልዕክት በማስተላለፍ የምልመላ ሂደቱን ውጤታማ ማድረግ እንደሚገባ ተናግረዋል።
አቶ ሚፋታ አክለውም የመከላከያ ሠራዊት ምልመላ ለሀገራዊ ጥሪ ምላሽ ከመስጠት ባለፈ ለወጣቶች የስራ ዕድል መፍጠርን ታሳቢ በማድረግ ሁሉም ባለ ድርሻ አካላት የሚጠበቅበትን ኃላፊነት በተገቢው ሁኔታ መወጣት አለበት ብለዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ የወረዳችን ወጣቶች በሀገር መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ያላቸውን ተሳትፎ ለማሳደግ በቁርጠኝነት እንደሚሰራ ገልፀው ባለፉት ጊዚያት በመከላከያ ሠራዊት ምልመላ ወቅት የነበሩ ጉድለቶችን በማረምና በአሁኑ 2019 ዓ.ም አንደኛ ዙር ዕቅድን በተገቢው መንገድ ለማሳካት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት ይጠበቅበታል ሲሉ አሳስበዋል።
ሐምሌ 06/2018 ዓ.ም
ለትምህርት ጥራት መረጋገጥና የተማሪዎች ስነ ምግባር ለማሻሻል የርዕሰ መምህራን የመሪነት ሚና ከፍተኛ መሆኑነን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅህፈት ቤት አስታወቀ ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህንን ያስታወቀው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት የ2018 ዓ.ም አጠቃላይ እቅድ አፈፃፀም ግምገማና የቀጣይ የክረምት በቅድመ ዝግጅት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ ባካሄደበት ወቅት ነው።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየሁ ኬኔ በመድረኩ እንደተናገሩት የ2018 ዓ.ም የርዕሳነ መምህራን የማጠቃለያ ግምገማ ትምህርት ቤቱ ያስቀመጠውን የትምህርት ዘመን እቅድ አፈፃፀም፣ የመማር ማስተማር ሂደቱን ስኬቶች፣ የተማሪዎችን ውጤት መሻሻል፣የትምህርት የአመራር ብቃትን እና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን የሚለይበት ወሳኝ ሂደት መሆኑን ገልፀዋል።
የትምህርት ቤቶች ሀብት አጠቃቀም የተማሪዎችን የመማር ማስተማር ሂደት ውጤታማ ለማድረግ የትምህርት ቤቱን በጀትና ሀብት በአግባቡ የማስተዳደርና የመቆጣጠር ሂደት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የገለፁት አቶ አለማየሁ የተማሪዎችን ውጤትና ስነ ምግባር ለማሻሻል የተማሪ ወላጆችና መምህራን በጋራ መስራት እንዳለባቸው በመግለፅ ፣በመልካም ስነምግባር ተማሪው ትኩረቱን በትምህርቱ ላይ እንዲያደርግና ከፍተኛ ውጤት እንዲያስመዘግብ፣ እንዲሁም በመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ እርስ በርስና ለመምህራን ተገቢውን ክብር እንዲሰጡ እንደሚያግዝ ገልጸዋል ።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አህመዲን ሰኢድ እንደገለፁት ለትምህርት ቤቶች ምቹ አከባቢ በመፍጠር የተማሪዎችን የአእምሮ፣ የስነ-ልቦና እና የአካል እድገት በማጎልበት የተሻለ የትምህርት ጥራት ለማረጋገጥ ወሳኝ መሆኑ በመግለፅ ክበባት በትምህርት ቤቶች መመስረታቸው ሀገር ገንቢና ተረካቢው ትውልድ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደትን ከወዲሁ እንዲለማመዱ እንደሚያግዝ ተናግረዋል።
የትምህርት ቤቶችን ግብዓቶች የማሟላትና ጥገና ስራዎች ከማከናወን ባሻገር ፣ ትምህርት ቤቶችን ለመማር ማስተማር ስራ ለማመቻቸት፣ ሳቢና ማራኪ ለማድረግ የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብሮችን ማከናወን ተግባራዊ ማድረግ እንደሚያስፈልግ አመላክተዋል።
የትምህር ቤቶች ርዕሳነ መምህራን አመታዊ ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በመድረኩ የትምህርት ቤት ዋና እና ምክትል ርዕሳነ መምህራን ፎካል ፐርስኖች የፅህፈት ቤቱ ባሙያዎች ተገኝተዋል መድረኩ ለሁለት ቀናት የሚቆይ እነንደሆነ ተመላክቷል።
ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም
የፍትህ ተቋማትን ነጻነትና አቅም በማሳደግ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን በማስፈን እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የተገልጋይን እርካታ ማሳደግ
እንደሚገባ ተገለፀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የፍትህ ስርዓትን የበለጠ ተደራሽ፣ ፈጣንና ተጠያቂ ለማድረግ ያለመ የፍትህ አገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ውይይት ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተከሄዷል።
የውይይቱ አላማ የፍትህ አገልግሎት ፍጥነትና ጥራት የህግ የበላይነት ማስከበር፣ የተቋማት ቅንጅት ማጠናከር፣ የህዝብ ቅሬታ አያያዝና የተጠያቂነት ስርዓት ማስፈን እንዲሁም የተገልጋይ እርካታ ላይ ያተኮረ ውይይት ተደርጓል።
በመድረኩ የፍትህ ተቋማት የ2ኛ ግማሽ አመት ሪፖርት አቅርበው ውይይት ተካሂዷል።
ውይይቱን የመሩት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳደሪ እና የፍትህ ማሻሻያ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ሚፍታ ሁሴን እንደገለፁት የፍትህ ስርዓት የህዝብ እምነት መሰረት በመሆኑ በዘርፉ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በመለየት ተግባራዊ መፍትሄዎችን ማስቀመጥ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።
ዋና አስተዳዳሪው አክለውም የፍትህ አገልግሎት ቀልጣፋ ፣ ከሙስና የፀዳና ለሁሉም እኩል የሚደርስ መሆን እንዳለበትም አስገንዝበው ፤ በህብረተሰቡ ሰላምና ደህንነት እንዲሁም ህጋዊ መብቶች ላይ በአላስፈላጊ ሁኔታ የሚመጡ አደረጃጀቶችና ክሶችን የመከላከል ስራ በትኩረት መሠራት እንደሚገባ አቅጣጫ ሰጥተዋል።
የፍትህ ማሻሻያ የፍትህ ተቋማትን ነጻነትና አቅም በማሳደግ፣ ግልጽነትና ተጠያቂነትን ለማስፈን እንዲሁም የአገልግሎት አሰጣጥን በማቀላጠፍ የተገልጋይን እርካታ ማሳደግ ላይ ትኩረት መደረግ እንዳለበት አቶ ሚፋታ ሁሴን ተናግረዋል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በዘርፉ ያሉ ተግዳሮቶችን በማንሳት የህዝብ እምነትን ለማጠናከር የጋራ ርብርብ እንደሚያስፈልግ ገልፀው፣ እስረኞች በተገቢው መያዝና ስብዓዊ መብቶችቻቸው መጠበቅ እንዳለበት የተያዙ መዝገቦች በጊዜ ወሳኔ አለመስጠት ፣የፍርድ ቤት ውሳኔ መታየት መቻል እንዳለበት ፤ፖሊስ ከአስገድዶ መድፈር ጠለፋና ከሌሎች ወንጀሎች በተገቢው ይዞ መስራት እንዳለበት የሚሉት ናቸው።
በመድረኩ የፍትህ ዘርፍ አመራሮች፣ የፖሊስ አባላት፣ የፍርድ ቤት፣አቃቤ ህጎች እና የሚመለከታቸው አካላት ተሳትፈዋል።
ሐምሌ 02/2018 ዓ.ም
የከተሞች ሁለንተናዊ ልማትና ዕድገት ለማፋጠን በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህ የተገለጸው የመሀል አምባ ከተማ የሚገኙ የንግድ ቤቶችን የፊትለፊት ገፅታ በማሻሻል ከተማዋን ዘመናዊ ለማድረግ የሚያስችል ሰፊ የምክክር መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው።
የወረዳው የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን የቤቶች ልማት ባለሙያ የሆኑት አቶ መቻል ደገፍ ለመድረኩ የተዘጋጀውን የልማትና የመልካም አስተዳደር አፈጻጸም እና መሀል አምባ ከተማ የፊት ለፊት ገፅታ ግንባታ የተዘጋጃውን ሰናድ አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
የውይይት መድረኩን የመሩት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን የከተማችንን ውበት እና ደረጃ ከፍ ማድረግ የሁላችንም የጋራ ኃላፊነት ሊሆን ይገባል በማለት በአሁኑ ወቅት በአገሪቱ እየተተገበረ ካለው የኮሪደር ልማት ትልቅ ልምድ መወሰድ እንዳለበት ገልጸው።
የንግድ መስመሮች ላይ ወጥ የሆነ፣ ማራኪ እና ዘመናዊ የህንፃ ዲዛይን መተግበር እንደሚገባ ጠቅሰው ይህ አሰራር ከተማውን ከማስዋቡም በላይ ፍትሃዊና ስልታዊ የሆነ የንግድ እድገት ለማምጣት ወሳኝ መሆኑን አስታውቀዋል።
አቶ ሚፋታ አክለውም ንግድ ቤቶችን ከጭቃ ወደ ህንፃ ከመቀየር ጎን ለጎን፣ አካባቢን በፅዳትና በውበት መጠበቅ የባህል ለውጥ መምጣት እንዳለበት ተናግረዋል።
የወረዳው ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ጽ/ቤት ኃላፊ
አቶ ተማም አደም በበኩላቸው፣የከተሞች ልማትና ሁለንተናዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ በመግለፅ የቀረበው ወጥ የህንፃ ዲዛይንና ደረጃ ለመተግበር ለሚንቀሳቀሱ የንግድ ማህበረሰብ አባላት መሥሪያ ቤታቸው ፈጣንና ቀልጣፋ የግንባታ ፈቃድ አገልግሎት እንዲሁም አስፈላጊውን ሙያዊ ድጋፍ በቅርበት እንደሚያመቻች አስገንዝበዋል።
በመድረኩ የተገኙ ነዋሪዎች በስጡት አስተያየት ትኩረት እንዲሰጠው ፤የመሀል አምባ ከተማ የፊት ለፊት ገፅታ ለመቀየር እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ፣የህብረተሰቡን የመልካም አስተዳደር ጥያቄ የነበሩ ለመፍታት የተደረገው እንቅስቃሴ ለአብነት የመብራት ፤የውሀ ፣የውስጥ ለውስጥ የተሰራው መንገዶች ጠጠር የማልበስ በጥንካሬ የጠቀሱ ሲሆን በአንጻሩ ጉድለት ያለባቸው ቆሻሸን የሚፆየፍ ማሀበረሰብ በዘላቂነት ችግሩ ከመቅረፍ ፣ያለ አግባብ የሚደፍ መንገዶች፣፣ የመሰረት አውታሮች ጥበቃ ከማድረግ ፣የመሰረተ ልማት ተደራሽ ማድረግ ትኩረት መስራት እንደለበት ፣ ነዋሪዎቹ ገልጸው ወጥ የሆነውን የህንፃ ዲዛይን ለመተግበር ዝግጁ መሆናቸውን በመግለፅ፣ የተደረገውን ውይይት በመደገፍና ወደ ተግባር ለመግባት ቃል ገብተዋል።
ሐምሌ 01/2018ዓ/ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ2018/19 በጀት ዓመት የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች የሥራ ግብር አሰባሰብ በይፋ ተጀመሯል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ገቢዎች ጽ/ቤት ከወረዳው ንግድና ገብያ ልማት ጽ/ቤት በመቀናጀት የ2018 የግብር አሰባሰብ ስራ እና የ2019 ንግድ ፈቃድ እድሳት ስራ በዛሬው እለት ተጀምሯል።
በእወጃ መርሃ ግብሩ ላይ የጉራጌ ዞን የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣
የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን ፣የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳን ጨምሮ የአስተባባሪ አካላት እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሰኔ 30/2018 ዓ.ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ገቢዎች ፅ/ቤት የ2018 የግብር ዘመን ግብር አከፋፈልን ለማሳካት ለባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ገቢዎች ፅ/ቤት የ2018 የግብር ዘመን የደረጃ "ሀ" እና "ለ" ግብር ከፋዮች ግብር አከፋፈልን በውጤታማነት በአጭር ቀናት ውስጥ ለማስፈጸም ከባለድርሻ አካላት የስራ ስምሪት ተሰጠ።
በስምሪቱ ወቅት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን እንደገለጹት ግብርን በወቅቱ መክፈል የወረዳውን የልማት ስራዎች ለማፋጠን ቁልፍ ሚና እንዳለው ገልጸው፤ የንግዱ ማኅበረሰብ የሚጠበቅበትን ኃላፊነት እንዲወጣ አሳስበዋል።
የገቢ አሰባሰብ ስራውን በከፍተኛ ቅንጅትና ተጠያቂነት ለማከናወን ባለድርሻ አካላት ጋር ልዩ ስምሪት መሰጠቱን ገልጸው ለስራው ስኬት ከባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል።
የስራው አፈጻጸም በየቀኑ ከተቋሙ እና ከወረዳው አስተባባሪዎች በጋራ እንደሚገመገም አቶ ሚፋታ አክለው ገልጸዋል።
የወረዳው ገቢዎች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ረመዳን ከድር የ2018 የግብር ዘመን እቅድ ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት
የግብር አከፋፈል ስራው በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ ታቅዶ ወደ ስራ የተገባ መሆኑን ጠቅሰው ግብር
ከፋዮ ማህበረሰብ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ውስጥ ግብሩን በመክፈል ከአላስፈላጊ ቅጣትና ወለድ ራሳቸውን እንዲከላከሉ ግንዛቤ እየተፈጠረ ሲሆን ባለድርሻ አካላት በጠንካራ ቅንጅት በጋራ መስራት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
በውይይቱ ላይ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን ፣የወረዳው ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳን ጨምሮ የአስተባባሪ አካላት እንዲሁም ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሰኔ 29/2018 ዓ.ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር ዓቀፍ የተፍጥሬ ሳይንስ ተማሪዎች ኦረንቴሽን እና ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርስቲ ሽኝት መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው በተፈጥሮ ሳይንስ እና ማህበራዊ ሳይንስ ቁጥራቸው 321 ተማሪዎች በሀገር ዓቀፍ ፈተና ላይ እንደሚቀመጡ ተገልጿል።
የተፍጥሮ ሳይንስ ወንድ=56 ሴት= 49 በድምሩ 96 ተፈታኝ ተማሪዎች በዛሬው እለት ሽኝት ወደ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተደርጎላቸዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የወረዳው ትምህርት ቤቶች ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ ለተማሪዎች ኦረንቴሽን አስመልክቶ ዝርዝር ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን በተፍጥሮ ሳይንስ ወንድ=56 ሴት=40 በድምሩ 96 ተፈታኝ ተማሪዎች መኖራቸውን ገልጸዋል።
በዘንድሮ ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና በማህበራዊ ሳይንስና በተፈጥሮ ሳይንስ 321 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ አቶ አለማየው በኦረንቴሽኑ ላይ ተናግረዋል።
በሽኝቱ ወቅት የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን ተማሪዎች የወረዳው ህዝብ አምባሳደር መሆናቸውን ተገንዝበው ክልከላ ከተደረገባቸው ጉዳዮች ራሳቸውን በመጠበቅ ጥብቅ ዲሲፕልን በተሞላበት ሁኔታና ከኩረጃ በፀዳ መልኩ ፈተናቸውን በመውሰድ ለውጤታማነት መንቀሳቀስ እንደሚገባቸው ገልጸዋል።
ተማሪዎች በስነ ልቦና ዝግጁ በመሆን የፈተናን ደንብ አክብረው በመፈተን የተሻለ ውጤት ማምጣት እንዲችሉ ጠቅሰው መልካም የፈተና ጊዜ እንዲሆንላቸው ምኞታቸውን ገልጸዋል።
የተፍጥሮ ሳይንስ ፈተና ከሐምሌ 01/2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 03/2018 ዓ.ም ለተከታታይ 3 ቀናት እንደሚቆይ ከኦረንቴሽኑ ለመረዳት ተችሏል።
መድረኩ የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣
የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አለማየው ኬኔ፣
የወረዳው ትምህርት ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አህመዲን ሰኢድ፣የጉራጌ ዞን ትምህርት መምሪያ የሙያ ፈቃድ አሰጣጥና እድሳት ዳይሬክቶሬት ባለሙያ አቶ ወንድሙ ገብሬ እና የጉራጌ ዞን ትራንስፖርትና መንገድ ልማት መምሪያ ባለሙያ አቶ ደሊል ዘርጋው ተገኝተዋል።
