912
Subscribers
-124 hours
+37 days
-730 days
Posts Archive
ሐምሌ 24/2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ወቅታዊ የንቅናቄ ተግባራት አፈፃፀም ተገመገመ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በመድረኩ ወቅታዊ የንቅናቄ ተግባራት በዋናነት የመከላከያ ሰራዊት ምልመላ ፣ የክርምት በጎ ፍቃድ ስራዎች፣ የግብርና ስራዎች ፣ የአረንጓዴ አሻራ ስራዎች፣ የስራ እጥ ልየታና ስምሪት ፣ የፋይዳ መታወቅያ ምዝገባና ኢትዮኮደር እና ሌሎችም ስራዎች ያሉበት ደረጃ ሁሉም የወረዳና የቀበሌ አመራሮች በተገኙበት በዝርዝር ተገምግሟል።
መድረኩን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍተሰ ሁሴን እና የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ አ/ረሂም ርዳ የመሩት ሲሆን ወቅታዊ የመንግሥትና የፓርቲ ተግባራትን አቀናጅቶ በመምራት በሁሉም ዘርፍ ውጤታማ አፈፃፀም ማስመዝገብ እንደሚገባ ጠቅሰዋል።
ወቅታዊ ተግባራትን አቀናጅቶ መምራት፣ የተገኙ ውጤቶችን ይበልጥ ማጠናከርና ጉድለቶችን ፈጥኖ ማረም ያስፈልጋል በማለት የቀጣይ አቅጣጫና የስራ ስምሪት ተሰጥቷል።
በመድረኩ የወረዳው አስተባባሪ አካላት ፣የወረዳ አጠቃላይ አመራሮች ፣ የቀበሌ ሊቀመንበሮችና ፓርቲ ፅ/ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም የቀበሌ ስራስኪያጆች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም
የመሃል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል አገልግሎት አሰጣጥ ማሳደግ እንደሚገባ ተገለፀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህ የተገለጸው በጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የመሀል አምባ የሆስፒታሉ የቦርድ አመራሮች የ2018 ዓ.ም የ12 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን ባስቀመጡበት ወቅት ነው።
የመሃል አምባ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶክተር ሙሉጌታ ቱሉ የተቋሙን የ2018 ዓ.ም የ12 ወራት ዕቅድ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን ሆስፒታሉ አገልግሎቱን በተሟላ መልኩ ለመስጠት ከፍተኛ የባለሙያ ፍልሰት፣ የነዳጅ እጥረት እና የኮምፒውተር እጥረት ትልቅ ተግዳሮት መሆናቸውን በሪፖርታቸው በመግለጽ የቦርድ አባላት ተወያይቶ የመፍትሄ አቅጣጫ ማስቀመጥ አለበት ብለዋል።
የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አየለ ፈቀደ በመድረኩ ተገኝተው እንዳሉት የሆስፒታሉን አጠቃላይ የጽዳት ሁኔታ የተሻለ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንደሚገባ ጠቅሰው የሕክምና አገልግሎቱን ውጤታማ ለማድረግ ሆስፒታሉ ከጤና ጣቢያዎች ጋር ተቀናጅቶና በመደጋገፍ መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።
መንግስት ተቋሙን በግብዓትና በሰው ሃይል ለማሟላት የጀመረውን ትግል አጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅሰው በጉድለት የተነሱ ጉዳዮችን በባለቤትነት ወስዶ መስራት እንደሚገባ አቶ አየለ ፈቀደ ገልጸዋል።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን በበበኩላቸው ሆስፒታሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ መሻሻሎችን እያሳየ መሆኑን ጠቅሰው ከህብረተሰቡ የጤና አገልግሎት ፍላጎት አንፃር የቅድሚያ ቅድሚያ በሚሹ ርዕሠ ጉዳዮች ላይ መስራት ይጠበቃል ብለዋል።
አቶ ሚፋታ አክለውም መንግስት ሁለንተናዊ ድጋፍ ያደርጋል በአንፃሩ ባለሙያዎች ሙያዊ ስነ- ምግባር በተላበሰ መልኩ ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት የዜጎች ጤና ባለቤትነት ለማረጋገጥ የሚደረገውን ሁለንተናዊ ርብርብና ማገዝ እንደሚጠበቅባቸው ጠቅሰው በወረዳ ደረጃ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
የቦርድ አባላቱ በበኩላቸው ያጋጠሙትን አንገብጋቢ ተግዳሮቶች በተለይም የባለሙያ ፍልሰትን፣ የነዳጅና የኮምፒውተር ችግሮችን በዘላቂነት ለመቅረፍ እንዲሁም የቀረቡትን የባቤሙያ የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ ለመፍታት ሙሉ ድጋፍ እንደሚያደርጉና አስፈላጊውን የፋይናንስና የቁሳቁስ እገዛ እንደሚያመቻቹ አረጋግጠዋል።
"ለሰዎች ችግር ከመድረስና ደስታቸውን ከመካፈል በላይ እርካታ የሚሰጥ ተግባር የለም"
አቶ አ/ረሂም ርዳ
የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ
ሐምሌ 19/2018 ዓ/ም
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት በተለያዩ ተግባራት ተጠናክሮ ቀጥሏል።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በወረዳው መሀል አምባ ከተማ ነዋሪ ለሆኑት አቅመ-ደካሞች አረጋዊያን ወይዘሮ አስለፈች እሸቱ እና ወይዘሮ አሚና ከድር አዲስ መኖሪያ ቤት ግንባታ የሚሆን ለአንዳንዳቸው 40 ቆርቆሮና ሚሰማር ድጋፍ ተደርጓል።
በድጋፉ ላይ የተገኙት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን መንግስት በዘንድሮ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ሠፊ ዕቅድ አቅዶ በመንቀሳቀስ አሁን ላይ የህብረተሰቡን ብሎም የወጣቶችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነት በተጨባጭ እያረጋገጠ ይገኛል ብለዋል።
የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት የህብረተሰቡን ገንዘብ፣ ጉልበትና እውቀት በማስተባበር በራስ አቅም የመልማት እድልን የሚፈጥር መሆኑን ጠቅሰው በዘንድሮ አመት በ16 የስምሪት መስኮች ከ117 ሺህ በላይ ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
አቶ ሚፍታ አክለውም በሁሉም የገጠር ቀበሌዎች እንዲሁም በከተሞች ለአቅመ ደካሞች አዲስ ቤት መገንባትና መጠገን በልዩ ትኩረት እየተሠራበት መሆኑን ጠቅሰው ወይዘሮ አሰለፈች እሸቱ እሸቱ እና ወይዘሮ አሚና ከድር ከነዚሁ ድጋፍ ከሚያሻቸው አቅመ-ደካማ አረጋውያን መካከል በግንባር ቀደምትነት ተጠቃሽ በመሆናቸው መንግስት ለሁለቱም አቅመ ደካማ እናቶች በመሀል አምባ ከተማ ላይ መሬት በማዘጋጀት እንዲሁም ለግንባታው አስፈላጊውን የግብአት ቁሳቁስ ማለትም ለእየንዳንዳቸው 40 ቆርቆሮና ሁለት ካርቶን ሚስማር በመንግስት በኩል እገዛ ማድረጋቸውን በመግለፅ ህብረተሰቡ እና በጎ ፍቃደኛ ወጣቶች ባጠረ ጊዜ ስራውን አጠናቆ በማስረከብ የመረዳዳት ባህሉን ማስቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ከዓድዋ እስከ ቀይ ባሕር - በህልውናዋ የማትደራደረው ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 18፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኢትዮጵያ የራሷን መብት ከማስጠበቅ አልፋ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ያለመገዛትና የአሸናፊነት ማሳያ፣ የነጻነት ተምሳሌት የሆነች ምድረ ቀደምት ሀገር ናት፡፡ ሉዓላዊነቷን በመዳፈር የሚመጡትን አሳፍራ የመመለስ ደማቅ ታሪክ ያላት፡፡
በዓድዋ ወራሪ ጠላት ላይ ድል በመጎናጸፍ የራሷን ሉዓላዊነት ከማስከበር አልፋ ለሌሎች በቅኝ ግዛት ስር ለወደቁ ሀገራት የነጻነትና የአሸናፊነት ተምሳሌት መሆኗን ዓለም የመሰከረላት።
የዓድዋ ጦርነት መነሻው ኢትዮጵያን በማታለል ለተገዢነት ሊዳርጋት የቋመጠው ፋሺስት ጣሊያን ያሰፈረው ስምምነቷን ያልጠየቀው የውጫሌ ውል አንቀጽ 17 ነበር፡፡
ለበርካታ ጊዜ የዓባይ ግድብን ገድባ መጠቀም እንዳትችል የተለያየ አጀንዳ በማንገብ ጦርነቶችን ለማስነሳት ከመስራት ጀምሮ ለማተራመስና ኢትዮጵያን የግጭት ቀጠና ለማድረግ ጠላቶቿ ይሰራሉ፡፡ ግብፅና ሱዳን በዓባይ ጉዳይ ላይ ከ86 በመቶ በላይ ለወንዙ አስተዋጽኦ ያላትን ኢትዮጵያ ያላካተተ ስምምነት አድርገዋል፡፡
ኢትዮጵያ ዓባይን ለመገደብ ማሰብ የጀመረችው በቀደሙ ነገስታት ቢሆንም ሁኔታዎችና አጋጣሚዎች በፈቀዱላት ጊዜ ግድቡን አስጀምራ ያለምንም የውጪ እርዳታ በራሷ አቅም በደምና በላብ ማጠናቀቅ ችላለች፡፡
የባሕር በሯን እንድታጣ የተደረገውም እንዲሁ ከጉዳዩ ጋር ቀጥተኛ የታሪክና የስነ ልቦና ትስስር ያለው የኢትዮጵያ ህዝብ ባላመነበት እንዲሁም ህዝቡ በወከላቸው አካላት ባልተደረገ ስምምነት፣ ህገወጥ በሆነ መንገድ በጥቅም ትስስር በተደረገ አካሄድ ነው፡፡
የኢትዮጵያን ውድቀት የሚሹ ኃይሎች ከህዝብና ሀገር እውቅና ውጪ የሆኑ አጥፊ ስምምነቶችን በማድረግ ሀገሪቷን እስረኛ ለማድረግ ይሞክራሉ፤ ነገር ግን ኢትዮጵያ በውሳኔ ሰጪ አካልነት ያልተካተተችበትን የትኛውንም ስምምነት የመቀበል ግዴታ ውስጥ አትወድቅም። ይልቁን ያለአግባብ ለተካሄደበት ሁሉ የታሪክ ፍትህን ታሰፍናለች፡፡
ኢትዮጵያ ለሁሉም ችግር መግባባትን እንደ መጀመሪያ የመፍትሄ ርምጃ ብትወስድም አሻፈረኝ ብሎ ሉዓላዊነቷን ሊዳፈር ለመጣ ግን በአንድ ተሰባስቦ ጠላትን ማንበርከክን አሳምራ ታውቅበታለች፡፡ ጠላቶቿም ይህንን ጠንቅቀው ያውቁታል።
ለኔ ብቻ የሚል ሳይሆን የጋራ ጥቅምን መሰረት ያደረገ ዲፕሎማሲዊ አካሄድን የምትከተለው ኢትዮጵያ የኃይል መንገድን ተጠቅመው የሚመጡ፣ ህልውናዋን የሚፃረሩ አካላትንም አሳፍራ የምትመልስበት ብርቱ ክንድ አላት፡፡
ከሀገር አልፎ በሌሎች ሀገራት ላይ ለሚካሄዱ የሰላም ማስከበር ዘመቻዎች ቀዳሚ ተሰላፊ በመሆን ለቀጣናው ሳይቀር አይበገሬ የሆነ ስልጡን የመከላከያ ሰራዊት ያላት ሀገር ናት፡፡
ኢትዮጵያ የራሷ ያልሆነውን አትጠይቅም፤ ነገር ግን ብሔራዊ ጥቅሟንና ህልውናዋን የሚነኩ ጉዳዮችን ከማንሳትና ሉዓላዊነቷን ከማስከበር ወደ ኋላ አትልም፡፡
በቤተልሔም ግርማ
ሐምሌ 15/2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በክረምት ወቅት ታቅደው እየተሰሩ ያሉ ተግባራት በመስክ ምልከታ ተደረገ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የጉራጌ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች መምርያ ኃላፊ አቶ ሸምሱ አማን፣የወረዳ ዋና የመንግስት ተጠሪ አቶ አብድረሂም ርዳና የወረዳው አስተባባሪዎች ጨምሮ ሌሎች አመራሮች በወረዳው በመኸር ወቅት የተሰሩ የግብርና ልማት ተግባራትና የክረምት በጎ ፍቃድ እንቅስቃሴ በመስክ ተዘዋውረው ምልከታ አድርገዋል ።
በወረዳው በክረምት በጎ ፈቃድ የተሰሩ ቤቶችና በመሰራት ላይ የሚገኙትን ተዛሩረው በማየት ቁሳቁሶችንም ድጋፍ አድርገዋል።
የመስክ ምልከታው በኢንጌ፣አንባልታና ቤደር ቀበሌዎች ተካሂዷል።
በወረዳው በክረምት በጎ ፈቃድ ለመስራት ከታቀዱት 38 ቤቶች ውስጥ 15 የሚሆኑት ተጀምረው በጥሩ ሁኔታ ላይ እንዳሉ ተመላክቷል።
በወረዳው በመኸር ወቅት ታቅደው እየተሰሩ ያሉ ተግባራት የተሻሉ በመሆናቸው የበለጠ አጠናክሮ መስራት እንደሚገባም ተገልጿል።
